⛪️መንፈሳዊ መጻሕፍትን እናንብብ እንወቅ⛪️
Open in Telegram
በዚህ ቻናል የሚቀርቡ ፩.ተከታታይ የቤተክርስቲያን ትምህርቶች ፣ ፪. መንፈሳዊ መጻሕፍት ጥቆማ፤ ፫. የተለያዩ አጫጭር የቤተክርስቲያን መጣጥፎች ፣ ወጎች ፣ ታሪኮች ፤ ፬. ለተለያዩ ጥያቄዎች መልስ እና ወቅታዊ ትምህርቶችን እንማማራለን ፣ ፭. ዘወትር #ቃለ_ወንጌል የእለቱ(በግፃዌ) ይቀርባሉ። ተከታታይ ትምህርቶች ለማግኘት 👇👇 @EOTC_teketatay ለጥያቄ👉 @Temechache
Show more5 004
Subscribers
+224 hours
+117 days
+3430 days
Posts Archive
“ክርስቲያን” ተብለህ መጠራትህ ዋስትና አይኾንህም፤ ዋስትና የሚኾንህ …
በመንገድ ዳር ላይ ዘርን የሚዘሩ ሰዎች ምንም የሚያገኙት ጥቅም እንደ ሌለ ኹሉ፥ እኛም ለልጅነታችን የሚገባ’ ምግባር ከሌለን ክርስቲያኖች ተብለን ከመጠራት የምናገኘው በቁዔት የለም፡፡ ይህ እንዴት ይኾናል የምትለኝ ከኾነም የጌታችን ወንድም የተባለው ያዕቆብን ምስክር አድርጌ እነግርሃለሁ፡፡ እርሱ፡- “ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው” ብሎአልና (ያዕ.2፡17)፡፡ ስለዚህ ለእኛ (ለክርስቲያኖች) ምግባር መያዝ ግዴታ ነው፡፡ ምግባር ከሌለን ግን “ክርስቲያን” የሚለው ስም ለእኛ የሚፈይደው ምንም ነገር የለም፡፡ በዚህ ተደነቅህን? እንኪያስ ንገረኝ ! በዓውደ ውጊያ የማይሳተፍ፣ ለሚመግበው ንጉሥም የማይዋጋ ከኾነ አንድ ወታደር ወታደር ተብሎ ቢጠራ ምን ጥቅም አለው? ለንጉሡ ክብር የማይዋጋ ከኾነስ ወታደር ተብሎ ባይጠራ ይሻለዋል፡፡ ይህ ሰው በንጉሡ የሚመገብ ኾኖ እያለ፥ ነገር ግን ንጉሡ በጠላቱ ላይ ድል እንዲያደርግ የማይዋጋ ከኾነ እንዴት ከቅጣት ሊያመልጥ ይችላል? ንጉሡን ምሳሌ አድርጌ ልናገረው የፈለግሁትስ ምንድን ነው? ልለው የፈልገሁት እግዚአብሔር በትንሹ ስለ ገዛ ነፍሳችን እንድንጠነቀቅ (ምግባር መያዝ እንድንችል) ኃይል (ዓቅም) ሰጥቶናል ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#ቃለ_ወንጌልጷጉሜ 3/13/2017 ማቴዎስ 25:31-ፍጻሜ የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል። ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና። ጻድቃንም መልሰው ይሉታል ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ? እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ? ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን? ንጉሡም መልሶ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና። እነርሱ ደግሞ ይመልሱና ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል። ያን ጊዜ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል። እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።
መልእክታትዕብራውያን 7:1-5 ይሁዳ 1:11-17 ሐዋ፡ሥራ 5:17-26
ምስባክመዝሙር ፵፱ : ፪ - ፫ እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጉም እግዚአብሔር ግልጥ ኾኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል
ሐሞቱንና ጉበቱን ከዕጣን ጋር ጨምረህ ስታጤስበት በሣራ አድሮ የነበረው አስማንድዮስ ጋኔን ወጥቶ ይሄዳል፤ ፈጽሞም ወደ እርሷ በገባህም ጊዜ ሁለታችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው እግዚአብሔር ጸልዩ፤ እርሷም የተዘጋጀች ናት፤ ከእኛ ጋርም ወደ ሀገርህ ይዘናት እንሄዳለን›› አለው፡፡ ጦብያም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ደስ አለው፤ እርሷን ብቻ እንዲያገባ በሙሉ ሐሳቡ ወሰነ፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ራጉኤል ቤት እንደ ደረሱ ሣራ በደስታ ተቀበለቻቸው፤ ቅዱስ ሩፋኤልን ያንን በመንገድ የነገርከኝን አሁን ፈጽምልኝ ሲለው ሰምቶ ስለ ልጅቷ መሆኑን ስለ ገባው ራጉኤል ጦብያን ‹‹ልጄ ይህች ልጅ ላንተ የምትገባ ናት፤ ሰጥቸሃለሁ፤ አይዞህ፤ አትጠራጠር፤ አሁንም ብላ፤ ጠጣ፤ ለዛሬም ደስ ይበልህ›› አለውና ሣራ ካለችበት የጫጉላ ቤት አግብተው ዘጉት፡፡ ጦብያም ሣራን ‹‹በይ እኅቴ! ኑሮዋችን እንዲቃናልንና ጋብቻችን እንዲባረክልን አስቀድመን ወደ ፈጣሪያችን ጸሎት እናድርግ›› አላትና አብረው ጸሎት ካደረጉ በኋላ ያንን የያዘውንና የዓሣ ጉበትና ሐሞት ከዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤስበት በሣራ አድሮ ባሎችዋን ይገድልባት የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ከሣራ ለቆ ወጥቶ ለመጨረሻ ላይመለስ ሄደ፤ ከዚያ በኋላ አልተመለሰም፡፡ እነርሱም በሰላምና በጤና አደሩ፡፡ በመሆኑም የጦብያንና የሣራን ጋብቻ የባረከ ቅዱስ ሩፋኤል ስለሆነ “መልአከ ከብካብ” ይባላል፡፡ ዛሬም በምልጃው ላመኑት ጋብቻን ይባርካል፣ ትዳርንም ያጸናል፡፡
፯. ከሳቴ እውራን (ዓይነ ስውራንን የሚያበራ)
የሣራንና የጦቢያን የጤንነታቸውን ነገር ሲረጋገጥ የሰርጉ ቀን የሚሆን የዐሥራ አራት ቀን በዓል እስኪፈጸም ድረስ ጦብያ ወደ ሀገሬ አለሔደም ነበር፤ የዐሥራ አራት ቀን በዓለ መርዓ ከተፈጸመ በኋላ ግን ጥሬ ገንዘብና የከብት ስጦታ አድርጐ መርቆ ወደ ሀገሩ ሰደደው፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ሚስቱንና ግመሎቹን ይዞ በመጣ ጊዜ የጦብያ አባት ጦቢትም ልጅህ መጣ ሲሉት ዓይነ ሥውር ስለ ነበር እርሱን እቀበላለሁ ሲል ወደቀ፤ እንደ ወደቀም ወዲያው ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን የአባቱን ዓይን ሲቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ፡፡ በመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል አማካኝነት የጦቢያን አባት የጦቢትን ዓይን በራለት እንዳበራለት ቅዱስ ሩፋኤል ዛሬም በሒዲስ ኪዳንም በምልጃው ለሚያምኑት ሥጋዊ ዓይንና መንፈሳዊ ዓይንን የሚያበራ መልአክ ነው፡፡
የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ጸሎትና አማላጅነት ልጅ ለሌላቸው መልካም የልጅ ፍሬን፣ ለታመሙት ድኅነትን፣ ለባለ ትዳሮች እግዚአብሔር የፈቀደውን መልካም ትዳርን እንዲሰጥልን የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱስ ሩፋኤል ተረዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁንልን፤ አሜን፡፡
(ምንጭ:መጽሐፍ:- ቅዱስ፣ መጽሐፈ ስንክሳር፣ ተአምረ ሩፋኤል)
👇👇👇
@Eotc_spritual_books
@Eotc_spritual_books
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል በጳጉሜን ሦስት ቀን የሚዘከር በዓል ነው፡፡ “ሩፋኤል” የሚለው ስያሜ ትርጉም “ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ” ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከዕብራይስጥ ሁለት ቃላት ጥምረት የተገኘ ቃል ነው፡፡ “ሩፋ” ማለት ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት ማለት ሲሆን “ኤል” ሚለው በሌሎቹም መላእክት ስም ላይ የሚቀጸል ስመ አምላክ ነው:: ይህም “መልአኬን በፊትህ እሰዳለሁ፤….. ስሜ በእርሱ ስለሆነ አታስመርሩት” እንዲል፤ (ዘፀ.፳፫÷፳-፳፪)፡፡ በመሆኑም “ሩፋኤል” የሚለው በጥምረት “ከአምላክ ለሰዎች የተሰጠ ፈውስ” የሚለውን ያስረዳል፡፡ “ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ” እንዲል፡፡ (ጦቢት ፲፪፥፲፭) ይህ መልአክ እንደ ሌሎቹ ሊቃነ መላእክት ሁሉ የሰው ልጆችን ይጠብቃቸዋል፡፡
ዠ (ዳን.፬÷፲፫፣ዘፀ.፳፫÷፳፤ መዝ.፺÷፲፩-፲፫) ያማልዳል፤ ከፈጣሪ ያስታርቃቸዋል፡፡ (ሉቃ.፲፫፥፮-፱፣ ዘካ.፩÷፲፪) ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያለ ማቋረጥ ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔርን ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነው፡፡
በተለይም በጳጉሜን ሦስተኛዋ ቀን ቅዱስ ሩፋኤል ዕለት ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚታሰብባት ወቅት ናት፤ የተለያየ ትንታኔም ይነገርባታል፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንም ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት አድርገው መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን በሰባት መንገዶች ይገልጡታል፡፡
፩. ፈዋሴ ዱያን (ሕሙማንን የሚፈውስ)
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን (መድኃኒትነት) ለእርሱ የባሕሪው ነው፤ የማዳንን ጸጋ ለቅዱሳን ሰጥቷል፤ ከቅዱሳን መላእክትም ቅዱስ ሩፋኤል የሰው ልጆች ከተያዙበት የኃጢአት ቍስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የሚረዳ መልአክ ነው፡፡ ሄኖክ “በበሽታ ሁሉ ላይ በሰው ልጆችም ቍስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው” በማለት ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል፡፡ (ሄኖክ ፲፥፲፫) ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ሆነ ቍስል ይፈውስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ሄኖክ “በሰው ቍስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” እንዳለ፡፡ (ሄኖክ ፮፥፫)፡፡ ለቈሰሉ ፈውስን የሚያሰጣቸው መልአክ ዛሬም ሁላችንን በጸሎቱ ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ይፈውሰን፤ አሜን፡፡
፪. ፈታሔ ማኅፀን፡ ማኅፀንን የሚፈታ
ብዙ እናቶች ከመካንነት የተነሳ ኀዘን ጸንቶባቸው የቆዩ መሆኑን በብሉያና በአዲስ ኪዳን ተገልጿል፤ ከእነዚህም ውስጥ ቅድሰት ሣራ፣ እናት ርብቃ፣ ራሔል፣ ቅደስት ሐና፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ፣ የድንግል ማርያም እናት ቅድስት ሐና ይገኙበታል፡፡ እግዚአብሔር የመካኒቱን ማኅፀን ፈትቶ የተባረከ ልጅን የመስጠትን ጸጋ ለመላእኩ ቅዱስ ሩፋኤልም ሰጥቶታል፡፡ የወላድን ማኅፀን እንዲፈታ ስለተሾመ ከጌታ አዋላጅ ብትኖር ባትኖርም ሐኪም ሩፋኤል አይታጣም በምጥ ጊዜ ሲጨነቁ ሴቶች ሁሉ የመልአኩን መልክ አንግተው ማርያም ማርያም ብለው ማየ ጸሎቱን ጠጥተው ቶሎ ፈጥነው ይወልዳሉ፡፡ ቅድስት ሣራን እና እንትኩይን (የሳሙኤል እናት) ወልዶ ለመሳም ያደረጋቸው ፈታሔ ማኅፀን የሆነው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ለነፍሰ ጡር ሴቶች ረዳታቸው ሲሆን ሕፃኑ (ኗ) በማኅፀን እያለ(ች) ተሥዕሎተ መልክዕ ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል በጥበቃው አይለያቸውም፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም ፈታሔ ማኅፀን ነውና ጭንቀታቸውን ያቀልላቸዋል፤ እናቶችንም ከመፅነስ እስከ መውለድ የሚራዳቸው፣ የመካኖችንንም ማኅፀን የመፍታት ጸጋ የተሰጠው መልአክ ነው፡፡
፫. ሰዳዴ አጋንንት (አጋንንትን የሚያሳድድ)
አጋንንትን የማስወጣት ሥልጣን ለቅዱሳን ሰዎችና መላእክት ጌታችን ሰጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በሣራ (ወለተ ራጉኤል) ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ሲያሰቃያት የነበረውን ይህን ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል (ጦቢት ፫፥፰-፲፯)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል “ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን፣ አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው” ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሄኖክ ፫፥፭-፯)፡፡ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ (ሄኖክ ፪፥፲፰) አዛዝኤል ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ ጋኔን ነበር፡፡
፬. አቃቤ ኆኅት (የምሕረትን ደጅ የሚጠብቅ)
ቅዱስ ሩፋኤልም ስለ ራሱ ማንነት በሰጠው ምስክርነት “የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ” አላቸው፤ (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡ በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በታነጸች ቤተ ክርስቲያን በወደቡ አጠገብ ነበረች፤ ብዙ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለምስጋና የታደሙትን ምእመናን ሊያጠፋ ዓሣ አንበሪውን ጠላት ዲያቢሎስ ዓሣ አንበሪው ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው፡፡ ምእመናኑም ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔር በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮሁ፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በበትረ መስቀሉ (ዘንጉ) ገሥጾ “እግዚአብሔር አዝዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጥ ጸጥ ብለህ ቁም!” አለው፤ አንበሪው ጸጥ አድርጎ በማቆም ምዕመናኑንም ከሞት ታድጓቸዋል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ሩፋኤል መዝገበ ጸሎት እና አቃቤ ኆኅት ይባላል፡፡
፭. መራኄ ፍኖት (መንገድ መሪ)
ቅዱስ ዳዊት “በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ” እንዲል (ዘፀ.፳፫፥፳)። ይህ ኃይለ ቃል ሰውን መንገድ የመምራትና የመጠበቅ ሥልጣን ቅዱስ እግዚአብሔር ለመላእክት እንደተሰጣቸው የሚያስረዳ ሲሆን የጦቢትን ልጅ ጦቢያን ከነነዌ የሜዶን ክፍል ወደ ሆነችውና ራጌስ ወደምትባለው ሀገር ሲሄድ አዛርያስ (ቅዱስ ሩፋኤል) በመንገድ ይመራው ነበር፡፡ ጦቢያና አዛርያስ ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ሲደርሱ ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረዶ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው ከባሕር ወጣ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል “ጦብያን ያዘው፤ ዓሣውን እንዳትለቀው” አለው፤ ጦቢያም ከዓሣው ጋር ግብ ግብ ገጥሞ እየጐተተ ወደ የብስ አወጣው፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል “ጦብያን ዓሣውን እረደው ጉበቱንና ሐሞቱን ተጠንቅቀህ ያዘው ሌላውን ግን ጠብሰን እንበላዋለን” አለው፡፡ ከዚያም መነገዱደን እየመራቸው ለመሄድ ከፈለጉበት ቦታ አደረሳቸው፡፡ በዚህም ቅዱስ ሩፋኤል “መራኄ ፍኖት” (መንገድ መሪ) ይባላል፡፡ (መጽሐፈ ጦቢት)
፮. መልአከ ከብካብ (ጋብቻን የሚባርክ መልአክ)
የራጉኤል ልጅ ሣራ ሰባት ጊዜ ብታገባም ሰባቱም ባገቧት ሌሊት ደርቀው /ሞተው/ አድረዋል፡፡ ይህንን ክስትትም የጦቢት ልጅ ጦቢያ ያውቅ ነበር፡፡ ለአዛርያስም “ስለዚህ እኔ ለአባቴና ለእናቴ አንድ ልጅ ነኝ፤ እርስዋን አግብቼ ከዚህ በፊት እንዳገቧት ሰዎች እኔም የሞትኩ እንደሆነ አባቴንና እናቴን የሚረዳቸው የለም፤ ቢሞቱም የሚቀብራቸው አያገኙምና እፈራለሁ” አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ግን ‹‹አባትህ ከዘመዶችህ ወገን ካልሆኑ በስተቀር ሌላ ሴት እንዳታገባ ሲል የነገረህን ረሳኸውን? በል ሰባት ባሎቿ ሙተውባታል ስለምትለው እኔ መድኃኒቱን አሳይሃለሁ፤ አይዞህ አትፍራ፤ አትሞትም፤ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ያዘው ያልኩህ ለምን ይመስልሃል?
እግዚአብሔር ሲቀጣን
"አንድ ሐኪም አእምሯቸውን የሳቱ ሰዎች ቢሰድቡት፥ ስድባቸውን ከቁም ነገር አይቆጥረውም፡፡ እንዲህ አእምሯቸውን እንዲስቱ ያደረጋቸውን ምክንያት ያስወግድላቸው ዘንድ ይተጋል እንጂ፡፡ 'ሰድበውኛል' ብሎ የራሱን ጥቅም አያይም፤ የሕሙማኑን እንጂ፡፡ በጥቂቱም ቢኾን ሻል ካላቸውና ራሳቸውን መግዛት የሚችሉ ከኾነም እጅግ ደስ ይሰኝባቸዋል፡፡ ውስጡ በፍጹም ሐሴት ይሞላል፡፡ መድኃኒት መስጠቱን በፊት ከሚያደርግላቸው ይልቅ ተግቶ ይሰጣቸዋል፡፡ 'ከዚህ በፊት ሰድበውኛልና ልበቀላቸው' ብሎ በፍጹም አያስብም፡፡ ይበልጥ እንዲጠቀሙና ወደ ቀድሞ ጤናቸው ይመለሱ ዘንድ ተግቶ ይሠራል እንጂ፡፡
"እግዚአብሔርም እንደዚህ ነው፡፡ ምንም እንኳን እጅግ ጥልቅ በኾነ ኃጢአት ውስጥ ብንወድቅም፥ ኹሉንም ነገር የሚያደርገው እኛን ከመቅጣት አንጻር አይደለም፤ የሚቀጣን ስለ ሠራነው የኃጢአት ዓይነት አይደለም፡፡ ከዚህ ሕመማችን እንድንፈወስ ብሎ ነው እንጂ፤ በዚሁ መንገድ ሊመለሱ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ነው እንጂ፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#ቃለ_ወንጌል
ጷጉሜን 2/13/2016
ሉቃ፲÷፩-፲፪
ከዚህም በኋላ ጌታ ሌሎቹን ሰብዓ ሾመ፥ ሁለት ሁለትም አድርጎ እርሱ ሊሄድበት ወዳለው ከተማና ስፍራ ሁሉ በፊቱ ላካቸው። አላቸውም መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዴህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት።
ሂዱ እነሆ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ። ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ። ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ። በዚያም የሰላም ልጅ ቢኖር፥ ሰላማችሁ ያድርበታል፤ አለዚያም ይመለስላችኋል። በዚያም ቤት ከእነርሱ ዘንድ ካለው እየበላችሁና እየጠጣችሁ ተቀመጡ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋልና።
ከቤት ወደ ቤት አትተላለፉ። ወደምትገቡባትም ከተማ ሁሉ ቢቀበሉአችሁ፥ ያቀረቡላችሁን ብሉ፤ በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች በሉአቸው።
ነገር ግን ወደምትገቡባት ከተማ ሁሉ ባይቀበሉአችሁ፥ ወደ አደባባይዋ ወጥታችሁ ከከተማችሁ የተጣበቀብንን ትቢያ እንኳን እናራግፍላችኋለን፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ በሉ።
"ለሰዎች የምትሰጠው ምንም ነገር ባይኖርህ ሞቅ ያለ ፈገግታ እና መልካም ቃልን ስጣቸው፣ ፍቅርን ስጣቸው፣ መልካምነትን ስጣቸው፣ የማበረታቻ ቃልን ስጣቸው፣ልብህን ስጣቸው..
ሰዎችን በማሳዘን ፈንታ ሁሌም ይህንን ብናደርግ #ኢየሱስ በእኛ እንዳለ ያኔ ይታወቃል።
አቡነ ሽኖዳ
ጳጒሜን
ጳጉሜን ማለት "ጭማሪ" ማለት ሲሆን በዓመቱ መጨረሻ የምትገኝ አምስት (በዘመነ ሉቃስ ደግሞ ስድስት) ቀናት ያሏት ወር ናት። ኢትዮጵያ "የአስራ ሦስት ወራት ጸጋ" ተብላ የምትታወቀውም በዚህ ምክንያት ነው።
በቤተክርስቲያናችን ካሉ ሁለት የፈቃድ አጽዋማት አንዱ በጳጉሜን የሚጾመው ጾመ ዮዲት ነው። ታሪኩ እንደሚነግረን፣ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር አገልጋዩን ሆሎፎርኒስን ብዙ ሀገራትን አስገብሮ እንዲመጣ ላከው። እርሱም ከአይሁድ ምድር ደረሰ፤ ህዝቡም በመከራ ላይ ወደቀ። ባሏ የሞተባት ንጽሕት ሴት ዮዲት ግን በጾምና በጸሎት ፈጣሪዋን ለመነች፤ በሦስተኛው ቀንም መልስ አገኘች። በዚህ ኃይል ታግዛ ጠላትን ድል በማድረግ ህዝቧን አዳነች።
ይህቺ ታሪክ ምዕመናን ዛሬም ድረስ በጾምና በጸሎት ውስጣዊ ጠላታችንን (ሥጋዊ ፈቃድን) ማሸነፍ እንደሚቻል የምታስተምር ምሳሌ ናት።
በተጨማሪም ዕለተ ምጽአት የሚታሰብባት ነች። ጳጉሜን ከጨለማው ክረምት ወደ ብርሃኑ ዘመን መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ፣ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፣ ከምድራዊው ወደ ሰማያዊው ህይወት የምንሸጋገርበት ጊዜ መሆኑን የምናስብበት ወቅት ናት።
#ቃለ_ወንጌል
#ዘሰንበት
ሉቃ 16:11÷31
••••••••••
እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል? በሌላ ሰው ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ የእናንተን ማን ይሰጣችኋል?ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።
እንዲህም አላቸው። ራሳችሁን በሰው ፊት የምታጸድቁ እናንተ ናችሁ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ልባችሁን ያውቃል፤ በሰው ዘንድ የከበረ በእግዚአብሔር ፊት ርኵሰት ነውና። ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ነበሩ፤ ከዚያ ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት ይሰበካል፤ ሁሉም ወደ እርስዋ በኃይል ይገቡባታል። ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ሊያልፍ ይቀላል። ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፥ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል። ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር።
አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት፤ ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ። በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ።
አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ። ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛና በእናንተ መካከል ታላቅ ገደል ተደርጎአል አለ። እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤ እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ።
አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው። እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ። ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው።
ምስባክመዝሙር ፵፱ : ፪ - ፫ እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጉም እግዚአብሔር ግልጥ ኾኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል
#ጾመ_ዮዲት
ከፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነውም ‹ጾመ ዮዲት (የዮዲት ጾም)› በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ነው፡፡ ዮዲት በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ትኖር የነበረች ስትሆን በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ሴት ነበረች፡፡ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስ ትእዛዝ ሰጠ፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ ፲፪ ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ ፲፪ ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሄድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ፤ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡
@Eotc_spritual_books
በዚያን ጊዜ ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡ የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በአዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡ በዚያም ነዋሪዎችን በማስፈራራት የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበሉትን ሁሉ እያሳደደ ስላስጨነቃቸው ማቅ ለብሰው፣ አመድ ነስንሰውና ድንጋይ ተንተርሰው ወደ ፈጣሪያቸው በመጮህ መለመን ጀመሩ። በጭካኔ የተሞላው የጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስም ይበልጥ እጅግ እንዲሠቃዩ ውኃ የሚቀዱበትን ስፍራ ተቆጣጠረው፤ በግዴታ ማርኮም እጅ እንዲሰጡ እንዳደረጋቸው በመጽሐፈ ዮዲት ላይ ተጽፏል፡፡ በአካባቢው ይኖር የነበረ ዖዝያን የተባለ አንድ ሰው የአባቶቻቸው አምላክ ጸሎታቸውን እንዲሰማቸው ለአምስት ቀናት በትዕግሥት ይጾሙና ይጸልዩ ዘንድ ሕዝቡን መከራቸው፤ እነርሱም በትዕግሥት ሊጠብቁ ተስማሙ፡፡ (ዮዲ. ፪፥፪-፳፰፣፬፥፲፫)
ሕዝበ እስራኤል የናቡከደነጾርን ጦር ተዋግተው ለመርታት ካልሆነ ግን እጅ ለመስጠት ተመካከሩ። ነገር ግን ዮዲት እግዚአብሔርን የምትፈራ ብቸኛዋ ሴት እርሷ ነበረችና ምክክራቸውን ስትሰማ ለምን «እግዚአብሔር ያድነናል አትሉም» ብላ ገሠጸቻቸው፡፡ ማቅ በመልበስ፣ አመድ በመነስነስና ድንጋይ በመንተራስም ሱባኤ ገባች። በሦስተኛው ቀንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቧን የምታድንበትን ጥበብ ገለጸላት፤ ዮዲትም እግዚአብሔር የሰጣትን ውበት ተጠቅማ ሕዝቧን ከጥፋት የምትታደግበትን ጥበብ ተረዳች። (ዮዲ. ፱፥፲፫)
በአልባሳትም ተሸልማ፣ ሽቱ ተቀብታና ተውባ የጠላት ሠራዊት ወዳሉበት የጦር ሰፈር በድፍረት ተጓዘች፡፡ ሠራዊቱም ውበቷን አይተው እጅግ በመደነቅ «ይህችስ ለአለቃችን ትገባለች» ተባብለው ከጦር መሪያቸው ዘንድ ወሰዷት። ዮዲትም ቀድማ ከጠላቷ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅታ ስለነበር የሠራዊቱ አለቃ ወደ ነበረበት ሥፍራ ከገባች በኋላ «ክቡር ጌታዬ ሆይ ርስት ተወስዶብኛል፤ እንድትመልስልኝ አስቀድሜ ደጅ ልጠና መጥቻለውና ርዳኝ፤ ትብብርህ አይለየኝ» ብላ ጠየቀችው፡፡ የሠራዊቶቹ አዛዥም በዝሙት መንፈስ ታውሮ ስለነበር የጠየቀችውን እንደሚፈጽምላት ነገራት። ዮዲትም ባማረ ድንካን አስቀመጣት፤ በእግዚአብሔር ረዳትነትም ጥበቧንም ተጠቅማ ማምለጫዋን አዘጋጀች፡፡ (ዮዲ. ፲፥፳፫፣፲፩፥፳፫)
@Eotc_spritual_books
ዮዲትም ለቀናት በድንኳኑ ከተቀመጠች በኃላ የሠራዊቱ አበጋዝ የምሳ ግብዣ አዘጋጅቶ ከጎኑ አስቀመጣት፤ ከበሉና ከጠጡ በኋላም ሁሉን ሰው አስወጥቶ እልፍኙን በመዝጋት ከእርሷ ጋር ብቻውን ቀረ፤ ነገር ግን እንቅልፍ ጣለው፡፡ በዚያን ጊዜም ዮዲት ወደ አምላኳ በመጸለይ ፈጣሪዋ እንዲረዳት ለመነች። ከዚህ በኋላ የሠራዊቱን አለቃ ከራስጌው ሰይፉን በማንሣት አንገቱን ቀላችው፤ በድኑንም ከመሬት ጣለችው። የሆሎፎርኒስን ሞት ሠራዊቱ በሰሙ ጊዜም በያሉበት ተበተኑ። እስራኤላውያንም ከሞት ተርፈው በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረጉ፤ በደስታም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። (ዮዲ. ፲፪፥፪፣፲፫፥፳)
ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት በመትጋት እንዲሁም በእግዚአብሔር አምላክም ኃይልና ብርታት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም ሰዎች ጥንተ ጠላቶታችንን ለማሸነፍ በወርኃ ጳጉሜን ፈጣሪያችንን በጾም በጾሎት ተግተን ልንማጸነው በፈቃድ እንጾማለን፡፡
ጠንካራዋ ሴት ዮዲት ጠላቶቿን ድል ያደረገችው ሱባኤ በመግባት በጸሎትና በጾም በመትጋት በመሆኑ ይህንን ታሳቢ በማድረግ እንደ እርሷ ሱባኤ ገብተን፣ ማቅ ለብሰን፣ አመድ ነስንሰንና ድንጋይ ተንተርሰን አብዝተን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባል፡፡ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነትን አሳጥቶ፣ እርስ በርስ አጣልቶ እንዲሁም ከክብራችን አዋርዶ ወደ ዘለዓለማዊ እሳት ሊጥለን ዘወትር ይቃጣልና ሳንታክት መጸለይና መጾም ይገባናል፡፡
ለሁሉም እንዲደርስ ሼር አድርጉ 👇👇👇
@Eotc_spritual_books
@Eotc_spritual_books
@Eotc_spritual_books
#ቃለ_ወንጌል
#ዘሰንበት
ሉቃ 16:11÷31
••••••••••
እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል? በሌላ ሰው ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ የእናንተን ማን ይሰጣችኋል?ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።
እንዲህም አላቸው። ራሳችሁን በሰው ፊት የምታጸድቁ እናንተ ናችሁ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ልባችሁን ያውቃል፤ በሰው ዘንድ የከበረ በእግዚአብሔር ፊት ርኵሰት ነውና። ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ነበሩ፤ ከዚያ ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት ይሰበካል፤ ሁሉም ወደ እርስዋ በኃይል ይገቡባታል። ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ሊያልፍ ይቀላል። ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፥ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል። ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር።
አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት፤ ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ። በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ።
አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ። ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛና በእናንተ መካከል ታላቅ ገደል ተደርጎአል አለ። እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤ እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ።
አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው። እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ። ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው።
ምስባክመዝሙር ፵፱ : ፪ - ፫ እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጉም እግዚአብሔር ግልጥ ኾኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል
"ሰውን ከእግዚአብሔር አምሳልነቱ የተነሳ ሁልጊዜ ውደደው፤ በእርሱ ውስጥ ያለውን ክፋት ግን አትውደድ"
ቅዱስ ዮሐንስ ዘከሮንስታድት
#ቃለ_ወንጌል
30/12/2018
ሉቃስ 24:13-23
እነሆም፥ ከእነርሱ ሁለቱ በዚያ ቀን ከኢየሩሳሌም ስድሳ ምዕራፍ ያህል ወደሚርቅ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር ይሄዱ ነበር፤ ስለዚህም ስለ ሆነው ነገር ሁሉ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር። ሲነጋገሩና ሲመራመሩም፥ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ነበር፤ ነገር ግን እንዳያውቁት ዓይናቸው ተይዞ ነበር።
እርሱም እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ፥ እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሩአቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው? አላቸው። ቀለዮጳ የሚባልም አንዱ መልሶ አንተ በኢየሩሳሌም እንግዳ ሆነህ ለብቻህ ትኖራለህን? በእነዚህ ቀኖች በዚያ የሆነውን ነገር አታውቅምን? አለው። እርሱም ይህ ምንድር ነው? አላቸው።
እነርሱም እንዲህ አሉት በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ፤ እርሱንም የካህናት አለቆችና መኳንንቶቻችን ለሞት ፍርድ እንዴት አሳልፈው እንደ ሰጡትና እንደ ሰቀሉት ነው። እኛ ግን እስራኤልን እንዲቤዥ ያለው እርሱ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገን ነበር፤ ደግሞም ከዚህ ሁሉ ጋር ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው። ደግሞም ከእኛ ውስጥ ማልደው ከመቃብሩ ዘንድ የነበሩት አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን::
ምስባክመዝሙር 92:4-5 መንክር ተላህያ ለባሕር መንክርሰ እግዚአብሔር በዓርያሙ ስምዐ ዚአከ እሙን ፈድፋደ ትርጉም ከባሕርም ታላቅ ሞገድ ይልቅ፡ እግዚአብሔር በከፍታው ድንቅ ነው። ምስክርህ እጅግ የታመነ ነው
ልጄ ሆይ ማናቸውንም ነገር በምትፈፅምበት ጊዜ ሥራህን በፀሎት ጀምር። የምትሰራቸውን ሥራዎች ሁሉ በትምህርተ መስቀል ባርካቸው።
በምትበላም፣ በምትጠጣም ጊዜ፣ በምትተኛም፣ በምትነቃም ጊዜ፣ በቤት ውስጥም ሳለህ ይሁን በጎዳና፣ ማማተብን አትዘንጋ። የጌታህን ስቅለት አስታውሶ ከክፋት የሚጠብቅህ ይህን የመሰለ ጠባቂ ከቶ አታገኝም።
እርሱ ለምታደርጋቸው ድርጊቶችህ ሁሉ እንደ ግንብ ነው (ማስተዋልን ይሰጥኻል)። ማማተብን በስርዓት ይፈፅሙት ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት ሁሌም በፊታቸው ይስሉ ዘንድ ለልጆችህ በጥንቃቄ አስተምራቸው።
#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ@Eotc_spritual_books
#ቃለ_ወንጌል
29/12/2018
ማቴዎስ 5:1-17
ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ፤ አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና። ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም። እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ::
#መልእክታት
ገላትያ 3:15-21
1 ዮሐንስ 4:9-18
ሐዋ.ሥራ 20:28-31
ምስባክመዝሙር 100:1-2 እዜምር ወእሌቡ ፍኖተ ንጹሐ ማዕዜ ትመጽእ ኀቤየ ወአሐውር በየዋሃተ ልብየ ማዕከለ ቤትየ ትርጉም እዘምራለሁ፥ ንጹሕ መንገዱንም አስተውላለሁ፤ ወደ እኔ መቼ ትመጣለህ? በቤቴ መካከል በልቤ ቅንነት እሄዳለሁ።
"ሰይጣን አንተን ኃጢአት በማሠራት ተስፋ ሊያስቆርጥህ ይፈልጋል። አንተ ግን በወደቅህበት ቁጥር 'አምላኬ ሆይ ማረኝ' እያልክ በመነሣት ሰይጣንን አሳፍረው። መውደቅህ የስንፍናህ ምልክት ቢሆንም፣ ደጋግመህ መነሣትህ ግን የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን ያረጋግጣል።"
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
#ቃለ_ወንጌል
28/12/2018
ማቴዎስ 22:23-34
በዚያችም ቀን ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጡ። እንዲህም ብለው ጠየቁት፥ “መምህር ሆይ፥ ሙሴ ልጅ ሳይወልድ የሞተ ሰው ቢኖር ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካለት ብሎአል። እንግዲህ ሰባት ወንድማማቾች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ታላቁም ሚስት አገባና ልጅ ሳይወልድ ሞተ፤ ለወንድሙም ሚስቱን ተወ። እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው፥ ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
ከሁሉም በኋላ ያቺ ሴት ሞተች። እንግዲህ ሙታን በሚነሡበት ጊዜ ከሰባቱ ለማንኛው ሚስት ትሆናለች? ሁሉም አግብተዋት ነበርና።” ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ባለማወቅ ትስታላችሁ። "ሙታንስ በሚነሡበት ጊዜ በሰማያት እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆነው ይኖራሉ እንጂ አያገቡም፤ አይጋቡምም። ስለ ሙታን መነሣት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ እንዲህ ተብሎ የተነገረውን አላነበባችሁምን? እኔ እግዚአብሔር የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንግዲህ የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።” ሕዝቡም ሰምተው ትምህርቱን አደነቁ::
#መልእክታት
ሮሜ 4:1-23
ያዕቆብ 2:20-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 7:1-9
ምስባክ
መዝሙር 120:1-2
አንሣእኩ አዕይንትየ መንገለ አድባር
እምአይቴ ይምጻእ ረድኤትየ
ረድኤትየሰ እምኀበ እግዚአብሔር
ትርጉም
ዐይኖቼ ወደ ተራራዎች አነሣኹ
ረዳቴ ከወዴት ይምጣ
ረዳቴ ከእግዚአብሔርዘንድ ነው
Repost from Henok Haile
ነቢዩ ቅዱስ ኤልያስ በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ከተነጠቀ በኁዋላ የተፈጸመው አንድ ነገር ሁሌም ያስደንቀኛል::
ኤልያስ ካረገ በኁዋላ ሃምሳ ሰዎች ወደ ነቢዩ ኤልያስ ደቀ መዝሙር ወደ ኤልሳዕ መጥተው ነበር::
እነዚህ ሰዎች ጭንቀታቸው ኤልያስ ወደ ላይ ያረገ ቢመስልም ምናልባት ወድቆ ቢሆንስ የሚል ነበር::
የእግዚአብሔር መንፈስ ወደ አንድ ተራራ ወይም ወደ አንድ ሸለቆ ጥሎት ቢሆንስ ብለው አስበው ነበር::
ወደ ኤልሳዕ መጥተው እባክህ እንፈልገው ብለው ለመኑት::
ኤልሳዕ በሰዎቹ ሃሳብ ባይስማማም እርሱ በኤልያስ ስለተተካ ኤልያስን እንድናገኝ አልፈለገም እንዳይሉት አፍሮ እሺ አላቸው:: አምሳ ሰዎች ለሦስት ቀናት ኤልያስን ቢፈልጉትም አላገኙትም:: ኤልሳዕም "አትሒዱ አላልኳችሁም?" አላቸው:: 2ነገ 2:15-18
የሰው ጠባይ እንዲህ ነው:: ወደ ላይ ሲወጣ ያዩትን ጉድጓድ ውስጥ መፈለግ : ከፍ ሲል ያዩትን ዝቅ ሲል ለማየት መመኘት : እግዚአብሔር ያነሣውን ሰው እግዚአብሔር ሲጥለው ለማግኘት መፈለግ አሳዛኙ የሰው ጠባይ ነው:: ሦስት ቀን ሃምሳ ሆነው ኤልያስን የፈለጉትን ኤልያስ ቢያገኙት ኖሮ "አይ ኤልያስ እኛ እኮ ወደ ሰማይ ተነጠቅህ ብለን አምነን ነበር ለካ አንተ እዚህ ወድቀሃል" ብለው ሊመጻደቁ ነበር:: ወደ ላይ ያረጉ ወደታች ሲወድቁ ለማየት ሦስት ቀን ሙሉ መንከራተት ምን ይባላል? የተከበሩ ሲዋረዱ : የተወደዱ ሲጠሉ ማየት የሚፈልጉ ሰዎች በዚህ ዘመን ከሃምሳ ሳይበዙ አይቀሩም::
ነቢዩ ኤልሳዕ ግን :- አትሒዱ አላልኳችሁም? ይላል::
ጉድጓድ ለጉድጓድ አትዙሩ:: ኤልያስ ዐርጎአል!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
