MAUMSJ Official page
👉 This channel is crated to inform you diffrent activities of Mattu University Muslim student jama'a (MUMSJ) If you have comments or questions use 👇👇 @meumsj_bot
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ከዱኒያ በላጮቹ ቀናቶች እነሆ ተጀምረዋልና አትዘናጉ ለዒባዳ ነቃ ነቃ በሉ!! ————— የመጀመሪያዎቹ አስር የዚል-ሒጃ ቀናቶች ————— አምላካችን አላህ ችሮታውና እዝነቱ ሰፊ ስለሆነ ለባሪያዎች በመልካም ስራ ላይ የሚሽቀዳደሙባቸውን ቦታዎችና ቀናቶችን አንዱን ከሌላው በማበላለጥ እድሉን አስፍቷል። እለተ ጁምዓ ከሌሎች ቀናቶች በላጭ እንዲሆን አድርጓል። የረመዷንን ወር ከሌሎች ወራቶች በላጭና መልካም ስራዎች ውድ የሚሆኑበት ልዩ ወር አድርጎታል። ከረመዷን ወር ውስጥም የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ልዩና አማኞች ለመልካም ስራ በተለየ መልኩ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው በመታጠቅ መልካም ስራዎችን የሚሰሩባቸው ታላቅ ቀናት አድርጓቸዋል። ልክ እንደዚሁ ከቀናቶች ውስጥ የመጀመሪያዎችን የዚል-ሒጃ ቀናት ውድና በእነዚህ አስር የመጀመሪያ የዚል-ሂጃ ቀናት የሚሰራን ስራ ከሌላው ጊዜ ሊወዳደር የማይችል ከፍተኛ ደረጃ የሰጠባቸው ውድ ቀናት አድርጓቸዋል። ይህ የአላህ ለባሮቹ የዋለው ውለታና ትሩፋት ነው። ምክንያቱም የሰው ልጆች በተለያየ ምክንያት ተዘናግተው መልካም ስራ ውድና ልዩ ደረጃ የሚያስገኝበት ጊዜ ቢያመልጣቸው እድሜ ሰጥቷቸው በሌላው ጊዜ ከደረሱ ተሽቀዳድመው እንዲጠቀሙ ይረዳቸዋል። በሌሎች ጊዜዎች በአግባቡ ሳያመልጣቸው ተጠቅመው ከሆነም በውድ ጊዜዎች በመልካም ስራ ላይ መልካም ስራ በመጨመር ጌታቸው ዘንድ ተወዳጅ እንዲሆኑ ይረዳቸዋል። ታዲያ በሌሎች ጊዜዎች ሁሉ ከሚሰሩ መልካም ስራዎች በላጭና ውድ የሚሆንባቸው ልዩ ቀናት የዚል-ሂጃ የመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት ናቸውና ነፍሲያችንና ሸይጧንን አሸንፈን በአግባቡ ልንጠቀምባቸው ይገባል። ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:- “በየትኛውም ቀን የሚሰራ መልካም ስራ ከነዚህ ቀናት የበለጠ ስራ ከየት አለ?!፣”…