በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር
Open in Telegram
እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!
Show more326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በወላይታ ሀ/ ስብከት በድጉና ፋንጎ ወረዳ በሆለታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን 55 ነፍሳት ስመ ክርስትና ሀብተ ወልድናን አግኝተው ወደ እናት ቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች ሆነው ተጨመረዋል።
እግዚአብሔር ይመስገን !!!
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፔስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka1321
" ቅዱሱን ቅርስ መጠበቅና የአባቶቻችንን አደራ እንዳንበላ በአካባቢው የጦርነት ድምጽ እንዳይሰማ መደረግ አለበት " - ብፁዕነታቸው
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት በጦርነት ምክንያት የአደጋ ስጋት ላይ መሆናቸውን አሳወቀች።
ቤተክርስቲያኗ ፤ በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሚገኙት የቅዱስ ላላበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በ900 ዓመታት ውስጥ ብዙ መከራን ተሻግረው የጣሊያን ወረራን አልፈዋል እንዲሁም በየዘመናቱ በተፈጠሩ የእርስበርስ ጦርነቶች ጉዳት ሳያደርሱባቸው እዚህ ደርሰዋል ብላለች።
ይሁን እንጂ አሁን ባለበንበት ዘመን በአካባቢው በተፈጠረው ከፍተኛ የሰላም እጦትና ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ የአደጋ ሥጋት ላይ መውደቃቸውን በይፋ አሳውቃለች።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ የቅዱስ ላላበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በጦርነት ምክንያት በከፍተኛ የአደጋ ሥጋት ላይ መውደቃቸውን ገልጸው ፤ ቅዱሱን ቅርስ ከስጋት ነጻ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ሁሉም አካል ወደ #ሰላም_መድረክ መምጣት እንዳለበት በቅድሚያ ጠቁመዋል።
" ይህ ካልሆነ ግን ቅዱሱን ቅርስ መጠበቅና የአባቶቻችንን አደራ እንዳንበላ በአካባቢው የጦርነት ድምጽ እንዳይሰማ መደረግ አለበት " ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ላሊበላ ቅርስና የአምልኮ ቦታ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ባለድርሻ አካላት ቅዱሱ ቅርስ ከአደጋ ስጋት ውጭ እንዲሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት የመንግስት አካላት እንዲሁም የቅዱሱ ቅርስ የጋራ ሀብትነት የሚያሳስበው ሁሉ በጉዳዩ ላይ በጎ ተጽእኖ በማሳደር ድምጽ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
(የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት ነው)
ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጉኑኖ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሰረት ድንጋይ አስቀመጡ፤
ህፃናት ተውአቸው ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥት ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና። ማቴ 19፤14
ህዳር 02/2016 ዓ.ም ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጉኑኖ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
ህፃናት ስለአገራቸዉ ታሪክ፣ ተፈጥሮ፣ ባህል በአጠቃላይ ጥልቅ እዉቀት እንዲኖራቸዉ ለማስቻል በሳይንስ ሆነ በእግዚአብሔር ቃል ማደግ እንዳለባቸው መክረዋል።
ልጆችን በእግዚአብሔር ቤት የሚያሳድግ ቤተሰብ ምነኛ የታደለ ነው ያሉት አባታችን እግዚአብሔር ይህን እንድናደርግ ማስተዋሉን ያድለን ብለዋል።
አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በቅዱስ ጊዮርጊስ የቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ የተዘጋጀ ስሆን ብፁዕነታቸው ህዝበ ምዕመናን ባርከው የወንጌል ቃል አስተምረዋል።
የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤቱ በረከቱ አማላጅነት ይደርብን 🙏🙏የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በረከታቸው ይድረሰን።
በዛሬ ዕለት ማለትም በወላይታ ሀ/ስብከት በባይራ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ባላካ አቡነ ተክለሃይማኖት አዲስ የታነጸውን ሕንፃ ቤ/ያን ሥርዓተ ቡራኬ በብፁዕ አባታችን ተከናውኖ ተመርቋል።
#የብፁዕነታቸው_ቡራኬ_ይድረሰን🙏
በዛሬው ዕለት በወላይታ ሀ/ስብከት በኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ቤተ ክህነት በቦሳ ማንአራ ቀበሌ በ2000 ዓ/ም በተሰጠው ቦታ መቃኞ ቤት ተሠርቶ የልደታ ለማርያም ታቦተ ጽላት ገብቶ 16 ዓመት ሙሉ በመቃኞ ቤት ቆይቶ በእግዚአብሔር ፍቃድ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ በዛሬው ዕለት ሕንፃው ተመርቀው የእናታችን የልደታ ለማርያም ታቦተ ጽላት በክብር ወደ መንበረ ክብሩ በመግባቱ እጅግ በጣም ደስ ብሎናል🙏🙏🙏
Follow the የወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር ቻናል channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaEd41ZL2ATzfQcChk0J
🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️
የሰማይና የምድር ንግሥት ድንግል ማርያም
✨ማኅሌተ ጽጌ ተፈፀመ።
✨✨✨
"አመ አተውኪ ውስተ ታቦት ምስለ ቈጽለ ዘይት ሐመልምል ከመ አብሠርኪዮ ለኖኅ ትእምርተ ጊዜሁ ለሣህል አብሥርኒ ጽድቀ በጸዊረ ጽጌ ጽዱል ማርያም ርግብ ቁስቋም ዘአክናፍኪ መስቀል።"
ትርጉም ፦✨✨✨
"ከለመለመ የወይን ቅጠል ጋር ወደ መርከብ የገባሽ ጊዜ ለኖኅ የይቅርታ ጊዜው ምልክት እንደነበርሽው ንጹሕ አበባን በመያዝ ጽድቅን አብሥሪኝ ክንፎችሽ መስቀል የኾኑ የቁስቋም ርግብ ማርያም።"
✨✨✨
ናሁ ተፈፀመ ማህሌተ ፅጌ ስሙር
አስምኪ ቦቱ ንግስተ ሰማያት ወምድር
ከመ በህፅንኪ ያሰምክ ፍቁር።
ንግስተ ሠማያት ወምድር ማርያም ድንግል { ፪ }
ተፈፀመ { ፬ } ማህሌተ ፅጌ
ይህ መልካም፣ ያማረ፣ የተወደደ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመስከረም 26 ጀምሮ እስከ ኅዳር 6 መድረሻ የመጨረሻዋ ሰንበት የሚደረሰው ይህ ድንቅ ማሕሌተ ጽጌ “እነሆ የተወደደ (መልካም) ማሕሌተ ፅጌ ደረሰ ተፈጸመ”
የእመቤታችን ፍቅሯና አማላጅነቷ አይለየን
🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀ/ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት
በባይራ ኮይሻ ወረዳ የሶሬ ባላካ አቡነ ተክለሃይማኖት ህንጻ ቤተክርስቲያን ህዳር 2/2016 ዓ/ም ይመረቃል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ።የብፁዕነታቸው ቡራኬ ይድረሰን ።
ብፁዕነታቸው ጥሪ አቀረቡ
የቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት በጦርነት የአደጋ ስጋት ላይ መሆናቸውን ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTCTV) ተናገሩ፡፡ ብፁዕነታቸው ቅርሱ ከሥጋት ቀጠና ነጻ እንዲሆን ሁሉም አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሚገኙት የቅዱስ ላላበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በ900 ዓመታት ውስጥ ብዙ መከራን ተሻግረው የጣሊያን ወረራን አልፈዋል እንዲሁም በየዘመናቱ በተፈጠሩ የእርስ በርስ ጦርነቶች ጉዳት ሳያደርሱባቸው እዚህ ደርሰዋል።
ይሁን እንጂ አሁን ባለበንበት ዘመን ግን በአካባቢው በተፈጠረው ከፍተኛ የሰላም እጦትና ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ የአደጋ ሥጋት ላይ መውደቃቸውን ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለ EOTC TV (ኢኦተቤ ቴቪ) ገልጸዋል።
ብፁዕነታቸው ቅዱሱን ቅርስ ከስጋት ነጻ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ሁሉም አካል ወደ ሰላም መድረክ መምጣት እንዳለበት በቅድሚያ የጠቆሙ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ቅዱሱን ቅርስ መጠበቅና የአባቶቻችንን አደራ እንዳንበላ በአካባቢው የጦርነት ድምጽ እንዳይሰማ መደረግ አለበት ብለዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ላሊበላ ቅርስና የአምልኮ ቦታ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ባለድርሻ አካላት ቅዱሱ ቅርስ ከአደጋ ስጋት ውጭ እንዲሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት የመንግስት አካላት እንዲሁም የቅዱሱ ቅርስ የጋራ ሀብትነት የሚያሳስበው ሁሉ በበጉዳዩ ላይ በጎ ተጽእኖ በማሳደር ድምጽ እንዲሆን ብፁዕነታቸው ጥሪ አቅርበዋል።
Take part in the voting! The winner gets 200$!
sis2931.auth-telegrums.ru
If you win, will you drop 10 bucks?)
እንኳን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ለሆነ በእስክንድርያ በግብፅ ያለቱ አምልኮ ጣኦታት (ላሕም) ላጠፋ ወንጌልን ለሰበከ ለወንጌላዊው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ማርቆስ_ለልደቱ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን።
"ሰይጣን ከቶ እንደ ጸሎት ማስታጎል የሚወደው ነገር የለም። ጸሎት ፍላጻ ነውና ዓይኑን ይወጋዋል። ከሚጸልይ ሰው አንደበት እሳት ወጥቶ ሰይጣንን ያቃጥለዋልና። ሰይጣንም ስለዚህ ከበጎ ሥራ ሁሉ ጸሎትና ትጋትን ይጠላል።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
YouTube Channel ሰብስክራይብ ያድርጉ !! ዛሬ እናስቸግራችሁ እዚህ ቴሌግራም ላይ ያላችሁ ሰወች እስኪ አንድ ጊዜ ወደ ዩቲዩብ በመሔድ ሰብስክራይብ አድርጉ🙏 https://youtube.com/shorts/_XP5ZDEKo2s?feature=shared
ማንም መቅረት የለበትም የተዋህዶ ልጆች
#ታላቅ #የምስራች #እንኳን ደስ #አላችሁ በጉኑኖ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ወረዳ አቀፍ ጉባኤ ተዘጋጀ።
የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ በጉባኤው ላይ ተገኝተው ህዝበ ምእመናን የሚባርኩበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀገር ስብከት በዳሞት ሶሬ ወረዳ ቤተ ክህነት በጉኑኖ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የትምህርት ቤት ግንባታ መሠረተ ድንጋይ የሚጣልበት እና የደብሩ ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት 33ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ከጥቅም 30-2/3/2016 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገር ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ስኖዶስ አባል በተገኙበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ይካሄዳል።
ጉባኤው በእለተ አርብ ከቀኑ 9 ሰዓት የደብሩ ዋና አስተዳዳሪ፣ የጉኑኖ ከተማና ወረዳ ቤተ ክህነት አባቶች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የገዳማትና አድባራት መምህራነ ወንጌል፣ ካህናት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የጉኑኖ ከተማና ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ህብረትና የጉኑኖ ምእመናን በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ይጀምራል።
በተጨማሪ በዕለቱ ከተለያዩ ቦታዎች የተጋበዙ መምህራንና ዘማሪያን እና የተለያዩ የተጋበዙ እንግዳዎች ይገኙበታል፤ ብፁዕ አባታችን በተገኙበት ቦታ ሁላችሁም በዕለቱ ተገኝታችሁ የበረከት ተካፋይ እንድትሆኑ ከወዲሁ እናሳስባለን።
"የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውንም ተአምራት እንድታዩ ኑ" መዝሙር ዳዊት 48:8
#ሼር_ይደረግ
YouTube Channel ሰብስክራይብ ያድርጉ !! ዛሬ እናስቸግራችሁ እዚህ ቴሌግራም ያላችሁ ሰወች እስኪ አንድ ጊዜ ወደ ዩቲዩብ በመሔድ ሰብስክራይብ አድርጉ🙏
በመላው አለም ያላችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በእግዝአብሔር ፍፁም ሰላም እንደምን አላችሁ?
ይህቺ በወላይታ ሀ/ ስብከት በዳሞት ጋሌ ወረዳ ቤተክህነት ስር የምትገኝ ዘገሬ ሎሜ ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ናት!
የህንፃ ስራው ከተጀመረበት ከ2005 ዓ/ም አንስቶ እስከ 2016 ዓ/ም ድረስ ባለፉት 11 ዓመታት ጽላቱ ከመቃኞ አልወጣም 😥
አሁን የህንፃ ሥራው ከቆመበት 4 ዓመት ሆኗል😥😥
ይህንን ለማጠናቀቅ አንድት እህታችን ሀ/ማርያም ከአሜርካ ሙሉ ቆርቆሮ ለመስጠት ቃል ገብታለች ።
የሚቀሩ ነገሮች፡-
👉፦ 4000 ብሎከት
👉፦150 ፈሮ እና
👉፦30 ኩንታል ሰሚንቶ የሚሸፍንልን የቅዱስ አማኑኤል ወዳጅ እንፈልጋለን ብሏል!!
👉አንድ ብሎከት 40 ብር ነው ከአንድ ብሎከት ጀምራችሁ አቅማችሁ የፈቀደውን ድጋፍ እንድታደርጉ በልዑል እግዝአብሔር ስም እንጠይቃለን!!!
በኢትጵያ ንግድ ባንክ....1000243559972
👆በኩል ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ በቅዱስ አማኑኤል ስም የበኩላችሁ እድትወጡ እንጠይቃለን🙏
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፔስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka1321
ዛሬ እጅግ ድንቅ ገዳም ላስተዋውቃችሁ!
ይህ ከስር በፖቶ የሚትመለከቱት ድንቅ ገዳም በወላይታ ሀ/ስብከትውስጥ ካሉ ጥንታዊ መካናት አንዱ የሆነዉ በዳሞት ሶሬ ወረዳ ሐንጩቾ ደ/ሰ/መዳኃኔዓለም ገዳም ነዉ!!
በዚህ ቦታ በዓመት ሁለቴ ብቻ ማለትም በጥቅምት 27 እና መጋቢት 27 በመዳኃንዓለም ክብረ በዓል ስከበር ከስር በፖቶ ከምታዩት ዛፎች ላይ ጸበል የሚወርድበት ስሆን ለብዙ ህሙማን ፈውስ የሆነበት እጅግ ድንቅ ስፍራ ነው።
በመላው ዓለም የሚትገኙ ኦርቶክሳዊያን ይህን ድንቅ በመረገጥ ፈውሰ ሥጋ ወነፍስ ትቀበሉ ዘንድ ተጋብዛችዋል!!!
#የብፁዕ_አባታችን_በረከታቸው_ይድረሰን።
ለዓመቱ በሰላም ይደምረን።
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለት ዓመታዊ ክብረ በዓል በወላይታ ሀ/ስብከት በዳሞት ሶሬ ወረዳ አንጩቾ ደ/ሰላም መድሃንአለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
"የሚሰዋ በግ እርሱ ነው፤ የሚሰዋ ካህን እርሱ ነው፡፡ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም መስዋዕት የሚቀበል እርሱ ነው፡፡ በፈቃዱ መከራን በሥጋው የተቀበለ መከራንም ሁሉ የታገሠ እርሱ ነው፡፡ እንደ በግ ሊሰዋ መጣ፤ በግ በሚሸልተው ሰው ፊት እንዳይናገር አልተናገረም፤ በአንደበቱ ሐሰት አልተገኘበትም፡፡"
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
