en
Feedback
2 230
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+1530 days
Posts Archive
በአዳማ ናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጥ በግቢው ይዞታ ላይ ሁለገብ ሕንጻ ሊገነባ ነው፡፡ ------------------------------------------- መስከረም 6/2017 ዓ.ም ሐ.ተ.ሚ ( አዳማ - ኢትዮጵያ ) በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በአዳማ ናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጥ ሁለገብ ሕንጻ ሊገነባ ሲሆን የሕንጻውም ዲዛይን ይፋ ሁኗል፡፡ መልአከ ብርሃናት ቆሞስ አባ ማርቆስ ብርሃኑ የአዳማ ናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል አስተዳዳሪ በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው እንደገለጹት በግቢ ውስጥ ሊሠራ የታሰበው ሕንጻ G+6 ሲሆን በ800 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፉ ሲሆን ይኽን ሁለገብ ሕንጻ መሥራት እንዲቻል አጠቃላይ ኦርቶዶክሳውያን መንፈሳዊ አሻራቸውን የሚያስቀምጡበት በዓይነቱ ልዩ የሆነ ከኅዳር 7 - 10/2017 ዓ.ም መንፈሳዊ ባዛር ይካሄዳል ብለዋል፡፡ ሁለገብ ሕንጻው ሲጠናቀቅ ከሕንፃው በሚገኘው ገቢ የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን በመርዳት ፡ እጓለ ማውታን (ወላጅ አልባ) ሕጻናትን በማገዝ ፡ አቅመ ደካማዎች አረጋውያንን በመርዳት ፡ ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት፡ የካቴድራሉን ሠራተኛ ኑሮ በማሻሻልን ረገድ አገልግሎቶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ምስሉን ያደረሱን ፡- ሊቀ አእላፍ መ/ር ደረጄ ታዬ እናመሰግናለን፡፡ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) መስከረም 6/2017 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA Tiktok :- ፎሎው ያድርጉ tiktok.com/@hameretewahedomedia

የታሪካዊው የቢሾፍቱ ደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሐ.ተ.ሚ ዐይን፡- _______ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይ
+9
የታሪካዊው የቢሾፍቱ ደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሐ.ተ.ሚ ዐይን፡- _______ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA

የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በታሪካዊው ቢሾፍቱ ደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ዋለ፡፡ --------------------------------------------- ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም ሐ.ተ.ሚ ( አዳማ - ኢትዮጵያ ) የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በታሪካዊው ቢሾፍቱ ደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ፡ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፡ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡባዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የጠቅላይ ቤተክህነት የማኅበራት ማደራጃና ቅርሳቅርስ መምሪያ ኃላፊ ፡ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የአቡነ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ፡ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፡ ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፡ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ ክፍል ኃላፊዎች ፡ ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ክፍል ኃላፊዎች ፡ የቢሾፍቱና አካባቢው ወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች የአድባራት ና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፡ የሰንበት ት/ቤት ዘማሪያን ፡የመንፈሳዊ ማኅበራት ወጣቶች ፡ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ዋለ፡፡ በዕለቱም በደብሩ ሊቃውንትና በደብሩ ከሣቴ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ዘማሪያን ያሬዳዊ ወረብ የቀረበ ሲሆን ክቡር መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ሩፋኤል የደብሩ አስተዳዳሪ አጠቃላይ ዓመታዊ ሪፖርት ቀርቧል፡፡ በሪፖርቱም በደብሩ በሚገኘው ታሪካዊ የአብነት ጉባኤ ቤት የተሠሩ ሥራዎች ፡ በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት የተሠሩትን በደብሩ ስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በተመለከተ ሰፊ በጎ ታሪካዊ የአፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በዋናነት ደብሩ ተራራማ ከመሆኑ የተነሳ በምሥራቅ አቅጣጫ የሚገኘውን ገደላማ ተራራን የግዙፍ መግቢያ በርና የደረጃ ሥራዎችን ኃላፊነት በመውሰድ የፒራሚዲ ሪዞርት ባለቤት አቶ ዳንኤል አስፋው 4,500,000 ( አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር ) ወጭ በማድረግ ተሠርቶ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት መመረቁ ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ ወጭ የወጣበት የመንገድ ሥራ በሙያና በገንዘብ ያገዙ የአቱ ሆቴል ባለቤት አቶ ኢዩኤል ከፍተኛ አበርክቶ ማበርከታቸው ተገልጿል፡፡ አጠቃላይ በክቡር መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ሩፋኤል የሚመራው ሰባካ ጉባኤ ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸምና ሰላማዊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ በመቀጠልም በደብሩ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ዳንኤል ንጉሡ አቅራቢነት በልዩ ልዩ ልማታዊ ሥራዎች ላይ ከፍተኛ አበርክቶ ላላቸው የምስክር ወረቀትና የሽልማት መርሐግብር ተከናውኗል ፡፡ በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " ከእኛ ጋር ያሉት ከእነርሱ ጋር ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ " (2ኛ ነገ 6:16) በሚል መነሻ ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡባዊ ትግራይ ሀገረ ስብከተት ሊቀ ጳጳስ የዕለቱን ታሪክ ከምዕመናን ሕይወት ጋር በማዛመድ አባታዊ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ታላቁ የበረከት አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ አባታዊ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ሁሉም ምስጋናችን ፡ ውዳሴያችን ፡ ልማታችን ሁሉ ለበጎና ለሰላም እንዲሆንልን መጸለይ ይገባል ያሉ ሲሆን " እግዚአብሔር ፈዋሽ አዳኝ ነው በልዩ ልዩ መንገድ ደግሞ ያድናል ያስተምራል ይኸው በቅዱስ ሩፋኤል ተባረክን ተፈወስን ይኽን የመላእክት ተራድዳይነት ዐይናችንን ከፍተን መመልከት መቻል አለብን ፡፡ ይኽ ታሪካዊ ደብር ምንም ሰው ባልነበረበት ቦታ ዋጋ ከፍለው አገልግለው ለእኛ ያስረከቡን የአባቶቻችን የበረከት ቦታ ነው፡፡ ልንጠብቀው ይገባል በማለት ይኽ ልማታዊ ሥራዎችን ለሠሩት ሁሉ ልባዊ ምስጋናቸውን በማቅረብ በጸሎተ ቡራኬ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ መርሐግብሩ፡- በመልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተመርቷል! ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( ቢሾፍቱ - ኢትዮጵያ) ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA

በቢሾፍቱ ደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል በ4,500,000 ( አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ) ብር ወጪ የተገነባው የመግቢ በር እና ከፍተኛ የመወጣጫ መንታ ደረጃ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ ተመረቀ፡፡ ይኽን ለመሥራት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ በውብ የኪነ ሕንጻ ጥበብ በራሱ ያስገነባው የፒራሚድ ሪዞርት ባለቤት አቶ ዳንኤል አስፋው ሲሆኑ ለቅኖች ምስጋና ይገባልና ቤተ ክርስቲያን በዐውደ ምሕረት ታላቅ ምስጋና በማቅረብ የክብር ካባ አበርክታለች፡፡ ከቤተ ክርስቲያኑ ምሥራቃዊ አቅጣጫ ገደላማ የነበረና ለቤተ ክርስቲያኑ ስጋት የነበረ ቦታ ሲሆን በመልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ሩፋኤል የሚመራው ሰበካ ጉባኤውና አሠሪ ኮሚቴ ከብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ እና ከሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ከመልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን መመሪያን በመቀበል ግንባታው ለፍጻሜ እንዲደርስ ከፍተኛ ሥራ ሠርተዋል፡፡ የታሪካዊው የደብረ ዘይት ቅዱስ ሩፋኤል በረከት አይለየን ! ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአዳማ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሩፋኤል እየተሠሩ የሚገኙ ልማታዊ ሥራዎችን ጎብኝተው አባታዊ መመሪያ አስተላለፉ ፡፡ ---------------------------------------- ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም ሐ.ተ.ሚ ( አዳማ - ኢትዮጵያ ) ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥኣ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ በአዳማ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሩፋኤል እየተሠሩ የሚገኙ ልማታዊ ሥራዎችን ጎብኝተው አባታዊ መመሪያ አስተላለፉ፡፡ ብፁዕነታቸው በደብረ ኃይል ቅዱስ ሩፋኤል በውብ የኪነ ሕንጻ ጥበብ እየተሠራ የሚገኘውን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንና የጥርጊያ መንገድ ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን ለጸበል አገልግሎት እንዲውል የተሠራውን ጸበል ቤት የባረኩ ሲሆን ቀሪ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑና ቀሪ ልማታዊ ሥራዎች በፍጥነት በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ኹሉም የሰበካ ጉባኤ አባላት ፡ የጽ/ቤት ሠራተኞች ፡ ማኅበረ ካህናትና ምዕመናን ርብር እንዲያደርጉ በማሳሰብ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ በጉኝት መርሐግሩ ላይ መልአከ ብርሃናት ቆሞስ አባ ገብረ ሕይወት ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ፡ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ፡ የደብሩ አስተዳዳሪ ፡ የሰበካ ጉባኤ አባላት ተገኝተዋል፡፡ ፎቶ፡- ዲ/ን ልዑል ተካ አድርሶናል እናመሰግናለሁ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA Tiktok :- ፎሎው ያድርጉ tiktok.com/@hameretewahedomedia

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በውብ የኪነ ሕንጻ ጥበብ እየተገነባ የሚገኘው የአዳማ ሰቀቀሎ ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ፡፡ ----------
+3
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በውብ የኪነ ሕንጻ ጥበብ እየተገነባ የሚገኘው የአዳማ ሰቀቀሎ ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ፡፡ ------------------------------ ለፍጻሜ በቅቶ እንድናየው ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ የራሱን አሻራ ማሳረፍና ርብርብ ማድረግ ይገባል ፡፡ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ ዋጋ ከከፈሉ አባቶችና የአካባቢው ምዕመናን ጎን በመሰለፉ ለፍጻሜ እንዲደርስ እናድርግ ! ለፍጻሜ ያብቃልን ! ---------------------------------------- ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA Tiktok :- ፎሎው ያድርጉ tiktok.com/@hameretewahedomedia

ሑሩ ወመሀሩ ውስተ ኩሉ ዓለም ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ " (የማርቆስ ወንጌል 16:15) ( በመልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ) ----------------------------------- ከሁሉ በማስቀደም ለዓመታት በሥራ አመራር የትምህርት ዘርፉ በዲፕሎማ መርሐግብር ስትማሩ ለቆያችሁና ከሀገረ ስብከታችን ከሁሉም ወረዳዎች ተውጣጣችሁ መሠረታዊ የሚባለውን የማሰልጠኛውን ኮርስ ለወራት ተምራችሁና በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፋችሁ ለዛሬዋ የምረቃ እለታችሁ እንኳን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ " ለፍጥረት ሁሉ ወንጌልን ስበኩ "የሚለውን መለኮታዊ ኃይለ ቃል ለደቀ መዛሙርቱ የተናገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በሞቱ ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገለጠው በሌሊት ፈጥነው ወደ መቃብሩ ላመሩት ለመግደላዊት ማርያም እና እርሷን ተከትለው ለመጡት ሴቶች ነበር፡፡ ወደ መቃብሩም በደረሱ ጊዜ ሁለት መላእክት ተገልጠውላቸው መግደላዊት ማርያምን “አንቺ ሴት ምን ያስለቅስሻል?” አሏት፡፡ እርስዋም “ጌታዬን ከመቃብር ውስጥ ወስደውታል፤ ወዴትም እንደወሰዱት አላውቅም” አለቻቸው፡፡ ይህን ተናግራ ወደ ኋላዋ መለስ ስትል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቆሞ አየችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም እንደሆነ አላወቀችም፡፡ … “ኢትልክፈኒ አትንኪኝ፤ ወደ አባቴ አላረግሁምና ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሂጂና ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬ ወደ አምላካችሁም አርጋለሁ አለ ብለሽ ንገሪያቸው” አላት፡፡ ማርያም መግደላዊት እና ሴቶቹም ፈጥነው ሄደው ሐዋርያት ተስፋ ቆርጠው በአንድነት ተሰብስበው እያዘኑና እያለቀሱ ሳሉ መግደላዊት ማርያም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መነሣት የምሥራች ነገረቻቸው፡፡ ነገር ግን አላመኗትም፤ ተረትም መሰላቸው፡፡ ሉቃስ እና ቀለዮጳም ተስፋ ቆርጠው ወደ ኤማሁስ ሲሄዱ እንደተገለጠላቸው ለሐዋርያቱ ምሥክርነት ቢሰጡም ሊያምኑ አልቻሉም፡፡ ከዚህ በኋላ ዐሥራ አንዱ ሐዋርያት በሐዘንና በትካዜ ውስጥ ሆነው ሳሉ ጌታችም መድኃኒታችን ኢሱስ ክርስቶስ በመካከላቸው ተገኝቶ ራሱን ገለጠላቸው፡፡ በመጨረሻም “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ለፍጥረትም ሁሉ ወንጌልን ስበኩ” በማለት ከተናገራቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ (ማር.16:15፤ ማቴ. 28:1፤ ሉቃ. 24:1)፡፡ ይህ ትእዛዝ ለሐዋርያት ብቻ ሳይሆን ከእነርሱ በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ለሚነሡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ መምህራንና ቃሉን ሰምተው አምነው ለሚያስተምሩ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዋስ ጠበቃ ለሆኑ ሁሉ ነው፡፡ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን ያመሰግኑ ዘንድ እንዲሁ ብርሃናችሁ በሰው ፊት ይብራ” ተብሎ እንደተጻፈ ጨለማውን ዓለም በወንጌል ብርሃንነት ተመርተው እንቅፋቱን ሁሉ ማስወገድ፣ እንደሚገባ ያስገነዝበናል፡፡(ማቴ 5:14 -16 ) የዚህ አምላካዊ ተልዕኮ ባለቤት ደግሞ ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት፡፡ ውድ የዛሬ ተመራቂ ደቀመዛሙርት ልጆቻችን ቤተክርስቲያን ዓለማት ከተፈጠሩ በኋላ በዓለመ መላእክት፣ በዓለመ መሬት በሕገ ልቡና እና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔር በመረጣቸው ነቢያትና ካህናቱ አማካኝነት ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ስታገናኝ ኖራለች። በዘመነ ሐዲስ ደግሞ በደመ ክርስቶስ ተዋጅታ ሕገ ወንጌልን ስትናኝ እና አምልኮተ እግዚአብሔርን ስታስፋፋ ኖራለች። በእነዚህ አዝማናት ሁሉ ስለ እርሷ ሳይፈሩና ሳያፍሩ አንገታቸውን ለሰይፍ፣ ጀርባቸውን ለግርፋት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት የሰጡላት፣ በብዙ መከራዎች የተጋደሉላትን አበው፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ሰማዕታትን እና በእነርሱ መንገድ የተጓዙ ብዙ ሊቃውንትን አፍርታለች (ዕብ 11)። የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሕገ አበውን፣ ሕገ ኦሪትንና ሕገ ወንጌልን አስተባብራ በመያዝ የጥበብ ምንጭ፣ የሥርዓት መፍለቂያ፣ የዕውቀት ባሕር ሆና ሁሉ የተሟላላት ስንዱ እመቤት ናት። በማኅበራዊ አገልግሎቷ ደግሞ የድኩማን መጠጊያ፣ ያዘኑና የተከፉ መጽናኛ፣ የማንነትም አሻራ ነች። ለዚህም የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በተለያዩ ገዳማት፣ አድባራት፣ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ የአብነት ትቤቶች ተቀዳሚ ተጠቃሾች ናቸው። በተለያዩ ጊዜያት የተንኮልና የክህደት ቋጠሮ ይዘው የመጡ አሳሳቾችን አፍረው የተመለሱት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በወጡ መምህራን ነው፡ከዚህም በተጨማሪ ለሀገር መሪ ለሕዝብ አስተማሪ በመሆን ሕዝብን ያገለገሉ ደጋጎች ከእነዚህ መንፈሳዊ የትምህርት ተቋማት በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያን የወጡ ናቸው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ የትምህርትና የልኅቀት ማዕከል ሆነው ዘመናትን ከተሻገሩ ተቋማት መካከል የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ካህናት ማሠልጠኛ አንዱ ነው፡፡ በዚህ ማሠልጠኛ በርካታ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፡ በቤተክርስቲያን ጠፈር ላይ እንደ ከዋክብት ያበሩ ዐይናማ ሊቃውንት ፡ በርካታ ሰባክያን ፈልቀውበታል ፡፡ ዛሬ ደግሞ በአረጋዊውና በታላቁ የበረከት አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አርቆ አሳቢነት የቤተክርስቲያንን የአስተዳደር ጉድለት እንዲሞላ ወደ ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ በማደግ በርካታ የአመራር ምሁራንን እያፈለቀ ይገኛል፡፡ በዚኽም ሀገረ ስብከታችን ሁሌም ሲኮራ ይኖራል፡፡ ተቋሙ በብፁዕነታቸው አባታዊ መሪነት ገና ወደ ዩኒቨርሲቲ አድጎ በዓለም ላይ ከገነኑ በግሪክ ፡ በራሺያ እንዲሁም በአሓት አብያተ ክርስቲያናት ከሚገኙ ታላላቅ የትምህርት ተቋም ጋር እንደሚነጻጸር እምነቴ ታላቅ ነው፡፡ ውድ የዛሬ ተመራቂ ደቀመዛሙርት ልጆቻችን በመጨረሻም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሥርዓተ አምልኮ ተጠብቆ እንዲኖር የቤተ ክርስቲያን ዶግማና ቀኖና እንዲሁም ሥርዓት ተከብሮ ዘመናትን እንዲሻገር ፡ ቤተ ክርስቲያናችን ያሉባትን አስተዳደራዊ ክፍተቶች በተማራችሁትና በተረዳችሁት እውቀት ከአባቶች ጋር ተመካክራችሁ በመሙላት የተጣለባችሁ አደራ መወጣት ይኖርባችኋል፡፡ መረሳት የሌለበት ጉዳይ ይኽ ምርቃት የስኬታችሁ መጨረሻ ሳይሆን መጀመሪያ መሆኑን በመረዳት ለበለጠ የትምህርት ደረጃ ራሳችሁ ማዘጋጀት ይገባችኃል ፡፡ ይኽን ማድረግ ስትችሉ አምላካችን ያዘዘውን " ለፍጥረት ሁሉ ወንጌልን ስበኩ " የሚለውን አምላካዊ ቃል ተግባራዊ ለማድረግ ሙሉ አቅም ይኖራችኃል ማለት ነው፡፡ አሁንም በተሰጣችሁ መክሊት ትዕዛዙን ተግባራዊ እንድታደርጉ አባታዊ መልእክቴን እያስተላለፉኩ በድጋሜ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ፡፡ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ( የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ) ------------------------- በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም የምረቃ መጽሔት ላይ ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት !

የወልዳ ዱካ ቡኦታ ( Waldaa Duuka Bu'ootaa ) ምሥራቅ ሸዋ ማዕከል የ2016 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ ጠቅላላ ጉባኤ በሀገረ ስብከቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ። ------------------------------------------- ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ሐ.ተ.ሚ ( አዳማ - ኢትዮጵያ ) የወልዳ ዱካ ቡኦታ ( Waldaa Duuka Bu'ootaa ) ምሥራቅ ሸዋ ማዕከል የ2016 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ ጠቅላላ ጉባኤ በሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ። ጠቅላላ ጉባኤውን ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በጸሎተ ቡራኬ ያስጀመሩ ሲሆን በመርሓ ግብሩ ላይ ክቡር መልአከ ሳሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተ ወልድ የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ ፡ የሀገረ ስብከቱ የየክፍሉ ኃላፊዎች ፡ ክቡር መልአከ ብርሃናት ቆሞስ አባ ማርቆስ ብርሃኑ የአዳማ ናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል አስተዳዳሪ ፡ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፡ የወረዳ ቤተ ክህነት ሊቃነ ካህናት የማኅበሩ የዋና ማዕከል ሰብሳቢና መሥራች መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ሺኖዳ ኡርጌ የሰላም አምባሳደር አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ የአዳማና አካባቢዋ የማኅበሩ አባላት ተገኝተዋል። በበጀት ዓመቱ በ2016 ዓ.ም በማኅበሩ የተከናወኑ ተግባራት በተመለከተ በዲያቆን ጌቱ አበራ በወልዳ ዱኮ ብኦታ ምሥራቅ ሸዋ ማዕከል ሰብሳቢ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ማኅበሩም በ2017 ዓ.ም በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ ወረዳዎችና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መሠራት ስለሚገባቸው እቅዶች በማቅረብ በጠቅላላ ጉባኤ አጸድቋል። ጠቅላላ ጉባዔው በቀሲስ ምስጋኑ ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቶ በአባቶች ጸሎትና ቃለ ምዕዳን ቡራኬ የጉባኤው ፍፃሜ ሆኗል ሲል የዘገበው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ነው፡፡ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA Tiktok :- ፎሎው ያድርጉ tiktok.com/@hameretewahedomedia

አንጋፋው የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ ያስተማራቸውን 47 ደቀመዛሙርት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ፡፡ ----------------------------------- ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም ሐ.ተ.ሚ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) አንጋፋው የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ በሥራ አመራር ( Leadership ) በዲፕሎማ መርሓ ግብር በበጋ የተተኪ መምህራን ስልጠና ያሰለጠናቸውን ሰባክያነ ወንጌል ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት ጉባዔ የቦርድ ሰብሳቢ ፡ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡባዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የማኅበራት ማደራጃና የቅርሳ ቅርስ መምሪያ ኃላፊ ፡ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ፡ የኮሌጁ የቦርድ አባላት ፡ ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የባቱ ከተማ መስተዳድር የመንግሥት ተወካዮች ፡ የኮሌጁና የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች የልዩ ልዩ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ፡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፡ የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል ፡፡ መርሐግብሩም በጸሎተ ወንጌል የተጀመረ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የእንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የከፈቱት ሲሆን የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች የምርቃት ሥነ ሥርዓት አከናውነዋል፡፡ በመቀጠልም በተመራቂ ደቀመዛሙርት ያሬዳዊ ወረብና ቅኔ የቀረበ ሲሆን መጋቤ ብሉይ ቆሞስ አባ አትናቴዎስ ወ/ጎርጎርዮስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ርዕሰ መምህር የገዳሙን ሪፖርት የቀረቡ ሲሆን የኮሌጁ ዋና ዲን መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ታፈሰ ወጋዬ አጠቃላይ የምረቃ ሪፖርት አቅርበዋል ፡፡ በማስከተልም በኮሌጁ ሬጅስትራር ክፍል ኃላፊ በኩል አጠቃላይ በሥራ አመራር ( Leadership ) 23 በበጋ የተተኪ መምህራን ኮርስ 24 በድምሩ 47 ደቀመዛርት የምረቃ ሥነ ሥርዓታቸው የተከናወነ ሲሆን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከፍተኛ ነጥብ ላስመዘገቡ ተመራቂዎች የተዘጋጀውን የሜዳሊያ ሸልማት አበርክተዋል፡፡ በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ምርቃቱን በማስመልከት አባታዊ ትምህርት ሲሰጡ የባቱ ከተማ የመንግሥት ተወካይ የእንኳን አደረሳችሁ የሰላም መልእክት አስተላልፏል ፡፡ በመጨረሻም ታላቁ የበረከት አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ለተመራቂዎች መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በተሰማሩበት አገልግሎት ውጤታማ እንዴት መሆን እንደሚችሉ መሠረታዊ የሚባሉ መንገዶችን በመጠቆም ቤተ ክርስቲያን የጣለችባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት በጥንቃቄ በመረዳት በትጋት መወጣት እንደሚገባቸው በማሳሰብ አባታዊ የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ፡፡ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ - ኢትዮጵያ) ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም Telegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ https://t.me/hameretewahedo Youtube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA Tiktok :- ፎሎው ያድርጉ tiktok.com/@hameretewahedomedia