en
Feedback
ትኩስ መረጃ

ትኩስ መረጃ

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel ትኩስ መረጃ

Channel ትኩስ መረጃ (@tekus_info) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 70 368 subscribers, ranking 3 642 in the Movies category and 435 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 70 368 subscribers.

According to the latest data from 10 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -1 340 over the last 30 days and by 229 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 1.61%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 1.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 131 views. Within the first day, a publication typically gains 847 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 4.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 11 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Movies category.

70 368
Subscribers
+22924 hours
+447 days
-1 34030 days
Posts Archive
የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ውስጥ ሊካተት ነው፡፡ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈፅሟል። የትም
የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ውስጥ ሊካተት ነው፡፡ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈፅሟል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረሕይወት (ፕ/ር) እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በሁለቱ አገራት መካከል እያደገ የሚገኘውን የባህል፣ የትምህርት እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ያስችላል ተብሏል፡፡ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩት የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት ከሰርተፊኬት ስልጠና ጀምሮ እስከ 2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም እንደሚያስተምር ይታወቃል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማስፋፋት ከአዲስ አበባ እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮዎች ጋር በቅርቡ ስምምነት መፈፀሙ ይታወሳል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ዶናልድ ትራምፕ «የዋጋ ንረቱን እወደዋለሁ» ማለታቸው  ውዝግብ ፈጥሯል   ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ወር የአሜሪካ የሸቀጦች ዋጋ ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት መጨመሩን የሚያሳዩ ይፋዊ መረጃዎች ከወጡ በኋላ ›› የዋጋ ንረቱን እወደዋለሁ››ሲሉ ተደምጠዋል። የዩናይትድ ስቴትስ የሰራተኞች ስታቲስቲክስ ቢሮ (BLS) የግንቦት ወር መረጃ እንደሚያሳየው ባለፉት 12 ወራት ውስጥ የዋጋ ንረቱ በ4.2 በመቶ  ጨምሯል ይህም  በሚያዝያ ወር ከነበረበት 3.8 በመቶ  ከፍ ያለው ይህ የዋጋ ጭማሪ  በዩኤስ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ከተቀሰቀሰው ጦርነት ማግስት በናረው  የነዳጅ  አቅርቦት ዋጋ ሳቢያ የመጣ ነው። ትራምፕ በነጭ ቤተ መንግስት በሰጡት መግለጫ «እወደዋለሁ  ቁጥሮቹ በጣም ጥሩ ነበሩ  ምን እንደምወድ ታውቃላችሁ? የዋጋ ንረቱን እወደዋለሁ» ሺሉ ተደምጧል ። ነገር ግን ከኢራን ጋር ያለው ጦርነት ሲያበቃ የናረው ዋጋ «እንደ ድንጋይ ቁልቁል እንደሚምዘገዘግ   ወይም በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ» ቃል ገብተዋል።   ነገር ግን ትራምፕ ቆየት ብለው ለኒው ዮርክ ፖስት (New York Post) በሰጡት አስተያየት ንግግራቸው ከዐውደ-ጽሑፉ ውጪ እንደተወሰደባቸው ገልጸው  ማለት  የፈለጉት የዋጋ ንረቱ ከዚያ በላይ ባለመጨመሩ የተሰማቸውን ደስታ እንደሆነ አስረድተዋል። ትራምፕ ለጋዜጣው  ሲናገሩ «የዋጋ ንረቱን ቁጥሮች የወደድኩት እኔ ከማወራው ነገር አንጻር ምክንያቱም  በጦርነት ውስጥ ብንሆንም እንኳ ቁጥሮቹ አስቀድሞ ከተገመተው በላይ እጅግ ዝቅተኛ መሆናቸውን ነው ስለዚህ  ከጦርነቱ ስንወጣ  ቁጥሮቹ ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበሩበት ደረጃም በታች ዝቅ ይላሉ» ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ በቅርብ የወጡትን የዋጋ ንረት መረጃዎች አስመልክተው በቅድሚያ በሰጡት አስተያየት  የአሜሪካ ጦር ኃይሎች ከኢራን  በሚሊዮኖች የሚቆጠር  በርሜል  ዘይት ለመውሰድ የሌሊት ዘመቻዎችን ማካሄዳቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ይህም ለነዳጅ ዋጋ መጠነኛ መቀነስ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል። አክለውም«ይህ ግጭት ሲያበቃ… የነዳጅ ዋጋው  ቀደም ሲል ወደነበረበት ደረጃ  ሲወርድ ታያላችሁ» ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ እ.ኤ.አ. በ2026 መጀመሪያ ላይ ወደ አዮዋ (Iowa) ያደረጉትን ጉዞን  በማስታወስ አንድ ጋሎን ቤንዚን በ1.85 ዶላር ሲሸጥ ማየታቸውን ጠቅሰው «በጣም በቅርቡ ወደዚያ ደረጃ እንመለሳለን» ሲሉ አክለዋል። ይሁን እንጂ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ዋጋ መመዘኛ የሆነው ብሬንት ክሩድ (Brent crude) አሁንም ቢሆን ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበረበት ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ ከፍ ብሎ እየተገበያየ ይገኛል።  @Tekus_Info @Tekus_Info

በቀናት ውስጥ ወደ ጦርነት…! ሬድዋን ሁሴን እና ጌታቸው ረዳ፤ "ህወሓት በቀናት ውስጥ ጦርነት ይከፍታል" አሉ። "ህወሓት በቀናት ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ወስኗል" ሲሉ የብሔራ
በቀናት ውስጥ ወደ ጦርነት…! ሬድዋን ሁሴን እና ጌታቸው ረዳ፤ "ህወሓት በቀናት ውስጥ ጦርነት ይከፍታል" አሉ። "ህወሓት በቀናት ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ወስኗል" ሲሉ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ አልጀዚራ ላይ ባስነበቡት ጽሑፍ አስጠንቅቀዋል፡፡ ሬድዋን እና ጌታቸው በጋራ ባስነበቡት ጽሑፍ፣ “ጽምዶ” በሚል ቅንጅት የፈጠሩ ኃይሎች ኢትዮጵያ ወደ ጦርነት ጎትተው ለማስገባት እየተንቀሳሱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአስመራ፣ በመቀሌ እና በሱዳን በድብቅና ግልጽ በሆኑ ስብሰባዎች የተፈጠረው የጽምዶ ጥምረት፣ በአሁኑ ወቅት ወደ ማጥቃት ለመሸጋገር ተዘጋጅቷል ብለዋል። ጌታቸው እና ሬድዋን "አክራሪና ርዝራዝ ቡድን ነው" ያሉት ህወሓት፣ በአስመራ ድጋፍና አጋዥነት፣ በሚቀጥሉት ቀናት ጥቃት ለመሰንሰር መወሰኑን አረጋግጠዋል፡፡ ህወሓት የትግራይ ሕዝብ ህወሓትና የጦርነት አጀንዳውን በግልጽ ውድቅ ቢያደርግም፣ ቡድኑ የግጭት መቀስቀስ አባዜውን አልተወም ብለዋል፡፡ ህወሓት ከኤርትራ መንግስት በቀጥታ በሚያገኘው ድጋፍ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተዋጊ ኃይል መመልመል፣ ማሰልጠን እና ማስታጠቅ ቀጥሏልም ሲሉም አክለዋል። @Addis_News @Addis_News

በህወሓት ላይ እርምጃ ይወሰድ-ኢዜማ‼️ የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ኢዜማ ጠየቀ‼️ አካሄዱ ‹መኢሶንን ይመስላል› በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት
በህወሓት ላይ እርምጃ ይወሰድ-ኢዜማ‼️ የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ኢዜማ ጠየቀ‼️ አካሄዱ ‹መኢሶንን ይመስላል› በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የፌዴራል መንግስቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቋል፡፡ ሕውሓት ደርግን ጥሎ ስልጣን ከተቆጣጠረ አንስቶ የሰራቸውን ጥፋቶች የሚዘረዝረው መግለጫው፤ አሁን ላለው አገራዊ ችግር መንስኤው ሕውሓት ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ እንደሆነ አንስቷል፡፡ ለፕሪቶሪያ ስምምነት አለመተግበር እና ለተፈናቃዮች አለመመለስ ሕውሓትን ብቻ ተጠያቂ ያደገው የፓርቲው መግለጫ፤ ‹‹ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል›› ሲል ጠይቋል፡፡ ‹‹እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል›› በማለት ሕውሃት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ @Addis_News @Addis_News

🚨 አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ 🚨 በቅርብ ጊዜ በቴሌግራም ላይ እጅግ አደገኛ የሆነ የአካውንት ጠለፋ እና የማጭበርበር ዘዴ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ጠላፊዎች አሳሳች ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም አስደን
🚨 አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ 🚨 በቅርብ ጊዜ በቴሌግራም ላይ እጅግ አደገኛ የሆነ የአካውንት ጠለፋ እና የማጭበርበር ዘዴ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ጠላፊዎች አሳሳች ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም አስደንጋጭ መልዕክቶችን በመጠቀም አደገኛ ሊንኮችን (Links) ይልካሉ። ❗ እነዚህ መልዕክቶች ከማታውቋቸው ሰዎች ብቻ ሳይሆን፣ አካውንታቸው ከተጠለፈ ጓደኞቻችሁ፣ ዘመዶቻችሁ ወይም የምታምኗቸው ሰዎች ሊመጡ ይችላሉ። ⛔ ሊንኩን ጠቅ እንዳደረጋችሁ ወይም እንደከፈታችሁት፣ የቴሌግራም አካውንታችሁ በጠላፊዎች ቁጥጥር ስር ሊገባ ይችላል። 📤ለምሳሌ :-"እዚህ ዌብሳይት ላይ ፎቶህን አየሁት" የሚል መልዕክት ደርሷችሁ ይሆናል 🔒 ራሳችሁን ለመጠበቅ የሚከተሉትን ያድርጉ፦ 1️⃣ Settings → Privacy and Security → Devices ውስጥ ገብታችሁ የማታውቁትን ወይም አጠራጣሪ የሆኑ ስልኮች (Sessions) Terminate ወይም Terminate All Other Sessions በማድረግ ያስወግዱ። 2️⃣ Two-Step Verification ከአሁኑ ይክፈቱ። Settings → Privacy and Security → Two-Step Verification ውስጥ በመግባት ጠንካራ የይለፍ ቃል (Password) ያስቀምጡ። Hint ላይ ሌላ ነገር አስገቡ ብዙ ሰው ፖስዎርዱን መልሶ ሲያስገባ አይቻለው 🙏 ይህን ማስጠንቀቂያ ለጓደኞቻችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁ እና ለሌሎች የምታምኗቸው ሰዎች በማጋራት ከዚህ አደገኛ ጥቃት እንዲጠነቀቁ አድርጉ። @Addis_News @Addis_News

ታይዋን ከቻይና ወደሚለያት የታይዋን ሰርጥ የተኮሰችው ሮኬት አሜሪካ ሰራሽና ከተተኮሰ በኋላ ጠላት በምላሹ እንዳያጠቃው ቦታ የሚቀይር ነው። ሂማርስ የተባለው ይሄ የአሜሪካ ሚሳኤል ማስወንጨፊያ ከዚህ ቀደም በታይዋን ቢሞከርም ሚሳኤሉ ወደ ታይዋን ሰርጥ ሲተኮስ ግን የአሁኑ የመጀመሪያ ነው። የታይዋን ጦር እንዳለው የጠላት ስጋት እየጨመረ በመምጣቱ አሁን የተደረገው የጦር መሣሪያ ሙከራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ጦሩ አክሎም አሁን የተተኮሰው ሚሳኤል የሚሸፍነው ርቀት እንዲቀንስና ከወዲሁ ከባህሩ ውሃ ላይ እንዲወድቅ ተደርጓል። አሁን ታይዋን ያደረገችው የሚሳኤል ሙከራ ከቻይና ጋር ያለውን ውጥረት እንዳያባብሰው ተሰግቷል። @Tekus_Info @Tekus_Info

ያን ጊዜ ያመኑን አመስግነውናል - ጀንቦሮ ሪል ስቴት 🔝በ5 ዓመታት ዉስጥ 4 ፕሮጀክቶችን ጥንቅቅ አድርጎ ገንብቶ ያስረከበዉ  ጀንቦሮ ሪል ስቴት  ⭐️አሁን ደግሞ በከተማችን ተመራጭና ዲፕሎማቲክ መንደር በሆነዉ ሳር ቤት ከሚገኘው ሳይታችን አፓርትመንት ሲገዙ እስከ 15% ቅናሽ ማድረጋችንን ስናበስርዎ በታላቅ ደስታ ነዉ! ➡️ሳር ቤት ሳይት በዲፕሎማቲክ መንደር 👉ከባለ አንድ እስከ ባለ ሁለት መኝታ ቤት ጀምሮ (በተለያዩ ካሬ አማራጭ) 👉በካሬ 140,000 birr 👉10% ብቻ የመጀመሪያ ክፍያ 📍 ከ 2 ዓመት እስከ 2 አመት ተኩል የክፍያ ጊዜ(ከምቹ የአከፋፈል ሲስተም ጋር) ⬇️በህንፃችን ላይ ያሉንን ተጨማሪ አገልግሎቶች ከስር ይመልከቱ⬇️:
💙ጂም እና ስፓ 💙 ሬስቶራንት 💙የልጆች መጫወቻ 💙ጌም ዞን 💙ሲኒማ 💙አዳራሽ 💙በቂ የሆነ ሊፍት ያለው (10) 💙የገበያ ማእከል 💙 የደህንነት ካሜራዎች 💙4 ቤዝመንት በቂ የመኪና ማቆሚያ 💙የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ስቴሽን 💙 ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ 💙ተጠባባቂ ጀነሬተር 💙 የከርሰ ምድር ውሃ
⭐️የምንገበያየዉ በኢትዮጵያ ብር ሲሆን በጊዜያት መቀያየር የሚኖር ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አለመኖሩ ጀንቦሮን እጅጉኑ ተመራጭ ያደርገዋል! ግድየሎትም ያውሩን በእጥፍ ያተርፋሉ ለበለጠ መረጃና ለሳይት ጉብኝት አሁኑኑ ይደውሉ ወይም በዋትስአፕ ያውሩን ☎️ +251-911-97-09-01 ☎️ +251-975-19-93-11 ❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️

ኦባሳንጆ መቀሌ ገቡ‼️ የፕሪቶሪያ ስምምነት አደራዳሪ ከነበሩት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ የአውስትራሊያና የኢንግሊዝ ተወካዮች ያካተቱ የልኡካን ቡድን ከትግራይ ክልላዊ መንግስት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ለመወያ
ኦባሳንጆ መቀሌ ገቡ‼️ የፕሪቶሪያ ስምምነት አደራዳሪ ከነበሩት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ የአውስትራሊያና የኢንግሊዝ ተወካዮች ያካተቱ የልኡካን ቡድን ከትግራይ ክልላዊ መንግስት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ለመወያየት መቐለ ከተማ ገብተዋል። ህወሓት በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን ወታደራዊ አፈሳ አጠናክሮ ቀጥሏል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

እውነታ_ማጣራት፡ ሀሰት: ምስጢረሥላሴ ታምራትን በተመለከተ የተሰራጩት እነዚህ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፍ ትክክለኛ አይደሉም ግንቦት 24 ቀን በተካሄደው የ2018 የኢትዮጵያ ምርጫ ዕጩ የሆነ
እውነታ_ማጣራት፡ ሀሰት: ምስጢረሥላሴ ታምራትን በተመለከተ የተሰራጩት እነዚህ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፍ ትክክለኛ አይደሉም ግንቦት 24 ቀን በተካሄደው የ2018 የኢትዮጵያ ምርጫ ዕጩ የሆነችውን ፖለቲከኛ ምስጢረሥላሴ ታምራት ያሳያል በሚል በፌስቡክ ማኅበራዊ ገጽ ላይ የተጋሩት እነዚህ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንዲሁም አንድ ፎቶግራፍ ሀሰት ናቸው። ይህ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው፣ ፖለቲከኞቹ በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ውድድር ላይ በንቃት እየተሳተፉ ባሉበት ወሳኝ ወቅት ላይ ነው። በተጨማሪም ተንቀሳቃሽ ምስሉ በማኅበራዊ ገጾች ላይ የተጋራው፥ ዕጩዎቹ የሚወክሉት ፓርቲ በተደጋጋሚ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪዎችን በማቅረብ ላይ በሚገኝበት ወቅት ነው። በዘንድሮ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ዕጩ ምስጢረሥላሴ ታምራት ላይ ያነጣጠሩና በፌስቡክ ማኅበራዊ ገጽ ላይ የተጋሩ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎችንና አንድ ፎቶግራፍ በጥልቀት የመረመረ ሲሆን፥ የተሰራጩት መረጃዎች በሙሉ ሀሰተኛ መሆናቸውን ተረጋግጧል። በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ በተደረጉ የፓርቲዎች ክርክር መድረክ ላይ በምታሳየው ድፍረት የተሞላበት የሃሳብ ፍልሚያ ከፍተኛ ድጋፍን እንዲሁም ጠንካራ ትችቶችን እያስተናገደች የምትገኘው ፖለቲከኛዋ ሚስጥርስላሴ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የስም ማጥፋት ዘመቻ (Character Assassination) ኢላማ ሆናለች። በተለይም…. Via_Addis standard @Addis_News @Addis_News

ዛሬ የሚጀምረው ተናፋቂው የዓለም ዋንጫ‼ በመላው ዓለም በጉጉት የሚጠበቀውና ከምድር ታላላቅ የስፖርት ሁነቶች አንዱ የሆነው የዓለም ዋንጫ ዛሬ በይፋ ይጀምራል። ይህ ታላቅ መድረክ ልዩ ልዩ ሀገራትን፣
+1
ዛሬ የሚጀምረው ተናፋቂው የዓለም ዋንጫ‼ በመላው ዓለም በጉጉት የሚጠበቀውና ከምድር ታላላቅ የስፖርት ሁነቶች አንዱ የሆነው የዓለም ዋንጫ ዛሬ በይፋ ይጀምራል። ይህ ታላቅ መድረክ ልዩ ልዩ ሀገራትን፣ ባህሎችንና በቢሊዮን የሚቆጠሩ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን በአንድነት የሚያስተሳስር ልዩ የደስታ በዓል ነው። በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ሀገራት — አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ ይህንን ውድድር ያስተናግዳሉ። ይህ ታሪካዊ እትም፣ የእግር ኳስን ዓለም አቀፋዊ ዕድገትና ሰዎችን የማስተሳሰር አስደናቂ ኃይል የሚያሳይ፣ በታሪክ እጅግ ግዙፍ እና ታላቅ ዓላማ ያነገበ የዓለም ዋንጫ እንደሚሆን ይጠበቃል። ከቦነስ አይረስ ጎዳናዎች እስከ አዲስ አበባ መንደሮች፣ ከአውሮፓ ከተሞች እስከ አፍሪካና እስያ ገጠራማ አካባቢዎች፣ የመላው ዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን ዓይኖች አሁን ወደ አንዱ ታላቅ መድረክ አቅንተዋል። ለሚቀጥሉት ሳምንታት፣ ሀገራት ለላቀው የእግር ኳስ ክብር በሚያደርጉት ፍልሚያ፣ መላው ዓለም በጋራ ይደሰታል፣ አብሮ ይጨነቃል፣ እንዲሁም አብሮ ያልማል። የዓለም ዋንጫ ከእግር ኳስ ውድድር በላይ ነው፤ ጀግኖች የሚወለዱበት፣ ክብረ ወሰኖች የሚሰበሩበት እና ታሪክ የሚጻፍበት መድረክ ነው። ውድድሩ ሲጀመር በቢሊዮን የሚቆጠሩ አድናቂዎች የሚጠይቁት አንድ ጥያቄ አለ፦ 🏆 የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ማን ያነሳ ይሆን? @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በመዲናዋ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ጀመረ የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱን የተሽከ
በመዲናዋ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ጀመረ የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት መጀመሩን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ በሰጡት መግለጫ፤ ሰሌዳው የሚሰጠው ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ሲሆን፣ ተመዝግበው ሲጠባበቁ የነበሩ ባለቤቶች በተመዘገቡበት ቅርንጫፍ በኩል በስልክ ጥሪ ተደውሎላቸው መውሰድ እንደሚችሉ ገልጸዋል። ነባር ሰሌዳ የሚጠቀሙትን በተመለከተ ወደፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል አቅጣጫ እንደሚቀመጥ አመልክተዋል። @Addis_News @Addis_News

MEXC በድንገት የኢትዮጵያን ብር (ETB) ከP2P ላይ አስወገደ። ዓለም አቀፉ የክሪፕቶ ምንዛሬ መድረክ የሆነው MEXC የኢትዮጵያ ብርን (ETB) ከP2P ሥርዓቱ ላይ ሙሉ በሙሉ በድንገት ማስወገዱ
MEXC በድንገት የኢትዮጵያን ብር (ETB) ከP2P ላይ አስወገደ። ዓለም አቀፉ የክሪፕቶ ምንዛሬ መድረክ የሆነው MEXC የኢትዮጵያ ብርን (ETB) ከP2P ሥርዓቱ ላይ ሙሉ በሙሉ በድንገት ማስወገዱ ተረጋገጠ። ኩባንያው ቀደም ሲል ይህን አገልግሎት የሚያቆመው እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 ቀን 2026 መሆኑን ገልጾ የነበረ ቢሆንም ከተቀመጠው ቀነ-ገደብ ሃያ ቀናት ቀድሞ ውሳኔውን በተግባር አውሏል። በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ብር ምርጫ ከፕላትፎርሙ ላይ ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያን የፋይናንስ ህግ መሰረት አድርገው ፦ - ቴሌግራም ዋሌት - ቢትጌት - ባይናንስ - ኦኬኤክስ - ባይቢት ... የመሳሳሉ መድረኮች በኢትዮጵያን ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶች (P2P) ማቆማቸው ይታወሳል። ብሔራዊ ባንክ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ሥርዓት ያለው የዲጂታል ፋይናንስ ተሳትፎ እንዲኖር የሚያስችል አጠቃላይ የቁጥጥር ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቆጣጣሪዎችና ከአገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑን መግለጹም ይታወሳል። @Addis_News @Addis_News

ትራምፕ ለኢራን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️ 👉ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል-ኢራን‼️ #አሜሪካ በኢራን ላይ አዳሯን ከባድ ጥቃት አደረሠች። # ዋሽንግተን በቶማሃውክ ሚሳኤል ጭምር እስከ #ቴህራን አ
+1
ትራምፕ ለኢራን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️ 👉ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል-ኢራን‼️ #አሜሪካ በኢራን ላይ አዳሯን ከባድ ጥቃት አደረሠች። # ዋሽንግተን በቶማሃውክ ሚሳኤል ጭምር እስከ #ቴህራን አቅራቢያ ጥቃት ማድረሷን በፕሬዚዳንቷ በኩል ገልፃለች። #ኢራንም በምላሹ በጆርዳን እና ኩዬት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች ላይ ከ12 በላይ ሚሳይል እና ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሰንዝራለች። በሆርሙዝ ሰርጥም ሁለት መርከቦችን መትቻለሁ” ብላለች። የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን #በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፍ የትኛውም ዓይነት መርከብ አይኖርም ያለችው ሰርጡ ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል ስትል በጦር ቃል አቀባያዋ በኩል ይፋ አድርጋለች። ኢራን ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቧል ካለች በኋላ አለምአቀፍ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የ 2 ዶላር ጭማሪ አሳይቷል። የአሜሪካ የቀጠናው ዕዝ ግን የንግድ መርከቦች አሁንም በሆርሙዝ እያለፉ ነው ሲል መግለጫ  ሰጥቷል። አሜሪካ በምሽቱ ጥቃት 49 አቶማሃውክ ሚሳዔሎችን በመጠቀም 18 ኢላማዎችን መምታታቸውን ትራምፕ አሳውቀዋል። ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ኢራን ወደ ስምምነት ካልመጣች ከምድረ ገፅ ይጠፋሉ ሲሉ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ ልከዋል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት «ኤር ካናዳን» ሲያበር የነበረው ካፒቴን ተያዘ ረቡዕ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የካናዳ ፖሊስ የ59 ዓመቱ የ«ኤር ካናዳ» ካፒቴን ጄፍሪ ዎል አስፈላጊው የበረራ
የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት «ኤር ካናዳን» ሲያበር የነበረው ካፒቴን ተያዘ ረቡዕ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የካናዳ ፖሊስ የ59 ዓመቱ የ«ኤር ካናዳ» ካፒቴን ጄፍሪ ዎል አስፈላጊው የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት በማጭበርበር በመስራቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቋል። ግለሰቡ ከ2009 እስከ 2025 ባሉት ዓመታት ውስጥ የሀሰት ሰነዶችን በመጠቀም ቦይንግ 767፣ 777 እና 787 አውሮፕላኖችን በመያዝ ከ900 በላይ በረራዎችን የመራ ሲሆን፣ ወደ 3 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ አግኝቷል። ኤር ካናዳ ጉዳዩን በጥብቅ እየመረመረው መሆኑን ገልጾ፣ አብራሪዎች በየስድስት ወሩ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ስለሚያልፉ የመንገደኞች ደህንነት አደጋ ላይ እንዳልወደቀ አስታውቋል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ብልፅግና ፓርቲ የተወዳደረባቸውን ወንበሮች በሙሉ አሸነፈ 👉 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ምንም መቀመጫ አላሸነፉም። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ብልፅግና ፓርቲ የተወዳደረባቸውን ወንበሮች በሙሉ አሸነፈ 👉 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ)  ምንም መቀመጫ አላሸነፉም። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ከፊል ውጤት እወጃ በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የሌሎች 22 የምርጫ ክልሎችን ውጤት አፅድቆ ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት፣ ከተገለጹት ጠቅላላ 48 የምክር ቤት መቀመጫዎች መካከል ከአንዱ በስተቀር የገዢው ብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ያሸነፉ ሲሆን፣ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ዕጩ ደግሞ በሶማሌ የክልል ምክር ቤት አንድ ወንበር ማሸነፉ ታውቋል። በደገ ሀቡር አንዱን ወንበር የኦጋዴን ግንባር ዕጩ የነበሩት አቶ መሀሙድ ሀሰን ሁሴን አሸንፈዋል። ለክልል ምክር ቤቶች በጠቅላላው የ12 የክልል ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ውጤቶች ተነግረዋል። የክልል ምክር ቤት ምርጫዎች በየምርጫ ክልሉ ብዙ መቀመጫዎች ያሏቸው በመሆኑ፣ በድምሩ የ38 መቀመጫዎች ውጤት የታወጀ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ ብልፅግና ፓርቲ 37ቱን አሸንፏል። ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላላው የ10 የምርጫ ክልሎች/ወንበሮች ውጤት የተገለጸ ሲሆን (1 ከአማራ፣ 3 ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና 6 ከኦሮሚያ)፣ 10ሩንም መቀመጫዎች በሙሉ የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች አሸንፈዋል። ውጤታቸው የተገለጹት የምርጫ ክልሎችም በአማራ ክልል ጎዛምን፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቀዲዳ ጋሜላ 2፣ ጉመር 1 እና እዣ 2 ሲሆኑ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ ሀብሮ 1፣ ቅንበቢት፣ ጥቁር እንጭኒ፣ ጀልዱ፣ ወሊሶ 2 እና ወሊሶ 1 የምርጫ ክልሎች ናቸው። በውጤት እወጃው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ)  ምንም መቀመጫ አላሸነፉም። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የደቡብ አፍሪካው ስታንቢክ ባንክ በኢትዮጵያ በብቸኝነት በባለቤትነት የሚያስተዳድረውን ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም እያሰበ መኾኑ ተሠማ። ባንኩ ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም ያሰበው፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵ
የደቡብ አፍሪካው ስታንቢክ ባንክ በኢትዮጵያ በብቸኝነት በባለቤትነት የሚያስተዳድረውን ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም እያሰበ መኾኑ ተሠማ። ባንኩ ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም ያሰበው፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የኢንቨስትመንት ወጪ እየቀነሠና ገቢው እየጨመረ መሄዱን እንደ ጥሩ ምሳሌ በመውሠድ እንደኾነ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ስታንቢክ ባንክ የግዙፉ የደቡብ አፍሪካ ስታንዳርድ ባንክ አንድ ካል ነው። ብሄራዊ ባንክ ያወጣው ሕግ፣ በአገር ውስጥ ባንክ የአክሲዮን ድርሻ መግዛት የሚፈልጉ የውጭ ባንኮች ድርሻቸው ከ49 በመቶ እንዳይበልጥ ገደብ ይጥላል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

'በአዲስ አበባ በጥበቃ ተሰማርተው የነበሩ ሁለት ደረሶች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ታወቀ‼️ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በሁለት ደረሶች አሰቃቂ ግድያ ዙሪያ ህብረተሰቡ መግለጫ እስኪሰጥ በትዕግስ
'በአዲስ አበባ በጥበቃ ተሰማርተው የነበሩ ሁለት ደረሶች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ታወቀ‼️ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በሁለት ደረሶች አሰቃቂ ግድያ ዙሪያ ህብረተሰቡ መግለጫ እስኪሰጥ በትዕግስት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል። ​በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 (ሰሚት ጨርቆስ ኮንዶሚኒየም መግቢያ) በጥበቃ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ ሁለት ደረሶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለው መገኘታቸውን ተከትሎ፣ የክፍለ ከተማው እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መረጃዎችን አጠናቅሮ መግለጫ እስኪሰጥ ድረስ ህብረተሰቡ በትዕግሥት እንዲጠብቅ አሳሰበ። ​ሟቾቹ ሙሐመድ አደም እና ሙሐመድ ዓሊ የተባሉ የጥበቃ ሰራተኞች ሲሆኑ፣ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ በመልካም ስነ-ምግባራቸው የሚታወቁ የዲን ተማሪዎች (ደረሶች) እንደነበሩ ተገልጿል። ከሟቾቹ መካከል ሙሐመድ ዓሊ የልጆች አባት መሆኑም ታውቋል። ​ግድያው የተፈፀመው ቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ል ሌሊት እንደሆነ የተገመተ ሲሆን፣ አስክሬናቸው ከሁለት ቀናት በኋላ ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ል መገኘቱ ተጠቁሟል። ሟቾች የጥበቃ ስራ በሚሰሩበት ስፍራ ምንም ዓይነት የንብረት ስርቆት ወይም የዘረፋ ምልክት አለመገኘቱ የግድያውን አሰቃቂነት አጉልቶታል። ​የሟቾች የቀብር ስነ-ስርዓት ትላንት ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ል በኮልፌ የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ተፈጽሟል። የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በጉዳዩ ዙሪያ ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁሞ፣ መረጃዎችን አጠናቅሮ ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥ በማስታወቅ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በትዕግሥት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የጭቃ ቤት ግንባታ ተከለከለ‼ አሁን ላይ ተፈፃሚ የሆነው በአንድ ክልል ነው በቀጣይ ግን በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚተገበር ተነግሯል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የከተማና መሠ
የጭቃ ቤት ግንባታ ተከለከለ‼ አሁን ላይ ተፈፃሚ የሆነው በአንድ ክልል ነው በቀጣይ ግን በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚተገበር ተነግሯል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ከተሞችን ለማዘመን እና ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተጣጣመ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት አዲስ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል። ደብዳቤው ከደረሰበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ማዘጋጃ ቤት በኩል የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃድ ማጽደቅ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። በእንጨትና ጭቃ ግንባታ ሳቢያ የሚመጣውን የደን መመናመን ለመግታት እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን የድርቅና የጎርፍ አደጋ ለመከላከል ነው። ማንኛውም ግንባታ ከተማን በሚያዘምኑና ደረጃቸውን በጠበቁ ግብዓቶች ማለትም በብሎኬት፣ በጡብ እና በተሻሻሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ብቻ መከናወን እንዳለበት ታዟል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ኩዬት ለኢትዮጵያውያን ፈቀደች‼️ ኩዌት ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን ለመቅጠር ፈቀደች። የኩዌት የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር የቤት ሰራተኞች ቅጥርን የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ዘገባ አመላከተ። ​በአዲሱ መመሪያ መሰረት ኩዌት ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን (ወንድም ሴትም) ለመቅጠር ፈቅዳለች። የተፈቀደላቸው ቀሪዎቹ ሀገራት ደቡብ አፍሪካ፣ ቤኒን፣ ፊሊፒንስ፣ ስሪላንካ፣ ሕንድ፣ ቪየትናም፣ ኔፓል እና ሴኔጋል (ለወንዶች ብቻ) ናቸው። ​የቅጥር ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግም ማመልከቻዎች በየግዛቱ በሚገኙ የአገልግሎት ማዕከላት በኩል እንደሚስተናገዱ የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል። @Tekus_Info @Tekus_Info

በኦሮሚያ ክልል ፤ አርሲ ውስጥ በጥቃት አድራሾች የተቃጠለው ቤተክርስቲያን ሊሠራ ነው ተባለ! «በአርሲ የተቃጠለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን መልሰን እንሠራለን።» -የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች።
በኦሮሚያ ክልል ፤ አርሲ ውስጥ በጥቃት አድራሾች የተቃጠለው ቤተክርስቲያን ሊሠራ ነው ተባለ! «በአርሲ የተቃጠለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን መልሰን እንሠራለን።» -የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከአንድ ሳምንት በፊት ስለተፈጸመው የኦርቶዶክሳውያን ግድያና የቤተ ክርስቲያን መቃጠል ኃዘናቸውን በመግለጥ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናቸውን ማሳወቃቸው ተዘግቧል ። በኦሮሚያ ክልል፤ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ ቀን እና በዋዜማው ግንቦት 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በተፈጸመው ጥቃት ንጹሐን ምእመናን መገደላቸው ተዘግቧል ። ከተፈጸመው ግድያ በተጨማሪ ከመቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደተቃጠለ ይታወሳል። @Addis_News @Addis_News