orthodox300
Open in Telegram
1 675
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1530 days
Posts Archive
1 675
ቅዱስ ኤፍሬም የጌታን ቀሚስ ጫፍ በእጇ ዳስሳ ስለዳነችው ሴት እንዲኽ አለ፦
ምንም እንኳ ጌታችን እኛን ለማዳን ሲል ራሱን መሥዋዕት አድርጎ ስለማቅረቡ የሚታዩ ምልክቶችን ያሳየን ቢሆንም ከዚሁ ጎን ለጎን እርሱ ሁሉን አዋቂ መሆኑን ለማሳየት ተሰውረው ያሉትን ምሥጢራት ይገልጥልን ነበር። እንዲያ ከሆነ ስለምን ታዲያ ጌታችን፡- “ልብሴን የዳሰሰው ማን ነው ብሎ ጠየቀ? እነ ስምዖንስ ስለምን ጌታችንን “አቤቱ፥ ሕዝቡ ያጫንቁሃልና ያጋፉህማል፤ የዳሰሰኝ ማን ነው ትላለህን?”(ሉቃ 8፥45) ብለው መለሱለት። በዚህ ሥፍራ ስምዖን ጌታችንን ሁሉም እየነካው እንደሆነ ለጌታችን ሲናገር ጌታችን ግን ከእነዚህ ሁሉ ሰዎች አንዱ ብቻ በእምነት እንደዳሰሰው ተናገረ። እርሱን የነካው ሕዝብ እጅግ ብዙ ነበር፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ግን አንዱ ከሕማሙ ለመወፈስ ዳስሶታል፡፡ ስምዖን ጴጥሮስ ምን ያህል ሰው እርሱን እንደሚያጋፉት ሲናገር ጌታችን ግን ለስምዖን ጴጥሮስ በእምነት እርሱን ስለዳሰሰው ሰው ነገረው።
ስለዚህ ብዙዎች እርሱን ቢጋፉትም ከብዙ ሕዝብ መካከል የአንዱ ብቻ መዳሰስ እርሱን እንደተሰማው ልብ በሉ። ጌታችንን ብዙዎች የተጋፉት ቢሆኑም ከእነዚህ መካከል ስለ አንዱ ብቻ “ልብሴን የዳሰሰው ማን ነው?” ማለቱ እርሱን ባለመረዳት የነኩት ሁሉ በእርሱ ዘንድ የታወቁ መሆናቸውን ገለጠልን። ሁሉም ባለማስተዋል እርሱን የነኩት ቢሆኑም እርሷ ብቻ ግን እርሱን አውቃ ዳሰሰችው። ብዙዎች እርሱን ሲጋፉት እርሱን ከፍጡር ቆጥረው ነው። ስለዚህ ይህቺ ሴት እግዚአብሔር እንደሆነ አውቃ እርሱን መዳሰሷን በማሳየት እንደ ፍጡር ቆጥረው እርሱን ይጋፉት የነበሩትን ገሠጻቸው። ጌታችን፡- “ልብሴን የዳሰስ ማን ነው? አለ፤ ከዚህም ሕዝብ መካከል ይህቺን ሴት ለይቶ በማውጣትና በመካከላቸው በማቆም እርሱን የነኩት ሁሉ እርሱን ሳይረዱት እንደነኩት እንደሚያውቅ አስተማራቸው።
ስለዚህም ማንም የጌታችንን አካል ሲነካ ፍጥረታዊ አካልን እንደነካ የሚያስብ ከሆነ ፍጥረታዊ አእምሮ ውስጥ ነው። ነገር ግን በመንፈሳዊ መረዳት ውስጥ ሆኖ ሥጋውን የሚዳስስ በሚዳሰሰው አካል ከማይዳሰሰው መለኮት ጋር ኅብረትን ይፈጥራል፡፡ ማንም ጌታችንን እንደ ዕሩቅ ብእሲ(ተራ ፍጡር ብቻ የሆነ/አምላክ ያልሆነ) ቆጥሮ አካሉን የሚነካ ባለማስተዋል ሆኖ የነካው ስለሆን ምንም አይጠቀምም፡፡ ነገር ግን አምላክን እንደዳሰሰ አውቆ የጌታችንን አካል የዳሰሰ ሰው ከሕመሙ ሁሉ የሚድንበትን መድኅኒት ከአምላክነቱ ግምዣ ቤት ያገኛል፡፡
ቢሆንም ግን ይህች ከሕመሟ በኅቡዕ የተፈወሰች ሴት በእርሷ የተፈጸመው ተአምር ከሕዝቡ እንደተሰወረ እንደ አመጣጧ ተሰውራ ብትሄድ ኖሮ ምንም እንኳ ከሥጋዊ ሕመሟ ብትድንም ከመንፈሳዊ ሕመሟ ባልዳነች ነበር። ይህች ሴት እርሱ ጻድቅ ስለሆነ እርሷን እንደፈወሰ ብታምንና ስለእርሷ አንዳች የማያውቅ ቢሆን ኖሮ እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን በተጠራጠረች ነበር። በእርግጥም ጻድቃንን ዳስሰው የዳኑ አሉ፤ ነገር ግን ቅዱሳኑ ከዳሰሱአቸው መካከል መንፈስ ቅዱስ ካልገለጠላቸው በቀር የትኛው እንደዳነ አያውቁም ነበር፡፡
ጌታችን ይህች ሴት በነፍሷ ትድን ዘንድ በሥጋዊ ፈውስ ወደ እርሱ አቀረባት፡፡ ስለዚህም “ልብሴን የዳሰሰው ማን ነው?” ብሎ ጠየቀ። በዚህም አንድ ሰው በእርግጠኝነት እንደዳሰሰው ተናገረ፤ ነገር ግን ማን እንደዳሰሰው አልገለጠም። እንዲህ ሲልም ሰዎችን በማታለል አታላይነትን ሊያጽድቅ አይደለም። ወይም ስለ እውነት ለመመስከር ፈቃዱ ስለሌለውም አይደለም። በእርግጥ እርሱን ይከተለው የነበረው ሕዝብ ይህን እንደፈጸመ እውነቱን መስክረዋልና።
1 675
1 ቀን ቀረው ልደታ ለማርያም ወዝክረ ቅዱስ ያሬድ ልዩ መርሀግብር
በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ። የዩኒቨርሲቲው ህንጻ 4ኛ ፎቅ ላይ
1 675
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሠሮ ለሰይጣን
አግዓዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዕዜሰ
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ ...አደረሰን ✞✞✞✞
መልካም በዓል 🙏🙏🙏
1 675
✨ጥንተ ስቅለቱ ለክርስቶስ
"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤
ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡
ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡
ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"
ቅዳሴ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
1 675
"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ። ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።"
ሉቃስ ወንጌል 2፡12-14
እንኳን አደረሳችሁ🙏❤️
1 675
ኤር 6:16 " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችዋዋን መንገድ ጠይቁ መልካሚቱን መንገድ ወዴት እንደሆነች እወቁ በርሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳችሁም እረፍት ታገኛላችሁ"
