1 492
Subscribers
-224 hours
-87 days
+1630 days
Posts Archive
❗️❗️❗️Grade 8: General Science short note
● Unit 1 -7 (ሁሉንም ምዕራፎች የያዘ)
ተማሪዎች ይጠቅማችኋል አውርዳችሁ ተጠቀሙበት። በጣም ብዙ ጥያቄዎችንም ያካተተ ነው!❗️❗️❗️
ተማሪነት
◉ ያለንበት ቦታ፣ ያለንበት ሁኔታ ምንም ይሁን ለተስፋ-ቢስነት ምክንያት ሊሆን አይችልም!!
● ለተስፋ-ቢስነታችን ምክንያት ሊሆን የሚችል ነገር ካለም የኛ ድክመትና ራሱ “ተስፋ-ቢስነታችን” ብቻ ነው!!
ውድ ተማሪዎች
➤ ❝ እኔ ባነብም አይገባኝም ❞
➤ ❝ እኔ ሒሳብ አልችልም ❞
➤ ❝ እኔን እንግሊዝኛ ይከብደኛል ❞
➤ ❝ መማር የኔ እጣ-ፋንታ አይደለም ❞
➚እንዲህ በሚሉ የደካሞችና የቀሽሞች አስተሳሰብ ውስጣችን ከሞላነው፤ በርግጥም ሁሉም ነገር ይከብደናል። ነገር ግን ከፊት ለፊታችን ያለውን ችግር በመጋፈጥ፣ ድክመታችንን ሊሸፍንልን የሚችል ስራ በመስራት፣ ይከብዱናል ያልናቸውን ትምህርቶች ቆራጥነት በተሞላበትና ቀጣይነት ባለው ጥረት የምንችለውን ያህል በማንበብ ስንፍናችንን መበቀል እንችላለን!
● ተማሪዎች አንድ ነገር እወቁ፦ እናንተ የማትችሉት የትምህርት አይነት ምንም የለም። እናንተ መስራት የማትችሉት ምንም አይነት ስራ የለም። እናንተ መድረስ ማትችሉበት ምንም አይነት ቦታ የለም።
➻ እናተ ዘንድ የሌለ ጉብዝና ሌላ ቦታ ሊኖር አይችልም!
➻ እናተ ዘንድ የሌለ መልካም ስብዕና ሌላ ቦታ መኖሩ የማይታመን ነው።
ወንድሞቼና እህቶቼ ተማሪነት ነገሮችን ሁሉ ለይተን የምናውቅበት ሽልማት ነው!
ተማሪነት የስኬትን መንገድ የሚያቅጣጨን ኮምፓስ ነው!!
ተማሪነት እራሳችን፣ ቤተሰባችንን፣ ማህበረሰቡን ብሎም ሀገራችንን ልንረዳበት የተሰጠን ስጦታ ነው!!
ተማሪነት በአላህ ፍቃድ ከችግር የምንወጣበት መሰላል ነው!!
ተማሪነት ድጋፍ የሚሹትን የምንደግፍበት ኃይል ነው!!
ተማሪነት መጥፎ ነገሮችን የሚያጠፋ መሣሪያ ነው።
ነገር ግን ከላይ ያልናቸውን ሽልማቶች ልንሸለም የምንችለው ጊዜያችንን በአግባቡ ስንጠቀምና በወደቅን ወይም በተሸነፍን ጊዜ ተስፋ ሳንቆርጥ ጥረታችንን ስንቀጥል ነው።
ያሳደገንን ማህበረሰብ እንዲሁም ተንከባክባ የጠበቀችንን ሐገር ለመርዳት መፍትሄው ተማሪነት ብቻ ነው።
እኛ የሰው ልጆች፦
◆ ከመታገል ይልቅ ለመሸነፍ ቅርብ...
◆ወድቆ ከመነሳት ይልቅ እዛው ለመቅረት...
◆ ደጋግሞ ከመሞከር ይልቅ ቶሎ ተስፋ ለመቁረጥ ቅርብ ነን።
➊ ዛሬ እኛ ለመብራት የምንጠቀመውን አምፖል የፈጠረው ሰውዬ አንድ ሺህ (1,000) ጊዜ ሞክሮ ነው በአንድ ሺህ አንደኛው (1,001) ነው የተሳካለት። ይህን ሁሉ ጊዜ ሙከራ ባያደርግ ኖሮ እኛ ዛሬ የምናበራው ነገር ባልኖረን ነበር!!
➋ ገናናው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ምንስትሪን (8ኛ ክፍልን) 8/9 ደጋግሞ ከወደቀ በኋላ ነው ተሳክቶለት ለዓለም ብዙ ፈጠራዎችን ያበረከተው።
ወንድምና እህቶቼ፦
ሳይታገል፣ ሳይለፋ፣ መስዋዕትነት ሳይከፍል ስኬትን የሚጎናፀፍ የለም!!
ደጋግሞ ወድቆ፣ ደጋግሞ ሳይነሳ ከፍ ብሎ የሚበር የለም።
⭕️ ቱርኮች ❝ከፈለክ ህይወትህን እጣ እንጂ ተስፋ እንዳታጣ❞ ይላሉ። አዎ ተስፋ ከቆረጥን ይችህ ዓለም ለኛ ቦታ አይኖራትም። ስለዚህ ውድ ተማሪዎች ውስጣችሁ ላይ ያለውን “አይሳካልኝም” የሚለውን ፍርሃታችሁን ጠንክሮ በማንበብ በስኬት ቀይሩት። ደግሞም ነገሮችን በመቀየር ከአናንተ የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያለው አካል ፈፅሞ የለም!!
◉ እናም በዚህ ብቃታችሁና ክህሎታችሁ ተጠቀሙበት። ለስንፍናችሁ ማንንም ተወቃሽ አታድርጉ፤ ምክንያትም አትደርድሩ!!
✍️ S.M
8ኛ ክፍል ለተፈተናችሁ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች በሙሉ ::ምዝገባችሁ በ2/12/2016 ስለሆነ በተባለው ቀን ሄዳችሁ ተመዝገቡ
+1
የካቲት 23 የተመደቡ ተማሪዎች በዚህ መልኩ ፕሮግራም የወጣላቸው ስለሆነ #የድላችንም ተመሳሳይ ሊሆን ስለሚችል #ድላችን በአካል ሄዳችሁ ጠይቁ #
👉 ከ8ኛ ክፍል ወደ 9ኛ ክፍል ያለፋችሁ (የገሊላ) የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች ሪፖርት ካርዳችሁ ባይመጣም soft copy print በማድረግ መመዝገብ ስለሚቻል በግል መመዝገብ የምትፈልጉ እኛ ስለምንመዘግብ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ማለትም
#የተማሪ ፎቶ
#የወላጅ ፎቶ
#መታወቂያ
#መመዝገብ የምትፈልጉ ቀድማችሁ በዚህ ስልክ ቁጥር ደውሉ
251799066142
የምዝገባ ቀን 6ኛ እና 9ኛ ክፍል
ከ6ኛ ክፍል ወደ 7ኛ ያለፋችሁ እና ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል ያለፋችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀኑ ፕሮግራም ነሀሴ 22/2016 ዓ.ም ነው።
ተማሪ ወላጆች በብዛት አየደወላችሁ የምትጠይቁ የለጠፍነውን ፕሮግራም ተጠቀሙ። ለሌሎችም ሸር አድርጉላቸው።
ከነሀሴ 22/2016 በፊት መመዝገብ የማይቻለው በኦንላይን ስለሚመዘገቡ ሰርተፊኬት ካርድ ያስፈልጋል። ካርድ ደግሞ ገና አልመጣም። ስለዚህ 7ኛ እና 9ኛ ክፍል ያለፉ ሚኒስትሪ ተፈትነው ምዝገባ ነሀሴ 22/2016 ዓ.ም ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ካርድ ሲመጣ እናሳውቃለን መቸ እንደሚመጣ አይታወቅም።
ለሌሎች ተማሪዋች እና ወላጆችም ያጋሩ ሸር በማድረግ
👇
🈯️ ለመመዝገብ ከተማሪዎች የሚያስፈልገው
- የክፍል ደረጃ
- ሰርተፍኬት
- የልደት ካርድ (ከሌለ የተወለዱበትን ቀን፣ወር እና አመተ ምህረት)
- ጉርድ ፎቶ 1 የወላጅ 1 የተማሪ
- የወላጅ መታወቂያ
- ሁለት የስልክ ቁጥር
- የእናት ስም እስከ አያት
- ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ
- የቤት ቁጥር
- ተማሪው ትምህርት የጀመረበት ዓ.ም (KG1)
ለጓደኞቻችሁ Share በማድረግ የተጣራ መረጃ በመስጠት ተመዝገቡ።
#የ2017 ዓ/ም የተማሪዎች Online ምዝገባ አገልግሎት
#የሁሉንም የመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች እስከ 12ኛ ክፍል እንመዘግባለን።
#አድራሻ አውቶብስተራ
#ስልክ 0924411323
መመዝገቢያ 150 ብር ብቻ!!!!
#ምዝገባን በተመለከተ የ9ኛ ክፍል ምዝገባ የሚጀምረው ነሀሴ ላይ ስለሆነ #ሪፖርት ካርዳችሁ እስኪመጣ በትዕግስት ጠብቁ
