en
Feedback
በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

Open in Telegram

እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!

Show more
326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ወላይትኛ_መዝሙር፦ታና_አሽዳጎ_2xMP3_320K.mp312.21 MB

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳወቀ ! ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ ይሰጣ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳወቀ ! ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫው በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ባይገለጽም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ተነግሯል። ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ለሚሰጠው መግለጫ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ላልሆኑና በቤተክርስቲያኗ ህዝብ ግንኙነት ለተመዘገቡ መገናኛ ብዙሃን በስፍራው እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

" ባልታወቁ ሰዎች በጥይት ከተመቱ በኃላ ህክምና ቢደረግላቸውም ሊተርፉ አልቻሉም " - ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አ
+1
" ባልታወቁ ሰዎች በጥይት ከተመቱ በኃላ ህክምና ቢደረግላቸውም ሊተርፉ አልቻሉም " - ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በኩረ ትጉኃን ዘርዓዳዊት ኃይሉ ተገደሉ። ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ በ11 ሰዓት ባልታወቁ ሰዎች በጥይት ተመትተው ህክምና ሲደረግላቸው ቆይተው ሊተርፉ ሳይችሉ ቀርቶ ሕይወታቸው ማለፉን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ አሳውቀዋል። ብፁዕነታቸው የግድያው ምክንያት እንደማይታወቅ ገልጸው በክስተቱ የተሰማቸውን መሪር ኃዘን ገልጸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኢኦተቤ ቴቪ ነው ያገኘነው።

#እንኳን_ደስ_አላችሁ የወንድሞቻችን የካሴት ምርቃ የዘማሪ ዲ/ን ንጋቱ ማክሶ እና የዘማሪ ዲ/ን ካሳሁን ከበደ ቁጥር 1የወላይተኛ ቋንቋ መዝሙር ምረቃ ስነስርዓት ዛሬ እሁድ በድምቀት ተመርቋል!!
+1
#እንኳን_ደስ_አላችሁ የወንድሞቻችን የካሴት ምርቃ የዘማሪ ዲ/ን ንጋቱ ማክሶ እና የዘማሪ ዲ/ን ካሳሁን ከበደ ቁጥር 1የወላይተኛ ቋንቋ መዝሙር ምረቃ ስነስርዓት ዛሬ እሁድ በድምቀት ተመርቋል!!

አርባ ምንጭ ከተማ 71 ልጆቿን አስጠምቃ የቅድስት ሥላሴ ልጀነትን እንዲያገኙ በማስደረግ ከኦርቶዶክሳዊ በረት ቀላቅላለች። *** እግዚአብሔር ይመስገን ዛሬ ህዳር 30 በአርባምንጭ ደብረ ጸሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በቁጥር 71 የሚሆኑ ከልዩ ልዩ ቤተ እምነቶች የተወጣጡ ነፍሳት በኦርቶዶክሳዊ ምስጢረ ጥምቀት ዳግም ተወልደው የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን እንዲያገኙ ተደርገዋል። ይህን ያደረገ ቅዱስ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን !! #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ 👉👉 https://t.me/httplif👈👈 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

ብፁዕ አባታችን በአሜርካ በርጂኒያ በረከታቸው ይድረሰን በእውነቱ🙏 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.
+2
ብፁዕ አባታችን በአሜርካ በርጂኒያ በረከታቸው ይድረሰን በእውነቱ🙏 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

#ኢየሱሳ_ኑ_ሴባው _የተሰኘ_የወላይተኛ_ቋንቋ_መዝሙር የዘማሪ ዲ/ን ካሳሁን ከበደ እና የዘማሪ ዲ/ን ንጋቱ ማክሶ ቁጥር አንድ የመዝሙር CD ምርቃ ፕ/ም ተዘጋጆቷል !! በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ
+1
#ኢየሱሳ_ኑ_ሴባው _የተሰኘ_የወላይተኛ_ቋንቋ_መዝሙር የዘማሪ ዲ/ን ካሳሁን ከበደ እና የዘማሪ ዲ/ን ንጋቱ ማክሶ ቁጥር አንድ የመዝሙር CD ምርቃ ፕ/ም ተዘጋጆቷል !! በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተክህት አረካ ደብረ ሠ/ቅ/ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጉባኤው የሚጀምረው ከዛሬ አርባ ህዳር 28-30/2016 ዓ/ም ሲሆን ሲዲው የሚመረቀው ደግሞ በዕለተ እሁድ ከጠዋቱ ጀምሮ ታላላቅ እንግዶች በተገኙበት በደመቅ ሁኔታ ይመረቃል። መቅረት አይታሰብም!!! #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

ስብሐት ለከ ኢየሱስ በአፈ ኩሉ ውዱስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቀዳሴ ሥጋ ወነፍስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ለዕሩቃን ልብስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ዘኢይትሰዓር ንጉሥ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቃለ አብ ቅዱስ።
ስብሐት ለከ ኢየሱስ በአፈ ኩሉ ውዱስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቀዳሴ ሥጋ ወነፍስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ለዕሩቃን ልብስ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ዘኢይትሰዓር ንጉሥ፣ ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቃለ አብ ቅዱስ። «መቅድም ዘተአምረ ኢየሱስ»

#እንኳን ለጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም አመታዊ የእረፍት በዓላቸው በሰላም በጤና አደረሳችሁ /አደረሰን🙏 #የጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም ረድኤት ፣በረከታቸው ፣ጸሎት ፣ ልመናቸው አይ
#እንኳን ለጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም አመታዊ የእረፍት በዓላቸው በሰላም በጤና አደረሳችሁ /አደረሰን🙏 #የጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም ረድኤት ፣በረከታቸው ፣ጸሎት ፣ ልመናቸው አይለያችሁ /አይለየን🙏 #ጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም በተሰጣቸው ቃል ኪዳን ሀገራችንን ኢትዮጵያ በዕለተ ቀናቸው ከመከራ ስቃይ፣ ከዲያብሎስ ፈተና ይጠብቁልን🙏😢አሜን ፫ #ጻድቁ አባታችን #አቡነ_ሐብተማርያም(፳፮)አበርቱኝ🙏❤️ #ጾም ፣ጸሎት፣ ልመናችንን እግዚአብሔር ይቀበልልን 🙏

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አምስት በዚህች ቀን የስሙ ትርጓሜ መርቆሬዎስ የሆነ ፒሉ ፓዴር በሰማዕትነት አረፈ። መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው ሁለተ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አምስት በዚህች ቀን የስሙ ትርጓሜ መርቆሬዎስ የሆነ ፒሉ ፓዴር በሰማዕትነት አረፈ። መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው ሁለተኛ ትርጓሜ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዲስ መርቆሬዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜ።

​​በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤ "ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤ ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።" 1ኛ ጴጥርስ 4፥12:13 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ  አሜን        በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤ የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣ በዲገሎ ማርያም፣ በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ሀገረ ስብከቱ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል። በዚሁ ጥቃት በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በዛሬው ዕለት ደግሞ በዲገሉ ማርያም ቤተ ክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ተቃጥሏል።  ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸው ይታወሳል። የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም ርምጃ እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ  በላከው ሪፖርት አረጋግጠዋል። ይህ ዐይነት ሃይማኖት ተኮር ጥቃት በምእመናን ላይ መድረሱ አግባብነት የሌለውና እምነትን በነጻነት የማራመድ መንግስታዊ መብትን የሚጥስ በመሆኑ መሰል  ሕገ ወጥ ጥቃትን ለመከላከልና  ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት መብቶቻቸውን ተቋማዊ በሆነ መንገድ ማስከበር እንዲችሉ  ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ድርጊቱን በማውገዝ ችግሩ ከመሠረቱ እንዲፈታ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መፈለግ ሲገባው በዝምታ በማለፉ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ቅሬታ ተሰምቷታል። ይህ ዐይነቱ ኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ በኩል እየተደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በድርጊቱ እጅጉን ማዘኑን እየገለጸ ጉዳዩን  ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር  በመሆን የሚከታተለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት ሪፖርት እንዲልኩ ቀደም ሲል በደብዳቤ በተላከላቸው የስልክና ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብንና ለሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን በመጸለይ የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት የሚደርሱ ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙና መሰል ጥቃት እንዳይፈጸም ለኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ከለላ እንዲሰጡልን እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ምንጭ: የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

#ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ ሐዋርያዊ አገልግሎት በሀገረ አሜሪካን እያደረጉ ይገኛሉ! የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ኅዳር 21/2016 ዓ ም በዲሲ ርዕሰ አድባራት ደብረ
#ብፁዕ አባታችን አቡነ ይስሐቅ ሐዋርያዊ አገልግሎት በሀገረ አሜሪካን እያደረጉ ይገኛሉ! የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ኅዳር 21/2016 ዓ ም በዲሲ ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ድንግል ማርያም በዓሉን በማህበረ ካህናት ከምዕመናን ጋር አክብረው በዕለቱ የተሰበሰቡ ምዕመናንን ቀድሰው አቁርበዋል በተጨማሪ በእለተ ሰንበት ቨርጂኒያ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ተገኝተው የኅዳር ጽዮን በዓል ላይ ተገኝተው ትምህርተ ወንጌል አስተምረው ቀድሰው አቆረቦዋል። በቦታውም ቀደም ብሎ በወላይታ ሀገረ ስብከት በሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃነትና የኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ሰባኬ ወንጌል መምህር ጥዑመ ልሳንም ብፁዕነታቸውን ከካህናትና ምዕመናንን ጋር ልዩ የሆነ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ቡራኬአቸው ይድረሰን🙏🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

''ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፣ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረዋ
''ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፣ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረዋልምና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ'' ራዕ ፬፥፲-፲፩ እንኳን አደረሰን🙏🙏🙏

#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉባኤ በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተክህነት ጦቂሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት #በብዙ_ፈተና_ያለፈችው_ተአምረኛዋ_የጦቂሳ_ኪዳኔ_ምህረት_ቤተክርስቲያ_ጥሪ!! ለጦቅሳ ቅ/ኪዳነ ምህረ
#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉባኤ   በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተክህነት ጦቂሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት #በብዙ_ፈተና_ያለፈችው_ተአምረኛዋ_የጦቂሳ_ኪዳኔ_ምህረት_ቤተክርስቲያ_ጥሪ!! ለጦቅሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት ምዕመናንና በአጠቃላይ በመላው ዓለም አቀፍ ላሉ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ ታላቅ ደስታ የሆነውን ድንቅ ታምር ታዩ ዘንድ በዕለቱ በቦታው በመገኘት ሁላችሁም እንዲትባረኩ በጦቅሳ በኪዳኔ ምህረት ስም ታላቅ ጥሪ ተደርጎላቿል!!   ታህሳስ 14,2016 ዓ/ት #መቅረት_የለበት!!!          #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏

"ሰይጣንም የአንቺን ምስጋና ወሬ ሲሰማ በብስጭት ጥርሱን ያፏጫል የምስጋናሽ ወሬ በእርሱ ዘንድ መራጃ ነውና እራሱን ይቆርጠዋል፡፡ ከስምሽ አጠራር የተነሣ መብረቅ በኃይል ሲጮህ እንደ ሰማ ሁሉ ይደነግ
"ሰይጣንም የአንቺን ምስጋና ወሬ ሲሰማ በብስጭት ጥርሱን ያፏጫል የምስጋናሽ ወሬ በእርሱ ዘንድ መራጃ ነውና እራሱን ይቆርጠዋል፡፡ ከስምሽ አጠራር የተነሣ መብረቅ በኃይል ሲጮህ እንደ ሰማ ሁሉ ይደነግጣል፡፡ አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ ፈጽሞ ዕረፍት አላገኘም፡፡ ባንቺ ታመመ በልጅሽም ተጨነቀ በአንድ ልጅሽ መስቀል ሥቃይ አገኘው፡፡ ከፍጡራን ወገኖች ሁሉ ይልቅ ሰይጣል አንቺን ይጠላል፡፡" / አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /

ዓመታዊው የኅዳር ጽዮን ክብረ በዓል በወላይታ ሀ/ስብከት በወላይታ ሶዶ ከተማ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማሪያም ቤ/ያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል!
+2
ዓመታዊው የኅዳር ጽዮን ክብረ በዓል በወላይታ ሀ/ስብከት በወላይታ ሶዶ ከተማ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማሪያም ቤ/ያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል!

#ህዳር ★21★ እንኳን ለጽዮን ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏 በዚህች ቀን የእስራኤላውያን መመኪያ የሆነችው በእመቤታችን ስም የተሰየመችው ታቦተ ጽዮን ዳጐን በተባለው ጣኦት ላይ ኃይሏን
#ህዳር ★21★ እንኳን ለጽዮን ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏 በዚህች ቀን የእስራኤላውያን መመኪያ የሆነችው በእመቤታችን ስም የተሰየመችው ታቦተ ጽዮን ዳጐን በተባለው ጣኦት ላይ ኃይሏን ክብሯን የገለጸችበት ቀን ነው። ቅድስት ቤተክርስቲያን ጽዮን ማርያም ስትል ዕለቱን ሰይማ ታከብረዋለች! ሰላም ለ👉💚💛❤🙏🙏🙏