en
Feedback
ጽርሐ ጽዮን ሰ/ት/ቤት(ዘፈጬ ማርያም)

ጽርሐ ጽዮን ሰ/ት/ቤት(ዘፈጬ ማርያም)

Open in Telegram

ይህ በፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን የጽርሐ ጽዮን ሰ/ት/ቤት ይፋዊ የTelegram ገጽ ነው።

Show more
953
Subscribers
-324 hours
-17 days
No data30 days
Posts Archive
ክርስቶስ ''ክርስቶስ ራሱን እንድንበላውና እንድንጠጣው የሰጠን ለእኛ ካለው ታላቅ ፍቅር የተነሳ ነው። ይህንን ያደረገው ከእርሱ ጋር ፍጹም አንድ እንድንሆንና ከእርሱ ጋር አንድ አካል እንድንሆን ነው
ክርስቶስ ''ክርስቶስ ራሱን እንድንበላውና እንድንጠጣው የሰጠን ለእኛ ካለው ታላቅ ፍቅር የተነሳ ነው። ይህንን ያደረገው ከእርሱ ጋር ፍጹም አንድ እንድንሆንና ከእርሱ ጋር አንድ አካል እንድንሆን ነው።"    ( ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ) 🙏📖✨
▪︎ጌታ ሆይ ለቅዱስ ማዕድህ አብቃን!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ርዕስ:-አዲሱ ንጋት በጌታ ማዕድ! ✨
ሰላም ውድ የሰንበት ት/ቤታችን ቤተሰቦች!
ወደ ጌታ ቅዱስ ማዕድ የምንቀርብበትና የአገልግሎት ዘመናችንን በበረከት የምናትምበት ታላቁ ዕለት ሊደርስ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ይህንን ሰማያዊ በረከት ይበልጥ ምቹ በሆነ መንገድ ለመሳተፍ የሚከተሉትን ማስተካከያዎች በፍቅር እንድታውቁልን እንወዳለን፦ 〇.የታናናሽ ሕፃናት ዝግጅት (ከኬጂ - 3ኛ ክፍል / ዕድሜ 5 - 13) ▪︎ሕፃናት በረቡዕ ዕለት (ጳጉሜ 4) እስከ 9:00 ሰዓት መጾም ሊከብዳቸው ስለሚችል፣ በልዩ ሁኔታ ሐሙስ ጠዋት (ጳጉሜ 5) ይቆርባሉ። ▪︎ውድ ወላጆች፤ ልጆቻችሁን አዘጋጅታችሁ ሐሙስ ጠዋት ለቅዱስ ቁርባን እንድታበቁልን በፍቅር እንጠይቃለን። 〇.ከ4ኛ ክፍል እስከ አመራር ድረስ! ▪︎ሁላችንም በአንድነት ራሳችንን በንሰሐና በጸሎት አዘጋጅተን በረቡዕ ዕለት (ጳጉሜ 4) ቅዱስ ቁርባን እንቀበላለን። 〇.ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ አገልጋዮች (ከኮዬ፣ ቦሌ አራብሳና መሰል አካባቢዎች) ▪︎በያላችሁበት ቅርባችሁ ወደሚገኝ ቤተክርስቲያን በመሄድ መቁረብ ትችላላችሁ። ▪︎በየትኛውም ቦታ ብንሆን፣ እኛን በአንድ መንፈስ የሚያስተሳስረንና አንድ የሚያደርገን የጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ነው። እራሳችንን ለዚህ ታላቅ የፍቅር ግብዣ በንሰሐና በጸሎት እናዘጋጅ።
''ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።''( ዮሐ 6÷54 )
( ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ! ) 🙏📖✨

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ርዕስ:-አዲሱ ንጋት በጌታ ማዕድ! ✨
ሰላም ውድ የሰንበት ት/ቤታችን ቤተሰቦች!
ወደ ጌታ ቅዱስ ማዕድ የምንቀርብበትና የአገልግሎት ዘመናችንን በበረከት የምናትምበት ታላቁ ዕለት ሊደርስ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ይህንን ሰማያዊ በረከት ይበልጥ ምቹ በሆነ መንገድ ለመሳተፍ የሚከተሉትን ማስተካከያዎች በፍቅር እንድታውቁልን እንወዳለን፦ 〇.የታናናሽ ሕፃናት ዝግጅት (ከኬጂ - 3ኛ ክፍል / ዕድሜ 5 - 13) ▪︎ሕፃናት በረቡዕ ዕለት (ጳጉሜ 4) እስከ 9:00 ሰዓት መጾም ሊከብዳቸው ስለሚችል፣ በልዩ ሁኔታ ሐሙስ ጠዋት (ጳጉሜ 5) ይቆርባሉ። ▪︎ውድ ወላጆች፤ ልጆቻችሁን አዘጋጅታችሁ ሐሙስ ጠዋት ለቅዱስ ቁርባን እንድታበቁልን በፍቅር እንጠይቃለን። 〇.ከ4ኛ ክፍል እስከ አመራር ድረስ! ▪︎ሁላችንም በአንድነት ራሳችንን በንሰሐና በጸሎት አዘጋጅተን በረቡዕ ዕለት (ጳጉሜ 4) ቅዱስ ቁርባን እንቀበላለን። 〇.ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ አገልጋዮች (ከኮዬ፣ ቦሌ አራብሳና መሰል አካባቢዎች) ▪︎በያላችሁበት ቅርባችሁ ወደሚገኝ ቤተክርስቲያን በመሄድ መቁረብ ትችላላችሁ። ▪︎በየትኛውም ቦታ ብንሆን፣ እኛን በአንድ መንፈስ የሚያስተሳስረንና አንድ የሚያደርገን የጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ነው። እራሳችንን ለዚህ ታላቅ የፍቅር ግብዣ በንሰሐና በጸሎት እናዘጋጅ።
''ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።''( ዮሐ 6÷54 )
( በነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይርዳን!) 🙏📖✨

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ርዕስ:-አዲሱ ንጋት በጌታ ማዕድ! ✨ ሰላም ውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን ቤተሰቦች! ወደ ጌታ ቅዱስ ማዕድ የምንቀርብበትና የአገልግሎት ዘመናችንን በሰማያዊ በረከት የምናትምበት ታላቁ ዕለት ሊደርስ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ይህንን የበረከት ግብዣ ይበልጥ የተዋበ፣ ሥርዓቱን የጠበቀና ለሁላችንም ምቹ ለማድረግ ጥቂት ማስተካከያዎችን በፍቅር ይዘንላችሁ መጥተናል። የምንወዳቸው ታናናሽ ሕፃናት (ከኬጂ እስከ 3ኛ ክፍል ያላችሁ፣ ዕድሜያችሁ ከ5-13 የሆናችሁ) ረቡዕ ዕለት እስከ 9:00 ሰዓት መጾም ሊከብዳችሁ ስለሚችል፣ በልዩ ሁኔታ ሐሙስ ጠዋት (ጳጉሜ 5) ትቆርባላችሁ። ውድ ወላጆችም ይህንን አውቃችሁ ልጆቻችሁን ለሐሙስ ጠዋት ለቅዱስ ቁርባን እንድታዘጋጁልን በፍቅር እንጠይቃለን። ከ4ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ከፍተኛ አመራር ያላችሁ አባላት በሙሉ ደግሞ በአንድነት ራሳችንን በንሰሐ አዘጋጅተን በረቡዕ ዕለት (ጳጉሜ 4) የጌታን ሥጋና ደም እንቀበላለን። አገልግሎታችሁን ለማበርከት ከኮዬ፣ ቦሌ አራብሳና ከተለያዩ ሩቅ ቦታዎች እየመጣችሁ የምታገለግሉ ተማሪዎቻችን ደግሞ እዚያው ያላችሁበት አከባቢ የሚቀርባችሁ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ የጌታን ሥጋና ደም እንድትቀበሉ ማሳሰብ እንወዳለን። በየትኛውም ቦታ ብንሆን እኛን በአንድ መንፈስ የሚያስተሳስረንና አንድ የሚያደርገን የጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ነው። እራሳችንን ለዚህ ታላቅ የፍቅር ግብዣ በንሰሐና በጸሎት እናዘጋጅ።
''ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።''( ዮሐ 6÷54 )
( ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ! ) 🙏📖✨

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን እንደምን አመሻችሁ ውድ አባላት፤ ነገ ማለትም (2/13/2018 ዓ.ም) የልብሰ ስብሐት አጠባ ስለሚኖር፣ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ አጠባው ስለሚጀምር በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን። ✅ መዘፍዘፊያ (ባልዲ) ✅ ላርጎ እና ሳሙና ✅ የልብስ ማጠቢያ ብሩሽ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። ⚠️ ማሳሰቢያ ልብሰ ስብሐት የማጠብ አገልግሎት የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ፣ በዚህ መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆንና እንዳንቀር እናሳስባለን። ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን እንደምን አመሻችሁ ውድ አባላት፤ ነገ ማለትም (2/13/2018 ዓ.ም) የልብሰ ስብሐት አጠባ ስለሚኖር፣ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ አጠባው ስለሚጀምር በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን። ✅ መዘፍዘፊያ (ባልዲ) ✅ ላርጎ እና ሳሙና ✅ የልብስ ማጠቢያ ብሩሽ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። ⚠️ ማሳሰቢያ የልብሰ ስብሐት አገልግሎት የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ፣ በዚህ መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆንና እንዳንቀር በፍቅር እንጠይቃለን። ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️ ''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።" (መዝ
+1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️
''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።" (መዝ 118÷26)
ርዕስ፦ ታሪክ ራሱን ደገመ፤ ፪ኛው ዙር ተመራቂዎቻችን በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተመረቁ!
ተመራቂ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!
ተመራቂ ተማሪዎቻችን መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የ፲፪ኛ ክፍል ተማሪዎች፤ ዛሬ ነሐሴ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የምረቃ ሥነ-ሥርዓታቸውን በድምቀት አከናውኗል። ይህ የምረቃ መርሐ ግብር በሰንበት ትምህርት ቤታችን ታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን፤ አምና ፳፻፲፯ ዓ.ም የተጀመረው ይህ የተቀደሰ ጉዞ ዘንድሮም በስኬት ቀጥሎ ለቤተክርስቲያን ተተኪ ተማሪዎችን ማፍራት ተችሏል።ተማሪዎቹ በቆይታቸው መሠረታዊ የሆኑ የቤተክርስቲያን ትምህርቶችንና ሥነ-ምግባርን የቀሰሙ ሲሆን፣ተማሪዎቻችን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መመሪያ የተዘጋጀውን የምስክር ወረቀት ዛሬ በደስታ ተረክበዋል። 〇.በዚህ በ፪ኛው ዙር የምረቃ መርሐ ግብር ላይ ለምረቃ የበቁ ተማሪዎቻችን ስም ዝርዝር፦ ①.ዲ/ን ሚካኤል ኃይሉ ②.ዲ/ን ዳንኤል ተክላይ ③.አቶ በቃቢል ተሾመ ④.ሰላማዊት ፍስሐ በዕለቱ አባቶችና መምህራን ተገኝተው ለተመራቂዎቹ የምስክር ወረቀት የሰጡ ሲሆን፤ በቀጣይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚኖራቸው ቆይታ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎታቸውንና ኦርቶዶክሳዊ ማንነታቸውን ጠብቀው እንዲጓዙ አባታዊ ምክር ተሰጥቷቸዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሰንበት ት/ቤታችን የሰጠው የዕውቅና ምስክር ወረቀትም በዕለቱ ተበርክቷል።
ቀን:- ፴/፲፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
      ( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️ ''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።" (መዝ
+1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️
''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።" (መዝ 118÷26)
ርዕስ፦ ታሪክ ራሱን ደገመ፤ ፪ኛው ዙር ተመራቂዎቻችን በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተመረቁ!
ተመራቂ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!
ተመራቂ ተማሪዎቻችን መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የ፲፪ኛ ክፍል ተማሪዎች፤ ዛሬ ነሐሴ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የምረቃ ሥነ-ሥርዓታቸውን በድምቀት አከናውኗል። ይህ የምረቃ መርሐ ግብር በሰንበት ትምህርት ቤታችን ታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን፤ አምና ፳፻፲፯ ዓ.ም የተጀመረው ይህ የተቀደሰ ጉዞ ዘንድሮም በስኬት ቀጥሎ ለቤተክርስቲያን ተተኪ ተማሪዎችን ማፍራት ተችሏል።ተማሪዎቹ በቆይታቸው መሠረታዊ የሆኑ የቤተክርስቲያን ትምህርቶችንና ሥነ-ምግባርን የቀሰሙ ሲሆን፣ተማሪዎቻችን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መመሪያ የተዘጋጀውን የምስክር ወረቀት ዛሬ በደስታ ተረክበዋል። 〇.በዚህ በ፪ኛው ዙር የምረቃ መርሐ ግብር ላይ ለምረቃ የበቁ ተማሪዎቻችን ስም ዝርዝር፦ ①.ዲ/ን ሚካኤል ኃይሉ ②.ዲ/ን ዳንኤል ተክላይ ③.አቶ በቃቢል ተሾመ ④.ሰላማዊት ፍስሐ በዕለቱ አባቶችና መምህራን ተገኝተው ለተመራቂዎቹ የምስክር ወረቀት የሰጡ ሲሆን፤ በቀጣይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚኖራቸው ቆይታ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎታቸውንና ኦርቶዶክሳዊ ማንነታቸውን ጠብቀው እንዲጓዙ አባታዊ ምክር ተሰጥቷቸዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሰንበት ት/ቤታችን የሰጠው የዕውቅና ምስክር ወረቀትም በዕለቱ ተበርክቷል።
ቀን:- ፴/፲፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
      ( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️ ━━━━━━━━━━━━━━━━━          ልዩ መንፈሳዊ ሥልጠና ርዕስ:-ሰንበት ተማሪና አገልግሎት!
ክፍል  ፫ ( 3 ):- የማጠቃለያ ሥልጠና!
''አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።'' ( 2ኛ ጢሞ 4÷5 )
💡 አገልግሎት ምንድነው? ከዚህ በፊት በክፍል 1 እና 2 ሥልጠና መማራችን ይታወቃል። ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ክፍል ሦስት እንማራለን። የማጠቃለያ ሥልጠና እንደ መሆኑ መጠን ለአንድ ሰንበት ተማሪ በጣም ልዩና ወሳኝ ሥልጠና ስለ ሆነ ሁላችሁም እንድትገኙ ከወዲሁ ማሳሰብ እንወዳለን። ሥልጠናው የሚመለከታቸው? ①.የሰንበት ት/ቤቱ አመራሮች ②.7ኛ ክፍል ( ቀዳማይ ) የጨረሱ ወጣት ተማሪዎች እና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ተማሪዎች ሁሉ! ③.በሰንበት ት/ቤታችን ከአንድ ዓመት በላይ በገና የተማራችሁ ወጣት ተማሪዎች ( የበገና ተማሪዎች ) እድሜያችሁ ከ 18 ዓመት በላይ የሆነ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📝 በሥልጠናው የሚዳሰሱ ነጥቦች፦ 🔹 አገልግሎትና ፈተናዎቹ በሰንበት ት/ቤት አገልግሎት የሚገጥሙንን መሰናክሎች እንዴት እንሻገራለን? 🔹 አገልግሎት በሰንበት ት/ቤት ሕይወት:- በሰንበት ት/ቤት ውስጥ ያለው አገልግሎት እና አገልጋዮች? 🙋‍♂መርሐ ግብር:- 📅 ቀን፦ ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 🕒 ሰዓት፦ 10:00 ሰዓት ላይ 😇 ቦታ፦ የሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ 🗣️ አሰልጣኝ፦ ዲ/ን ቃለአብ ተካ
▪︎ሰንበት ት/ቤቱን የሚወድ ሁሉ ሥልጠናው ላይ መገኘት አለበት። የሚያሰለጥኑን መምህር በሰንበት ት/ቤት ሕይወት በአመራርነት እና በተለያዩ አገልግሎቶች ከ 15 ዓመት በላይ የቆዩ መምህር እንደመሆናቸው መጠን ብዙ ትምህርት የምናገኝበት ሥልጠና ነው። ሁላችሁም በሰዓት እንድትገኙ ከወዲሁ ማሳሰብ እንወዳለን መቅረት በፍጹም አይፈቀድም።
            ( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ✨ 🕊️ ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት 🕊️ ━━━━━━━━━━━━━━━━━          ልዩ መንፈሳዊ ሥልጠና ርዕስ:-ሰንበት ተማሪና አገልግሎት!
ክፍል  ፫ ( 3 ):- የማጠቃለያ ሥልጠና!
''አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።'' ( 2ኛ ጢሞ 4÷5 )
💡 አገልግሎት ምንድነው? ከዚህ በፊት በክፍል 1 እና 2 ሥልጠና መማራችን ይታወቃል። ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ክፍል ሦስት እንማራለን። የማጠቃለያ ሥልጠና እንደ መሆኑ መጠን ለአንድ ሰንበት ተማሪ በጣም ልዩና ወሳኝ ሥልጠና ስለ ሆነ ሁላችሁም እንድትገኙ ከወዲሁ ማሳሰብ እንወዳለን። ሥልጠናው የሚመለከታቸው? ①.የሰንበት ት/ቤቱ አመራሮች ②.7ኛ ክፍል ( ቀዳማይ ) የጨረሱ ወጣት ተማሪዎች እና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ተማሪዎች ሁሉ! ③.በሰንበት ት/ቤታችን ከአንድ ዓመት በላይ በገና የተማራችሁ ወጣት ተማሪዎች ( የበገና ተማሪዎች ) እድሜያችሁ ከ 18 ዓመት በላይ የሆነ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📝 በሥልጠናው የሚዳሰሱ ነጥቦች፦ 🔹 አገልግሎትና ፈተናዎቹ በሰንበት ት/ቤት አገልግሎት የሚገጥሙንን መሰናክሎች እንዴት እንሻገራለን? 🔹 አገልግሎት በሰንበት ት/ቤት ሕይወት:- በሰንበት ት/ቤት ውስጥ ያለው አገልግሎት እና አገልጋዮች? 🙋‍♂መርሐ ግብር:- 📅 ቀን፦ ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 🕒 ሰዓት፦ 10:00 ሰዓት ላይ 😇 ቦታ፦ የሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ 🗣️ አሰልጣኝ፦ ዲ/ን ቃለአብ ተካ
▪︎ሰንበት ት/ቤቱን የሚወድ ሁሉ የነገው ሥልጠና ላይ መገኘት አለበት። ነገ የሚያሰለጥኑን መምህር በሰንበት ት/ቤት ሕይወት በአመራርነት እና በተለያዩ አገልግሎቶች ከ 15 ዓመት በላይ የቆዩ መምህር እንደመሆናቸው መጠን ብዙ ትምህርት የምናገኝበት ሥልጠና ነው። ሁላችሁም በሰዓት እንድትገኙ ከወዲሁ ማሳሰብ እንወዳለን መቅረት በፍጹም አይፈቀድም።
            ( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

ጌታዬ ሆይ! 😇 ''አንተ አትተወኝ አትጣለኝም አንተ ከእኔ ጋር ካልሆንህ፤ ከእነርሱ መካከል አነስተኛ ከተባለው ጋር እንኳ ልዋጋ አልችልም።'' ( ቅዱስ አባ እንጦንስ ) 🙏📖✨ ▪︎ሁሌም ቢሆን የ
ጌታዬ ሆይ! 😇 ''አንተ አትተወኝ አትጣለኝም አንተ ከእኔ ጋር ካልሆንህ፤ ከእነርሱ መካከል አነስተኛ ከተባለው ጋር እንኳ ልዋጋ አልችልም።'' ( ቅዱስ አባ እንጦንስ ) 🙏📖✨
▪︎ሁሌም ቢሆን የጌታ ጸጋ አይለየን!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✨እንኳን ደስ አላችሁ ለተመራቂ ተማሪዎቻችን!✨ በመንፈሳዊ ትምህርታችሁ ጉዞአችሁን አጠናቅቃችሁ ለምረቃ ለበቃችሁ የ ፳፻፲፰ ዓ.ም የ12ኛ ክፍ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✨እንኳን ደስ አላችሁ ለተመራቂ ተማሪዎቻችን!✨ በመንፈሳዊ ትምህርታችሁ ጉዞአችሁን አጠናቅቃችሁ ለምረቃ ለበቃችሁ የ ፳፻፲፰ ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ! የድካማችሁን ፍሬ የምታዩበትና የምትመረቁበት ዕለት ደርሷል። ርዕስ፦ የመንፈሳዊ ትምህርት የ12ኛ ክፍል ተመራቂዎች የምርቃት ቀን! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መመሪያ ባዘጋጀው መርሐ ግብር መሠረት የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በሚከተለው ዝርዝር ይከናወናል፦ 📝 መርሐ ግብር:- 🗓️ ቀን፦ ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከቀኑ (6:30) ጀምሮ 🙋‍♂️ ቦታ፦ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ▪︎ይህ ዕለት በመንፈሳዊ ዕውቀት የታነጸ ትውልድ ለቤተክርስቲያን የሚረከብበት ታላቅ ቀን ነው። ተመራቂ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆችና የአመራር አባላት በሙሉ በዚህ ታላቅ ቀን ላይ እንድትገኙ ጥሪ እናቀርባለን። ''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።'' ( መዝ 118÷26 )
ለዚህ ክብር ያበቃችሁ አምላከ ቅዱሳን ስሙ የተመሰገነ ይሁን! መልካም የምረቃ በዓል ይሁንላችሁ!" 🕊️✨
ቀን.፳፯/፲፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✨እንኳን ደስ አላችሁ ለተመራቂ ተማሪዎቻችን!✨ በመንፈሳዊ ትምህርታችሁ ጉዞአችሁን አጠናቅቃችሁ ለምረቃ ለበቃችሁ የ ፳፻፲፰ ዓ.ም የ12ኛ ክፍ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✨እንኳን ደስ አላችሁ ለተመራቂ ተማሪዎቻችን!✨ በመንፈሳዊ ትምህርታችሁ ጉዞአችሁን አጠናቅቃችሁ ለምረቃ ለበቃችሁ የ ፳፻፲፰ ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ! የድካማችሁን ፍሬ የምታዩበትና የምትመረቁበት ዕለት ደርሷል። ርዕስ፦ የመንፈሳዊ ትምህርት የ12ኛ ክፍል ተመራቂዎች የምርቃት ቀን! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መመሪያ ባዘጋጀው መርሐ ግብር መሠረት የምረቃው ሥነ-ሥርዓት በሚከተለው ዝርዝር ይከናወናል፦ 📝 መርሐ ግብር:- 🗓️ ቀን፦ ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከቀኑ (6:30) ጀምሮ 🙋‍♂️ ቦታ፦ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ▪︎ይህ ዕለት በመንፈሳዊ ዕውቀት የታነጸ ትውልድ ለቤተክርስቲያን የሚረከብበት ታላቅ ቀን ነው። ተመራቂ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆችና የአመራር አባላት በሙሉ በዚህ ታላቅ ቀን ላይ እንድትገኙ ጥሪ እናቀርባለን። ''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።'' ( መዝ 118÷26 )
ለዚህ ክብር ያበቃችሁ አምላከ ቅዱሳን ስሙ የተመሰገነ ይሁን! መልካም የምረቃ በዓል ይሁንላችሁ!" 🕊️✨
ቀን.፳፯/፲፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
( የሰንበት ት/ቤቱ ትምህርት ክፍል ) 📚

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ርዕስ፦አዲሱ ንጋት በጌታ ማዕድ!✨  
ሰላም ውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን ቤተሰቦች!
የ፳፻፲፰ ዓ.ም የአገልግሎት ጉዟችን ማብቂያ ላይ ደርሰናል። ልክ እንደሚያምሩና ደምቀው እንደሚበሩ ሻማዎች፣ እያንዳንዳችሁ በየአገልግሎት ዘርፋችሁ ስታበሩ ከርማችኋል። አሁን ግን ይህንን የሁላችንንም ብርሃን ይበልጥ የሚያደምቅ፣ አገልግሎታችንንም በሰማያዊ በረከት የሚያትም ታላቅ ዕለት ተቃርቧል። አዲሱ ዓመት (2019 ዓ.ም) ሲመጣ፣ እንደ አንድ ቤተሰብ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በታላቅ ተስፋና በንጹሕ ልብ ልንቀበለው ይገባል። ይህንን ደግሞ የምናደርገው ከብርሃናት ሁሉ ብርሃን ከሆነው ከጌታችን ጋር አንድ በመሆን ነው! ከKG ሕፃናት ጀምሮ እስከ ከፍተኛው አመራር ድረስ፤ ያላችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ፤ የዓመቱን አገልግሎታችንን በቅዱስ ቁርባን በማተም፣ አዲሱን ዓመት የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም እንድንቀበለው ጥሪ እናቀርባለን። የጌታን ሥጋና ደም መቀበል ማለት፣ በውስጣችን ያለውን ብርሃን ማደስና ከምንጩ ጋር ማገናኘት ማለት ነው።2018ን በምስጋና መዝጋት ብቻ ሳይሆን፣ 2019ን ከአምላክ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ ለመጀመር ኃይልን ማግኘት ነው። አንድ ሻማ ብቻውን ከመቆም ይልቅ ከሌሎቹ ጋር ሲተባበር ክፍሉ እንደሚበራ ሁሉ፤ እኛም በአንድነት ስንቆርብ ሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍቅርና የቅድስና ማደሪያ ትሆናለች። ቀጠሯችን፦ጳጉሜ 4 (ረቡዕ) ነው። እራሳችንን ለዚህ ታላቅ የፍቅር ግብዣ በንሰሐና በጸሎት እናዘጋጅ። 🔔መልዕክት🔔 ○.የማይተካ ብርሃን፦የአንተ/የአንቺ መገኘትና መቆርብ ለቤተክርስቲያናችን ትልቅ ትርጉም አለው። ብርሃናችንን አናጥፋ! 💡 ○.አዲስ ጅማሬ፦ 2019ን በቁርባን መጀመር ማለት፣ ዓመቱን ሙሉ በጌታ ጥበቃና ረድኤት ውስጥ መኖር ማለት ነው። 😇 ○.የማይጠፋ ብርሃን፦ ይህን ዓመት በቁርባን ስናትመው፣ መጪው ዓመት በበረከትና በስኬት የተሞላ እንደሚሆንልን ሙሉ ተስፋ አለን። 🤝
"ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።'' ( ዮሐ 6÷56 )
                ( ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ! ) 🙏📖✨