በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር
Open in Telegram
እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!
Show more326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያን በታሪክም ሆነ በትውልድ የሚያኮራ ውጤታማ ሥራን እንድትሠራና ከቃል ወደ ተግባር እንድትሸጋገር ለማድረግ ይህ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
"የሰው ልጅ እልቂት፣ ሞትና ስደት፣ የአብያተ ክርስቲያናትና የመንፈሳዊ ቅርሶች ውድመት፣ የካህናትና የሊቃውንት ስደትና መከራ፣ የቋሚና የተንቀሳቃሽ ንብረቶች ውድመት፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት፣ በዜጎች መካከል ጥላቻ መስፋት፣ መተማመን መጥፋት፣ የኑሮ ዋስትና ማጣት፣ በስጋት መኖር፣ የማያባራ መከፋፈል፣ የሰብአዊ ክብር ማጣት፣ የመብት ጥሰት፣ የኑሮ ውድነትና የሕዝቦች መፈናቀል በአደባባይ እየታዩ ያሉ ሰብአዊ ሰቆቃዎች ናቸው።"
ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)
ሀገራዊ ሰላምን ፣ መረጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መግለጫ አውጥቷል።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
“ሰላምየ አኀድግ ለክሙ ወሰላመ አቡየ እሁበክሙ፡- ሰላሜን እተውላችኋለሁ፥ የአባቴ ሰላምም እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.14፡27)
ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፤
ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና ደኅንነት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ቀዳሚ ተልእኮዎች ናቸው፡፡ በሃገራችን ሰላምን ለማስፈን ቅድስት እናት ቤተ ክርስቲያን ከቀድሞ ጀምሮ ብዙ ጥረት ስታደርግ ኑራለች፡፡ አሁንም ሊኖራት የሚገባውን ተግባራዊ ሚና መወጣት ይኖርባታል፡፡
በተለይም ሰላም በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊ፣ በግለሰብ፣ በተቋም፣ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ክበብ ውስጥ ያለውን የተሣሠረ ሁለንተናዊ ትርጉም ከግምት ውስጥ ያስገባ ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
ለሰላም መደፍረስና መታጣት ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳትና ያስከተሉትን የሰው ልጅ እልቂት፣ ሞትና ስደት፣ የአብያተ ክርስቲያናትና የመንፈሳዊ ቅርሶች ውድመት፣ የካህናትና የሊቃውንት ስደትና መከራ፣ የቋሚና የተንቀሳቃሽ ንብረቶች ውድመት፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት፣ በዜጎች መካከል ጥላቻ መስፋት፣ መተማመን መጥፋት፣ የኑሮ ዋስትና ማጣት፣ በስጋት መኖር፣ የማያባራ መከፋፈል፣ የሰብአዊ ክብር ማጣት፣ የመብት ጥሰት፣ የኑሮ ውድነትና የሕዝቦች መፈናቀል በአደባባይ እየታዩ ያሉ ሰብኣዊ ሰቆቃዎች ናቸው፡፡
“ብፁዓን ገባርያነ ሰላም እስመ እሙንቱ ውሉደ እግዚአብሔር ይሰመዩ፡- የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና” (ማቴ.5፡9) በማለት ጌታችን ያስተማረው ትምህርት የቤተ ክርስቲያን መመርያ ነው፡፡
የቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአስታራቂነት ድርሻ፣ የሃገር አንድነትና የሕዝብን ሰላም ለመጠበቅ በታሪኳ ያደረገችው አስተዋጽኦ በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፡፡
የቤተ ክርስቲያን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነትና የሊቃውንቷን ሰላምን የማስፈን ክሂሎት፣ ችግርን የመፍታት ጥበብ አሁንም ተጠናክሮ መተግበር ይኖርበታል፡፡
የሰላምን ወሳኝ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባትና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የሰላምና የዕርቅ ሰነድ በማዘጋጀት የመሪነት ተሳትፎ እንድትፈጽም ገለልተኛና ሰውን ማእከል በማድረግ ታገለግላለች፡፡
ካህናትና መላው አገልጋዮች የሰላም ልዑካን እንዲሆኑ፤ ሰላምን ግንባር ቀደም ሐዋርያዊ ተልእኮዋ አድርጋ ትንቀሳቀሳለች፡፡
በሃገራዊ የሰላምና የዕርቅ ጥረቶች አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚያስችል ይፋዊ ውክልና እንዲኖራት፣ በሥነ ምግባርና በግብረ ገብነት ትምህርት የራስዋን ኃላፊነት እንድትወጣ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሃገራዊም ሆነ በራስዋ መዋቅር በሰላም ዙርያ አስተዋጽኦዋን ለማሳደግና የሚጠበቅባትን ለመወጣት ትችል ዘንድ የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ለቤተ ክርስቲያን መመርያዋ ጽድቅን፣ እምነትን፣ ፍቅርን አጥብቀህ ተከተል ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ያዘዘው መመሪያ ነው፡፡ (፪ኛ ጢሞ. ፪፡ ፳፪)
ሰላምን ሳታዳላ በሩቅም በቅርብም ላሉት ትሰብካለች፡፡
• “ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ” እንዲል (ኤፌ.፪፡፲፯)፡፡
ለቤተ ክርስቲያን ሰላም መሣርያዋ፣ ሕይወቷ፣ ጸሎቷ፣ ቀኖናዋና ዶግማዋ ነው፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ስለዚህ “ሰላም ከሌላችሁ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የለም” በማለት የሰው ልጅ ሰላማዊ እንዲሆን ታስተምራለች፡፡
ጥላቻን አጥብቃ ትቃወማለች፡፡ “ጥልን በመስቀሉ ገደለ” የሚለውን መልእክት እንደ ሰንደቅ የምትጠቀምበት መለያዋ ነው፡፡ ስለዚህ በሰዎች መካከል የተከሰተውን ጥላቻ በተሰጣት መንፈሳዊ ጥበብ ማስወገድ ተልእኮዋ ነው፡፡
በሰላም ግንባታ ኢትዮጵያውያንን ያለ ልዩነት በማሳተፍ ቤተ ክርስቲያን የሰላም ሚናዋን በጥበብና በማስተዋል በቋሚነት ትሠራለች፡፡
ሰላምን ያሳጡን ጦርነቶችና ግጭቶች ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙና በአጭሩ እንዲቋጩ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፤ እምቢ ባዮችንም በማውገዝ ዘላቂ መፍትሔ የሚገኝባቸውን ሂደቶችን ትቅይሳለች፡፡
የሰላም ሰነዶችን በማዘጋጀት አስቸኳይ የሆነ ሃገራዊ የሰላም ንቅናቄ በፍጥነት እንዲጀመርና በዚህም ውስጥ ውጤት ሊያመጣ የሚችል ሥልት ተቀይሶ ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረግ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም፡፡
ቤተ ክርስቲያን የራስዋ የሰላም ከፍተኛ ልዑክ ኖሯት በመዋቅሯ ሁሉ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ የሰላም ሥምሪት ለማድረግ የሚያስችል ንቅናቄ ታደርጋለች፡፡
በሃገራዊ የሰላም ጥረቶች፣ የውይይትና የምክክር መድረኮች ባለድርሻ እንድንሆን ከሚመለከተው ጋር ተቀራርቦ መሥራት የሚቻልበትን አሠራር ትዘረጋለች፡፡
በማኅበራዊ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪ ተቀባይነት እንዲኖረው በትጋት ትሠራለች፡፡
በሰብአዊ ድጋፍና በእርዳታ ማስተባበር ለወገኖቻችን መድረስ እንዲቻል ልጆቿን አስተባብራ ትንቀሳቀሳለች፡፡
በመግቢያችን እንደተጠቀሰው “ፈኑ እዴከ አንሥእ ኃይለከ” ብለው የለመኑ ነቢያትን የሰማ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታችንን እንደሚሰማን ከልባችን በማመን በእርሱ ያለንን ትምክህታችን ይህ በመሆኑ ከጽኑ ተስፋና ፍቅር ጋር እንድንፈጽመው አደራ እንላለን፡፡
በተጨማሪ ይህንን መንፈሳዊ ሥርዓትና መደበኛ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሁሉም በቅንነት እንዲረዳው በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
ዓለማውያን ምሁራን ሃገሮቻቸውን ለመጠበቅ፣ የሕዝባቸውን አንድነት ለማስቀጠል፣ የተረጋጋና እርስ በርሱ የሚተማመን ማኅበረሰብን ለማጽናት በሕግ የሚያስቀጡ “የጥላቻ ንግግርን” የሚያስቀር አዋጅ ያወጣሉ፡፡ ሃገራችንም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን የሚከለክል አዋጅ አላት፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጥላቻንና ሐሰተኛ ትርክቶችን ታወግዛለች፡፡
የአሁኑ ጸሎተ ምኅላ የሚደረገው አለመግባባት በምክክር፣ በውይይት፣ በመደማመጥ እንዲፈታ፤ መከራን በመረዳዳት እንድንሻገር፣ እንደየ ኃላፊነታችን የሚጠበቅብንን ለመወጣትና የሕዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ እንድንችል፣ ችግራችን ሁሉ ተፈትቶ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ከሃሊው አምላክ እንዲያግዘን በአንድነት ለመጮኽ ነው፡፡
ስለዚህ ይህ ዓላማው መንፈሳዊ ብቻ የሆነ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ አዋጅ መሆኑን ተረድታችሁ የሚድያ፣ የትምህርትና የፍትሕ፣ መሰል ተቋማት በሚያስፈልገው ሁሉ እንድትተባበሩን በዚሁ አጋጣሚ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አባታዊ ማሳሰቢያን እናቀርባለን፡፡
ወር በገባ በ፩፩ የቤተክርስትያን ምሶሶ የሱራፌል አምሳያ ማህሌታይ እንድሁም መላ አካሏ የሆነ ኢትዮጵያን ከመላእክት ጋራ በምስጋና አንድ ያደረገ ቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ነው።
እንኳን አደረሳችሁ የተዋሕዶ ልጆች💚💛❤🙏🙏🙏
ለቅዱስ ላሊበላ ገዳም አዲስ አስተዳዳሪ ተሾመ❗❗
አሜሪካ ገብተው በቀሩት አባ ጽጌ ምትክ ለደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም አዲስ አስተዳዳሪ መሾሙን የቤተ ክህነት ምንጮች ገልፀዋል።
የወልድያ መንበረ ጵጵስና ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አስተዳዳሪ የነበሩት አባ ሕርያቆስ ጸጋዬ የገዳሙ አስተዳዳሪ ሆነው መሾማቸውን ምንጮች ገልፀዋል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ቃል ለዘያጸምዖ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ሥጋ ለዘይበልዖ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ደም ለዘይሰትዮ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ፄና ለዘያፄንዎ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ዝክር ለዘይነግር ዜናሁ።
ስሙ የጣፈጠ፣ ቃሉ የጣፈጠ፣ ሥጋው የጣፈጠ፣ ደሙ የጣፈጠ፣ መታሰቢያው የጣፈጠ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይጠብቀን። ከጣዕሙ ያሳትፈን። አያጉድለን።
❤️🙏❤
#ዋዱ_ቁስቋም_ማሪያም_ወላይታ ሶዶ
መልካም ዕለተ ሰንበት💕🙏💕
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132
#followlikecommentandshare
#ዋዱ_ቁስቋም_ማሪያም_ወላይታ ሶዶ
መልካም ዕለተ ሰንበት💕🙏💕
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132
#followlikecommentandshare
📸 Watch this video on Facebook
https://www.facebook.com/share/r/Tau3VpdyQkjXHvFu/?sfnsn=mo&mibextid=vG3cyz
የዋዱ ቁስቋም ማርያም ቤ/ያን
እለተ ቅዳሜ የተደረገ መንፈሳዊ የእግር ጉዞ ከኦቶና ደብረ ፂዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ዋዱ ቁስቋም ማርያም ቤ/ያን
#ድርሻ_አሻራችሁን_ሳታስቀምጡ_እንዳያመልጣችሁ
𝗖𝗕𝗘 𝟭𝟬𝟬𝟬𝟬𝟴𝟱𝟲𝟮𝟭𝟭𝟵𝟯 የልባችሁን መሻት ላኩ
#ታላቅ_ጉባኤ_የዋዱ_ቁስቋም_ማርያም
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ Wolaita Sodo University ተማሪያን ተጀምሮ ታንፆ እና ተውቦ ለማጠናቀቂያ ይረዳን ዘንድ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ ትምህርተ ወንጌል እና #ገቢ_ማሰባሰቢያ ጉባኤ
ደጉዋ እናታችን ቁስቋም ማርያም
#ህንፃማጠናቀቂያ ታላቅ ገቢ ማሰባሰቢያ
CBE 1000085621193 ስለ ድንግል ማርያም
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132
ኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማሪያም ቤ/ያን ወላይታ ሶዶ
🔔ሰናይ ቅዳሚት ሰንበት💕🙏💕
👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
👉ልንኩን በመጫን የፔስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132
የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የቅዳሴ ቤቱ ክብረ በዓል በወላይታ ሶዶ ከተማ በደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም በድምቀት ተከበረ።የሰማዕቱ አማላጅነት አይለየን💕🙏💕
#የዋዱ_ቁስቋም_ማርያም
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ Wolaita Sodo University ተማሪያን ተጀምሮ ታንፆ እና ተውቦ ለማጠናቀቂያ ይረዳን ዘንድ የተዘጋጀ #ሀገር አቀፍ ትምህርተ ወንጌል እና #ገቢ_ማሰባሰቢያ ጉባኤ
ደጉዋ እናታችን ቁስቋም ማርያም
#ህንፃማጠናቀቂያ ታላቅ ገቢ ማሰባሰቢያ
CBE 1000085621193 ስለ ድንግል ማርያም
ሀዳራ ጦሶ ታ ነሶ ያስ ነኬታን ዳናው ታ ዶራስ
https://youtube.com/watch?v=E2Qp7QTS2-o&feature=shared
#ህዳር 6
+በዚች ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ እንዲሁም ከዮሴፍ እና ሰሎሜ ጋር 3 ዓመት ከ 6 ወር በስደት ከተንገላታች በኋላ ወደ ሀገራቸው የተመለሱበት ቀን ነው።
ታድያ ጌታችን በእመቤታችን ጀርባ ላይ ሆኖ በእነዛ የምህረት ጣቶቹ ወደ #ኢትዮጵያ ይጠቁም ነበር እመቤታችንም ልጄ ሆይ ለምንድነው ጣትህን ምታመለክተው ስትለው ""ያቺ የተባረከች ሀገር ናት"" እኔን የሚያመልኩ አንቺን የሚማልዱ በፍቅርሽ የነደዱ ቅዱሳን መነኮሳት የሚፈልቁባት አገር ናት!!ያንቺ ዘመዶች ሰቅለው ይገሉኛል በዚች አገር ያሉ ግን ሳያዩ ያምኑኛል አስራት በኩራት ትሁንሽ ብሎ ሰቷታል በቅዱስ እግራቸውም ጣና ሀይቅን ዋልድባንና ሌሎችንም ዞረው እንደባረኩም ድርሳነ ኡራኤልና ታምረ ማርያም ላይ በስፋት ተጽፏል።
እመቤታችንን ከሐና መሀፀን ፈጥሮ ከፍጥረት አለም ለይቶ ከሁሉ አልቆ የእናት አማላጅ ትሁናችሁ ብሎ የሰጠን ልዑል እግዚአብሔር ይመስገን ! የእመቤታችን ቁስቋም ማርያም ምልጃዋና በረከቷ አይለየን !! ሀገራችንን ሰላም ታድርግልን !!
ኀዳር 6 ቀን ወደ ግብጽ አገር ተሰዳ ስትመለስ ቁስቋም በምትባል አገር ገብታ ያረፈችበት በዓል ነው፡፡
ከገነት የተሰደደውን አዳም ወደ ገነት ለመመለስ ሲል ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከአረጋዊው ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ወደ ግብጽ ተሰደደ፡፡
ጌታችን ከ3 ዓመት ከ6 ወር የግብጽ ስደት በኋላ ወደ እስራኤል እንደሚመለስ አስቀድሞ ነቢየ ልኡል ሆሴዕ በትንቢት መነጽርነት ተመልክቶ “ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት ” ብሎ ተናግሯል ሆሴ 11÷1
ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር - እነሆ የተወደደው ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ!
«ተመየጢ ተመየጢ ሱላማጢስ ...ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ » መኃ ፯፥፩ የተዋህዶ ልጆች እንኳን እመቤታችን ከስደት ተመልሳ ቁስቋም የገባችበት በዓል ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
Follow the የወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር ቻናል channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaEd41ZL2ATzfQcChk0J
