en
Feedback
Yoni Motivation

Yoni Motivation

Open in Telegram

ከማንም አትጠብቅ

Show more
698
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለላውን አይቴክ አትጀምር ለእሱ ሰለተሳካ ለአንተም ይሳካል ማለት አይደለም የራስህ የሆነ ነገር ካልሆነ ያአንቴ passion ካልሆነ በጣም ትለፍለህ ግንጰ አትቀጥልበትም ቶሎ ታቆማለህ በስመትህ ተነሳስቴ ምንም ነገር አታደርግ ያ ስመት የሚቆየው ለዛች ደቂቃ ብቻ ነው ከዛ በኃላ ትተዋለህ እውነተን ነው ምልህ አላማ ይኑርህ!!

በህይወትክ ወዴ ሃላ እያየክ ጊዜህን አታጥፍ ህይወት ማለት ወዴ ፍት መቀጠል እንጂ ቆሞ ለትላንቱ ማልቀስ አይደለም ንቃ

ሁሉም ስመቶች እንደምያልፉ እየተርዳው ነው አውነቱን ልንገርህ አታልቅስ፣ ይህም ያልፍል፣ አታልቅሽ ያስከፍሽ ቀን አልፎ ቀና የምትይበት ጊዜ እየመጣ ነው። አስታውስ! መቼም ብሆን የሰውን ልጅ አትጉዳ መልሶ ባይጎዳህም እንኳን ፀፀት ይሆንባሃል ! ውለታ የዋለልህን ሰው፣ ማንም ካአንተ ጋር ባላነበረበት ጊዜ ካአንተ ጋር ለሆነ ሰው፣ የደስታው ምክንያት መሆን ካልቻልክ ለሀዘኑ ምክንያት አትሁን ።ካደረግከው ጥፍት በላይ ለአንቴ ስል የከፈለው ዋጋ ያንገበግበዋል !! እንኳንም አጣው የተሻለ አግኝቼዋለሁ ጠላቴ ደስ አይበልክ በጣም ተመችቶኛል !!

ልብ ይድናል! የፈሰሰው እንባ ይታበሳል፤ የደረሰው ውድመት ይተካል። ከባድ ጊዜያት ጥሩ ወዳጅን ያሳውቃሉ፤ መልካም ጊዜያት ወዳጅነትን ያጠነክራሉ። ብዙ ያለፉ ታሪኮች አሉን፣ በብዙ ህመም መሃል አልፈናል፣ ብዙዎች ትልቅ ዋጋ ከፍለዋል በዚህ ሁሉ መሃል ግን እንደ አምላክ ፍቃድ እኛ በህይወት አለን። ካለፈው በተሻለ በህይወት ያለው ሰው ነገሮችን ያስተካክላል ማንም በተበዳይ ልክ የደረሰበትን በደል፣ ያየውን ችግር፣ የፈተነውን ውጣውረድ ሊገነዘብ አይችልም። ለዘመናት ያልተሻረ፣ ለረጅም ጊዜ መጥፎ ጥላን ያጠላ፣ እጅጉን በጣም ስር የሰደደ፣ እንደ መጥፎ ታሪክ የተመዘገበ፣ ህመሙ የሰረፀ፣ ስቃዩም የከፋ የልብ ስብራትና የውስጥ ሃዘን ይኖራል። ነገር ግን ሁሌም ከህመም ድህነት፣ ከስቃይም እረፍት ይሻላል። ስጋ ይታመማል፣ ነፍስ ግን ውስጧ ይደማል፤ ገፅታ ይበላሻል፣ አካል ይጎዳል፣ ልብ ግን ከምንም በላይ እረፍት ታጣለች፣ አዕምሮ በደሉን ሁሉ ይዘረዝራል። ነገር ግን ህይወትን በዚህ መልኩ መግፋት አይቻልምና ሁሌም የይቅርታ ልብን መምረጥ፣ ስለተቀረው ሰው ማሰብና እርስ በእርስ መተጋገዝን ማስቀደም ያስፈልጋል። የትኛውም ተበዳይ የሚካሳው በእግዚአብሔር ብቻ ነው፤ የትኛውም አጥፊም የሚዳኘው በፍፁሙ ፈራጁ በፈጣሪ ነው። ሁሉን ለአምላክ ሰጥቶ መጪውን ለመቀበል ዝግጁ ሲኮን ልብ ይድናል፤ ስብራት ይጠገናል፤ እምባ ይታበሳል፤ ሃዘንም ይርቃል። የእግዚአብሔርን ፍቃድ ማስቀደም፣ እርሱም ስራውን ይሰራ ዘንድ መፍቀድ የሰው ልጅ የውዴታ ግዴታ ነው። ያያል እግዚአብሔር!!

ጫወታው አያዋጣሽም! ብዙ ልብ እንዳለሽ ብዙ ሰው በልብሽ ተሸክመሽ አትዙሪ። በመታመን ፋንታ ከዳተኛ፣ ቃልን በመጠበቅ ቦታ ቃልን ማጠፍን፣ ቅድሚያ ከመስጠት ይልቅ ማቅለልና ማጠልሸት ይቅርብሽ። እራሱን ለሰጠሽ ሰው እራስሽን ባትሰጪው እንኳን ክህደትን ግን ልትሰጪው አይገባም፤ ከልቡ የሚያከብርሽን ሰው ማክበር ቢያቅትሽ እንኳን ንቀትሽ ግን አይመጥነውም፤ የወደደሽን መውደድ ባትችይ ጥላቻና ክፋትሽ ግን ፈፅሞ አይገባውም፤ አብዝቶ ደጅሽን ለሚጠና ሰው ፍላጎት ባይኖርሽ እንኳን ልቡን ግን መስበር የለብሽም። ወዶ የመጣን ሁሉ የመውደድ ግዴታ የለም፤ ነገር ግን ቢያንስ በልቡ ያለው ጥላቻ ሳይሆን ፍቅር ነውና ክብር ይገባዋል፤ ጊዜ መስጠትና በሚገባ ማስረዳት ያስፈልጋል። አልፈልግም ወይም እፈልጋለው የሚል ምላሽ በሌለው ሽፋን ሰውን ማንከራታት፣ አብዝቶም ደጅ ማስጠናት አቁሚ። እንዳሻሽ ትሆኚበት ዘንድ ፍቃዱን የሰጠሽ ሰው አንድ ቀን የሰጠሽን ሁሉ ፈቃድ እንደሚቀማሽ እወቂ። ጫወታው አያዋጣሽም! አንዱን በግላጭ ሌላውን በድብቅ የማስከተሉ ጫወታ፣ በአንዱ ፊት የማስመሰሉ በሌለው ፊት የመዋሸቱ ጫወታ፣ ልብን ሸጦ፣ እምነትን አጥፍቶ፣ ቃልን ረስቶ፣ ብረሃንን ሸሽቶ ጨለማን ተገን አድርጎ የመጓዙ ጫወታ በፍፁም አያዋጣሽምና ይቅርብሽ። እያወቅሽ ለውድቀት እራስሽን አታመቻቺ፤ ግልፅ በሆነ መንገድ እራስሽን አታርክሺ፣ ማንነትሽን አታሳንሺ፣ አዕምሮሽን አትበርዢ። እራስሽን ካልጠበቅሽ ማጣት የሌለብሽን ልታጪ እንደምትችይ እወቂ። ለእራስሽ ካልታመንሽ ከአስከፊው ውድቀት እንደማታመልጪ እወቂ። ተገደሽ ሳይሆን ፈልገሽ ለምትገቢበት ለእያንዳንዱ በደል ከተጠያቂነት አታመልጪም። ውስጥሽ ሁሉን ያውቃልና አንድ ቀን በገዛ እራስሽ ስትወቀሺና ስትከሰሺ እንደምትገኚ አትጠራጠሪ። ከማያዋጣ አጉል ጫወታ እራስሽን ጠብቂ፤ ለማንም ሳይሆን ለእራስሽ ብለሽ ታማኝ ሁኚ። የወዳጅ ብዛት እንዳያሰናክልህ ተጠንቀቅ፤ የፈላጊ ብዛት መታመንህ ላይ አደጋን እንዳይደቅን እራስህን ጠብቅ። እምነትን ማጉደል፣ እዚም እዛም ማለት ስልጣኔ ሳይሆን ኋላቀርነት እንደሆን ተገንዘብ። ብዙ አስደሳች ጫወታ አለ፤ በሰው እድሜና ስሜት መቀለድና መጫወት ግን በፍፁም አስደሳች ጫወታ ሊሆን አይችልም። አምላክ በማይፈቅደው መንገድ እየተጓዙ፣ ክብር በሌለውና ፍፁም ከስረዓት ባፈነገጠ አኳሃን እየተራመዱ የእግዚአብሔርን ይሁንታ መጠበቅ፣ እርሱን ከውርደት እንዲታደግ መጠበቅ እጅግ ነውርና አሳፋሪ ነው። በእጅህ ላይ ላለ ሰው ክብር ሳይኖርህ ገና ለሚመጣ ሰው በፍፁም ክብር ሊኖርህ አይችልም። በጀመርከው አጉል ጫወታ ተጠልፈህ እንዳትቀር በጊዜ እራስህን ያዝ አድርገው። በእራስህ ላይ እርምጃ በመውሰድ ነፀና የተረጋጋ ማንነትን መገንባት ጀምር። እምነትህ ትርፉ ለእራስህ እንደሆነ እወቅ።

ትላንት ለእነሱ ስትል በጣም ብዙ ዋጋ ከፍለሃል፣ በከፈልከው ዋጋ ልክ በእነዛ ሰወች ታማሃል፣ ቆስለሃል በጣም ብዙ ነገርህን አጥተሃል፣ ነገን ማሰብ እስክያቅትህ ጓድተውሃል፣ ዛሬም ግን በትላንቱ ቦታ ይጠብቁሃል፣ በየዋህነትህ እንደገና ወዴ ወጥመዳቸው ልያስገቡክ ያስባሉ፣ ግን አይችሉም፣ መጀመርያም ሞኝ ስለሆንክ ሳይሆን ፣ዝም ያልከው ልታጣቸው ስለማትፈልግ እንደሆነ አሳውቃቸው። እንዳትሰማ ዋዋ ነግርሃለሁ !!

ቶሎ የሚናደዱ ሰዎች 10 ባህሪያቸው !! 1.ሲበዛ ሰው ያምናሉ ለሰው ይኖራሉ ሰውን ይረዳሉ ሰው ግን እነሱን አይረዳም 😢 2. ጮኧው ስለሚናገሩ ቁጡ ናቸው ተነጫናጭ ይባላሉ 😫 3.ህመማቸውን ደብቀው መኖር ይችላሉ ከራሳቸው በፊት ለሰው ቅድሚያ ይሰጣሉ ፣ የውስጣቸውን ህመም ይዘው ይስቃሉ 😫 4.ሲናደዱ ከመናገር ዝምታን ይመርጣሉ 🙇‍♂️ 5.ሲበዛ አፍቃሪ ናቸው ላፈቀሩት ሰዉ ምንም ያደርጋሉ ❤️ 6.ታማኝ ጓደኛ የላቸውም ሰው ከእነሱ ጋር ለጥቅሙ ሲል ነው የሚቆየው የፈለገውን ካገኘ በኋላ ሰብሯቸው ይሄዳል 💔 7.ከስህተታቸው ሳይማሩ ደግመው ሰውን ያምናሉ ምክንያቱም ብቸኝነትን ስለሚፈሩ ❤️ 8.በጣም ተጫዋች ናቸው ፣ የሚሰማቸውን ፊት ለፊት ነው የሚናገሩት ምንም ቢሆን ምንም ❤️👍 9. ሲከፉ ሆደ ቡቡና አልቃሻም ናቸው 😢 10. ሁሌም ግን በፍቅር አሸናፊዎች ናቸው ፣ ይቅር ባይ ናቸው ፣ ቂም አይዙም ፣ ከወደዱ አይጠሉም ፣ ከጠሉም ዞር ብለው አያዩም ፣ ህይወት ይቀጥላል ነው መርሀቸው ❤️😍

ከተሰበረ ተመልሶ የማይጠገነው ሸክላ ብቻ ነው ።የሰው ልጅ ከተወለደበት ቀን ጀምሮ በህይወቱ በጣም ብዙ ነገሮችን ያሳልፋል። ባመነው ሰው ይከዳል፤ ያዝኩት ያለው ከእጁ ያመልጣል፤ ቁኑ ይመሽበታል፤ መግብያ መውጫ ያጣል፤ ያለቅሳል፤ ራሱን ለማጥፋት ይሞክራል፤ ከዛም ይመለሳል፤ ይረጋጋል! ታድያ አንተ የሰው ልጅ አይደለህም? ራስህን እንደ ሸክላ ለምን ታያለህ? የተበላሹ ነገሮችን ለማስተካከል እኮ ትችላለህ! እጅህ ብሰበር ተሰብሯል በቃ! ከአሁን በኃላ አይጠቅመኝም ብለህ አትቀመጥም፤ ወገሻ ቤት ትመላለሳለህ፤ መልሰህ ለመጠቀም። በህይወታችን የሚገጥሙን የትኛውም ችግሮች ከእንዝህ ጋር አንድ አይነት ናቸው። መልሰህ ራስህን ስራ፤ ከቁስሉ ለማገገም ሁለተኛ ዕድልህን ተጠቀም! በዛ መንገድ ስጓዝ ድንጋይ አደናቀፈኝ ሁለተኛ በዛ መንገድ አልጓዝም ብሎ እንደማለት ነው ።ህልምህን ለመኖር ስትጀምር በጣም ብዙ ዋጋ ያስከፋላል ዋጋውን ከፍለህ ስትጨርስ መጨራሻው ግን እጅግ በጣም ያስደስታል ያኮራልም እያለፈ ነው...😏😏

ምንድነው የምታደርገው? ምንድነው የምታደርገው? መቼ? ማንም ሰው ሳያምንብህ ሲቀር፣ መቼ? ማንም ከጎንህ በሌለበት ሰዓት፣ መቼ? የሚረዳህን ባጣህበት ሰዓት፣ መቼ? በውድቀትህ ጊዜ፣ በተሳሳትክ ወቅት፣ ቀኑ በጨለመብህ፣ መሔጃ በጠፋብህ፣ ተስፋህ በተመናመነበት፣ እቅዶችህ ሁሉ በከሸፉበት ወቅት ምንድነው የምታደርገው? በእርግጥ ምን ትከውናለህ? ቁጭ ብለህ እራስህን ትወቅሳለህ ወይስ አይንህን ከፍተህ ለመጪው ጊዜ እራስህን ታዘጋጃለህ? ምክንያት እየደረደርክ ታለቃቅሳለህ ወይስ ለሆነው ሁሉ ሃላፊነትን ትወስዳለህ? ቁጭ ብለህ እራስህን ታረጋጋለህ ወይስ እራስህን መውቀስ ትጀምራለህ? ጉዞህን ትገታለህ ወይስ ይበልጥ ጠንክረህ ረጅም ለመጓዝ ትነሳለህ? ምንድነው የምታደርገው? ሁሌም ነገሮች አልጋ በአልጋ የማይሆኑበት አለም ውስጥ ነው የምትኖረው፣ ሁሉም የከበበህ ሰው መልካሙን በማይመኙልህ ሁኔታ ውስጥ ትኖራለህ፣ ሁሉም እርምጃህ ውስጥ የሚያበረታታ ነገር ላታገኝ ትችላለህ፣ በየትኛውም ሙከራህ መሃል መውደቅ፣ መሳሳትና በሰዎች መተቸት ሊገጥምህ ይችላል። ብቻህን እንደጀመርከው ብቻህን ረጅም ርቀት መጓዝ የሚኖርብህ ሰዓት አለ፤ ምናልባት ካንተ የሚያገኙትን ነገር ሲያጡ የሚለዩህም ሰዎች ሊያጋጥሙህ ይችላል። ብዙ ፈተናዎች ሲደራረቡብህ የውስጥ ጩሀትህ ከወትሮው በተለየ ያይላል፣ ሙከራህ ሲከሽፍ፣ የጥረትህ ዋጋ ሳያገኝ ሲቀር፣ የጠበከው ሳይሆን ሲቀር ጭንቀት ወዳጅህ ይሆናል። ህልምህን ጨለማ ይወረዋል፤ ተስፋህን ውሃ ይበላዋል፤ አላማህ እንዳልነበር ይቀበራል። ያንን ጮክ ያለ ተስፋ የመቁረጥ፣ ዋጋ የማጣት፣ ተፈላጊ ያለመሆን፣ የስብራትና የህመም ድምፅ ስትሰማ በህይወትህ ምንም እንዳልቀረህ ታስባለህ፤ ለእራስህ መሆን እንደማትችል ይሰማሃል። ነገር ግን በዚህ ሰዓት ይህን ጥያቄ እራስህን ጠይቅ፦ "ምንድነው የማደርገው? የሚያድነኝ፣ የሚያነሳኝ፣ የሚያበረታኝ፣ ተስፋዬን የሚመልሰው አይነተኛ ተግባር ምንድነው? ምንስ ባደርግ የቀድሞ ማንነቴን መልሼ አገኘዋለሁ?" ብለህ እራስህን ጠይቅ። ጊዜያዊ ውድቀትህ እንዲጫወትብህ አትፍቀድ፤ አላፊው ጨለማ ህይወትህን እንዲያመሰቃቅል አታድርግ፤ ነገ በሚረሳ ጉዳይ ዋጋህን አታሳንስ። ቆም በል፣ ተረጋጋ ሌላኛውን ውስጣዊውን የለሆሳስ ድምፅ ለማዳመጥ ሞክር። በአምላኩ እንደሚተማመን የሚነግርህን ድምፅ፣ ነገ ሌላ ቀን እንደሆነ የሚያሳውቅህን ድምፅ፣ ከዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ የምትወጣበት መንገድ እንዳለ የሚነግርህን እውነተኛና በእግዚአብሔር መንፈስ የተሞላውን ድምፅ አዳምጥ። ከአንበሶች መንጋጋ ልጁ ዳንኤልን የታደገ አምላክ ሁሌም አብሮህ እንዳለ መቼም እንዳትረሳ።💪💪🙏

ለሰው ልጅ ከፈተናዎቹ ሁሉ በጣም ከባዱ ምን እንደሆነ ታውቃላቹ! በአመኑት ሰው መከዳት ፣መቼም የማይጠገን የልብ ስብራት፣ በአንድ ጊዜ ባዶ መሆን ፣ የተጠራቀሙ ውሸቶች ልብን ብቻ ሳይሆን አጥንትንም ጭምር ይሰብራሉ ድጋመ ቆመ እንዳትሄድ ያደርጋሉ ሞትን ቢቻ እንድታስብ ልያደርጉህ ይችላሉ ያ የሆነው ግን እኛ ሞኝ ስለሆነን አይደለም በእኛ ላይ እንዲጠቀሙ ፍቃድ ሰጥተናቸው እንጅ ለእነሱ ግን እኛ ሞኝ የሆነኝ አየመሰላቸው ያጡናል የማትፈልጉትን ሰው ለጊዜ ማሳለፈያነት አትጠቀሙ ሰው እንጂ ሮቦት አይደለም በኃላ በጣም ይፀፅታቿል መልካም ቅዳሟ

እነሱን መልሰህ መጉዳት የአንተን ቁስል አይፈውስልህም

ራስህን በጣም የምትወድ ከሆነ ሌላውን ለመጉዳት በተአምር አትፈልግም

የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

👉Yoni listen 👌No one is coming to save you.This life is 100% your responsibility 😕

የሆነው እንኳን ሆነ የቀረውም እንኳንም ቀር ያለፈው እንኳን አለፈ የሄደውም እንኳን ሄደ የሚበልጠው እየመጣ ነው የጣሁት ነገር ሁሉ መስሎኝ እንጂ መጀመርያም የእኔ አልነበረም ሌላ የተሻለ እየመጣ ነው !! መልካም ምሽት

በጣም ብዙ ፈተና በጣም ብዙ መከራ የምትችሉት የማይመስል ከባድ የሆነ ፈተናና ችግር ሁላችንንም ይገጥመናል ወደዚህ መንገድ እንድናመራ የሚገፋፋ😥😥😥 ነገር ግን ያቺን ሰአት እንደምንም ትግስት ኖሮ
+3
በጣም ብዙ ፈተና በጣም ብዙ መከራ የምትችሉት የማይመስል ከባድ የሆነ ፈተናና ችግር ሁላችንንም ይገጥመናል ወደዚህ መንገድ እንድናመራ የሚገፋፋ😥😥😥 ነገር ግን ያቺን ሰአት እንደምንም ትግስት ኖሮ ማለፍ እንደዚህ አይነት ስሜት ሲሰማቹ አብዝቶ መፀለይ ያስፈልጋል ሁሉም ነገር ያልፋል ከታገሱ የማያልፍ ምንም ነገር የለም እግዚአብሔር ከእንዲህ አይነት የሚያስጨንቅ ነገር ይጠብቀን🙏🙏🙏 ነፍስ ይማር አህቴ🙏😥😥😥

ግን እኮ ሁላችንም ታመናል ቁስላችንን በሆዳችን ይዘን በሁኔታዎች እለት እለት እርጥብ ቁስላችን እየተወጋጋ ነገ መልካም ይሆናል ያልፋል ብለን የሩሩሩቅ ተስፋ ሰንቀን እየኖርን እንጂ ሁላችንም ደክመናል ግን እግዚያብሔር እያበረታን እንዲሁም ትንሻዋ ውስጣችን ያለችው ተስፋ ዛሬ አድርሰውናል አይዞን Yoni motivation አይዞን አው ደሞም ዛሬ እንደዚ ያልፋል ነገ ደግሞ መልካም ይሆናል 🙏