ሐበሻ ኢስላሚክ ሚድያ
Open in Telegram
قال الله تعالى ( وَلَا تَلْبِسُوا الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُوا الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ )البقرة (42) አሏህ በእርግጥም አለ፦[እውነትን በውሸት አትሸፍኑ እናንተ እውነታውን እያወቃቹህ] ምንጭ፦«ሱረቱ አል–በቀራህ አንቀፅ /42/ በኡስታዝ ሐምዛ [አሰዱሏህ]
Show more1 994
Subscribers
-124 hours
-107 days
-3530 days
Posts Archive
1 994
በማለት ኣሱብክይ ይህ የተክፊር ጉዳይ "ሙስሊም ማሕበረሰቡም ዘንዳ"በማለት ለቃድይ ብቻ ነገርዪውን ጥለው እንዳላለፉ ያስረዳል።ይልቅንስ የኩፍር ውሳኔ ሚያሳርፍበት ነገር የተናገረ እንደሆነ ይህን ሰው በሐቅ ማክፈሩ አይከለከልም።ይህም ፈኽሩዲን በነ ሱብክይ ንግግር ላይ ያለው የአረዳድ ክፍተትን አጉልቶ ያሳያል።ሆኖም ሙስሊም ዘንዳ መባሉ ቀዋዒዱን ያሟሏ በመሆኑ ላይ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።የሁሉ መዋኛ ገንዳ አይደለም።የተክፊር በር ልቅ እንዳልሆነ የኩፍሩንስ ቃል የተናገረ ሰው በምላስ ወለምታ፣በግዳጅ፣ በሒካያህ በኢጅቲሃድ፣ በአቅል መራቅ አልያስ በማለት ከስሮቻቸውም የተለያዩ ገደቦች በመዘርዘር እነኚህ የእውቀቱ አምባ የማክፈርያን እንዲሁ ያለማክፈርያን ነጥብ በዝርዝር ያስቀምጣሉ። ለዚህም የሐበሻው የዒልመል ሓዲስ ኻዳሚ ሚሰኙት ኣሸይኽ ዓብዱሏህ አል ሃረሪይ ኣሲራጥ፣ ሶሪሑል በያን፣ቀዋዒድ እንዲሁ ሌሎችንም ኪታቦቻቸው ይህን በተመለከተ የሰጡትን ማብራርያ መመልከት ያስፈልጋል።እርሳቸውም ያለ ሐቅ የማክፈርን አደገኝነት እንዲህ በማለት ይናገራሉ፦
ثم إنَّ الحكمَ على شخصٍ بالكفرِ أو الإسلامِ إنْ كان مُسْتندًا إلى دليلٍ فذاك صوابٌ عندَ اللهِ، وإن كانَ لا يستندُ إلى دليلٍ فهو هلاكٌ على صاحِبِهِ. قالَ العلماءُ: إدخالُ كافرٍ في الملّةِ أمرٌ عظيمٌ وإخراجُ مسلمٍ عنها أمرٌ عظيمٌ. المعنى أنَّه لا يُحكمُ لشخصٍ بأنَه مسلمٌ بدونِ دليلٍ شرعيٍ ولا يُحكَمُ على مسلمٍ بالكفرِ إلا بدليلٍ شرعيٍ.
[«አንድ ሰው ላይ በኩፍር አልያ በኢስላም መፍረድ በማስረጃ ተደግፎ ከሆነ ትክክለኛውም መንገድ እርሱ ነው።ማስረጃን ተመርኩዞ ካልሆነ ግን ባለቤቱ ላይ ጥፋትን ታስከትላለች።ለዛም ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል፦"ለአንድ ሰው በእስልምና መፍረድ ከባድ ነው።በኩፍርም እሱን መፈረጅ ከባድ ነው"።ይህም ማለት ለአንድ ሰው ያለ ሸሪዓዊ ማስረጃ በእስልምና አይፈረድለትም እንዲሁ ያለ ሸሪዓዊ ማስረጃ ኩፍርም አይታወጅበትም»]።
በማለት ሸይኸ ዓብዱሏህ ያስጠነቅቃሉ።ይህም ሊታወቅ ሊገነዘቡት የተገባ ይሆናል።ከውጪ የሚሳለው ሁሉ ቀርበህ ስታይ ውሸት ሲደጋገም እውን ይመስላል የሚለውን አባባል እውን ሆኖ ታገኘዋለህ።
✧ አህሉል ቂብላና መከፈር ሚገባቸው አንጃዎች…
②“አል_ሙጅተሂዱ_ጦበሪይን_ወይስ_ፈኽሩዲንን”
በአህሉል ቂብላ ስም የተሸፈነ ሁሏ ሙስሊም ነው የሚል ስያሜ እንደማይሰጠው ይልቅንስ የተውሒዱ ትክክለኝነት በዋነኝነት ለዚህ ስያሜ ጉልህ ሚና እንዳለው የሚያሳዩ ማስረጃዎች ውስጥ አል ሓፊዙ ኣጦበርይ ያሉት ንግግር ሲሆን፤ ይህም ፈኽሩዲን እና ዝና ፈላጊ ወጠጤዎችን በአፍጢማቸው የተከለ ንግግር ነው።
قال الحافظ ابن حجر ما نصه [قلتُ وممن جنح إلى بعض هذا البحث الطبري في تهذيبه فقال بعد أن سرد أحاديث الباب - يعني أحاديث الخوارج - فيه الرد على قول من قال لا يخرج أحد من الإسلام من أهل القبلة بعد استحقاقه حكمه إلا بقصد الخروج منه عالما"]
፨ ኣል ሓፊዙ ኢብኑ ሓጀር ከጦበርይ ሲያስተላልፉ እንዲህ ይላሉ፦[“ወደዚህ ፍለጋ ከገቡት መሀከል ኣጦበርይ ተህዚባቸው ላይ ስለ ኻዋሪጆች የተጠቀሱትን ሓዲሶች ካወሱ ቡሀሏ እንዲህ ሲሉ አስፍረዋል፦("በዚህ ላይ የሙርተድነት ፍርድ እየተገባው ወደ ቂብላ ዞር ከሰገደ ከእስልምና ለመውጣት ካላሰበ በስተቀር አይከፍርም: ላሉ ሰዎች መልስን ይዟል”)]።
ጦበርይ ኻዋሪጆችን ያለ ምንም መነጠል በጠቅላላቸው ካከፈሩ የሰለፍ ዑለማዎች ውስጥ አንዱ ነበሩ።በዚህም ላይ ወደ ቂብላ የዞረ ሁሉ ሙስሊም ነው በማለት: ሽንጣቸውን ገትረው ለሙጀሲሙ አለመክፈር ለሚሞግቱና፣እንዲሁ የሙስሊምን የመክፈርን ቅድመ ሁኔታ ሲጠቅሱ ኩፍር መሆኑን አውቆ ካልሆነ አይከፍርም፤ ለሚሉ ሰዎች መልስ በዚህ መልኩ የሰጡበት መሆኑን ልብ ልትል ይገባል።
③ ኣቡ ሓሚድ ኣል ገዛልይ ወደ ቂብላ ዞሮ የሚሰግድን በኩፍር መፈረጅ እንዲሁ ደሙን ማፍሰስ ስህተት ነው።ሲሉ የትኞችን የቂብላ ሰዎችን ነው በማለት በማስተንተን ፋንታ የፈኽሩዲን ጨለምተኛ አስተሳሰብ አሁንም እርሳቸው ያልፈለጉበትን በህቡእ ኪታቦቻቸው ላይ መቅጠፍን ከአጋሮቹ ጋር ተያይዞታል።
قال الغزالي في كتاب التفرقة بين الإيمان والزندقة والذي ينبغي الاحتراز عن التكفير ما وجد إليه سبيلاً فإن استباحة دماء المصلين المقرين بالتوحيد خطأ،
✧ አል-ገዛልይ “አተፍሪቀቱ በይነል ኢማኒ ወዘንደቃህ” በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ይህን ማለታቸው ተቀምጧል፦«የተገባው የሆነ ነገር መውጫ መንገድ እስካገኘ ድረስ ከማ*ክ*ፈር መቆጠብ ነው።(በተውሒድ) በመፅናት ወደ ቂብላ ዞረው ሚሰግዱ ሰዎች ደምን ማፍሰስ ስህተት ነው”]።
ይህ የገዛልይ ንግግር እውቀት አለኝ በማለት ለሹመት እራሱን ላጨ ቀርቶ በዚህ ሰው ዙርያ በጅህልና እያጨበጨበ ለሚገኘው በራሱ በቂ ትንተናን እርሳቸው አኑረው አልፈዋል።ኣቡ ሐሚድ ረሒመሁሏህ የማክፈርን ፍርድ ከመስጠት የከለከሉት በተውሒድ የመጣን ሰው በመሆኑ ላይ ግልፅ ነው።ተውሒድ ደግሞ ያለ ተንዚህ አይሆንም።ምክነያቱም ተሽቢህ ያለበት ሰው አሏህን ከፍጡሩ በሲፋ የለየ አልሆነም።ይህ ደግሞ ከተውሒድ ምሰሶዎች የሚመደብ ነውና ሙሸቢህ ተውሒድ ስለሌለው እዚህ ውስጥ እርሱን ማስገባት በራሱ ትልቅ ስህተት እንዲሁ የተውሒድን ፍቺ ካለመረዳትም የመነጨም መሆኑ በግልፅ ሊታወቅ ይገባል።ገዛልይ ሙጀሲምን እንደሚያከፍሩ ከመታወቁም ጋር ሙጀሲምን ላለማክፈር ይህን በማስረጃነት ማምጣት እጅጉን አስገራሚና አወዛጋቢም ነው።እንዲሁ የቂብላ ሰው በመሰኘቱ ብቻ እስልምና እንደማያሰጠው ኡማህ ተብሎ ሲባልም ገለፃው የአማኞች እንጂ የሰጋጆች ብቻ እንዳልሆነ ሲገልፁ በ"ኣል ሙስተስፋ" ላይ እንዲህ ይላሉ፦
قال الغزالي في المستصفى ”أما إذا كفر ببدعته، فعند ذلك لا يعتبر خلافه، وإن كان يصلي إلى القبلة ويعتقد نفسه مسلماً.لأن الأمة ليست عبارة عن المصلين إلى القبلة، بل عن المؤمنين، وهو كافر، وإن كان لا يدري أنه كافر“
[«በቢድዓው የከፈረ እንደሆነ በዛ ግዜ ልዩነቱ ቦታ አይሰጠውም።ወደ ቂብላ ዞሮ በመስገድ እራሱን ሙስሊም አድርጎ ቢያስብም፤ ምክነያቱም ኡማህ ሲባል ወደ ቂብላ ዞረው የሚሰግዱ ሰዎች ገለፃ ሳትሆን ይልቅንስ የትክክለኛ አማኞች ናት።ይህ ደግሞ ካ*ፊር ነው።መክፈሩን ባያውቅም»]።
ሲሉ አቋማቸውን ለመረረው ይምረረው በሚመስል መልኩ ያስቀምጣሉ።ይህ ነው እንግዲህ የነዛህ ታላላቆቹ መንገድ።የከፈረን ከፍረሀል።ሙስሊምን ሙስሊም ነህ እንጂ እስልምናን ከ ኩፍር ሚደባልቁ አልነበሩም።በአቋማቸው ፅኑም ነበሩ።እኔ ሳይሆን አሏህና ረሱሉ ካሉ ነበር የሚሉት።አሏህ የተሻለን መረዳት እንዲሁ መልካም መጨረሻን ይግጠመን።
1 994
فقد جاء في كتاب "الإعلام بقواطع الإسلام" لابن حجر الهيتمي ص 9 ما نصه: "ومعنى كفّر الرجل أخاه نسبته إياه إلى الكفر، بصيغة الخبر نحو: "أنت كافر"، أو بصيغة النداء نحو: "يا كافر"، أو باعتقاد ذلك فيه كاعتقاد الخوارج تكفير المؤمنين بالذنوب…ثم قال ابن حجر في الصحيفة 10 ما نصه "ومع ذلك فالموافق للقواعد أنه حيث ثبت كفره باطنا كان حكمه حكم المرتد، ولا تعزير على من قال له يا كافر".اهـ
[«አንድ ሰው ወንድሙን አስከፈረ ማለት እርሱን ወደተከሰተበት ድርጊት ወደ ኩ*ፍሩ ባለፈ ድርጊት ዘይቤ "ከፍርሃል" አልያ በጥሪ መልኩ ያ "ካፊር" ብሎ እርሱን ወደዛው ክስተት ማስጠጋት አልያ ያንኑ ክስተት በእርሱ ላይ መከሰቱን በማመን፤ ሊሆን ይችላል።ለምሳሌ ኻዋሪጆች ምእመኑን በሓጢያት ከፍረዋል በማለት እንደሚያምኑት ማለት ነው።…በስተመጨረሻም እንዲህ በማለት ይዘጋሉ፦ "ነገር ግን በመሆኑም ከሕግጋቶች ጋር ተስማሚ የሚሆነው ክሕደቱ መረጋገጡ እስከታወቀ ድረስ የዚህ ሰው ፍርዱ የሙርተድ ፍርድ ይሆናል።"አንተ ካ*ፊር ብሎ በጠራውም ላይ ቢሆን መቀጮ የለበትም»]።
✧ በማለት ኢብን ሓጀር ይህን የኩፍር ፍርድ ለቃዲይ ብቻና ብቻ የተተወ ሳይሆን ይልቅንስ አንድ ሰው መመርያውን ተከትሎ የሀገሪቱን የቋንቋ ዘይቤ፣ ቃሉም ስንት ትርጉም እንደሚሸከም ጨምሮ ለዛ የሚፈልጉ መሳርያዎችን ካሟሏ የኽሊፋነት አልያ የቃዲይነት ስልጣን ባይሰጠውም የከፈረን ካፊር ነው። አልያ ከፍሯል በማለት በየቂይን ቢሰይም ምንም ችግር እንደሌለው አመላክተውናል። ይልቅንስ ይህ የሸሪዓንም መመርያ ይስማማልም በማለት በስተመጨረሻ አኑረዋል።
✧ ዑለማዎች የሪዳህን ነጥብ ሲጠቅሱ ሰውን ከማስፈራራት ጀርባ ሓቂቃዊ ፍርድ የለውም፤ ብለው ሚሞግቱ ሰዎች አልጠፉምና ለነኚህ ሰዎች የምንላቸው የዚህ ፍርድ ኪታቡ ላይ መጠቀሱ ለኪታብ ማጌጫነት ከሆነ ይህን ኪታብ ተመርኩዘው ፍርድ ሲፈርዱበት የነበሩ ኽሊፋዎች አልያ ቁዷቶች በሰው ሒይወት ላይ ሰውን ለማስፈራራት ሙርተድነህ በሚል ፅንፈኝነት የንፁሀንን ደም እያፈሰሱ ነበር በሚል ውንጀላ እየፈረጃችሁ መሆኑን መዘንጋት የለበትም።
ሰሞኑ በ "AI" የዒልም ተወላጆች በሆኑት ፈኽሩዲን ጨምሮ የተክፊርን ሓሳብ በማንሳት እርስ በእርሱ የተጣረሱ ብዙ የሚባሉ ሓሳቦችን ሲያነሱ በነበሩት ስብስብ ላይ በጣት የማይቆጠሩ ትዝብቶችን ወስደንበት ሳለ ነገር ግን ከዛም አለፍ ብሎ ይህ ሰው እየጠቀሳቸው ያለው ሪዳን በማስመልከት አንዳንድ ዑለማዎች ለማስፈራራት ነበር እንጂ የእውነት ፍርዱ ኩፍር ስለሆነ አይደለም: ብለዋል በማለት ብዕር የተፋውን ሁሉ አግንቻለው ብሎ ሲዘረዝር ሰምተናል። ታድያ፦
① “ሙሓቂቁን_ኢብኑ_ኑጀይምን_አልያስ_ፈኽሩን”?
እርሳቸው በፈኽሩዲን ነቅል ላይ ትችታቸውን በዚህ መልኩ አሳርፈውበት ያልፋሉ፦
"ويحكى عن بعض من لا سلف له أنه كان يقول : ما ذكر في الفتاوى أنه يكفر بكذا وكذا فذلك للتخويف والتهويل لا لحقيقة الكفر وهذا كلام باطل، وحاشا أن يلعب أمناء الله تعالى - أعني علماء الأحكام - بالحرام والحلال والكفر والإسلام بل لا يقولون إلا الحق الثابت عن سيد الأنام عليه الصلاة والسلام."
[ከአንዳንድ ለንግግሩ ቀዳሚ ከሌለው ሰው እንዲህ ብሏል ተብሎ የሚወራው፦«“ኣል ፋታዋ ላይ በዚህ በዚህ ነገር ይከፍራል መባሉ ለማስፋራራት እንዲሁ ለማስደንገጥ ነው ማለታቸው ይህ "ውድቅ" የሆነ ንግግር ነው።ፈፅሞን የአሏህ ዲን ታማኞች (የዲን ሕግጋት አዋቂዎች)በሐላል፣በሓራም፣በኩፍር እንዲሁ በኢስላም ይጫወታሉ ማለት ከነርሱ የራቀ ነው። በእርግጥም እነኚህ ዑለማዎች የፍጡር አይነታ ከሆኑት ነብዩ ከእርሳቸው የተረጋገጠን ቢሆን እንጂ በሌላ አይፈርዱም ”]።
እንግዲህ ኪታብ አንብበን ብቻ ዒልምን ምንጣራ ሰዎች ኢብኑ ኑጀይም አትቅጠፉ የአሏህ ታማኞች በአሏህ ሕግጋት ላይ አይቀልዱም ሲሉ ይህን ንግግር በከባዱ አጥብቀው ያነውራሉ። አንባቢውም ያለ ማረጋገጫ ወረቀት ይዞታል፣ ቀለም ተደፍቶበታል፣ርዕሱም ተሰይሟል እንዲሁ ፃሀፊም ተበጅቶለታል በማለት ያገኘውን ማግበስበስ እንደማይችል ይልቅንስ ይህን የማግኛው ብቸኛ መፍትሄ መማርና መማር ብቻ መሆኑን ሊሰመርበት ዘንዳ የተገባ ነው።ሓቁን ከባጢል የመለያ መሳርያ እነርሱ ዘንዳ ስለሆነ ማለት ነው።
ፈኽሩዲን በተክፊር ዙርያ ስማቸውን በተደጋጋሚ ከሚያነሳው ሰዎች መሀከል አንዱ የሆኑት ኣሸይኽ ኣንይ "አል ፈታዋ" የተሰኘ ኪታባቸው ላይ ይህን ስለመሰለ ነጥብ ሲናገሩ ይህ የማስፋራራት እንጂ ሓቂቃዊ ኩፍር ስለሆነ አይደለም ስለሚሉት ንግግር ከዑለማኡል ኢስላም የማይጠበቅ የመሀይማን ጥርቅም አስተሳሰብ እንደሆነ በዚህ መልኩ ያሰፍራሉ፦
قال الآني في الفتاوى: وأما ما تسوّل به نفوس الجهلة من أن التكفير بالأشياء التي ليست بمكفرة إنما هو لتخويف العوام وتهديدهم جهل عظيم وجراءة.
[“ነገር ግን የተክፊር ጥማት ያለባት የአንዳንዱ መሀይማን ነፍስ ኩፍር ያልሆኑትን ኩፍር ነው በማለት በዚህም የተፈለገው (ተራውን ማህበረሰብ ማስፈራራት) የሚለው ትልቅ መሀይምነት እንዲሁ በአሏህ ዲን ላይ ትልቅ ድፍረት ነው”] ሲሉ ይገልፁታል። ታድያ ስለየትኞቹ አንዮች ነው ምታወሩት?
በዚሁ ተክፊርን የማስጠንቀቅ የተሰኘ ርዕስ በተሰጠው እርስ በእርሱ የሚጣረስ ውይይት ሌላው ፈኽሩዲን ታላቁ ኢማም ተቂዩዲን አሱብክይ ይህ የተክፊይር ሑክም ለአሏህና ለመልዕክተኛው ብቻ ሚተው ነው ብለዋል ሲል ያስቀምጣል። እነሆ ይህ ከሆነ እርሳቸው “በጦበቃታቸው” ላይ ካስቀመጡት ንግግር የተጣረስ እንዲሁ የሚሉትን አያውቁም ወደ ሚል የንግግር ዘይቤ ይወስዳል።ይህ ብቻ ሳይሆን እስከዛሬ ቁዷቶች በሪዳ እንዲሁ በተለያዩ አይነት ምክነያቶች በግልፅ አሏህና መልዕክተኛ በሁሉም አንቀፅ በአንቀፅ አለመጠቀሱ ማንም ማይክደው ሐቅ ሆኖ ሳለ ታድያ ይህ ፍርድ ለማንም ቀዋዒድን ተከትሎ በቅያስ የመፍረድ እድል ካልተሰጠው እነኚህ ሁሉ ቁዷቶች የሰው ነፍስ ላይ በሙርተድ በሚል የሓሰተኛ ልጥፍ እየተጫወቱ ነበር ሚልን አያሲዝምን? ነገር ግን ሱብክይ ይህን የተክፊይር በር በአሏህና በመልዕክተኛው ብቻ ያልተገደበ ይልቅንስ ከዛም ውጪ ላሉ ለእውቀት ባልተቤቶች እንደተሰጠ በዚህ መልኩ ያስቀምጣሉ፦
قال تاج الدين السبكي في طبقاته (۲) ما نصه: «ولا خلاف عند الأشعري وأصحابه بل وسائر المسلمين أن من تلفظ بالكفر أو فعل أفعال الكفر أنه كافر بالله العظيم مخلد في النار وإن عرف بقلبه اهـ.
[“ኣሽዓርይም፣የእርሳቸው ባልደረባዎች ጋርም ሆነ የተቀሩት ሙስሊሞች ዘንዳ አንድ የኩፍርን ቃል በተናገር አልያ ያመነ ከሃዲ እንዲሁ እሳት ውስጥ ዘውታሪ በመሆኑ ላይ ልዩነት የለም።በልቡ አውቆም ቢሆን”]።
1 994
መረጃ ይዳኘን ክፍል ⑧
قال الله تعالى {وَقُلۡ جَاۤءَ ٱلۡحَقُّ وَزَهَقَ ٱلۡبَـٰطِلُۚ إِنَّ ٱلۡبَـٰطِلَ كَانَ زَهُوقࣰا (٨١)}
[በል «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና]።«አል ኢስራእ 81»
✧ አሏህና መልዕክተኛው ባደረሱን ነገር በጠቅላላው እብለት የለውም በማለት ያለ ማስተባበል መቀበል ከኢማን መስፈርት ውስጥ በዋነኝነት እንደ ምሰሶ የሚካተት ጉዳይ ነው።ታድያ ይህ ምሰሶ ተናደ ማለት የመዘውተሪያው ዓለም ዋነኛ መግቢያ የሆነውን ኢማን የተሰኘን ቁልፍ ማጣት እንደማለት ነው።
✧ በፍርዳቸው ላይ የፍትህ ሙሉነት ለአሏህና መልዕክተኛው የተገባ ነው።አድሎን ሆነ በደልን ፍርዳቸው አያውቀውም።ከጉድለት ባሕሪያትም አንዱን ወደነርሱ ያስጠጋ አማኝ ከተሰኘ ማዕረግ ካፊ*ር ወደሚል ቁልቁለት ያስከረብተዋል። የሙርተድነት ስያሜ በመሰጠት የዛን ዋጋ የተባለን ደግሞ በዱንያ ሞትን፤ በቀጣይኛው ዓለም ዘላለማዊ እሳትን እንደሚቀምስ ከትልቁ ሰው የመጡልን ክወናዎች በዚህም ላይ ምስክሮች ናቸው።ከነዛም ውስጥ ኣል ቡኻርይ ሶሒሓቸው ውስጥ ይህን አስፍረዋል፦
قالَ النبيُّ صلّى اللهُ عليه وسلّم: "مَن بدَّلَ دينَه فاقتُلوهُ"
«ዲኑን የለወጠ ግደሉት»
አንዳንዱ ሰው ይህ ሲነገረው "ነገር ግን ከላይ የተጠቀሰው ሰው ዲኑን መች ለወጠ ሙስሊም ነኝ ብሎ እያለ እንዴት ሙርተድ ይሰኛል ብሎም እንዴትስ ይገደላል"? የሚል ትችት አዘል ጥያቄ ማንሳቱ አይቀሪ ነው።በመጀመርያ ለዚህ ሰው ምንለው የአሏህና የመልዕክተኛውን ክብር በሚያጎድፍ ቃል የተናገረ እንደሆነ ካፊር በመሆኑ ላይ የዑለማዎች ገለፃ በየኪታቡ አለ።ለምሳሌ "ኣሺፋን" የመሰለ የቃዲይ ዒያድ ኪታብ በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል።በመሆኑም ንግግርና ዕምነት ለሪዳህ መከሰት መጣመራቸው በቅድመ ሁኔታነት እንደማይቀመጥ: ብሎም ሰውዪው ይህን በመሰል ንግግሩ ብቻ ዲኑ እንደሚበላሽ ስግደቱና ፆሙም ዋጋ ቢስ እንደሆኑ፤ እርሳቸው ትልቁ ሰው በዘመናቸው በተከሰተው ክስተት ልዩ ትምህርት ሰጥተውን አልፈዋል። ለዚህም ኣል ኢማም አል ዒመራንይ ኣሻፊዒይ “አል-በያን” በተሰኘ ኪታብ ላይ እንዲህ በማለት ይዘግባሉ፦
ذَكَرَه الإمام العمراني الشافعي في كتاب البَيان أنه رُوِيَ: أن رجلًا مَرَّ بالنبي صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وهو يَقسِم الغنيمة، فقال: يا مُحَمَّدُ، اعْدِلْ فإنك لم تَعْدِلْ، فقال النبي صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "وَيْلَكَ، إذَا لَم أَعْدِلْ فَمَنْ يَعْدِلُ"، ثم مَرَّ الرَّجُل، فَوَجَّهَ النبي صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أبا بكر وراءه ليقتله فوجَدَه يصلي، فقال: يا رسول الله وَجَدْتُهُ يُصَلِّي، فوَجَّهَ عُمَرَ ليقتله فوجده يصلي، فقال: يا رسول الله وجدته يصلي، فوجَّه بعلي رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ وقال: "إنَّكَ لَن تُدْرِكَهُ" فذهب علي رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ فلم يجده. انتَهى الحديث.
[«መልዕክተኛው ከምርኮ የተገኘን ገንዘብ በማከፋፈል ላይ ሳሉ በአጠገባቸው አለፍ ሲል የነበረ አንድ ሰው "ሙሐመድ ሆይ በፍትሕ አከፋፍል አንተኮ በፍትሓዊነት እያከፋፈልክ አይደለም አላቸው"። የአሏህም መልዕክተኛ ዓለይሂ ሶሏቱ ወሰላም እንዲህ በማለት ምላሽን ሰጡት፦ "ወየውልህ እኔ በፍትሓዊነት ካላከፋፈልኩ ማነው በፍትሕ ሚያከፋፍል" ቀጥሎም እኚህ የፍትሑ ቁንጮ ይህ ሰው ከሄደ ቡሀሏ አቡበክርን ሄዶ እንዲገድለው አዘዙ።እርሳቸውም ሊገድሉት በሄዱ ጌዜ ሲሰግድ አገኙት።እርሳቸውም ወደ መልዕክተኛው በመመለስ እየሰገደ አገኘሁት አሉ። በቀጣይም ዑመርን ላኩት እንዲገድለውም አዘዙ። እርሳቸውም ሊገድሉት በሄዱ ጊዜ ሲሰግድ አገኙት ዑመርም ወደ መልዕክተኛው በመመለስ እየሰገደ አገኘሁት አሉ።በስተመጨረሻም ለዓልይ ይህን ትዕዛዝ አስተላለፉ።እንዲህም አሉት "አንተኮ አትደርስበትም" ሰይዱና ዓለይም በሄዱ ጊዜ አላገኙትም»]።
✧ ከዚህ_ሓዲስ_የምንማረው_ሁለት_ትልልቅ_ቁም ነገሮች_አሉ።እነርሱም፦
የመጀመርያው፦በመልዕክተኛው ላይ ይህ ሰው ያወጣባቸው መረን የለሽ ስዳዊ ቃል ኢማኑን እንዳበላሸበት በዚህም ኢማኑን በማጣቱ ምክነያት እንዲገደል ማዘዛቸውን ሲሆን:ይህ ሰው ከኢማን እንደወጣ አለማወቁ ለሙርተድነት ፍርድ እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደማይቀመጥ ሓዲሱ ያስረዳል።
ሁለተኛው፦ ወደ ቂብላ መዞሩ ብቻውን ሙስሊም እንደማያስብለው ይልቅንስ ምላሱና ልቡ በኢማን መጣመር እንዳለባቸው የሚያስረዳ ነው።ማለትም አቡበክር ረዲየሏሁ ዓንሁ እየሰገደ ነው ሲሉ ዑመርን እንዲገድለው መላካቸው ወደ ቂብላ መዞሩ ብቻ ሙስሊም ብያስብለው:ዑመርን ቀጥሎም ዓለይን እንዲገድሉት በየተራ ባላዘዙ ነበር። ይህ ማለት ትልቁ ሰው በዚህ በኩል የእርሳቸውን ክብር ማጉደፍ አልያ ማንነታቸውን ማይመጥን ቃል መወርወር በእርሳቸው ከማመን ጋር ይፃረራልና የዚህም ውጤት ሪዳህ አልያ ኩፍር በመሆኑ ፍርዱን ቁልጭ በማድረግ በድርጊታቸው አኑረው ሕጉን ደንግገው አልፈዋል።
✧ ሆኖም ምንም ያህል በአሁኑ ሰኣት ይህን በመሰለ ሰው ላይ የሙርተድነት ህግን መተግበር ባንችልም ነገር ግን ይከ*ፍራል የሚለው ፍርድ በመኖሩ ላይ ምንም ጥርጣሬ የለውም።
ይህን ሪዳህ የተባለ ሕግም ከአራቱ ኽሊፋዎች አንስቶ ከዛ ቡሀሏም ይህ ስልጣን የተሰጣቸው መሪዎች የሙርተድን ሕግ ከኪታብ አልፎ በተግባርም ሲያውሉት እንደነበር እነኚሁ መፅሀፍቶች በብዛት ያትታሉ።ይህን እውነት መሻር የሚችል አንድም የለም።ታድያ በአሁኑ ግዜ ምእመኑ ኸሊፋን የማቋቋምን አቅም ባይኖረውም ነገር ግን የሙርተድ ሕግጋቱ አልያ ውሳኔው ይጠፋል ማለትን አያሰጥም። በዚህ ግዜም ልናደርገው ምንችለው በዋነኝነት በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ይሆናል ማለት ነው።
ይህ ሰው ይህን መሰል ነገር በነብዩ ላይ ቢፈፅም በመጀመርያ ሙርተድ አልያ ካፊር ይሰኛል።ነገር ግን እኛ ስላልነው አይደለም የከፈረው ይልቅንስ ሰውዪው ቀድሞን በተከሰተበት ነገር ነው ኢማኑ ሊበላሽ የቻለው፤የእርሱም ምክንያት የነብዩን ክብር ማጉደፉ እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል። አንዳንዱ በዚህ ላይ የበለጠ ገለፃ ይፈልጋል።ምክነያቱም አንድ ሰው ካፊር ስላልነው አልያ ሙስሊም ስላልነው አይከፍርምም አይሰልምም።
ይልቅንስ የከፈረው በራሱ ንግግር ነው። የሚሰልመውም ሸሃዳ ሲይዝ ብቻ ነው። ታድያ እኛ ከፍረሀል ስንለው ምን ማለታችን ነው? በጥርጣሬ ሳይሆን በእርግጥ ኩፍሩ የተረጋገጠን ሰው መመርያዎችን ጠብቆ ከፍረሀል አልያ ካፊር ማለትስ በተናጋሪው ላይ ሚያመጣው ጉዳት አለውን? የሚለውን ታላቁ ኢማም ኣሸይኽ ኢብን ሐጀር አል ሐይተምይ “አል ኢዕላም ቢቀዋጢዒል ኢስላም” ላይ እንዲህ በማለት ገለፃ ያደርጋሉ፦
1 994
መረጃ ይዳኘን ክፍል ⑧
«ኢብኑ ኑጀይምን ወይስ ፈኽሩን
ነቅልና ተሕቂቅ»
ማክሰኞ ምሽት ③:30
[በል «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና]።
«አል ኢስራእ 81»
1 994
«የእውነት ባልተቤቶች ዝም ሲሉ፤ የባጢል ተከታዮች በሓቅ ላይ እንዳሉ ያስባሉ»
¤ እወቁልን እዩልን ሲሉ የነበሩ ሰዎች አትዩን አትወቁን በማለት በየስርቻው በመመሸግ ለውይይት ብሎ ለደወለላቸው የብሎክ ናዳ በማዝመት መጠመዳቸውን: ከወንድሞች የሰማሁት ብሎም በራሴ የተከሰተ አስደንጋጭ አጋጣሚ ነው።
1 994
¤ ማጠቃለያው፦አንድ ሰው አሏህን "ጅስም" በሚል ቃል ከገለፀ እናም የቃሉን ትርጓሜም የሚረዳ እንደሆነ አሏህን የተገጣጠመ ነው፤ እያለ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።ከዛ አስከትሎ "ላ ከል አጅሳም" ማለቱ ሙነዚህ ነው በምንም መልኩ ሊያስብለው አይችልም።ምክነያቱም የተገጣጠመ ነው ነገር ግን እንደተገጣጠሙት አይደለም ማለት ወደ ትርጉሙ ሲመጣ ዋጋ ቢስ እንዲሁ ሰውዪውን ከመክፈር የማያድነው ሆኖ እናገኘዋለን።ስለዚህ ሙጀሲምን ንግግሩ በሚያሲዘው ብቻ አይደለም እያከፈርነው ያለነው ቃሉ እራሱ ስድብና ፍጡር ማለት ስለሆነም ጭምር እንጂ፤ አሏህን በዲናችን ላይ ሰላምን እንጠይቃለን።
HAMZA
....ASEDULLAH
1 994
¤ ኣ·ሸይኹ ሙሓመድ ኣ·ሸንቂጥይ ይህን እርዕስ አስመልክተው እንዲህ ይላሉ፦[«ነገር ግን ሰውዪው ከንግግሩ የሚያሲዘው (ላዚሙ)ነገር ግልፅ ከሆነ ልክ #እንዳለበት በመሆኑ ላይ ዑለማዎች ዘንዳ #ልዩነት የለውም።ግልፅ የሚሆነው ነገር ለአሏህ አቅጣጫን ያፀደቀ አሏህን አካል እያለ እንደሆነ ግልፅ ነው»]።
ምንጭ፦<ኢስቲሓለቲ ኣል መዒየቲ ቢዛት>
📍ሆኖም ከዚህ ውጪ በስድ (ላዚሙል መዝሃቢ ለይሰ ቢመዝሃቢን) አልያ ሰውዪው ከንግግሩ የሚያሲዘው ነገር እንዳለበት አልያ ብለህበታል ተብሎ አይያዝበትም። የሚል የስድ መመርያ ካገኘህ ገዳቢ እንዳለው እርሱም የሚያሲዘው ግልፅ ካልሆነ በማለት ልትረዳው ዘንዳ በነዚህ የዑለማዎች ንግግር ትገነዘባለህ።
✧ ስለዚህ ዑለማዎች በዚህ ሰው ከንግግሩ ሚያሲዘው ነገር እንዳለበት ነውና ያን አያይዘው ይከፍራል አልያ አይከፍርም የሚልን ልዩነት በስፋት የገለፁበት መመርያ በዚህ መልኩ ግልፅ ባልሆነበት ቦታ ላይ እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል። ምክነያቱም ይህ ሰው ቢስሚላህ ሲል በምግብ የያዘውን ልምድ ብቻ ተከትሎ በመጠጡ በረካንም ሆነ ውዴታን ማግኘት አስቦ ላይሆን ይችላልና የዑለማዎች በላዚሙ የማክፈር ሂደት ልዩነቱ ንግግሩ የሚያሲዘው ነገር ግልፅ ባልሆነበት ቦታ ላይ እንደሆነ ሊሰመርበት የተገባ ይሆናል በማለት ደጋግሜ ላሰምርበት እሻለው።
🚨ተጨማሪ ላዚሙል መዝሃብ (ንግግሩ የሚያሲዘው ነገር ግልፅ) የሆነ እንደሆነ ብሎበታል እንደሚባል፤በዚህም ላይ ጥቂት የዑለማኡል ኢስላምን ንግግር አጠር ባለ መልኩ ልገልፅ ወደድኩ እነሆ፦
①፦قال الشيخ محمد الدُسوقي في [ حَاشِيَةُ الدُّسُوقِي عَلَى الشرح الكبير للشيخ الدردير، (٢٨١/٦)]. (قَولُهُ: وَيَسْتَلْزِمُ إِلَحْ أَي وَأَمَّا قَولُهُم لَازِمُ المَذهَبِ لَيسَ بِمَذهَبٍ فَمَحْمُولُ عَلَى اللَّازِمِ الخَفِي».
¤ ኣ·ሸይኽ ሙሐመድ ኣዱሱቅይ የኩፍርን ማስፈረጃ የሆኑ ነገራቶች በሚያብራሩበት ክፍል ላይ ያስይዛል "ويَسْتَلْزِمُ"በተባለበት ላይ ገለፃ ሲሰጡ እንዲህ ይላሉ፦[«ነገር ግን አንዳንድ (ዑለማዎች) "ላዚሙል መዝሃቢ ለይሰ ቢመዝሃቢን" ማለታቸው ("ድብቅ") በሆነ ላዚም የሚተረጎም ነው»]።ምንጭ፦<ሓሺየቱ ኣ·ዱሱቅይ ዓለ ሸርሒል ከቢይር>
②፦وقال الكوثري في شرح العقيدة الطحاوية ص٣٦٤" وهذا الاستلزام بين وما يقال من أن لازم المذهب ليس بمذهب إنما هو فيما إذا كان اللزوم غير بين، فاللازم البين لمذهب العاقل مذهب له،" انتهى
¤ ኣል–ኢማሙ ዛሂዱኒል ከውثَሪይ እንዲህ
ይላሉ ፦[«ላዚሙል መዝሃቢ ለይሰ ቢመዝሃቢን የሚለው "ላዚሙ (ንግግሩ የሚያሲዘው) ግልፅ ካልሆነ ነው።ነገር ግን የሚያሲዘው ነገር ግልፅ ከሆነ እርሱ ለጤነኛው ሰው ንግግር መንገዱ ተደርጎ ይቆጠራል»]።ምንጭ፦<ሸርሑ ኣል–ዓቂይደቲ ኣጦሓውያህ>
③፦وَقَالَ التَّقِيُّ السبكي رَحِمَهُ اللهُ: وَمَن أَطلَقَ القُعُودَ وَقَالَ: إِنَّهُ لَم يُرِدْ صِفَاتِ الْأَجْسَامِ؛ قَالَ شَيْئًا لم تَشهَد بِهِ اللَّغَةُ، فَيَكُونُ بَاطِلًا، وَهُوَ كَالمُقر بالتجسيم المنكر له فيؤاخذ بإقراره ولا يفيده إنكاره. انتهى.
¤ ኣል–ኢማም ተቂይዲን ኣ·ሱብክይ አሏህ ይዘንላቸውና እንዲህ ይላሉ፦[«ለአሏህ የመቀመጥን ባህሪ አስጠግቶ ነገር ግን የፍጡርን ባህሪ አልፈለኩበትም ያለ እንደሆነ፤ ይህ ሰው ቋንቋ በማይዘው ትርጉም አልባ በሆነ ነገር የተናገረ ይሆናል።ይህም ውድቅ ሲሆን፤ይህ ሰው የሚያስተባብለውን የሆነ የተጅሲም ባህሪን በእውነታው ሲታይ ለአሏህ አፅዳቂ ይሆናል ማለት ነው በዛው ይያዛል ማስተባበሉ አይጠቅመውም»]። ምንጭ፦<ኢትሓፉ ሳዳቲል ሙተቂይን>
↪ምክነያቱም ከንግግሩ አሏህን ተቀምጧል ማለቱ አሏህን በፍጡር ባህሪ አልገለፅኩም ቢልም ከፍጡር ጋር እንዳመሳሰለው ናውና ላዚሙ (ሚያሲዘው) ግልፅ ነው።
④፦قال الحافظ السخاوي ناقلا عن شيخه الحافظ ابن حجر العسقلاني: «〔والذي يظهر أن الذي يحكم عليه بالكفر من كان الكفر صريح قوله، وكذا من كان لازم قوله وعرض عليه فالتزمه،〕
¤ ኣል–ሓፊዙ ኣሰኻውይ ከሸይኻቸው ኣል–ሓፊዙ ኢብን ሓጀር ኣል–ዐስቀላንይ ሲያስተላልፉ እንዲህ ይላሉ፦ [«ግልፅ የሆነው ነገር አንድ ሰው ላይ በኩፍር የሚፈረጀው ግልፅ ንግግሩ ይህን ሲያመለክት ነው፤እንዲሁ ንግግሩ የሚያሲዘው ኩፍር ከሆነና ያን ኩፍር ፈልጎበት እንደሆነ ሲጠየቅ ከተቀበለ ከእስልምና ይወጣል»]።
ምንጭ፦<ፈትሑል ሙغِይثْ>
⑤፦قال الشيخ الكَشمِيري في إكفار الملحدين: " أن من لزم من رأيه كفر لم يشعر به، وإذا وقف عليه أنكر اللزوم وكان في غير الضروريات وكان اللزوم غير بين فهو ليس بكافر، – أي إن لم يلتزمه".
¤ የሱነኑ ኣቲርሚዝይ ሻሪሕ የሆኑት ታላቁ ዓሊም ኣ·ሸይኽ አልኪሽሚሪይ በዚህ *ንግግርህ የሚያሲዘው ነገር አንተ ባትልበትም እንዳልከው ይቆጠራል አልያስ አይቆጠርም በሚለው የ ፉቀሃኦች
"لازم المذهب هل هو مذهب أم غير
مذهب"
የሚለው ነጥብ ላይ በሰጡት ማብራርያ እንዲህ ይላሉ፦[“ሰውዪው ሳያስበው በንግግሩ ኩፍርን ሚያስፈርጅ ከሆነ ነገር ግን በንግግሩ ምክነያት የሚያሲዘውን ተጠይቆ እርሱን አልፈልግበትም ብሎ ከመለሰ ያም ነገር ከአንገብጋቢ የእውቀት ክፍል እንዲሁ (የሚያሲዘው ነገር ግልፅ) ካልሆነ ማለትም *ላዚሙ በይን* ካልሆነ አይከፍርም። ማለትም በኩፍር ሚያስፈርጅበትን ትርጓሜ ካልያዘበት”]።ምንጭ፦<ኢክፋሩል ሙልሒዲይን>
📍 ተመልከት አንድ ሰው የኩፍር ንግግር ከተናገረ ላዚሙ አልያ ንግግሩ የሚያሲዘው ግልፅ ከሆነ ያለ ምንም ንትርክ ይከፍራል።
⑥፦قال الخُرشِي في حاشية مختصر سيدي خليل〔إلا أن يقال لازم المذهب ليس بمذهب ظاهره ولو بينا مع أن اللازم إذا كان بينا يكون كفراً ولا يخفى أن اللازم هنا بين فلينظر ذلك〕
📌 ኣል ኹርሽይ በሰይድ ኽሊል ላይ ባዘጋጁዋት ሓሺያቸው የጥሪ ቃሉን ባልተቤት ንግግር አስታከው ስለ ኩፍራዊ ንግግሮች እየጠቀሱበት ባለበት ላይ እንዲህ ይላሉ፦[ነገር ግን ላዚሙል መዝሃቢ መዝሃብ አይደለም እስካልተባለ ድረስ የተባለው ንግግር ሚያሲዘው ነገር በይን አልያ ግልፅም ቢሆን የሚል ያስመስላል:ነገር ግን እዚህ ንግግር ላይ የሚያሲዘው ግልፅ ነው ይህም ኩፍር ነውና፤ ምልከታ ያስፈልገዋል”]።
ምንጭ፦<ሓሺዩል ኹርሽይ>
※ በማለት ስለ ላዚሙል መዝሃብ ለይሰ ቢመዝሃብ በሚል መመርያ በስድ የሚያውጁ ኪታቦች ገደብ እንዳላቸው ያሳውቃሉ።እንዲሁ ላዚሙል ቀውል ግልፅ ከሆነ ልክ እንዳለበት ተደርጎ እንደሚቆጠርም የዑለማዎቹ ትንታኔ ያስረዳል። በዚህም ላይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ያገላበጠ ሁሉ እያወጣ ሚናገርበት መምታት ስለቻለ ብቻ እንደ ኳስ ሜዳ ሚራገጥበት ዲን አይደለም ሰይደል ውጁድ ያወረሱት ይህም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።
1 994
ሰውዪው ይህን አስቦ እንጂ በሌላ መልኩ ሊለው አይችልም በሚባልበት መልክ አይደለም)።#ከንግግሩ የሚያሲዘው አልያ لازِمُ الْمَذْهَبِ ደግሞ ማለትም የሰውዪው ንግግሩ የሚያሲዘው #ግልፅ (በይን) ካልሆነ እርሱ ብሎበታል አይባልም።ልክ በዚህ ምሳሌ የተጠቀሰው ሰውን ይመስል”]።
ምንጭ፦<ኪታቡል ፉሩውቅ>
✧ ስለዚህ ዑለማዎች በዚህ ሰው ከንግግሩ ሚያሲዘው ነገር ልክ እንደተናገረበት ተደርጎ ይቆጠራል አልያ አይቆጠርም የሚለውን ሓሳብ በመንተራስ ይከፍራል አልያስ አይከፍርም የሚልን ልዩነት ያመጡት በዚህ መልኩ ንግግሩ የሚያመለክተው ፍቺ ግልፅ ባልሆነበት ቦታ ላይ እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል።ምክነያቱም ይህ ሰው ቢስሚላህ ሲል (በምግብ የያዘውን ልምድ ብቻ ተከትሎ በመጠጡ በረካንም ሆነ ውዴታን ማግኘት አስቦ ላይሆን ይችላልና የዑለማዎች በላዚሙ የማክፈር ሂደት ልዩነቱ ንግግሩ የሚያሲዘው ነገር ግልፅ "#ባልሆነበት" ይህን በመሳሰሉት ቦታ ላይ እንጂ ሰውዪው ባሻው ሁሉ ንግግር አፉን እያልከሰከሰ በቃ እርሱ አልፈለገበትም፤ በማለት ሁሉን አቃፊ በመምሰል ይድንበታል የሚያስብል እንዳልሆነ በጥብቅ ሊሰመርበት የተገባ ይሆናል ማለት ነው።
✧ አንተ ቅኑን መንገድ ለመመራት ከጃይ የሆንክ ወንድሜ ሆይ ኣል-ኢማሙል ኣል-ቀራፍይ ስለ ላዚሙል መዝሃብ መች ነው ለይሰ ቢመዝሃብ ወይም መዝሃቡ ነው: በሚል መመርያ የማክፈርና ያለ ማክፈር (ልዩነት)፤ የሚለውን እንዲሁ እንዳልክበት አልያ (መዝሃብህስ) ነው በመባል ደግሞ ያለ ምንም ማስተባበያ ዑለማዎቹ ዘንዳ ያለ ልዩነት ይከፍራል ስለተባለው ሰው ግልፅ የሆነ ጠቋሚ ማብራርያ ሰጥተው አልፈዋል።የዑለማዎችም ልዩነት የሚያሲዘው ንግግሩ ግልፅ ባልሆነ ላይ መሆኑንም አስምረውበታል።ነገር ግን አንድ ሰው ንግግሩ የሚያሲዘው ቃሉ ኩፍር ከሆነና እርሱም ግልፅ ከሆነ እርሱን መዝሃብህ አልያ እንዳልክበት ነውና በማለት የሚደረገው የማክፈር ሂደት ዑለማዎች ዘንዳ ልዩነት የለም። እንዲሁ ሰውዪው አላልኩበትም ያለም እንደሆነ ዑዝር ሳይሰጠው የከፈረ ይሆናል።የተናገረበትን ቃል የተገነዘበ እንደሆነ ማለት ነው።ይህንም ከዑለማዎች አንደበት ከተወሳ ምሳሌ ጋር አያይዤ ለመጥቀስ ልሞክር፦
(لَازِمْ المَذْهَبِ مذْهبٌ إن كان بينََا)
📍አንድ ሰው ከንግግሩ የሚያሲዘው ውጤት ግልፅ ከሆነና እርሱም ኩፍር ከሆነ በዛ ውጤት አልያ በቃሉ አመልካች ነገር እንዳልክበት ነው በመባል ይፈረጅበታል።
√ وَقَالَ الشيخ مُحَمَّدُ عَلِيش المالكي في منح الجليل]: وَسَوَاء كَفَرَ بِقُول صَرِيح في الكفر... أو بلفظ يقتضيه، أي يستلزم اللفظ الكفر استلزامًا بَيْنَا ... وكاعتقادِ جِسمِيَّةِ اللَّهِ وَتَحْيَزِهِ، فَإِنَّهُ يَسْتَلزِمُ حُدُوثَهُ وَاحْتِيَاجَهُ إِلَى مُحدِث». إلخ
¤ ኣ·ሸይኽ ሙሐመድ ዒለይሽ አል–ማሊክይ እንዲህ ይላሉ፦[«ግልፅ በሆነ የኩፍር ቃል ቢናገርም አልያ (“ኩፍርን የሚያስፈርጅ”) በሆነ ንግግርም ቢሆን ማለትም ቃሉ ወደ ኩፍር በመምራቱ ላይ “ግልፅ” በሆነ መልኩ አመላካች ከሆነ ያከፍረዋል።ለምሳሌ ያህል አሏህን አካል አልያ የተቀጣጨ ነው ብሎ የሚያምን ከሆነ ይህ ነገር አሏህን ፍጡር እንዲሁ ወደ ፍጡር ፈላጊ መሆኑን ያስይዛል»]።
ምንጭ፦<ሚነሑል ጀሊይል>።
✧ ይህን ንግግር ለመቀበል ፍትሓዊ መሆን እንጂ ሌላን እንደማይጠይቅ እብለት የለውም። አሸይኽ ሙሐመድ ዒለይሽ አንድ ሰው ንግግሩ የሚያሲዘው ግልፅ ከሆነና እርሱም ኢማኑን የሚያበላሽ ንግግር ከሆነ ይከፍራል በማለት አስፍረዋል።ይህም ተናጋሪው ሰው ምንም ያህል አልፈለኩበትም በሚል ህሳቤ ቢሞግትም የተናገረበት ቋንቋን መረዳት የሚችል እስከሆነ ድረስ ካፊር ነው እንላለን ማለት ነው። እርሳቸው በምሳሌነት የጠቀሱትም አሏህን #አካል (ጅስም) አልያ #የተቀጣጨ ነው ብሎ አንድ ሰው የሚያምን ከሆነ ይህ ሰው አሏህ #ፍጡር እንዲሁ ፈላጊ እንዳለ ነውና ይከፍራል ማለታቸውን አስተውል።አሏህን ጅስም ነው ያለ ሰው አሏህን ፍጡር ነው እንደማይል ሙጀሲማዎችም ቢሆን አሏህ ፍጡር ነው በግልፅ እንደማይሉ የታወቀ ሆኖም ሳለ:ነገር ግን አካል ሆኖ ፍጡር ያልሆነ የለምና ሁሉም አካል ፍጡር በመሆኑ አሏህን በአካልነት የገለፀ ግዜ አሏህን ፍጡር እንዳለ ነው።ይህም ሰው አሏህን ፍጡር ብለሀል አሏህንም በጉለት ገልፀሀል በማለት ይከፍራል።ቢክድም ፍጡር ሳይሆን አካል ነው ያልኩት ቢልም እንዳልክ ነው በማለት ቃሉን እስከተገነዘበ፣ ተገዶም እስካልሆነ የምላስም ወለምታ እስካልገጠመው በኩፍሩ ይፈረጃል ማለት ነው።ምክነያቱም ንግግሩ ሚያሲዘው ግልፅ ነውና በዚህ ቦታ ላይ ደግሞ እንዳልክበት ነው በመባል ፍርድ በመሰጠቱ አህሉል ዒልሞች ዘንዳ ልዩነት የለውም።
📍በዚሁ (لَازِمْ المَذْهَبِ مذْهبٌ إن كان بينََا) እንደሆነ ተጨማሪ የዑለማዎችን ንግግር እንጥቀስ፦
√ قَالَ الشَّيخُ مُحَمَّدُ عَبدُ العَظِيمِ الزَّرْقَانِي فِي كِتَابِهِ [مَنَاهِلِ العِرفانِ: وَقَدْ كَفَرَ العِرَاقِي وَغَيْرُهُ مُثبِتَ الْجِهَةِ لِلَّهِ تَعَالَى، وَهُوَ وَاضِح؛ لِأَنَّ مُعتَقِدَ الجِهَةِ لَا يَمكِنُهُ إِلَّا أَن يَعْتَقِدَ التَّحَيرُ وَالجِسْمِيَّةَ، وَلَا يَتَأَنَّى غَيْرُ هَذَا ، فَإِن سَمِعتَ مِنهُم سِوَى ذَلِكَ فَهُوَ قَولَ مُتَنَاقِضُ وَكَلَامُهُم لَا مَعنَى لَهُ» انتهى.
¤ ኣ·ሸይኽ ሙሐመድ ዓብዱል ዓظِይም ኣ·ዘርቃንይ እንዲህ ይላሉ፦[«ዒራቅይም ሆነ ሌሎቹ ለአሏህ አቅጣጫ የሚያፀድቅን አክፍረዋል።ይህ የማክፈራቸው ምክነያት ደግሞ (“ግልፅ”) ነው። ምክነያቱም ለአሏህ አቅጣጫን ያፀደቀ ለአሏህ ቦታና አካልነትን ማድረጉ አይቀሪ ነው።ከዚህ ውጪ አይሆንም። ከዚህ ውጪ ያለን ከነርሱ ከሰማህ ያልተጣጣመ ንግግር ነውና ትርጉመ ቢስ ይሆናል»]።ምንጭ፦<መናሂሉል ዒርፋን>
»>በዚሁ ንግግራቸው ላይ ማስተዋል እንደሚቻለው አዘርቃንይ ለአሏህ አቅጣጫን ያፀደቀ መክፈሩ (#ግልፅ) ነው ማለታቸው ምክነያቱም ላዚሙ አልያ ሚያሲዘው ነገር ግልፅ የሆነና ግልፅ በሆነ ንግግር ደግሞ የሰውዪው መዝሃቡ አልያ ልክ እንደተናገረበት እንደሆነና ከዛ ውጪ አላልኩበትም ቢል ተቀባይነት የለውም በማለት ላዚሙ ግልፅ ከሆነ ልክ እንዳለበት ነው እንደሚባል በፅኑ ያስረዳል።በዚህም ላይ ልዩነት አልያ ንግግሩ መርጁሕ አልያ የተበለጠ የተባለበት መመርያ አይደለም።ለዚህም በዛ ያሉ ንግግሮችን እየጠቀስን እንሂድ፦
√ وقال الشيخ محمد الخضر الشنقيطي (ت: ١٣٥٤هـ) في كتاب استحالة المعية بالذات وما يضاهيها من متشابه الصفات: وأما إن كان اللزوم بينا فهو كالقول بلا خلاف، والذي يظهرُ أنَّ الجهة لازم عليها التجسيم لزوما بينا اهـ
1 994
መረጃ ይዳኘን ክፍል ⑦
«ላዚሙል መዝሃብ ለይሰ መዝሀበን»?
ይህን ካነበብክ የሙተመሽዒሮች ማምታቻ ግልፅ ይሆንልሀል።
يقولُ اللهُ تبارك وتعالى:
{وَلَكِنْ كُونُوا رَبَّانِيِّينَ بِمَا كُنْتُمْ تُعَلِّمُونَ الْكِتَابَ وَبِمَا كُنْتُمْ تَدْرُسُونَ}سورة آل عمران ٧٩.
✧ «ነገር ግን ለሰዎች በምታስተምሩት መፅሀፍ እንዲሁ በምታነቡትም እውቀትን በአቅም ምታበጁ ሁኑ» [ኣለ ዒምራን 79]
↪ ዘመኑ ሓቅ እንዲሁ ባልተቤቶቹ እንደ ሓጢያተኛ ሚኮነኑበት የውድቀት መስመር አበጂዎች የአንድነትን መስመር ጠባቂ በሚል ስያሜ ሚሞከሹበት።እውቀት አለው የሚባለው የ እውቀቱን ጡንቻ ለመለካካት ወደ ማህበራዊ ሚድያ የሚወጣበት፤ በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ሃሏ ቀርነት እየሆነ የመጣበት አስከፊ ግዜ ላይ ቆመን እንገኛለን።
↪ ይህ ውድቀት ደግሞ ከራስ አልፎ ሌላ በንፁህ አንደበት ተገርቶ ያደገን ትውልድ መቀመቅ ውስጥ መዝፈቅም ጭምር እንደሆነ መዘንጋት የለበትም። ለዛም አሏህ በምናስተምረው እንዲሁ በምንማረው የእውቀት ማድ ሰዎችንም ሆነ እራሳችንን እውቀት ስናቀስም የመረዳት አቅምን ባማከለ መልኩ ከትላልቁ የእውቀት መሶብ ከመጀመር ይልቅ ከትናንሾቹ መሆን እንዳለበት አሏህ ይነገረናል። ምክነያቱም ይህ ሳይሆን ከቀረና አዕምሮ ሙኽተሶራቶችን መቀበል እንጂ ሙጦወላቶችን ለመረዳት ብቁ ካልሆነ በዚህ ሰው ላይ ሰይዱና ዓልይ ያሉት ንግግር መከሰቱ የራቀ አይሆንም።
"قال عَليٌّ: حَدِّثوا النَّاسَ بما يَفهمون، أتُحِبُّونَ أن يُكَذَّبَ اللهُ ورَسولُه" رواه البخاري
✧ሰይዱና ዓልይ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ይላሉ፦[«ሰዎች በሚረዱት ልክ አናግሯቸው። አሏህና መልዕክተኛው እንዲዋሹ ትፈልጋላችሁን!»]
<ሶሒሕ አል–ቡኻርይ>
✧ እውቀቱ ጠቃሚ ቢሆንም ምንጩ እንዲሁ ገለፃዎቹ በሰዎች የግንዛቤ መጠን እንዲሰጥና እንዲለያይ ያደርገዋል። አሏህም እነኚህን ሰዎች ነው ከላይ በጠቀስነው የቁርኣን አንቀፅ ያወደሰው። ምክነያቱም እውቀት ሁሉም ጡንቻውን ለማሳየት ወረፋ ሚጠብቅበት ሲሆንና ያንን እውቀት ለመቅሰም የሚመጣው ሰው አቅሙ ካልዳበረ ከሰሚው በኩል ብዥታን በመፍጠር አሏህ ያላለውን ብሏል።ነብዩ ያላዘዙትን አዘዋል በሚል በስተመጨረሻም ጠሞ አጥማሚ በጅህልና ደልቦ መንገድን ስቶ አሳች ቀጣፊ በመሆን አስተማሪውም ፊደል ቆጣሪውም ያልደረሰበትን በመድረስ ይጣራል።
↪ የዚህም ውጤት ነው፤ሰሞኑ በማህበራዊ ሚድያ የኣቡ ጧሊብን እስልምና እንዲሁ የፊርዓውንን አማኝነት ለማወጅ የደፈሩ አንደበቶች ብቅ ብቅ ማለት የጀመሩት።ስንዴና ገለባን ያለየ ከኪታቡ የተኖረን ሁሉ ሓቅ ነው በማለት የነገደ፤ ነገ አንዱ ተነስቶ ነብዩን ጥቁር ነበሩ የሚል ኺላፍ፤ ኪታብ ላይ አይቻለው ብሎ እንደማይመጣ ምንም ዋስትና አይኖርም።
✧ እኛም ከላይ በተጠቀሰው የቁርኣን አንቀፅ ለመስራት በሚል ሕሳቤ ሰሞኑ አሏህን «جِسْمٌ كالأجسامِ» ያለን ማለትም “#አሏህን አካል ነው ልክ #እንደኛ አካል የሆነ ”ያለ እንደሆነም ከማክፈራችን በፊት (ላዚሙል ቀውል) ምንድን ነው? አልያ ንግግሩ ምንን ያሲዛል በማለት እንጠይቀዋለን :የሚሉ አፈንጋጭ አስተሳሰብ ያላቸው ቡድኖች መበራከታቸውን መታዘብ ችለናል ።ለዚህም እንደ መደበቅያነት የሚጠቀሟት ፉቀሃኦች ዘንዳ ምትነሳ፦
(«لَازِمُ الْمَذْهَبِ لَيْسَ مَذْهَبََا»)
የሚልን ስዳዊ አ/ነገርን (መመርያ) ሲሆን፤ይህንን ዓ,ነገርም በተገቢው መልኩ ባለመረዳታቸው በዚህም አንድ ሰው ምኑንም ያህል "ኩፍራዊ ቃላቶች ቢከሰቱበት የሸሪዓን ሕግ በንግግርህ አስክደሀል እንዲሁ አሏህን አመሳስለሀልና ትከፍራለህ ከማለት በፊት "ምን አስበህ ነው የተናገርከው? አልያ ምን ነይተህ ነው በውስጥህ? አለፍ ሲልም ተናጋሪው በሚፈልገው ትርጉም እንጂ በቃሉ አመላካችነት ብቻ ፍርድ አይሰጥም መመርያው ሚለው፦
«لَازِمُ الْمَذْهَبِ لَيْسَ مَذْهَبََا»
ስለሆነ በማለት ሲሞግቱ አስተውለናል።ይህ ውድቅ እና የእውቀት መቀጨጭ የተስተዋለበት ንግግር እንደሆነ ለሁሉ ወዳቂ አንሺ አይጠፋውምና ያገኙትን በየስርቻው ከመጠመድ ለማይታክቱ ለነኚህ የፊትና ሰዎች ይህን ነጥብ አስመልክቼ ጥቂት ማብራርያ ልስጥበት።
📍በመጀመርያ ብዙ ሰው ያልተረዳው ነገር ፦
«لَازِمُ الْمَذْهَبِ لَيْسَ مَذْهَبََا»
ማለት ምን ማለት ነው? ቀጥሎም ወደ ዑለማዎች ማብራርያ እንጓዛለን።
፨«لَازِمُ፦ብሎ ማለት፦[የአማረኛው ፍቺ
*የሚያሲዘው* ማለት ሲሆን]።
፨«الْمَذْهَبِ፦ብሎ ማለት እዚህ ቦታ ላይ [ንግግር ማለት ነው]።
፨ ليسَ مَذْهَبََا ፦ብሎ ማለት [ያንተ ንግግር አልያ መንገድህ አይደለም ማለት ነው]።
📌✧ አጠቃላይ ትርጓሜውም [አንድ ሰው ከንግግሩ የሚያሲዘው ነገር የእርሱ ንግግር አይደለም] የሚል መመርያ ሆኖ እናገኘዋለን።ይህ ነገር በቀላሉ ሊገባ አይችልምና ከዑለማኦች ምሳሌ ጋር አያይዤ ለመጥቀስ እሞክራለው እነሆ፦
قال في الفروق "إن قال بسم الله الخ عند شرب الخمر ونحوه يكفر على ما في الخلاصة لأن التبرك والاستعانة بذكره لا تتصور إلا فيما فيه إذنه ورضاه"
📌ኣል–ኢማም ኣል-ቀራፍይ ኣል-ፉሩቅ ላይ እንዲህ ይላሉ፦[“አንድ ሰው ኽምርን ሲጠጣ ቢስሚላህ ብሎ የጀመረ እንደሆነ ኣል-ኹሏሷህ ላይም እንደተቀመጠው #ይ*ከ*ፍ*ራ*ል። ምክነያቱም በረካንም ሆነ በአሏህ እገዛን መከጀል የሚጠየቀው የእርሱ ፍቃድ እንዲሁ ውዴታው ባለበት ድርጊት ላይ አንጂ አይታሰብምና ነው”]።
…ማለትም አሕባቢ ይህን የዑለማዎች ንግግር ልብ ብለን ካተኮርንበት እነኚህ ዑለማዎች ሰውዪው መጠጥን ሲጠጣ "ቢስሚላህ" በሚል ንግግሩ በሚያሲዘው ነገር እያከፈሩት እንደሆነ ልብ ልንል ይገባል።እነርሱ ለማክፈር ያቀረቡትም መንስኤ አንድ ሰው ቢስሚላህ ሚለው የአሏህ ፍቃድ እንዲሁ ውዴታ ባለበት ስራ ላይ ነውና።ይህ ሰው መጠጥ ሲጠጣ ቢስሚላህ ማለቱ መጠጡ ፍቁድ እንዲሁ የአሏህ ውዴታ አለበት (እንዳለ ነውና) ይ*ከ*ፍ*ራል።ይላሉ።
📌አስከትለውም ኣል-ቀራፊይ የከፊል ዑለማዎች መንገድ በዚህ በኩል መጠጥ ሲጠጣ ቢስሚላህ በማለቱ ብቻውን (አ*ይ*ከ*ፍ*ር*ም)። የሚልን አቋም ካንፀባረቁ ቡሀሏ ለዛም አንተርሰው እንዲህ በማለት ከፊሎቹ ላከፈሩበት ምክነያት በዚህ መልኩ አያይዘው (#መልስ)።ያስቀምጣሉ፦
وقال أيضا " لو سلمنا إن الاستعانة والتبرك به لا تتصور إلا فيما فيه إذنه ورضاه فهو أمر لم يقصده، وإنما هو لازم لما فعله ولازم المذهب ليس بمذهب إذا لم يكن اللزوم بين كما هنا خصوصاً"
√ [“(ይህ የከፈረው) እናንተ እንዳላቹት እገዛም ሆነ በረካን መፈለግ የሚሆነው የአሏህ ውዴታ እንዲሁ ፍቃዱ ባለበት ስራ ላይ ነውና (ይህ ሰው ደግሞ በረካ እንዲሁ ስራዪ ውዴታ አለው ብሎ #እንዳለ ነው። በማለት ያስያዛችሁት ላዚሙል ቀውል) ይህ ሰው በእርግጥም ቢስሚላህ ሲል የአሏህን ውዴታ እንዲሁ ሸሪዓው ፈቅዶልኛል የሚል አስቦ #ላይሆን ይችላል። ይልቅንስ ይህ ሰውዪውን ያከፈራቹበት ላዚሙ በይን (ቀጥተኛ ትርጓሜው) ሳይሆን ከንግግሩ (#በሚያሲዘው በሆነ ነገር እንዲሁ ያም ቢስሚላህ በማለቱ ብቻ የሚያሲዘው ግልፅ ባልሆነበት ማለትም
1 994
✧ አርራዝይ በዚህ ኪታባቸው ያስተላለፉት የጋራ አቋም የአራቱ መዛሂቦችን ብቻ ሳይሆን የዲኑን ሊዋእ ዋና ተሸካሚ የሆኑት የነብያቶችን የጋራ ስምምነት እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል።እርሱም ከአሏህ ውጪ ያለን የተገዛ አልያ ያመለከ ካ*ፊ*ር እንደሆነ ነው። እንደተመለከትነው የኮከብና የመሬት ያህል እርቀት ያላቸው እኚህ ንግግሮች እንዴቱንስ ከአንድ ሰው ይከሰታሉ የሚለውን የአስተውሎት ባለቤት ይቀበለዋል? በፍፁም! እንደሚታወቀውም ከአሏህ ውጪ ያለን የተገዛ ሙስሊም ተብሎ ፈፅሞን ሊሰየም እንደማይችል ሁሉም ዘንዳ የታወቀ እውነት ነው።
↦ቀጥሎም እዛው ኒሃያ ኪታብ ላይ እንዲህ ሚል ሰፍሮ እናገኛለን ፦
✘ أما الذي ذكروه في تكفير المشبهة؛ فالذي قالوه أولا: من أنهم جهال بالله تعالى، فهو ضعيف؛ لما مر.أن الجهل بالله تعالى لا يقتضي الكفر على الإطلاق.
[«ነገር ግን ሙሸቢሃዎች ይከፍራሉ ብለው የፈረዱ ሰዎች ለዚህም "አሏህን አላወቁም" በማለት ለማክፈር ሚያነሱት ምክነያት ላለፉት ነጥቦች ሲባል ደካማ ነው።ምክነያቱም አሏህን አለማወቅ በስድ ሁሌ መክፈርን አያስፈርጅም»]
ምንጭ፦<ኒሃየቱል ዑቁውል 297>
¤ የዚህ ንግግር ይዘትም ሙሸቢህ አሏህን ከፍጡራን ጋር ቢያመሳስልም ነገር ግን ፈፅሞ ጌታውን አላወቀም (በፈጣሪው ላይ መሀይም ነው) የሚል ፍርድን አያሲዘውም።የሚል ድንግርት አጫሪ ህሳቤን ያዘለ ነው።
〽️ ከዚህ በተቃራኒ ይህን በሚጣረስ መልኩ ደግሞ አሏህን ከቦታ እንዲሁ ከአቅጣጫ አጥርቶ አለማወቅ “መሀይምነት” አንደሆነ ተፍሲራቸው ላይ በዚህ መልኩ ቁልጭ አድርገው ያኖራሉ፦
وقال الإمام فخر الدين الرازي في تفسيره ما نصه " وإن لم يقطع بتنزيه الله تعالى عن المكان والجهة بل بقي شاكا فيه فهو جاهل بالله تعالى «انتهى
[«አሏህን ከቦታ እንዲሁ ከአቅጣጫ በማጥራት ላይ በቁርጥ ካላመነ ይልቅንስ ተጠራጣሪ ሆኖ ከቆየ ይህ ሰው ጌታውን አላወቀም»]።
ምንጭ፦<ተፍሲሩ ኣርራዚ>
¤ ይህ ብቻ አይደለም። ይልቅንስ የተሽቢህ እምነት ባልተቤት የሆነ ሰው ኩፍር ውስጥ ወድቋልም በማለት በተለያዩ ቦታዎች በኡሱልና በተፍሲራቸው ኪታቦቻቸው በግልፅ እና በተደጋጋሚ ያወጁ ሲሆን ከነዛም ውስጥ ጥቂቱን እንጥቀስ፦
قال في كتابه الخمسون في أصول الدين مانصه " ["الحجة الرابعة: هو أن الحكم على الشمس والقمر بكونهما لا يصلحان للإلهية لكونهما جسما، فلو جاز كون الإله جسما لما بقي دليل على امتناع إلهية الشمس والقمر، وهذا اعتقاده عين الكفر والإلحاد، "انتهى
[«ፀሀይ እንዲሁ ጨረቃ ለጌትነት አይበቁም የሚለው ፍርድ የተሰጠው ምክነያቱም ሁለቱም አካል ስለሆኑ ሲሆን:የዓለም ፈጣሪ አካል መሆን ቢያመች ኖሮ የፀሀይ ሆነ የጨረቃ ጌትነት ለመከልከሉ ማስረጃ ባልኖረ ነበር።ፈጣሪን አካል አድርጎ መያዝ ደግሞ እራሱ ኩ*ፍ*ር ነው»]።
ምንጭ፦<ኡሱል ኣዲን>
¤ በቅርብ ግዜ እንደምናስታውሰው የፊትና ሰዎች አርራዝይ ሙጀሲምን አያከፍሩም። ይልቅንስ የእርሳቸውም ጎራ ያለ ማክፈር አቋምን ነው የያዙት በማለት በይፋ ሲያውጁ የሰማነው የመሳለቅያችን ትዝታዎች እንደነበሩ አይዘነጋም። ታድያ ራዝይ ስለ ሙጀሲማዎች ያላቸውን ትክክለኛ አቋም ከላይ በሰፈረው መልኩ ሆኖ እናገኘዋለን።እንዲሁ በዛው በኡሱል ኪታባቸው ላይ እንዲህ በማለት ይናገራሉ፦
وقال أيضا في كتابه "معالم أصول الدين" و نص عبارته : "بَل الأقرب أَنَّ المُجَسِمَة كُفَّار لأنَّهم اعتقدوا أنَّ كُلَّ ما لا يكون متحيزاً ولا في جهة فليس بموجود.ونحْنُ نَعْتَقِدُ أَنَّ كُلَّ مُتحيّز فهو مُحْدَثٌ وخالِقَهُ مَوْجود لَيْسَ بِمُتحَيّز ولا في جهة فالمُجَسَّمَة نَفَوا ذات الشيء الذي هو الإله فيلزمهم الكفر" . انتهى
¤ [«ይልቅንስ ትክክለኛው ፍርድ #ሙጀሲማዎች ኩፋሮች ናቸው የሚል ነው።ምክነያቱም በእነርሱ ዕምነት በአንድም አቅጣጫ የማይቀጣጭ ከሆነ የለም ስለሚሉ ነው።እኛ ደግሞ በአቅጣጫ የሚሰፍር ባጠቃላይ ግኝ ነው ብለን እናምናለን። የሚቀጣጭ ነገር ፈጣሪ ደግሞ ያለ አቅጣጫ ያለ ሲሆን:ሙጀሲማዎች ደግሞ ሊያመልኩት ዘንዳ የሚገባውን ያለ አቅጣጫ ያለውን የአሏህን እውነታ ነው የካዱትና: መክፈራቸው የተገባ ነው»]።
ምንጭ፦<መዓሊሙ ኡሱሊ ኣ·ዲን>
※ እንዲህም ሲሉ በተፍሲራቸው ሙጀሲም የፈጣሪን መኖር የካደ መሆኑን ይጠቅሳሉ፦
وقال في تفسيره ما نصه :
" إن الدليل دل على أن من قال إن الإله جسم فهو منكر للإله تعالى، وذلك لأن إله العالم موجود ليس بجسم ولا حال في الجسم، فإذا أنكر المجسم هذا الموجود فقد أنكر ذات الإله تعالى، فالخلاف بين المجسم والموحد ليس في الصفة، بل في الذات فصح في المجسم أنه لا يؤمن بالله" اهـ.
[“አሏህን አካል ነው የሚል የእርሱን የመኖር ባህሪ የካደ እንደሆነ ማስረጃዎች አመላክተዋል። ምክነያቱም የዓለም ፈጣሪ ያለ ነው እርሱም አካል አይደለም።በአካልም የሰፈረ አይደለም።ሙጀሲም ይህን አካል ያልሆነ እንዲሁ በአካል የማይሰፍርን በመኖር የሚገለፅን ፈጣሪ ከካደ በእርግጥም የፈጣሪን መኖር ክዷል።በሙጀሲምና ጌታውን ከአካል በሚያጠራ ሰው መሀከል ያለው ልዩነት በባህሪ አይደለም።ይልቅንስ በእውነታው ላይ ነው።(ማለትም በፈጣሪ መኖር አለመኖር ላይ ነው)።በእርግጥም ሙጀሲም አሏህን እንደማይገዛ ተረጋግጧል”]።
ምንጭ፦<ተፍሲሩ ኣርራዝይ>
¤ ታድያ የፈጣሪን መኖር የካደ ፈጣሪውን አውቋል አልያ በሁሉም መንገድ አላዋቂ አያሰኘውም። ለዚህም ሙስሊም ተብሎ ይሰየማል ለማለት ከየት የመጣ ድፍረት ነው?!
–––ይህም ብቻ አይደለም።እንዲሁ ሙጀሲም (ሙሸቢህ) አሏህን ተገዝቷል ወይ ለሚለው ጥያቄ ይህን የመሰለ ምላሽ አላቸው፦
وقال:"المجسم ما عبد الله قط لأنه يعبد ما تصوره في وهمه من الصورة ، والله تعالى منزه عن ذلك " انتهى
[«አሏህን አካል ብሎ የሚያምን አሏህን ፈፅሞ አልተገዛም።ምክነያቱም ይህ ሰው እየተገዛ ያለው በአዕምሮ ውስጥ የተቀረፀን ምስል ነው።አሏህ ደግሞ እርሱ ከሳለው ምስል የጠራ ነው»]
ምንጭ፦<ተፍሲይሩ ኣርራዝይ>
¤ በስተመጨረሻም አርራዝይ በተፍሲርም ሆነ በኡሱል ኪታባቸው ላይ በተደጋጋሚ የሰፈረው የእርሳቸው አቋም ይህ ነው።ከዚህ ውጪ በኒሃያ ላይ ሰፍሮ የምናገኘው ይህን ሚፃረር ንግግር የእርሳቸው ሳይሆን እርሳቸው በአንደበታቸው እንደተናገሩት ይህን የመሳሰሉ ሸሪዓን የሚፃረሩ ንግግሮች የሓጢያተኛ እጆች ውጤት እንደሆነ በበቂ እንዲሁ ግልፅ በሆነ መልኩ መገንዘብ ይቻላል።
መረጃ ይዳኘን
ክፍል ⑦ ይቀጥላል…
HAMZA
...ASEDULLAH
1 994
መረጃ ይዳኘን
ክፍል –⑥
قال الله تعالى {{ كُنتُمْ خَيْرَ أُمَّةٍ أُخْرِجَتْ لِلنَّاسِ تَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَتَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ }} <سورة آل عمران 110>
"ለሰዎች ከተገለጸች ሕዝብ ሁሉ በላጭ ኾናችሁ በጽድቅ ነገር ታዛላችሁ፤ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ።" [አል-ዒምራን 110]
✧ ፈጣሪን በማመፅ ሓጢያትን የተላመዱ አካላቶች፣ ኩነኔን በመናገር ሒሳብን ያቀለሉ አንደበቶች፤ ይህ አልበቃ ብሏቸው የታላላቅ የአሏህ ዲን ጠባቂ ሪጃሎች ስሜታቸውን ሰብረው ፍላጎታቸውን ገተው ለትውልዱ ይበጃል በማለት ቀን ከሌት ለዘመናት ሳይታክቱ ባበጁዋቸው ፋናዎቻቸው ላይ የተለመደ የወንጀል ብትራቸውን በማሳረፍ አሁን ላለንበት የፊትና ባልተቤቶች የመፈልፈያ እንደ ትልቅ ምንጭ በመሆን ማገልገላቸው የማይካድ ሀቅ ነው። እኔም ከላይ በተወሳው ቁርኣናዊ አንቀፅ ለመስራት በሚል በጎ አላማን በማንገብ እነኚህን የመሳሰሉ ሙንከራቶች ለመጠየፍ ሰውንም በመልካም ለማዘዝ ይህን አጠር ያለን ፁሁፍ አዘጋጅቻለው።
✧ የነኚህ አመፀኞች ብትር ካረፉባቸው ታላላቅ የእስልምና ሊቃውንታት መሀከል አንዱ ከሆኑት ውስጥ ታላቁ ዓሊም ኣል–ኢማም ፈኽሩ ዲን አርራዝይ ይገኙበታል፤ታድያ እጅጉን እውቅና የተሰጣቸው የዚህ የእውቀት ተምሳሌት ሰው ኪታቦችም ከነዚህ ለማዳ ሓጢያተኛ እጆች መእበል ያመለጡ አልነበሩም።ይልቅንስ እነኚህ አመፀኛ እጆች ጥቁር አሻራቸውን በድፍረት ማሳረፍ የጀመሩት በሕይወት ሳሉ ጀምሮ እንደሆነ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
«وَلَعَلَّ السَّبَبَ في وُقُوعِ أَمثالِ هذِهِ الكَلِمَاتِ في الكُتُبِ أَنَّ كَثِيرًا مِنَ النَّاسِ يُطالِعُونَ هذِهِ الكُتُبَ وَلَا يَفهَمُونَ الكَلَامَ فَهمًا صَحِيحًا مُطابِقًا، بَل يَتَخَيَّلُونَ أَشياءَ فاسِدَةً، وَيَظُنُّونَ أَنَّهَا هِيَ الوُجُوهُ الصَّحِيحَةُ، فَيُثبِتُونَ تِلكَ الكَلِمَاتِ المُشَوِّشَةَ عَلَى حَواشِي الكِتَابِ، ثُمَّ إِنَّ النَّاسِخَ الجَاهِلَ يَظُنُّ بِهَا أَنَّهَا مِن أَصلِ الكِتَابِ فَيُدخِلُهَا في الكِتَابِ؛ فَلِهذَا السَّبَبِ تَتَشَوَّشُ هذِهِ الكُتُبُ. فَإِنِّي قَد رَأَيتُ في تَصانِيفِي كَثِيرًا مِنَ النَّاسِ كَتَبُوا عَلَى حَواشِيها زَوائدَ فاسِدَةً، ثُمَّ إِنَّ قَومًا ظَنُّوا أَنَّهَا مِن أَصلِ الكِتَابِ فَأَدخَلُوها في المُتنِ، ثُمَّ رُبَّما جاءَ بَعضُهُم بِتِلكَ النَّتيجَةِ فَأَراها مَملُوءَةً مِنَ الحَشوِ وَالزَّوائدِ الفاسدة» انتهَى.
[«ኪታቦች ላይ ይህን የመሳሰሉ ስህተት የመከሰታቸው ምክነያት ብዙ ሰዎች እነኚህን ኪታቦች ያነቡና ነገር ግን ከፃህፊው ፍላጎት ጋር ተስማሚ ባልሆነ መንገድ በመረዳታቸው ይሆናል። ቀጥሎም የተበላሸ የሆነን ግንዛቤ በውስጣቸው በማሳደር ትክክለኛዋ መንገድ እርሷ ናት የሚል አስተሳሰብ ያሰርፃሉ።ያቺንም የጎደፈች ቃላት በኪታቡ ግርጌ ጋር ያስቀምጧታል።ቀጥሎም ኪታቡን ሊያሳትም የሚመጣው መሀይሙ ፀሀፊ የሙሓሺው (የሌላ ሰው ጭማሪ)የሆነች ንግግር መሆኗን ሳይረዳ ከዋናው የኪታብ እርዕስ ክፍል በማድረስ ይሰገስጋታል።በዚህም ምክነያት ኪታቦች ተበርዘዋል።“#እኔም በራሴ ኪታቦች ውስጥ ሰዎች በኪታብ ግርጌ ላይ ብዙ የተበላሹ ነገራቶችን ማስፈራቸውን ተመልክቻለው“።አንዳንድ ሰዎችም ከኪታቡ አንድ አካልም በማድረግ ከጥሬ ቃሉ አስገብተዋታል»። ምንጭ፦<ሸርሑ ዑዩውኒ አል–ሒክማህ>
✧ ይህ ንግግራቸው እርሳቸው ረዲየሏሁ ዐንሁ በሕይወት ሳሉ የሰጡት ሊሻር ማይቻል ህያው ምስክርነት ነው።እኛም ደግሞ ይህን ንግግራቸው በመመርኮዝ ከእርሳቸው ኪታብ ውስጥ የተገኘውን በሸሪዓህ ሕግ መሰረት አልባ እንዲሁ ኢማንን የሚነጥቁ የሆኑ ይዘት ያላቸውን ንግግሮችን ለማስመልከት አንባቢውንም ለማስጠንቀቅ ወደድን።
↬ በዛሬው ዳሰሳዪ ኒሃየቱል ዑቁውል በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ስለታዩ ገለፃዎች ሲሆን:እርሳቸው አርራዝይ በዚህ ኪታባቸው ገፅ 297 ላይ እንዲህ የሚል አደገኛ የሆነ ንግግር #ሰፍሮ እናገኛለን፦
✘ثم نقول : عابد الصنم إنما كفر؛ لأنه عبد غير الله مع اعترافه بأنه عبد غير الله، فهو إنما كفر لذلك، وأما المشبه فإن عبد غير الله تعالى مع ظنه أنه عبد الله تعالى فلا جرم لا يجب أن يكفر.
[«ጣኦትን የሚገዛ ሰው የከፈረው ከአሏህ ውጪ ያለን ከማምለኩ ጋር ሌላን ነገር በመገዛቱ #ስለመሰከረ ነው።እርሱ የከፈረው በመመስከሩ ነው።ነገር ግን ሙሸቢህ አሏህን እገዛለው ብሎ በማሰብ ከአሏህ #ውጪ ያለን ነገር ቢገዛ ክፋት የለበትም። ማክፈሩም ግድ አይደለም»]።
↣በኛ እምነት ይህ አይነቱ ንግግር ከእርሳቸው ተከስቷል አንልም።ይልቅንስ እርሶዎ በሕይወት ሳሉም እንደመሰከሩት ይህ የሓጢያተኛ እጆች አሻራ እንጂ የእርሳቸው አለመሆኑን ላሳውቅ እወዳለው። ይህን የመሳሰሉ መሰረት አልባ ፍርዶች ከዚህ ከመሰለ የእውቀት ፋና ቀርቶ ከአንድ ተራ ግለሰብ መከሰቱ የሚጠና ጉዳይ መሆኑ እብለት የለውም።
አደገኛ ይዘቶች፦
¸¹ በዚህ ንግግር ሕሳቤም አንድ ሰው ጣኦትን በማምለኩ ብቻ አይከፍርም የሚል ነው።ይልቅንስ የሚከፍረው ጣኦትን ነው ምገዛው በማለት መመስከርን ካቆራኘ ጭምር ነው።
¸² ቀጥሎም እንዲህ ሚል ነው፥አንድ ሙሸቢህ አሏህን የተገዛ መስሎት #ነገር ግን ከአሏህ “ውጪ” ያለን ቢያመልክ (ቢገዛ) ማክፈሩ ግድ አይደለም። በዚህም ንግግር ከማንም እንደማይሸሸገው "የአሏህ ልጆች ነን ያሉት የሁዳዎች እንዲሁ መሲሕ ማለት አሏህ ነው።አልያ ልጁ ነው" ያሉ አንደበቶች አይከፍሩም ሚያሰኝ ነው።ምክነያቱ አሏህን እየተገዛን ነው ብለው ስሚያስቡ።ይህ ንግግር የራዝይ ኪታብ ላይ ምንም ቢገኝ ትክክል እንዳልሆነ እንዲሁ የሓጢያተኛ እጆች ቅሪት ስለመሆኑ ምናውቅበት ሌላኛውና ዋነኛው መንገድ ከኒሃያ በመቀጠል ባዘጋጁት ተፍሲር ኪታባቸው ላይ ይህን አቋም ሙሉ በሙሉ የሚሽር የሆነን የነብያቶች የጋራን አቋም በግልፅ አስፍረው እናገኛለን እንዲህ ይላሉ፦
فنقول : أجمع كل الأنبياء عليهم السلام على أن عبادة غير الله تعالى كفر، سواء اعتقدوا في ذلك الغير كونه إلها للعالم أو اعتقدوا فيه أن عبادته تقربهم إلى الله تعالى ، لأن العبادة نهاية التعظيم.
✧ [እንላለን፦«ሁሉም ነብያቶች ከአሏህ ውጪ ያለን መገዛት #ክህደት በመሆኑ ላይ ተስማምተዋል።በዛ ነገር ላይ የዓለም ፈጣሪነትን ቢያምኑም አልያ የእርሱ አምልኮ ወደ አሏህ ታቃርበናለች በሚል ሕሳቤ ቢሆንም።ምክነያቱም አምልኮ የሚባለው የመጨረሻ ልቅና ነውና»]።
ምንጭ፦<ተፍሲይሩ አርራዝይ>
1 994
📌 { ግልፅን ቋንቋ አሻሚ ትርጓሜ እንዲኖረው ማድረግ የቅናት ውጤት አልያስ የእዝነት ተምሳሌት}
قال الشيخ: ثم إنه يشترط الحصول ثواب الصلاة على النبي تصحيح حرف الصاد مميزة عن السين، فمن لا يميز بينهما في النطق فلا ينال ثواب الصلاة على النبي، كذلك يشترط عدم زيادة الياء في كلمة صل» كما يزيد بعض الناس، قال العالم الفقيه طه عمر بن طه عمر الحضرمي الشافعي الذي كان من أهل القرن الحادي عشر في كتاب المجموع لمهمات المسائل من الفروع (ص/ ۹۷) ما نصه : وقال عبد الله بن عمر : من قال في تشهده اللهم صلي بالياء لم يجزه ولو جاهلاً أو ناسيا بل العامد العالم بالعربية يكفر به لأنه خطاب مؤنث اهـ .
¤ ሸይኻችን “ኣል ከዋኪቡ ኣ·ዱርያህ ፊይ መድሒ ኽይሪል በሪያህ” በተሰኘ ኪታባቸው ላይ ስለ ሶሏተ ዓለ ነብይ የማድረግያ ትክክለኛን መንገድ ሲያስጠነቅቁ እንዲህ ያላሉ፦« በነብዩ ላይ ሶለዋት ስናወርድ ምንዳ ልናገኝ ዘንዳ ቅድመ ሁኔታ ከሚሆኑ ነገራቶች መሀከል ሷድን ፊደል ከሲይን ለይተን ማውጣት አለብን።በሁለቱ ፊደላቶች መሀከል የማይለይ በሶለዋቱ ላይ ምንዳን አያገኝም።እንዲሁ «صلّ» በምትለዋ ቃል በስተመጨረሻ ያን በመጨመር «صلّيْ» በማለት እንዳይስብ አንዳንድ ሰዎች እንደሚጨምሩት።#ኣል–ዓሊሙ ኣል–ፈቂሁ ጧሃ ዑመር ብኑ ጧሃ ዑመር ኣል–ሓድረሚይ ኣሻፊዒይ በ 11 መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩት እኚህ ሰው ዓብዱሏህ ብኑ ዑመር እንዲህ ብለዋል በማለት ሲያስተላልፉ እንዲህ ይላሉ፦[“ተሸሁድ ሲያደርግ (اللهم صلّيْ) በማለት ያን ከጨመረ መሀይም እንኳ ቢሆን ተሸሁዱ አይበቃም። አልያ ረስቶም ቢሆን ቢል አይበቃም። ይልቅንስ ሆን ብሎ ዓረበኛ እያወቀ ይህን ካለ #(ይ*ከ*ፍ*ራ*ል)።ምክነያቱም አሏህን በሴት ፆታ ማናገር ስለሆነ ነው»]።
ምንጭ፦<ኣል መጅሙዑ ሊሙሂማቲል መሳኢል ገፅ 97>።
وهذا كثير في الحبشة يقولون اللهم صلي وسلم على سيدنا محمد وعلى اله يزيدون ياء في صل بعد اللام، فإن المعنى يتغير بزيادة الياء فيكون تأنيثا لله تعالى وهذا كفر .
✧ ሸይኻችንም ይህን ንግግር አስታከው እንዲህ ይላሉ፦ ["ይህ ነገር በሓበሻ ውስጥ በብዛት ይከሰታል።አሏሁመ (ሶሊይ) ዓላ ሙሓመዲን ወዓለ ኣሊሂ በማለት ሶሊ ሚለው ላይ (ሶሊይ) በማለት ከላም ቡሀሏ ያን ይጨምራሉ።በዚህም ምክነያት ትርጓሜው የሚለወጥ ሲሆን።አሏህን ሴት ማድረግ ያለበት ሲሆን:ይህ ደግሞ ኩ*ፍ*ር ነው"]።
📌 ታድያ ሸይኻችን ይከፍራል ያሉት ሆን ብሎ ዓረበኛን እያወቀ በተናገረው ሰው ላይ በመሆኑ ግልፅ ነው።የዚህን ያህል ሸይኻችን የኻዋሪጅ መዝሃብ ጥማት እንዳለባቸው አድርጎ የመቅረፅ ዘመቻ ከምን የመጣ ይሆን? አሁንም ሊታወቅ የሚገባው እርሳቸው ያከፈሩት ሆን ብሎ ዓረበኛን እያወቀ ያለን እንጂ ሳያውቅ አልያ ሳይረዳ ያለው እንደሆነ አይከፍርም።ስለዚህ ይህን የሚቃወሙ ሰዎች በመጀመርያ ያለው ስህተት ዓረበኛ ያለመረዳት እንደሆነ ሊያውቁ እንዲሁ የመረዳት አቅማቸውን እንዲፈትሹ ስል በግልፅ ላሳውቅ እወዳለው።
الله المستعان
HAMZA
....ASEDULLAH
1 994
በመረጃ ይዳኘን
ክፍል ⑥
«ኢል–ኢማም ፈኽሩዲን አርራዝይ
"እና" ሓጢያተኛ እጆች»
¤በዚሁ እርዕስ ላይ የሚካተቱ ዋና ዋና ሓሳቦች፦
① በሙጀሲም ዙርያ የአርራዝይ አቋም።
②አርራዝይ ሙጀሲምን አያከፍሩም የሚለው #የሙተመሽዒሮች ጥሪ ውድቅ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ።
③አርራዝይ በሕይወት ሳሉም ሓጢያተኛ እጆች ኪታቦቻቸውን በመበረዝ ላይ እንተጠመዱ።
ሌሎችም…
#ሼር እያደረግን።
ሰኞ ምሽት ④:00
HAMZA
....ASEDULLAH
