እስልምና እና ክርስትና
Open in Telegram
t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!
Show more315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ስለ መግደል የሚያሰስተምረው እምነት
( እስልምና ወይስ ክርስትና? )
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፧፦፦፦
ከቀደሙት የኢትዮጵያ ነገስታት የግድያ ታሪክ የቀጠለ፦ የዚህን ሙሉ ተከታታይ ክፍል ለማግኘት t.me//AkeelComparative ይቀላቀሉ
ክፍል - ⓾
⓾ - #በዕደ_ማርያም ፦ በዕደ ማርያም የዘርዓ ያዕቆብ ልጅ ሲሆን በ1468 አባቱን ተክቶ ስልጣን ያዘ።
- #በዕደ_ማርያም እርሱም በተራው አገዎችን በሀይል ክርስቲያን የማድረግና የሙስሊሞችን ሀይል ማዳከም ተያያዘው።
- በ1471 ከአዳል ሱልጣኔት ውጪ ባሉት ሙስሊሞች ላይ ዘመተ። በሐይቅና አምባላጌ አካባቢ ይገኙ የነበሩትን የዶባስ ሙስሊሞች ወረረ። አብዛኛውን ህዝብ በግድ ክርስትና እንዲነሱ አደረገ፤ በነርሱ አገርም የማሪያም ቤተክርስቲያን ገነባ ፤ ጠላና ጠጅን እንዲለምዱ አደረገ። ( #ምንጭ ፦ Ibid, P.11)
- በዕደ ማርያም በ1472 አዳልን በመውረር ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ፈፀመ፤ በርካቶችን ማረከ። ( #ምንጭ ፦ Islam in Ethiopia, P.81) በዚህ ጊዜ የአፋር ሙስሊሞች አመፁ።
- በ1473/4 ሁለት የክርስቲያን ጦር አመፁን ለመስበር ተላከ ሆኖም ሳይሳካለት ቀረ።
- በ1474 ለሶስተኛ ጊዜ የክርስቲያኑ ጦር ወደ አዳል ዘመተ። በዚህ ዘመቻ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የክርስቲያኑ ጦር እና ከፍተኛ የጦር አመራሮች ተደመሠሱ። ( #ምንጭ ፦ Islamic history and Culture in Southern Ethiopia, P.72)
- በዕደ ማርያም በ1478 ሞተ።
⓫ - #አፄ_እስክንድር ዙፋን ላይ መጣ። እስክንድር የበዕደ ማርያም ልጅ ሲሆን በ1478 ላይ ከአባቱ ሞት በኋላ ነገሰ።
- እስክንድር እንደነ አባቶቹ እርሱም ጸረ ኢስላም እንቅስቃሴ ማድረግ ጀመረ። በዚህም ነፃነቷን ላለማስደፈር ትታገል የነበረችውን የአዳል ሱልጣኔት ላይ ዘመተ። ከዘይላው #ላድዕ_ኡስማን ጋር ጦር ገጠሙ። በዚህም ላድዕ ኡስማን ተገድሎ ጦርነቱ አበቃ። ( #ምንጭ ፦ Islamic History and Culture in Southern Ethiopia, P.30)
- በ1478 ሱልጣን ሸምሰዲን ቢን ሙሐመድ ላይ ጥቃት በመክፈት የአዳልን ዋና ከተማ ደካርን አጠቃ። ( #ምንጭ ፦ Encyclopedia Aethiopica, Vol.2, P.72)
- በ1494 አፄ እስክንድር የማያ ህዝቦች በመርዛማው ቀስታቸው በምስራቅ እንደርታ ወግተው ገደሉት። ( #ምንጭ ፦ Islamic history and culture in southern Ethiopia, P.45)
⓬ - #አፄ_ናኦድ
አፄ ናኦድ የአፄ እስክንድር ልጅ ሲሆን አባት ሲሞት ቀጣይ የንግስናው የዙፋኑ ወንበር ተቆናጠጠ።
- አፄ ናኦድ ከአባቱ ከአፄ እስክንድር አራት ሚስቶች መካከልም ከሮማን ወርቅ የሚወለድ ልጅ ሲሆን ሮማን ወርቅ ክርስትና እንድትነሳ የተገደደች ሙስሊም ነበረች። ናኦድ ሙስሊሙን በሀይል ማስገበሩን ተያያዘው። አንገብርም ያሉትንም በተለይም ኢማም ማህፉዝን ጋር መዋጋቱንም ቀጠለ።
- በመጨረሻም በኢፋት ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ለመክፈት ዘመተ። በ1508 በአርብ (ስቅለት) <ጄንጄኖ> ልዩ ስሙ መካነ ስላሴ በተባለ ስፍራ በሙስሊሞች እጅ ተገደለ። ( #ምንጭ ፦ Histiricak geohraphy of Ethiopia, P.105)
⓭ - #አፄ_ልብነ_ድንግል
ክፍል - 11
#የኢማም_አህመድ (አህመድ ግራኝ) እና #የአፄ_ልብነ_ድንግል ወደር የለሹ ትንቅንቅ በቀጣይ ክፍል ይቀጥላል...
ስለመግደል የሚያስተምረው እምነት
(እስልምና ወይስ ክርስትና)
ክፍል ⓽
ከቀደምት የኢትዮጵያ ነገስታት #የግድያ #ታሪክ የቀጠለ
⓽ - #ዐፄ_ዘርዓ_ያዕቆብ ቀጥሎም በ1434 ነገሰ። የሐዲያዋን ሙስሊም እሌኒን ክርስትና በማስነሳት አገባ።( #ምንጭ ፦ Church and state in Ethiopia, P.229) ወዲያውኑ ፀረ ኢስላም ዘመቻዎችን ጀመረ። ሙስሊሞችንም ማረከ። ነገር ግን በሰባት አቅጣጫዎች በሙስሊሞች ተሸነፈ። ( #ምንጭ ፦ ኢንባእ አል ጉምር... ጥራዝ 2, ገጽ 112)
- ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ከሁለት ዓመታት በኋላ ወደ አክሱም ጽዮን በመሄድ በዚያው ቤተክርስቲያን ተቀባ። ቀጥሎም በ1437 በሙስሊሞች ላይ መጠነ ሰፊ ዘመቻውን ጀመረ።
- በ1441 ኢስላምን እና ነብዩን(ሰዐወ) እጅግ የሚያንቋሽሸው << #ተዓምረ_ማርያም >> የተሰኘውን መጽሐፍ በግዕዝ እንዲዘጋጅ አደረገ። ዘወትር እሁድ በአብያተ ክርስቲያናቱ እንዲነበብ ደነገገ። ( #ምንጭ፦ Haggai Ehrlich, The cross and River, Ethiopia, Egypt and the Nile. P.47)
ይህም ጸረ ኢስላም አስተሳሰብ በህዝቡና በቀጣዩ ትውልድ ልብ እንዲሰርፅ በማለም ነበር።
- ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ በ1443 የሙስሊሞችን መሪ ሱልጣን ሺሐቡዲንን ሊያጠቃ ወደ ባሌ ሙስሊሞች የዘመተ ቢሆንም ነገር ግን በዚህ ዘመቻ ሽንፈት አጋጠመው። የዓፄ ዘርዓያዕቆብን የፀረ ኢስላም ዘመቻ እየታገለ ለ13 ዓመታት የቆየው ሱልጣን ሺሐቡዲን ከ13 ዓመታት ትግል በኋላ አከተመለት። በዚህም ዓፄው የሱልጣኑን አካል አስቆራረጠ። ወደ ተለያየ ስፍራም ተላከ።
( #ምንጭ ፦ Enrico Cerulli, P.137-138)
ተክለ ፃድቅ መኩሪያ ሟቹ ሱልጣን ሺሐቡዲንን <<ከሐዲ>> በሚል ጠቅሠው እንዲህ ይተርካሉ፦
" የከሐዲው (ሺሐቡዲን አህመድ ) ጭንቅላቱም እጁም ሌላውም አካል ተቆረጠና በየአገሩ ተላከ። ጭንቅላቱ ወደ <አምባ> (ትልቅ የገበያ ማዕከል)፤ የቀረውም ወደ <አክሱም ፣ ወደ መንሐድሌ፣ ወደ ዋሽል፣ ወደ ጅጅሮ፣ ወደ ላዎ፣ ወደ ዊዝ ተላከ።... በተረፈው ሰውነቱ ላይ (ክርስቲያኑ) የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ድንጋይ እየወረወረ ወገረው።... ይህን ሁሉ ካደረጉ በኋላ ንጉሱ በደስታ ወደ ተወለዱበት አገር ወደ ጥልቅ (ፊጣጋር) ተመለሱ። "
( #ምንጭ ፦ የኢትዮጵያ ታሪክ ከአፄ ይኩኖ አምላክ እስከ አፄ ልብነ ድንግል ፤ ገጽ 232)
- ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ጅምላ ጭፍጨፋ ፈጽሞ የሙስሊሞችን ግዛት ወረረ። በወረረውም አካባቢ በርካታ አብያተክርስቲያናት አሳነፀ። ( #ምንጭ ፦ Islam in Ethiopia, p.75)
- አክራሪው አፄ ዘርዓያዕቆብ በ1449 ኢስላምን ከምድረ ገጽ ሊያጠፋ ማውጠንጠን ጀመረ። ይህንንም ከዳር ለማድረስ #200 #መርከቦችን በመስራት #መካንና #ኢስላማዊ አገራትን በማጥቃት #ካዕባን ለማፍረስ አቀደ። ( #ምንጭ ፦ The cross and the River, P.46)
- በ1450 ዓፄው ኢስላምን በማጥፋት ላይ አጋዥ ለማፈላለግ በጣሊያናዊው ፒትሮ ሮምቦሎ የተመራ ልዑክ ወደ አውሮፓ ላከ። በጉዳዩም ዙሪያ የጋራ የሆነ ውይይት አደረጉ። ( #ምንጭ ፦ Ibid, p.230)
የሙስሊሞችን ደም ካልጠጡ ሰላም የሚነሳቸው የሆኑት እነዚህ ወገኖች በተለያየ ጊዜ መጠነ ሰፊ ጥቃት በሙስሊሞች ላይ ሲፈፅሙ የኖሩ ሲሆን ፤ ቁጥር ስፍራቸው የማይታወቁ ሙስሊሞችን በተለያዩም የአለማችን ክፍሎች በነዚህ ፅንፈኞች በግፍ ተገድለዋል፤ ብዙ መስጊዶችን ፈራርሰዋል፣ በርካታ የሙስሊም ንብረቶችንም ተዘርፈዋል፣ እንዲሁም ወደፊትም መግደል ይችሉ ይሆናል ነገር ግን #እስልምናን #ማጥፋት #አይቻላቸውም ። ምክንያቱም ጠባቂ አለውና!!። ታድያ ኢስላምን ከምድረ ገጽ ሊያጠፉ አስበው በአውሮፓ ለውይይት የተቀመጡት እነዚህ ፀረ-ኢስላሞች ለምን ሴራቸው እንደከሸፈ ግልጽ ነው። ለዚህም ደግሞ፦
5፡64
"... በመካከላቸውም ጠብንና ጥላቻን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ጣልን፡፡ #ለጦር #እሳትን #ባያያዙ ( #ባጫሩ ) #ቁጥር #አላህ #ያጠፋታል፡፡ በምድርም ውስጥ ለማበላሸት ይሮጣሉ፡፡ አላህም አበላሺዎችን አይወድም፡፡"
- ወደ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ልመለስና ይህ ፀረ-ሰላም ንጉስ ክርስትናን በማህበረሰቡ ለመጫን በርካታ ተግባራትን ፈፅሟል። < #ተዓምረ_ማርያም >ን ጨምሮ ከአረብኛ (በግብፅ ክርስቲያኖች የተፃፈ) የተለያዩ መጻህፍት ወደ ግዕዝ አስተርጉሟል። በራሱም ደግሞ << #መፅሃፈ_ብርሃን ፣ #መፅሐፈ_ምዕላድ ፣ #ጦማረ_ትስብእት ፣ #ክህዳተ_ሰይጣን ፣ #መፅሐፈ_ባህርይ ፣ #ተአቅቦ_ምስጢር እና #እግዚአብሔር_ነግሠ >> የተሰኙ መፅሃፍትን ደርሷል።
- አፄ ዘርዓ ያዕቆብ፦
➡ ሰዎች መስቀልን በግንባራቸውና በአካላቸው እንዲነቀሱ አስገድዷል!
➡ ከሩቅ ሆነው <<ቤተክርስቲያን የመሳለምን>> ስርዓት አስጀምሯል!
➡ <<የነፍስ አባት >>የሚባለውን ስርዓት አስጀምሯል!
➡ <<ተዓምረ ማሪያም>> የተሰኘው መፅሐፍ ከቅዳሴ በኋላ በቤተክርስቲያን እንዲነበብ አድርጓል!
... ክፍል ⓾ ይቀጥላል
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
t.me//AkeelComparative
ስለ መግደል የሚያስተምረው እምነት
( እስልምና ወይስ ክርስትና)
ክፍል - ⓼
- #አጼ #አምደ #ጽዮን ለሰራዊቱ እንዲህ ሲል ገልጿል፦ << እኔ የምላችሁን ስሙ። እንግዲህ በመጣንበት አንመለስም። የመጣንበት ጉዳይ አረመኔውን (እስላሙን) አጥፍተን በቦታው ክርስቲያን ህዝብ እስከምንተካ ድረስ አገሩን ሁሉ እያቀናንና ሹም ሽር አድርገን እንመለስ።>> ( #ምንጭ ፦ የጥንቷ ኢትዮጵያ ትንሳኤ ታሪክ፤ ገጽ 232)
- በ1329 አምደ ጽዮን የሙስሊሞች ሀገር ሐድያን ወርሮ መሪዋን አማኖንን ረታው። ሙስሊሞች ላይ እጅግ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ፈጸመ፣ መሪዋንና በርካታ ሰዎችን ወሰደ፣ ቁጥራቸው እጅግ በርካታ የሆኑ መስጊዶችን አፈራረሰ፣ አቃጠለ። በ1932 የደግዌን ከተማ አጠቃ፣ አቅራቢያው የነበሩትን የወርጂህ ሙስሊሞች ገደለ። ( #ምንጭ ፦ Ethiopian Borderlands, P.45)
ታድያ ይህ ሰው በባህሪው እኩይ ግለሰብ የነበረ ሲሆን የአባቱን ሚስት(የእንጀራ እናቱን) አግብቷል። ሁለት የገዛ እህቶቹንም አስገድዶ ደፍሯል።
( #ምንጭ ፦ ኢትዮፕያ ወል ዑሩባህ ወል ኢስላም ዐብረ ታሪኽ ፤ ጥራዝ 2, ገጽ 56)
- አምደ ጽዮን በ1344 ሞተ። በምትኩም ልጁ አፄ ሰይፈ አርዕድን (ንዋየ ክርስቶስ) ነገሰ።
⓹ - #አፄ #ሰይፈ #አርዕድ ከአባቱ ያመለጡ ሙስሊሞችን በግድ ክርስትናን እንዲቀበሉ ዘመተባቸው። አንቀበልም ያሉ በሰይፍ አረዳቸው። የተወሰኑት ሸሽተው ግብፅ ገቡ።
- አፄ ሰይፈ አርዕድ በ1371 ሞተ። ልጁ ንዋየ ማርያም ነገሰ።( #ምንጭ ፦ church and state in Ethiopia, P.149)
- በ1380 አፄ ንዋየ ማርያም ሞቶ በቦታው #ዳዊት ነገሰ።
⓺ - #ዳዊት ፦ እርሱም እንደ አባቶቹ ፀረ ኢስላም ዘመቻውን ቀጠለ። በ1381 ወደ አስዋን ዘመተ። በሙስሊሞችም ላይ ከፍተኛ ጥቃት አደረሠ።
- በ1397/8 (800 ዓ.ሂ) በኋላ ዐፄ ዳዊት በሙስሊሞች ላይ ዳግም ዘመተ። በርካቶችን ገደለ፣ ንብረታቸውንም አጠፋ፣ የሙስሊሞችን ሃይማኖታዊ መፅሐፍት (ኪታቦችን) አቃጠለ፣ አብዛኛዎቹ በግድ ክርስትናን እንዲቀበሉ አስገደዳቸው። ከሙስሊም መሪዎች መካከል ሰዓዲዲን ብቻ አልገብርም አለ። በመካከላቸው ጦርነቱ ተፋፋመ። በተደጋጋሚ ሰዓዲዲን ድል ያደርግ ነበር። ( #ምንጭ ፦ Church and State in Ethiopia, P.151)
- አፄ ዳዊት ለሃያ ዓመታት በሙስሊሞች ላይ በርካታ ጭፍጨፋ ፈጽሟል፣ መስጊዶችን አፈራርሷል፤ በመስጊዶች ምትክ አብያተክርስቲያናት ታንጸዋል። (ምንጭ ፦ Ibid, P.300)
- አፄ ዳዊት ወደ ሙስሊሞች አገር አዳል ለጥቃት ዘምቶ በነበረበት ወቅት በ1409 ተገደለ።
( #ምንጭ ፦ ኢንባእ አል-ጉምር ቢአብናኢል ዑምር ፤ ጥራዝ 1,ገጽ 362)
- አፄ ዳዊት ሲሞት ልጁ ቴዎድሮስ ነገሰ። እርሱም ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ቀጥሎ #ይስሃቅ ነገሰ።
( #ምንጭ ፦ አስ ሱሉክ ሊመዕሪፈቲ ዱወል አል ሙልክ፤ ጥራዝ 3, ገጽ 340)
⓻ - #ይስሃቅ እና ሱልጣን ሰዓደዲን ትግላቸውን ቀጠሉ። #ከይስሃቅ ጋር በበርዋ ከተመራው ሰራዊት ጦርነት ተጀመረ። ጦርነቱ ሲፋፋም ሰዓደዲን ወደ ዘይላ ወደብ ሸሸ ፤ በባህር ላይ ሳለ ተከበ፤ ግንባሩንም ተመታ፥ በኋላም በጦር ተወግቶ ሸሂድ ሆነ። ከርሱ ሞት በኋላ በርካታ መስጊዶች ፈራረሱ በምትካቸው ቤተክርስቲያን ተሠራባቸው። የተረፉት ወደ የመን ሸሹ። ( #ምንጭ ፦ ኢንባእ አል ጉምር ቢአብናኢል ዑምር ፤ ጥራዝ 1, ገፅ 282)
- በ1423 በእየሩሳሌም የምትገኘው ቤተክርስቲያን በመዘጋቷ #ዐፄ #ይስሐቅ እጅግ ተቆጣ። ንዴቱ በበቀል ሊወጣ ፈልጎ ወደፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ዘመተ። #ኢማም #አል-መቅሪዚ እንዲህ ይገልፀዋል፦
<<ቤተክርስቲያኒቱ በመዘጋቷ ምክንያት በርካታ የአገሩን ሙስሊሞች ገደለ። ሴቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ባሪያ አደረገ። ብርቱ ማሠቃየትን አሰቃያቸው። በአገሩ የነበሩ መስጊዶችን አፈራረሰ። የገደላቸውን ሙስሊሞች ቁጥር ለመገመት ያስቸግራል። >> ( #ምንጭ፦ ዝኒ ከማሁ፤ ገጽ 277)
- በአፄ ይስሀቅ ዘመንም የኋላ ኋላ የሙስሊም መሪዎች በጣም ጠንክረው ስለነበረ ዐፄው በየዘመተበት ዘመቻ ላይ ሽንፈት እያጋጠመው ሲሄድ መዳከም ጀመረ። በዚህም በ1430 የአዳል ሙስሊሞችን ለማጥቃት በዘመተበት ወቅት ዐፄው ተገደለ።( #ምንጭ ፦ ኢንባእ አል ጉምር.. ጥራዝ 1, ገጽ 362)
- ዓፄ ይስሃቅ ሲሞት ልጁ #እንድሪያስ ተተካ። እርሱም በአራት ወሩ ሞተ። ከዚያም የዓፄ ዳዊት ልጅ #ሀዝተናይ ነገሰ። እርሱም በ1431 ሞተ።
⓼ - #ሰለሞን የይስሃቅ ልጅ ቀጥሎም ነገሰ። በወቅቱ ጠንካራ የነበረው የሙስሊም መሪው ሱልጣን ጀማሉዲን የሰለሞንን ግዛት ተቆጣጠረ። ዓፄ ሰለሞን በጀማሉዲን እየተባረረ ለሁለት ወራት ያህል ሸሸ። በመጨረሻም በሴፕቴበር 1431 ዓፄው ሞተ።በአንድ አመት ብቻ አራት ንጉስ ተፈራረቀ።
( #ምንጭ ፦ አል መንሀሉ ሷፊ ወል ሙስተውፊ ፊ በዕደል ዋፊ፤ ጥራዝ 1, ገጽ 164)
በዚህ ጊዜ በሙስሊሙ ግዛት ሠላምና ፍትህ ሰፈነ፤ የዲን ትምህርት ተስፋፋ፤ በወቅቱ የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ይሰጡ ነበር። ከእነዚህ ውስጥ ሐዲስ አንዱ ነበር። ጀማሉዲን ግን በ1432 ሞተ፤ ለእርሱም ሞት ምክንያትም የአጎቱ ልጅ ሲሆን ለስልጣን ሲል እንደገደለውም በታሪክ ተፅፏል። ዐፄ እንድርያስ በወረርሽኝ በሽታ አማካኝነት ሲሞት ልጁ ተተክቶ ነበር።
ክፍል 9 ይቀጥላል
⓽ - #ዐፄ_ዘርዓ_ያዕቆብ
... ይቀጥላል
ቻናሉን 👇👇👇👇 ይቀላቀሉ
t.me//AkeelComparative
ክፍል ⓻
✔✔ ቀደምት የኢትዮጵያ መንግስታት(ዓፄዎች) በሙስሊሞች ላይ ያሳደሩት የግድያና የጦርነት ጠባሳ፦
⓵ - #በዛጉዌ #ዘመነ #መንግስት ግዛት ውስጥ የነበሩት ሙስሊሞች በሀይማኖታቸው ምክንያት ችግርና መንገላታት ይደርስባቸው ነበር። በዛጉዌ የግዛት ክልል(ሰሜን) ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከላሊበላ ከተማ የማባረር ስራ ተሰርቷል።
ለምሳሌ፦ #በገብረ #መስቀል ላሊበላ ዘመነ መንግስት ከ1189-1229 ባለው ጊዜ ውስጥ ቁጥራቸው 20 ሺህ የሚሆኑ ሙስሊሞች በዘዴ ከላሊበላ ተፈናቅለዋል። በቦታቸው ላይ ክርስቲያኖች እንዲሠፍሩ ተደርጓል።
<< የአገው ህዝቦችና የዛጉዌ ስርወ መንግስት ታሪኩ>>" የተሰኘው መፅሐፍ እንዲህ አስቀምጦታል፦
" ሺምሺህ የተባለው ቦታና በአሁኑ ወቅት የአውሮፕላን ማረፊያ የተሠራበት ስያሜውን ያገኘው የ20 ሺህ የእስልምና ተከታዮች መኖሪያ ስለነበረ ነው። እነዚያ
ሃያ ሺህ ሙስሊሞች በዚያ ተቀምጠው ሲዋለዱ ቅዱስ ላሊበላ በፈለፈላቸው ህንጻ መቅደሶች ዙሪያ የክርስትና ተከታዮች እየመነመኑ እንዳይሄዱና በሆነ ዘዴ ወደ ሌላ ቦታ ተዛውረው እንዲሰፍሩ ከመከረ በኋላ እንዲለቁ ተደርጓል።"
( #ምንጭ ፦ ዶ/ር አያሌው ሲሳይ ፣ የአገው ህዝቦችና የዛጉዌ ስርወ መንንግስት ታሪክ ፣ ንግድ ማተሚያ ድርጅት ፣ አ.አ ገጽ 176)
⓶ #ይኩኖ #አምላክ
የአምባሰልና የግሸን መሪ የነበረው #ይኩኖ #አምላክ በዛጉዌ ስርወ መንግስት ላይ ጦር በማንሳት የመጨረሻውን የዛጉዌ መሪን በተሸሸገበት የቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውስጥ በመግደል በ1270 ስልጣን ያዘ። በዚህም #ሰለሞናዊ የተባለውን አዲስ ሥርወ መንግስት አቋቁሟል።
ይህ ሰው ከንግስት ሳባና ከእስራኤላዊው ንጉስ ሰለሞን ዘር የሆንን በመሆናችን "እኛ መሪ ለመሆን ነው የተፈጠርነው ፤ እግዚአብሔር ደግፎናል፣ ሌላው ዝም ብሎ ይመራ።" የሚል አስተሣሠብ ከሀይማኖት ተቆራኘ።( #ምንጭ ፦Q.about kibre negest, p.34)
በክብረ ነገስት በምዕራፍ 117፥15 ላይ እስራኤላዊ ያልሆነ የመሪነት ስልጣን መጨበጥ አይገባውም። " የሚለውን ተንተርሶ
- #ይኩኖ #አምላክ ፦ ልክ እንደ ቀደሙት ሁሉ እርሱም ፀረ ሙስሊም ሰው ነበር። ለዚህም ይኩኖ አምላክ የገዛ ልጅ ራሱ እንዲህ በማለት መስክሯል፦ " አባቴ የሙስሊሞች ጠላት ነበር። እኔ ግን በፍፁም እንደ አባቴ አይደለሁም። በሁሉም ግዛቴ የሚገኙት ሙስሊሞች ጥበቃ አደርጋለሁ። " ሲል መስክሯል። ( #ምንጭ ፦ church and state in Ethiopia, P.12)
- በ1288 ይኩኖ አምላክ ሞተ። ( #ምንጭ ፦ Enrico Cerulli, P.212)
- በ1290 ዓፄ ይግባ ፅዮን ተተካ።
⓷- #ዓፄ #ዉድም #ርዕደ በ1299 ነገሰ። እርሱም ፀረ ኢስላም እንቅስቃሴ ጀመረ። ዐብደላህ ሙሐመድ የተባሉ ዐሊም ሙስሊሞችን ወደ አንድነት ሲጣሩ ነበርና 200,000 ሙስሊሞችን በራሳቸው ስር አደራጁ። በዐፄው ዉድም ርዕድ የተመራ የክርስቲያን አማራ ዓፄዎች በሙስሊሞቹ ላይ ጦርነት ከፈተ። በዚህም የሙስሊሞቹ አንድነታቸውና ትግላቸው በታተነባቸው።
( #ምንጭ ፦ አል መቅረዚ ፣አስ ሱሉክ ሊመዕሪፈቲ ዱወል አል ሙልክ ፣ ጥራዝ 1 ገፅ 318)
የሼኩንም አካባቢ በሀይል ተቆጣጥሯል። በአካባቢውም <<ዐብደላህ ጊዮርጊስ >> የሚባል ቤተክርስቲያን ተሠርቷል። ( #ምንጭ ፦ Church and State in Ethiopia (1270-1527), p.130-131)
⓸- በ1315 #ዓፄ #አምደ #ፅዮን " የክርስቲያኑ ሀገር" በሚሰኘው ሰሜን ነገሰ። ( #ምንጭ ፦ church and state in Ethiopia, P.132)
ግዛቱንና ክርስትናን ለማስፋፋት ተነሳ። በ1316/17 በሐብት የበለፀገችውንና የሙስሊሞች ግዛት የነበረችውን #የዳሞት ግዛት በመውረር ወደ ራሱ ጨመረ። ( #ምንጭ ፦ Ethiopia and the Red sea the rise and decline of the Solomonic dynasty and Muslim-European Rivalry in the region, P.22)
በዚሁ ጊዜ ኢስላማዊቷን አገር ሐድያንም አጠቃ። ህዝቦቿንም ማረከ። በዚህ ጊዜ የግብፅ መምሉክ ሱልጣን አል ናስር ሙሐመድ ቢን ቀለዑን <<በግብጽ ክርስቲያኖች ላይ ጭፍጨፋ ፈጸመ፣ አብያተ ክርስቲያናት አፈራረሰ>> የሚል አፄ አምደ ፅዮን ወሬ ሰማ። አፄው የፈራረሱ ቤተክርስቲያናቱ ዳግም እንዲሰሩ ይህ ካልሆነ የአባይን ወንዝ በመገደብ ውሀ ወደ
ግብጽ እንዳይወርድና የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መስጊዶች እንደሚያፈራርስ የሚዝት ልዑክ ወደ ካይሮ ላከ። ሱልጣኑ በመገረም መልዕክተኛውን መልሷል። (ምንጭ ፦ አስ ሱሉክ ሊመዕሪፈቲ ዱወል አል ሙልክ ፣ ጥራዝ 1, ገጽ 447)
- አፄ አምደ ፅዮን ሌላኛው የኢስላም ግዛት ወደ ሆነችው ኢፋት ዘመተ። ኢፋትን አጠቃ። ወርቅ፣ ብር፣ ነሀስ፣ መዳብ እና ልብሶችን ዘረፈ። ( #ምንጭ ፦ The Ethiopian Borderlands, P.41)
አለቃ ተክሌ እንዲህ ሲሉ ፅፈዋል፦ "ከዚህም በኋላ ከኢፋት ጀምሮ እስከ ዘይላ ድረስ በ9 ቀን መታው፤ እግር በራስ አነባበረው። ያዳልንም ንጉስ ያን ግዜ ሞተ። ቤቱ ተቃጠለ። ዘረፋው ተጠገበ። ከሰው ለዘር አልተረፈም። አርዶ አርዶ ጣለው... ንጉሱም አፄ አምደ ፅዮን ሐበሻን በጉልበቱ አስከበራት።..." ( #ምንጭ ፦ አለቃ ተክለ እየሱስ ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ, ገጽ.32)
- አፄ አምደ ፅዮን ዘቦይ የተባለችውን አገር ወረረ ሼህ አብደላህ የተባሉትንም ዓሊም ገደለ። መስጊድም አቃጠለ። ( #ምንጭ ፦ መሪ ራስ ኤ.ኤም በላይ፤ ገጽ 232)
ወደ ዳውሮ አርሲ በመሄድ አገሩን ከዳር እስከ ዳር አጠፉት። አዝመራቸውም ሳይቀር አጠፋው። የገና በዓልም በዚያው አከበረ።
ክፍል 8 ይቀጥላል
ይህንንና ሌሎች ፕሮግራሞች በተከታታይ ክፍል ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
t.me//AkeelComparative
ክፍል ❻
የክርስቲያኖች የግድያ ታሪክ
አሁን ባለው የክርስቲያኖች አለም የግድያና የጦርነት ሁኔታ ስንመለከት የሩሲያና ዩክሬንን ጦርነት ቁጥር አንድ ቦታ ይዞ ይገኛል። ታድያ የክርስቲያን ሀገሯ ሩሲያ ግዛቷን ለማስፋፋት በሚል የንፁህ ዩክሬናውያንን ደም በትቦ የምትመጥበትን ጦርነት በአይናችን የምናየው የሆነ የዚህ ዘመን ክስተት ሲሆን ከዛሬ አስራዎች አመታት በፊት ደግሞ ለክርስትና ዘብ ቆሜያለሁ ባይዋ አሜሪካንም ኢራቅን ወደ ፍርስራሽነት የቀየረችበትንና ህዝቦቿንም እንደ አርሶ አደር ዘር ያጨደቻቸው አይረሴ ታሪክም የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ሆኖ እናገኘዋለን።
ሌላው የክርስቲያን ሀገራት ከፈፀሟቸውና ታሪክ ከማይረሳቸው የግድያና ጦርነቶች መካከል ጀርመናዊው አዶልፍ ሂትለር አይሁዶችን እንደ ደራሽ ወንዝ ጎርፍ የጠራረገችበት ክስተት የሚጠቀስ ሲሆን ሃያላን የአለማችን የክርስቲያን ሀገሮች እርስ በርሳቸው እንደ አውሬ የተበላሉበት የሆነው የሁለተኛው የአለም ጦርነት ደግሞ ሌላኛው ከታሪክ ክስተቶች ውስጥ በዋነኛነች የሚጠቀስ ይሆናል። ታድያ ከአለም ህዝብ 2.5% የሚሆነውን የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ነፍስ የቀማውና እጅግ አስከፊ ስለነበረውም የሁለተኛው አለም ጦርነት በተመለከተ ከታሪክ አምድ በጥቂቱ ላስታውስ፦
👉 ሁለተኛው የአለም ጦርነት
ሁለተኛው የአለም ጦርነት እ.አ.አ ከ1939- 1945 ድረስ የተካሄደ የአለም ጦርነት ነው። በዚህ ጦርነት ላይ በተለይም አለም ላይ የሚገኙትን #የክርስቲያን ሀገራት በሁለት ቡድን ሆነው የተፋለሙበት ታላቅ የጦርነት ፍልሚያ ሲሆን በጦርነቱም የተሳተፉ ሀገራት #አላይድ #ሀገራት እና #አክሲስ #ሀያላት በመባል በሁለት ጎራ ተከፍለው ነበር።
-> በአላይድ ሀገራት በኩል፦በተባበሩት መንግስታት ሊግ በኩል የሚገኙ እነአሜሪካ ፣ብሪታንያ ቻይና ፣ሶቭየትህበረት፣ ፈረንሳይ፣ ፖላንድ፣ ካናዳ ፣ አውስትራሊያ፣ ኖርዌይ፣ ግሪክ፣ ኔዘርላንድ፣ ጎዝላቪያ ፣ ደቡብ አፍሪካና ኒውዚላንድ ሲመደቡ #በአክሲስ #ሃያላት ጎራ ደግሞ፦ ጀርመን ፣ ጃፓን ፣ ሮማንያ፣ ሀንጋሪ፣ ቡልጋሪያና በፋሺስት ሞሶሎኒ የሚመራው ጣሊያን ይገኙበታል።
👉 የጦርነቱ ምክንያቶች
❶ የቬርሳይ ስምምነት
በ1918 ይህም ማለት ከ1ኛው የአለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ #በቬርሳይ ስምምነት ላይ ጀርመን ለ1ኛው የአለም ጦርነት ሀላፊነት መውሰድ እንዳለባት በአሜሪካ ተፈረመ። በዚህም ስምምነት ቅኝ ግዛት እንዲቆም፣ የአየር ሀይል አጠቃቀምና በጦርነቱ አሸናፊ የነበሩ ሀገሮች የኢኮኖሚ ካሳ
እንዲከፍሉ ተወሰነ።
❷) የፋሺዝምና የብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲ
የክርስትናን እምነት አራማጅ በሆኑት በጣሊያንና በጃፓን የፋሺዝምና የብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲ ተመሠረቱ። በሀገረ ጣሊያን በ1920ዎቹ ወደ ስልጣን የመጣው የፋሺስቱ ፓርቲ ቤኔቶ ሞሶሎኒ በኢኮኖሚ ግትርነት፣በኢንዱስትሪ ቁጥጥርና በዜጎች ላይ በኢኮኖሚ ጫና በማሳደር የመንግስት ብሔርተኝነት አስተሳሰብ ተንቀሳቀሰ።
የጃፓን ግዛትም በብሔራዊ ስሜት፣ በልማትና በኢኮኖሚ ተስፋ ይነዳ ነበር። ይህ ንቅናቄ አዶልፍ ሂትለር ወደ ስልጣን የወጣበት የሠራተኛ ማህበር የተቀበለበት እና የሶሻሊስት ፓርቲ ወይም ናዚ ፓርቲ የተቋቋመበት ሰሜን ጀርመን ደርሷል።
❸) የሰላም ስምምነቶች አለመሳካት
አሜሪካ በጀርመን ላይ የወሰነችው ይህ ውሳኔ ጀርመንን የሚጎዳ በመሆኑ በወቅቱ ድምፄ ይሰማ ስትል ለአለም አቤት ስትል ፈረንሳይና ብሪታንያ የጀርመን ጩኸት ሰምተው አዲስ ጦርነት እንዳይከሰት የጀርመን ጥያቄ እሰጣለሁ በሚል ጀርመን ላይ ስምምነች አድርገው የነበረ ሲሆን በአሜሪካ በኩል ግን ውሳኔው የሚቀየር ባለመሆኑ ነው።
❹) የመንግስታቱ ሊግ ያልተሳካ ጣልቃ ገብነት
በ1919 የመንግስታት ማህበር ተፈጠረ። ይህም ሁሉም ብሄሮች አንድ እንዲሆኑና በየትኛውንም ችግር ቢፈጠር በጦርነት ሳይሆን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ልዩነቶቻቸውን እንዲፈቱ ነበር። ነገር ግን በ1930ቹ በተፈጠረው ቀውስ ብዙዎች ሳያምኑበት በመቅረቱ እንደ ጃፓንና USSR የመሳሰሉ ሀገራት የመከላከያ ሀይላቸውን አጠናከሩ።
❺) የጀርመን ሚሊሺያነትና የፖላንድ ወረራ
አንደኛው የአለም ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ የተፈረመው የቬርሳይ ስምምነት ጀርመንን ክፉኛ የሚጎዳ ስለሆነ የአንደኛው አለም ጦርነት ለሁለተኛው የአለም ጦርነት መከሰት ወይም መነሳት በዋነኛነት መንስኤ ሆነ። በዚህም በሂትለር የሚመራው የጀርመን ወታደራዊ ሀይል በ1935 እንደ ኦስትሪያ ያሉ ግዛቶችን በማካተት የቬርሳይስን ስምምነት መጣስ ጀመረች። ቀጥሎም ፖላንድን መውረርዋን እንደተያያዘችው ታሪክ ይናገራል። ከዚህም ጊዜ በኋላ የሁለተኛው የአለም ጦርነት በሁለት የጥምረት ቡድኖች መካከል መካሄድ ጀመረ።
ይህ የሁለተኛው የአለም ጦርነት በወቅቱ ብዙ ደም አፋሳሽነትን ያስከተለ በመሆኑም የተነሳ የብዙዎችን ህይወት የቀጠፈም ክስተት እንደ ነበር ታሪክ ያትታል።
በጊዜው የነጀርመን፣ ጣሊያንና ጃፓን ጥምረት የሆነው የአክሲስ ሀያላት ቡድንም በጦርነቱ ሽንፈት የተከናነቡ ቢሆንም ይህን ከፍተኛ የህዝብ እልቂት ያስተናገደው የአለማችን ትልቁ ጦርነት በተለያዩ የአለማችን ክፍሎችም እንደተካሄደና በተለይም በጃፓን ከተማ ላይ የተጣለው አቶሚክ ቦምብ ብዙዎችን ንፁሀን ዜጎች እንዳጠፋ ይነገራል። በአጠቃላይ በአለም ላይ እስከ 70,000,000 (ሰባ ሚሊዮን) የሚጠጉ ሰዎች በዚህ ጦርነት ህይወታቸው እንዳጡ በተለያዩ የታሪክ ድርሳናት ተፅፎ ይገኛል።
ታድያ ይህ አለማችን ያስተናገደቸው የጦርነት ታሪክ ሙስሊሞች ናቸው ይህንን ያደረጉት?
ክፍል ❼ በኢትዮጵያ ታሪክ ይቀጥላል
ወደ ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative
ክፍለ -❺
❺ #የምርኮኞችን #ደህንነት #እንዲጠበቅ እና #እንክብካቤ እንዲደረግላቸው መታዘዙ፦
76፡ 8-9
ويطعمون الطعام على حبه مسكينا ويتيما وأسيرا
إنما نطعمكم لوجه الله لا نريد منكم جزاء ولا شكورا
<<ምግብንም ከመውደዳቸው ጋር ለድኻ፣ ለየቲምም፣ #ለምርኮኛም #ለእስረኛም ያበላሉ፡፡
«የምናበላችሁ ለአላህ ውዴታ ብቻ ነው፡፡ ከእናንተ ዋጋንም ማመስገንንም አንፈልግም፡፡>>
ኢስላም በብዙ መልኩ ለሰላም ዘብ የቆመ ሐይማኖት ነው። ታድያ እጅግ የሚስደንቁና የእጅ መዳፍ በአፍ የሚያስጭኑም የሆኑ ፍትሀዊ የሆነና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን የያዘ እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ደግሞ ከዛሬ 1400 ዓመት በፊት ጀምሮ ይተገበር የነበረውን የእስረኞችና የምርኮኞችን ደህንነት የመጠበቅና የመንከባከብ የሰብዓዊ መብት ህግን ያፀደቀ ነው።
ስለዚህ እስልምና በጦርነት ወቅት ለተማረኩ ምርኮኞች እና እስረኞች ሰብዓዊ መብታቸውን እንዳይጣስ በማድረግ ከሁሉ በመቅደም የጀመረ የሆነ ድንቅ ሐይማኖት ነው።
ታድያ ዛሬ ኢስላምን የጭካኔ መሠረት ያደረጉት አውሮፓውያን ይህ የእስረኞችን ሰብዓዊ መብታቸው የሚያከብረው ህግ ያፀደቁት እጅግ በጣም ዘግይተው የነበረ ሲሆን በዚህም እስረኞች እንዳይደበደቡና እንዳይንገላቱ የሚያከብረው ህግ ያፀደቁት በ1977 በጄኔቭ በተደረገው ስምምነት ላይ ነበር።
❻) ዛፎችን መቁረጥ ፣አካባቢን ማጥፋትና እንስሳት ያለአግባብ መግደልን ስለመከልከሉ፦
የነብዩ(ሰዐወ) ባልደረባ የሆኑት አቡበክር(ረዐ) እንዲህ ይሉ ነበር፦
"እገስጻችኋለሁ ዛፎችን ላትቆርጡ ፣ ቤቶችንም ላታቃጥሉ፤ በግና ፍየሎችንም ለምግብነት ካልሆነ በቀር ላትገድሉ።" በማለት ይናገሩ ነበር።
በአሁኑ ወቅት የአለማችን የሙቀት መጠን በእጅጉ በመጨመሩም ምክንያት ከፍተኛ አደጋዎችን እያስተናገዱ ያሉት ምዕራባውያን በሁኔታው መላ ቅጡን ቢጠፋባቸው ለችግሩ መፍትሔ ፍለጋ ሁሉም
የየራሱ ርምጃ በመውሰድ ላይ የሚገኝ ሲሆን በዋነኛነት ችግሩን ይቀርፋል ተብሎ የታመነበት ደግሞ ዛፍ የመትከል ጉዳይ ነው።
ታድያ ከ1400 ዓመት በፊት ጀምሮ እስልምና በጦርነት ወቅት ሳይቀር ዛፍን አለመቁረጥ እና ዛፍ የመትከልን ተግባር እያካሄደች ነበር። በኢስላም ዛፍን መትከል ከሰደቃቱል ጃሪአ ይቆጠራል። በዚህ ዙሪያ ደግሞ የተለያዩ የሐዲስ ጥርቅሞች እናገኛለን፦
✔ አነስ(ረዐ) እንዳስተላለፉት ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል፦ "ከእናንተ ውስጥ ችግኝ በእጁ እንደያዘ እለተ ትንሳኤ የደረሰበት ሰው ይትከለው።"
✔በሌላ ዘገባ አነስ(ረዐ)እንዳስተላለፉት፦ "ነብዩ(ሰዐወ) ማንኛውም ሙስሊም ዛፍን ቢተክል ወይም ዘርን ቢዘራ ከእሱ ሰውም ሆነ እንስሳ ከተመገበ ለእርሱ ሰደቃ ነው።"
✔ አንድ የረሱል(ሰዐወ) ባልደረባ ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ብለው ሲናገሩ በጆሮዬ ሰምቻለሁ "ዛፍ ተክሎም እስክታድግ የተንከባከባት ፍሬ እስክታፈራም የጠበቃት አላህ በፍሬው ልክ ሰደቃ ይፅፍለታል።"
❼ በሐይማኖት ማስገደድ የለም፦
2፡ 256]
لا إكراه في الدين ۖ قد تبين الرشد من الغي ۚ فمن يكفر بالطاغوت ويؤمن بالله فقد استمسك بالعروة الوثقى لا انفصام لها ۗ والله سميع عليم
በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡
እናም በሐይማኖት ማስገደድ የሚሉት ነገር በሸሪዓው ስለሌለ እንዲሁም ሌሎች ካልደረሱብን በቀር በግድ የእኛን ተቀበል ተብሎ እስልምናንም ሆነ የሙስሊም ግዛት ለማስፋፋት የሚደረግ ጦርነትና ግድያ ድሮም አልነበረም ፤አሁንም የለም ፤ ወደፊትም አይኖርም።
ክፍል 6 ይቀጥላል
ስለመግደል የሚያስተምረው እምነት
(እስልምና ወይንስ ክርስትና)
ክፍል ❹
👉 በኢስላም ከተከለከሉ ሰባት ግድያዎች መካከል
( 7 የጦርነት ህጎች)
❶) ሴቶችና ህፃናት መግደል ስለመልከሉ
ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ አነስ ኢብኑ ማሊክ(ረዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) ህጻናትና ሴቶችን እንዳንገድል በጥብቅ አዘውናል" በማለት ተናግሯል። { ሙስሊም 4320 }
ይህ የነብዩ(ሰዐወ) ንግግር የሆነው የኢስላም የጦርነት ህግም በሙስሊሞች አለም ላይ ተቀባይነት ያገኘ ጉዳይ ሲሆን በመላው ሙስሊሞች ዘንድም ተግባራዊ የሚደረግ የኢስላማዊ የሸሪዓ ህግ ነው።
❷) ጦርነት ላይ ያልተሳተፉ ሽማግሌዎች ፣ የሐይማኖት አባቶችና ሰራተኞችን መግደል እንዲሁም የሐይማኖት ተቋማትን ማፍረስ ስለመከልከሉ፦
ኢብኑ አባስ(ረዐ) እንደዘገቡት የአላህ መልዕክተኛ (ሰዐወ) ለጦርነት ሲባል ሽማግሌዎችን ከመግደል አስጠንቅቀዋል። ( al Byhaqi 166689)
በሌላ ዘገባ ኢብኑ አባስ የአላህ መልዕክተኛ <መነኩሴዎችን ነው> በማለት ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪም በቅዱስ ቁርዓን ውስጥ እንዲህ ተገልጿል፦
22፡ 40
الذين أخرجوا من ديارهم بغير حق إلا أن يقولوا ربنا الله ۗ ولولا دفع الله الناس بعضهم ببعض لهدمت صوامع وبيع وصلوات ومساجد يذكر فيها اسم الله كثيرا ۗ ولينصرن الله من ينصره ۗ إن الله لقوي عزيز
ለእነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ከማለታቸው በስተቀር ያለ አግባብ ከአገራቸው የተባረሩ ለሆኑት (ተፈቀደ)፡፡ አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ ባልነበረ ኖሮ #ገዳማት ፣ #ቤተክርስቲያኖችም ፣ #ምኩራቦችም በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው #መስጊዶችም፤ #በተፈረሱ ነበር፡፡ አላህም ሃይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡
❸ #የሞተን #ሬሳ #በክብር #ስለማስቀመጥ ፦
በጦርነት ወቅት የሞተን ሬሳ በክብር ስለማስቀመጥ ነብዩ (ሰዐወ) ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦ "በአላህ መንገድ ላይ ታገሉ ፤ ቃልኪዳናችሁንም ጠብቁ ፤ ሬሳንም አትቆራርጡ ፤ ህፃናትም አትግደሉ።" ( ሙስሊም 4294)
❹) በጦርነት ወቅት የተማረኩትን ጠላቶች እንዳይገደሉና እንዳይባረሩ እንዲሁም ከጠላት ወገኖች መካከልም እኛን ያልተዋጉንን በሰላም መኖር እንዳለባቸው ኢስላም በጥብቅ ያዛል፦
2፡ 85
ثم أنتم هؤلاء تقتلون أنفسكم وتخرجون فريقا منكم من ديارهم تظاهرون عليهم بالإثم والعدوان وإن يأتوكم أسارى تفادوهم وهو محرم عليكم إخراجهم ۚ أفتؤمنون ببعض الكتاب وتكفرون ببعض ۚ فما جزاء من يفعل ذلك منكم إلا خزي في الحياة الدنيا ۖ ويوم القيامة يردون إلى أشد العذاب ۗ وما الله بغافل عما تعملون
ከዚያም እናንተ እነዚያ ነፍሶቻችሁን የምትገድሉ ከናንተም የኾኑ ጭፍሮችን በኃጢአትና በመበደል በነርሱ ላይ የምትረዳዱ ስትኾኑ #ከአገሮቻቸው የምታወጡ #ምርኮኞችም #ኾነው #ቢመጡዋችሁ #የምትበዡ #ናችሁ፡፡ እርሱ (ነገሩ) #እነርሱን #ማውጣት #በእናንተ #ላይ #የተከለከለ #ነው ፡፡ በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን? ከእናንተም ይህንን የሚሠራ ሰው ቅጣት በቅርቢቱ ሕይወት ውርደት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀንም ወደ ብርቱ ቅጣት ይመለሳሉ፡፡ አላህም ከምትሠሩት ሥራ ሁሉ ዘንጊ አይደለም፡፡
4፡ 90
إلا الذين يصلون إلى قوم بينكم وبينهم ميثاق أو جاءوكم حصرت صدورهم أن يقاتلوكم أو يقاتلوا قومهم ۚ ولو شاء الله لسلطهم عليكم فلقاتلوكم ۚ فإن اعتزلوكم فلم يقاتلوكم وألقوا إليكم السلم فما جعل الله لكم عليهم سبيلا
እነዚያ በእናንተና በእነርሱ መካከል ቃል ኪዳን ወዳላቸው ሕዝቦች የሚጠጉና ወይም እናንተን ለመጋደል ወይም ወገኖቻቸውን ለመጋደል ልቦቻቸው የተጨነቁ ኾነው የመጧዋችሁ ሲቀሩ፤ (እነዚያንስ አትጋደሉዋቸው)፡፡ አላህም በሻ ኖሮ በእናንተ ላይ ኀይል በሰጣቸውና በተጋደሉዋችሁ ነበር፡፡ #ቢተዋችሁና #ባይጋደሉዋችሁም ወደ እናንተም እርቅን ቢያቀርቡ አላህ ለእናንተ በነሱ ላይ ( #የመጋደል ) #መንገድን #አላደረገም፡፡
4፡ 91
ستجدون آخرين يريدون أن يأمنوكم ويأمنوا قومهم كل ما ردوا إلى الفتنة أركسوا فيها ۚ فإن لم يعتزلوكم ويلقوا إليكم السلم ويكفوا أيديهم فخذوهم واقتلوهم حيث ثقفتموهم ۚ وأولئكم جعلنا لكم عليهم سلطانا مبينا
ሌሎች ከእናንተ ለመዳን ከወገኖቻቸውም ለመዳን የሚፈልጉን ታገኛላችሁ፡፡ ወደ እውከት እንዲመለሱ
በተጠሩ ቁጥር በርሷ ውስጥ ይመለሳሉ፡፡ ባይተውዋችሁና እርቅንም ባያቀርቡላችሁ፣ እጆቻቸውንም ባይሰበስቡ፣ ባገኛችኋቸው ስፍራ ማርኩዋቸው፡፡ ግደሉዋቸውም፡፡ እነዚያንም ለእናንተ በነሱ ላይ ግልጽ ማስረጃን አድርገናል፡፡>>
5 #የምርኮኞችን #ደህንነት #እንዲጠበቅ እና #እንክብካቤ እንዲደረግላቸው መታዘዙ፦
ክፍል -❺ ይቀጥላል
ይህንን መረጃ ለሌሎችም ሼር ያድርጉት!
t.me//AkeelComparative
ስለ መግደል የሚያስተምረው እምነት
( እስልምና ወይስ ክርስትና)
ክፍል ❸
👉 ሌላው አንድ አሳዛኝ የሆነና በብቸኝነት መነሳት ያለበት የግድያ አይነት ይገኛል። ይህም ደግሞ ህፃናት ፣ ሴቶችና አቅመ ደካማ ሽማግሌዎችን በሰይፍ እንዲገደሉ የሚበይን የሆነ ፀያፍ የግድያ ህግ ነው። እንግዲህ የዚህ #የሠይፍ #ህግ #ነው #የክርስትናው #እየሱስ ይዤው መጣሁ ያለው። ምክንያቱም፦ #ማቴዎስ 5፥17 ላይ
" እኔ ህግና ነቢያት ለመሻር አልመጣሁም ፤ ይልቁንስ ልፈፅም ነው እንጂ"። ሲል ይናገራልና!!!
- ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 9
6፤ #ሽማግሌውንና ጐበዙን ቈንጆይቱንም #ሕፃናቶቹንና #ሴቶቹን ፈጽማችሁ #ግደሉ፤ ነገር ግን ምልክቱ ወዳለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ፤ በመቅደሴም ጀምሩ አላቸው። በቤቱም አንጻር ባሉ #ሽማግሌዎች #ጀመሩ።
- መፅሐፈ መሳፍንት 21፥10
" ማኅበሩም ወደዚያ አሥራ ሁለት ሺህ ኃያላን ሰዎች ሰድደው። ሂዱ በኢያቢስ ገለዓድም ያሉትን ሰዎች #ከሴቶችና #ከሕፃናት ጋር #በሰይፍ #ስለት #ግደሉ ።" በማለት ያዛል!!!
✔ ጦርነት እና ግድያ በእስልምና
ከዚህ ቀደም በነበረው ክፍል ላይ የጦርነትና የግድያን ፈቃድ በክርስትና ምን እንደሚመስል አይተን ነበር። ቀጥሎም ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የእስልምና የሸሪዓ ህግ ምን ይላል? የሚለውን ትምህርት በአላህ ፈቃድ እናያለን። የዚህንም የግድያ ህግ በምንመለከትበት ጊዜ አላህ(ሱወ) እንዲህ ሲል ተድንግጓል፦
17፡ 33
ولا تقتلوا النفس التي حرم الله إلا بالحق ۗ ومن قتل مظلوما فقد جعلنا لوليه سلطانا فلا يسرف في القتل ۖ إنه كان منصورا
<<ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ #ያለ #ሕግ #አትግደሉ፡፡ የተበደለም ኾኖ የተገደለ ሰው ለዘመዱ (በገዳዩ ላይ) በእርግጥ ስልጣንን አድርገናል፡፡ #በመግደልም #ወሰንን #አይለፍ፤ እርሱ የተረዳ ነውና፡፡>>
2፡ 190
وقاتلوا في سبيل الله الذين يقاتلونكم ولا تعتدوا ۚ إن الله لا يحب المعتدين
<<እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን (ከሓዲዎች) በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና፡፡>>
የእስልምና ዕውቀት ሳይኖራቸውም በተባለ ወሬ ብቻ የሚያምኑ እና እውነትን አምኖ ላለመቀበል በሚጥሩት ኢስላም ጠል በሆኑ ግለሰቦች ዘንድ የሰላም ፀር እንደሆነ የሚታየው የእስልምና የግድያ ህግም ምን እንደሚመስል ከላይ በተገለፁ የቁርዓን አንቀፆች እንደተመለከትነው ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም " በኢስላም አንድ ነፍስን ያለአግባብ ያጠፋ ሰው አለም በሙሉ እንዳጠፋ ይቆጠራል። " በማለት ነብዩ(ሰዐወ) ተናግረዋል።
✔✔ የጦርነትና የግድያ አስተምህሮ በእስልምና
በእስልምና የሸሪዓ ህግ ጦርነትም ሆነ ግድያ የሚፈቀደው በሀይማኖት ለተዋጉንና ከሀገር ለሚያስወጡን ከሀዲዎች መሆኑን አላህ(ሱወ) ይደነግጋል፦
60፡ 8
لا ينهاكم الله عن الذين لم يقاتلوكم في الدين ولم يخرجوكم من دياركم أن تبروهم وتقسطوا إليهم ۚ إن الله يحب المقسطين
ከእነዚያ #በሃይማኖት #ካልተጋደሏችሁ #ከአገሮቻችሁም #ካላወጡዋችሁ (ከሓዲዎች) መልካም ብትውሉላቸውና ወደእነርሱ ብታስተካክሉ አላህ አይከለክላችሁም፡፡ አላህ ትክክለኞችን ይወዳልና፡፡
ከላይ በተዘረዘሩት የቁርዓን አንቀፆች መሠረት መዋጋትና መግደል የሚቻለው በሀይማኖታችን ድንበር አልፈው ለመጡብን ከሀዲዎች በሀይል እንድንመክታቸው የሚፈቅድ ድንጋጌ ሲሆን
<< #ከሆነ #ጋር #የተገኘህ #ሰሊጥ #አብረህ #ተወቀጥ >> የሚለውን የእኛ አገር አባባል እስልምና ቦታ የለውም። ምክንያቱም ጉዳት ሊያደርሱብን ያልተነሱትን ሰዎች ሀይል በመጠቀም አግበስብሶ በጅምላ መግደል እንደማይፈቀድና መሠረተ ቢስ መሆኑንም ስለሚገልፅ ነው።
✔✔✔ በጦርነት ወቅት በኢስላም የተከለከሉ 7 ግድያዎች፦
ሀገራት ጦርነት በሚያከናውበት ወቅት ጅምላ ጨራሽ የሆነ ጭፍጨፋ የማየታችን ተግባር የተለመደ እውነት ሲሆን በዚህም ህጻናት፣ ሴቶችና ሽማግሌዎች የጦርነቱ ሰለባ ይሆናሉ። እናም ይህ ሴቶችን፣ ህጻናትና ሽማግሌዎችን ኢላማ ያደረገው የጅምላ ጨራሽ ጭፍጨፋ የክርስትና እምነት አበክሮ የሚፈቅደው ተግባር እንደሆነ #በትንቢተ #ሕዝቅኤል 9፥6-8 ላይ በግልፅ ተቀምጧል። ታድያ የእስልምና የሸሪዓ ህግ ይህንን ፀያፍ ጭፍጨፋ ህገወጥ ተግባር በመሆኑም በጦርነት ወቅት ይህ እንዳይደረግ ይከለክላል።
ክፍል ❹ ይቀጥላል
ይህንን እውነት ሌሎችም ሼር ያድርጉት
t.me//AkeelComparative
ስለመግደል
ክፍል - ❷
✔✔ ስለመግደል አስተምህሮ በመፅሐፍ ቅዱስ
እንደ እውነቱ ከሆነ የዚህ መፅሐፍ የመጠሪያ ስሙ መባል የነበረበት መፅሐፍ ቅዱስ ሳይሆን #መፅሐፈ #መግደል ነው!። ምክንያቱም መፅሐፉ ስለ እንደ መግደል በሰፊው የሚያስተምር ምንም ነገር የሌለ ሲሆን በተለያዩ ምዕራፎቹ በትንሹ ከ55 ጊዜ በላይ ስለመግደል ፈቃድ ይሰጣል። ይህም ሲባል #36 ጊዜ #ይገደል ፣ #13 ጊዜ #ግደሉ ፣ #2 ጊዜ #እንዲገደል ፣ #2 ጊዜ #ይግደል ፣ #2 ጊዜ ደግሞ #ይግደለው በማለት መግደልን የመጨረሻው አማራጭ አድርጎ ይሰብካል።
✔✔✔ የግድያዎቹ አይነቶች
1ኛ) የበቀል ግድያ
በጣም የሚገርመው ነገር በሀገራችን የሰሜኑ ክፍል አካባቢ በተለይም የክርስቲያን ደሴት በምትባለው ጎጃም ላይ ከጥንትም ትውልዶቿ ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣና እስከዛሬም ድረስ ተግባራዊ እየሆነ ያለ አንድ #ደም #መላሽ የሚባል ህግ አለ። ታድያ ይህ ደም መላሽ ወይም #ደም #መመለስ የሚባለው ህግ ሁኔታው #ኦሪት #ዘኁልቅ 35፥19ን መሠረት ያደረገ ነው።
ይህም ማለት አንድ x የተባለ ሰው ከቤተሰቦቹ አባላት መካከል በሆነ y በተባለ ግለሰብ ቢገደል ይህ x የተባለው ሰውዬ ጊዜውን ጠብቆ መልሶ yን በመግደል የመበቀል ህግ ነው። በዚህ ህግ ነፍሰ ገዳዩ y ቢሰወር ወይም እዚያው ቢኖር x ገዳዩን ያለበት ቦታ ድረስ በመሄድ አሳድዶ በመግደል ደም የመመለስ ተግባር ነው።
2) የስድብ ግድያ ህግ
በዚህ የመሣደብ ግድያ ህግ ላይ አንድ ሰው እናቱንና አባቱን ቢሳደብና ቢመታ እንዲሁም እግዚአብሔርን ደግሞ የሰደበ ሰው እንዲገደል የሚፈቅድ ህግ ነው።
3) የሰው ሻጭ ግድያ
ይህ ህግ ተፈፃሚ እንዲሆን የሚናገረው ሰው ሰውን የሰረቀ እንደሆነና ሰርቆም የሸጠ ከሆነ ሌባው እንዲገደል የሚያስችል ህግ ነው።
4) የሠንበት አርካሽ ሰው ግድያ
በዚህ ህግ ላይ ማንኛውም ሰው በሰንበት ቀን ስራ የሚሰራ ከሆነ ይህ ሰው እንዲገደል ተፈርዶበታል።
5) የግብረ ስጋ ግንኙነት ግድያ ህግ
በዚህ ህግ ከአባቱ ሚስት ጋር ግንኙነት የፈፀመ ሠውና ከእንስሳት ጋር ግንኙነት ያደረገ ሰው እንዲገደል የሚያደርግ ህግ ነው።
መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚህንና ሌሎችንም ግድያን ተግባራዊ እንዲሆን የሚፈቅድ የሆነ የመግደል ህጎች ይገኛሉ። የጥቂቶቹን ዝርዝር እንመልከት፦
- ኦሪት ዘሌዋውያን ምዕ. 20
9፤ ማናቸውም ሰው አባቱን ወይም እናቱን ቢሰድብ ፈጽሞ #ይገደል፥ አባቱንና እናቱን ሰድቦአልና፤ ደሙ በራሱ ላይ ነው።
11፤ ማናቸውም ሰው ከአባቱ ሚስት ጋር ቢተኛ የአባቱን ኃፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ሁለቱ ፈጽመው #ይገደሉ፤ ደማቸው በላያቸው ነው።
13፤ ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ ፈጽመው #ይገደሉ፤ ደማቸው በላያቸው ነው።
15፤ ማናቸውም ሰው ከእንስሳ ጋር ቢገናኝ ፈጽሞ #ይገደል፤ እንስሳይቱንም #ግደሉአት።
16፤ ማናቸይቱም ሴት ወደ እንስሳ ብትቀርብ፥ ከእርሱም ጋር ብትገናኝ፥ ሴቲቱንና እንስሳውን ግደል፤ ፈጽመው #ይገደሉ፤ ደማቸው በላያቸው ነው።
- ኦሪት ዘሌዋውያን 24፥16
"የእግዚአብሔርን ስም የተሳደበ ሰው #ይገደል።
- ኦሪት ዘጸአት ምዕ. 21
15፤ አባቱን ወይም እናቱን #የሚመታ ፈጽሞ #ይገደል።
16፤ #ሰውን #ሰርቆ ቢሸጥ፥ ወይም በእጁ ቢገኝ፥ እርሱ ፈጽሞ #ይገደል።
- ኦሪት ዘጸአት ምዕ. 31
14፤ ስለዚህ ለእናንተ ቅዱስ ነውና #ሰንበትን ጠብቁ፤ #የሚያረክሰውም #ሰው ሁሉ ፈጽሞ #ይገደል፥ ሥራንም በእርሱ የሠራ ሰው ሁሉ ከሕዝቡ መካከል ተለይቶ ይጥፋ።
15፤ ስድስት ቀን ሥራን ሥራ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር የተቀደሰ የዕረፍት ሰንበት ነው፤ #በሰንበት #ቀን #የሚሠራ ሁሉ ፈጽሞ #ይገደል።
- ኦሪት ዘኍልቍ ምዕ. 35
19፤ #ደም #ተበቃዩ ራሱ ነፍሰ ገዳዩን #ይግደል፤ ባገኘው ጊዜ ይግደለው።
21፤ ወይም በጥላቻ እስኪሞት ድረስ በእጁ ቢመታው፥ የመታው ፈጽሞ #ይገደል፤ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ደም ተበቃዩ ባገኘው ጊዜ #ነፍሰ #ገዳዩን #ይግደለው።
ክፍል- ❸ ይቀጥላል
.
ስለ መግደል የሚያስተምረው እምነት
( እስልምና? ወይስ ክርስትና?)
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሙሉውን መረጃ በተከታታይ ክፍል ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
የእስልምናን እምነት በማይከተሉና ስለእስልምና በቂ እውቀት በሌላቸው ወገኖች በኩል እስልምና ፅንፈኛና ፀረ ሰላም እምነት ነው በማለት የሚነገር ወሬ ዛሬ ላይ የተለመደ ጉዳይ ሲሆን በተለይም እውነት ጠል በሆኑት ምዕራባውያን ዘንድ ደግሞ ለእስልምና ጥቁር ጥላሸት መቀባቱም ስራዬ ብለው ተያይዘውታል። እነዚህ የእስልምናን ጥልቅ ሂወት ያልተጎነጩ ወገኖች ከስሙ ጀምሮ ስለ ሰላም የሚሰብከውን ሐይማኖት ንፁሀንን ለመግደል እንደተመሠረተና በሰይፍ የተስፋፋ እምነት እንደሆነ ያስባሉ። ያለመታደል ሆኖ ጦርነት የስልጣኔ አንድ አካል መሆኑ ለማናችንም ግልፅ ነው። አለም ሰለጠነች በተባለበት በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሳይቀር ራስን ለማበልጸግ ሲባልና ዘርዝረን በማንዘልቃቸው ምክንያቶችም የክርስትና አራማጅ የሆኑ ሀገራት ወደ ጦርነት ሲገቡ እያስተዋልን ነው።
ታድያ ስለእስልምና ስናወራ አሁን ላይ የራስን ሀያልነት ለማስጠበቅ ሲባል እንደሚደረገው የግዛት ማስፋፋትና ወረራ አልያም ነዳጅ ፍለጋ የሠው ነፍስ እንደሚቀማበት አስተሳሰብ ሳይሆን በኢስላም ያለው ለጦርነት ምክንያት ተደርጎ የተቀመጠው
መፍትሄ ህዝብን ወደ ዝቅጠት ለማሸጋገር የሚጥሩ ሰይጣናዊ ተግባራትንና ፀብ ጫሪነትን በማስቆም እንዲሁም የማህበረሰብን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲሆን ነው። ከነዚህ የክርስቲያን ሀገራት አንጻር ግን የኢስላምን ሸሪዓ ተግባራዊ የሚያደርጉ ሀገሮች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዚህ የሌሎችን ድርሻ በመቀማት ተልካሻ ተግባር ሲሳተፉና ጦርነት ሲያስነሱ አይታይም። በዚህም የእስልምና እምነት ብቸኛው የሠላም ባለቤት ያደርገዋል።
ምክንያቱን ደግሞ የሰላም ባለቤቱ አላህ(ሱወ) እንዲህ ሲል ያዛል፦
28፡ 77
وابتغ فيما آتاك الله الدار الآخرة ۖ ولا تنس نصيبك من الدنيا ۖ وأحسن كما أحسن الله إليك ۖ ولا تبغ الفساد في الأرض ۖ إن الله لا يحب المفسدين
«አላህም በሰጠህ ሀብት የመጨረሻይቱን አገር ፈልግ፡፡ ከቅርቢቱም ዓለም ፋንታህን አትርሳ፡፡ አላህም ወደ አንተ መልካምን እንዳደረገልህ (ለሰዎች) መልካምን አድርግ፡፡ በምድርም ውስጥ ማጥፋትን አትፈልግ፡፡ አላህ አጥፊዎችን አይወድምና» (አሉት)፡፡
ጉዳዩ << የእምዬን ወደ አብዬ >> ነውና በነዚህ ኢስላም ጠሎች አማካኝነት በተለያየ ጊዜ በሚፈጥሩት የስም ማጥፋት ዘመቻ ምክንያቶች እየተስተዋሉ ያሉትን የተዛቡ አመለካከቶች ለጊዜው ትንሽ ጥግ አቆይተነውም ወደ ርዕሳችን መለስ እንበልና #ስለመግደል #የሚያስተምረው #እምነት << እስልምና ነው? ወይስ ክርስትና ነው? >> የሚለውን እናያለን። በዚህም መሠረት ስለ ጦርነትና ስለመግደልን አስመልክቶ የክርስትናዊ ህግና የኢስላማዊው የሸሪዓ ህጎች( ቁርዓንና ሐዲስ) ምን ይላሉ፦
✔ ጦርነትና ግድያ በክርስትና እምነት
በብዙ ክርስቲያኖች ዘንድ የክርስትናን እምነት በደሙ እንደመሰረተው እና እምነቱም የሰላም እምነት ሆኖ ስለሰላም በመስበክም እንዳስፋፋው የሚናገሩለት እየሱስ እርሱም ለምድራችን ሰላም ያመጣ #የሰላም #አምላክ #ነው በማለት ይናገራሉ። ነገር ግን ለእስራኤል ብቻ የተላከ ነብይ የሆነው እየሱስም ሲናገር እንዲህ ይላል፦
- ማቴዎስ ወንጌል 10፥34
" በምድር ላይ #ሰላምን #ለማምጣት #የመጣሁ #አይምሰላችሁ፤ #ሰይፍን #እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም።" ይላል!!!
ክፍል - ❷ ይቀጥላል
. ክፍል - 8
እናም አብርሽ በዚሁ በእግረ መንገዴ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ፦
መቼም ማርያም እየሱስን በድንግልና እንደወለድችውና የእየሱስ ወላጅ እናት መሆኗን እናንተም አትክዱም እኛም ደግሞ በዚህ እናምናለን። ታድያም በእናንተ በክርስትና እምነት ዘንድ ማርያም ታማልዳለች አታማልድም በሚለው ዙሪያ ስለእሷ ያላችሁ አቋም የተለያየ ቢሆንም ነገር ግን እናትነቷን አትክዱም። ሆኖም ግን በየክርስቲያን መኖሪያ ቤቶችና በየቤተክርስቲያኑ የእሷን ፎቶ ተሰቅሎ እናገኛለን። ታድያ እኛ ሙስሊሞች ይህንን የማርያም ፎቶና የትኛውንም ፎቶ መለጠፍ የማንቀበለው እውነት ቢሆንም ነገር ግን ከእነዚህ የማርያም ፎቶዎች መካከል ማርያም ራሷን ሳትሸፍን ተገላልጣ የምትታይበት ፎቶ ልታሳየኝ ትችላለህን??? አንድም ፎቶ ልታሳየኝ አትችልም።
ከዚህም የመሸፋፈን ተግባር አንፃር ካየነው የማርያምን እምነት ተግባራዊ የምናደርገው እኛ ሙስሊሞች ነን እንጂ እናንተ ክርስቲያኖች አይደላችሁም።
👉 #ከመፅሐፍ_ቅዱስ
✔ እናንተ ክርስቲያኖች በመጽሐፋችሁ ያለው ነገር ተግባራዊ ባለማድረግ እኛን ትቃወማላችሁ እንጂ ባይብላችሁ እኮ ሴት ልጅ መሸፋፈን እንዳለባት በግልፅ ይናገራል።
- 1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 11
5፤ #ራስዋን #ሳትሸፍን ግን #የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር #ሴት #ሁሉ #ራስዋን #ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
✔ በሌላም በኩል ራሷን ያልሸፈነች ሴት ፀጉሯን መቆረጥ እንዳለባትም በግልፅ ያስጠነቅቃል፦
- 1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 11፥6
6፤ #ሴትም #ራስዋን #ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ #ራስዋን #ትሸፍን።
✔ ራሷን ያልሸፈነች ሴትም ወደ እግዚአብሔር መፀለይ እንደማትችል ያትታል፦
- 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥13
13፤ በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ #ሴት #ራስዋን #ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
✔ አሁን ላይ በየ ቤተ ክርስቲያናቱ ቴሌቪዥኖች ጣቢያ ላይ ወንዳወንድ ሆነው ወንድ መስለው የሚያስተምሩ ሴቶቻችሁ ጉዳይ ከዚህ 1ኛ ቆሮ 11 ምዕራፍ ጋር አይጋጭምን???
✔ በየ የክርስትና በዓላት ቀናቶች ላይ የሚታየው የሴቶቻችሁ አለባበስ ሁኔታስ ታዝበኸው ታውቃለህን? ከላይ በስስ ቲሸርት ሆነው ከታች ደግሞ እስከ ጉልበታቸው ድረስ ብቻ የሚሸፍን ሚኒ ቀሚስ ለብሰው፣ ከላይ ጡታቸውን ወጥረውና ከታች በሱሪ ተወጣጥረው፣ ፀጉራቸው ላይ ደግሞ ሻርፕ እንኳን ጣል ሳያደርጉበት በየመጠጥ ቤቱ የሚያጨፍሩና ካገኙት ወንድ ጋር የሚማግጡ እህቶቻችሁ የመጨረሻ እጣ ፈንታቸው ነገር ምን እንደሆነስ?
👉 ነብዩ ሙሐመድ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦
አቡ ሙሳ አል-አሻሪይ በዘገቡት ሐዲስ
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “ሴት ልጅ ያለውና መልካም ስነ ምግባርን ያስተማራት፣ ትምህርቷንም ያሳደገ፣ ከዚያም የዳረ ሰው እጥፍ ምንዳ ያገኛል። የአላህን መብትና የጌታውን መብት የጠበቀ ባሪያም እጥፍ ምንዳ ያገኛል። ."
(ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 3, መፅሐፍ 46, ቁጥር 723)
ከአንድ በላይ ማግባትና ሴት ልጅ ራሷን መሸፈን
( እስልምና v/s ክርስትና)
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ክፍል - 7
ሙግት -2
ፓስተር አብረሀም እስልምናን እንዲጠላ ካደረገው ምክንያቶች መካከል (በሙግት -1) ላይ የተመለከትነው ከአንድ በላይ ሚስት የማግባት ጉዳይ ሲሆን ሌላኛውና ሁለተኛው ምክንያቱ ደግሞ " #በኢስላም #ሴቶች #ተሸፋፍነው #መሄዳቸው #እስልምና #የሴቶችን #መብት #ይጋፋልና በዚህም ሐይማኖቱ እንድጠላው ምክንያት ሆኖኛል" የሚል ነጥብ አንስቶ ነበር።
ታድያም አልሐምዱሊላህ!!! እናቴ፣ እህቶቼ፣ ባለቤቴና በአጠቃላይ አለም ላይ የሚገኙ ሙስሊም እህቶቼን በሙሉ ራሳቸውን እንዲሸፍኑ ላደረገው ጌታዬ አሏህ ሰማይና ምድር የሚሞላን ምስጋና ለእርሱ ባይመጥነውም! ይህ ክብሩን የተላቀው ጌታ ምስጋና ይድረሰው።
ጅልባብ ሙስሊም ለሆነች ሴት ልጅ ውበቷ ነውና ጌታዋ ከለገሳት ፀጋዎች መካከልም ውዱ ስጦታ ነው። አላህ(ሱወ) ለሙስሊም ሴቶች በጅልባብ ራሳቸውን እንዲሸፍኑ ሲናገር እንዲህ ይላል፦
33፡ 59
يا أيها النبي قل لأزواجك وبناتك ونساء المؤمنين يدنين عليهن من جلابيبهن ۚ ذلك أدنى أن يعرفن فلا يؤذين ۗ وكان الله غفورا رحيما
አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም #ከመከናነቢያዎቻቸው #በላያቸው #ላይ #እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ እንዲታወቁና (በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡
- እኔም፦ አብርሽ ሰውነታቸው ለቀው የሚሄዱ ሴቶች በጅልባብ ከተሸፈኑ ሴቶች አንጻር ጋር በባለጌ ሰዎች የመለከፋቸውና የመደፈራቸው እድሉ በጣም ሰፊ ነው። ለዚህ የሚሆን አንድ አይነተኛ ምሳሌ ልጥቀስልህ ፦
ሰዎች በሚበዙበትና ብዙ ሰዎች በሚተላለፉበት መንገድ ላይ ሁለት ፅጌረዳ አበባዎችን ለእይታ አስቀምጣቸው።
1) አንደኛው አበባ የሰው እጅ እንዳይነካው በወረቀት ሸፍነው ፤
2) ሁለተኛው አበባ ደግሞ ሳትሸፍነው ዝም ብለህ ግልጥ አድርገህ ተወውና ሁለቱም አንድ ቦታ ላይ በእኩል እይታ አስቀምጣቸው።
እናም ሰዎች በቀላሉ የሚነካኩት አበባ የትኛው ይመስልሀል?
- ፓስተር አብረሃም፦ ያልተሸፈነው አበባ እንደሆነ ግልጽ ነው።
- እኔም ፦ አዎ ትክክል ነህ። የተሸፈነው አበባ ምንም አይነት የሠው እጅ ስለማይነካው ሳይጠወልግ እንዳበበ ለረጅም ጊዜ መቆየት ይችላል። ነገር ግን ያልተሸፈነው አበባ ግን ያየውን ሰው ሁሉ በእጁ ስለሚነካካው ቶሎ የመጠውለግ እድሉ በጣም ሰፊ ነው።
ታድያ አላህን ፈርታ በጅልባብ የምትሸፈን የሆነች ሙስሊም ሴት ልጅ ልክ እንደዛኛው እንደተሸፈነው አበባ ስትሆን የጅልባብ ጥቅምም እንደዚሁ የአበባው ሽፋን ብጤ ነውና ከባለጌዎች አደጋ ይጠብቃታል። እናም እነኚህ ጨዋ ሙስሊም ሴቶች ሁለመናቸው ለባለቤታቸው ብቻ ነውና ለእርሱ ሁሌም እንዳበቡ ይኖራሉ።
በሌላው በኩል ደግሞ ሰውነቷን ገላልጣ የምትሄድ ሴትም ልክ እንደዛኛው እንደ ገላጣውና የመጣውን ሁሉ እንደሚጨልፈው እንደ ሚጠወልገው አበባ ስትሆን በማንኛውም ወንድ በየመንገዱ የመለከፏና በባለጌ ሰዎች ተይዛ የመደፈሯ እድሏ የበዛ ነው።
ክፍል - 8 ይቀጥላል
ሙሉውን መረጃ በተከታታይ ክፍል ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
t.me//AkeelComparative
ክፍል - 6
- የሴቶቹን ቁጥር መብዛት ከወንዶች ቁጥር ማነስ ጋር ለማመጣጠን፦
በአለማችን ላይ ከሚስተዋለው የሴቶች ቁጥር መብዛትና የወንዶቹ ቁጥር ከማነስ ጋር በተያያዘ ይህን ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት። የወንዶች ቁጥር ከሴቶች ቁጥር ጋር እኩል ቢሆን ኖሮ ከአንድ በላይ ሚስት የማግባት ጠቀሜታው ይህን ያህል የጎላ ፋይዳ አይኖረውም ይሆናል። ነገር ግን በአለም አቀፍ ደረጃ የወንዶች ቁጥር ከሴቶቹ ቁጥር አንጻር ሲነጻጸር የወንዶቹ በጣም አነስተኛ ነው። ለዚህም ደግሞ በዋነኛነት ከሚጠቀሱት ምክንያቶች መካከል፦
1ኛ) የጦርነት ሰለባዎች በአብዛኛው ወንዶች መሆን፦
በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ወንዶች አያሌ ሴቶችን ካለባል በማስቀረታቸው በሀገረ ጀርመን እነዚህ ባሎቻቸው እንደወጡ የቀሩባቸው ሴቶች በመደራጀት የጀርመንን መንግስት ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት እንዲፈቀድ ጥያቄ አቅርበው ነበር። ግን ቤተ-ክርስቲያን ጥያቄውን ውድቅ በማድረጓ ነገሩ በጅምሩ ቀረ። ምክንያቱም ባሏን የሞተባት ሴት እንድታገባ አይፈቀድም። የእስልምና ተግባር ግን የዚህ ተገላቢጦሽ ነው።
2ኛ) ወንዶች ከሴቶች ይልቅ በቀላሉ ለበሽታ የተጋለጡ በመሆናቸው
3ኛ) በማዕድን ቁፋሮና በሌሎች በአደገኛ ስራዎች ላይ በአብዛኛው የሚሳተፉ ወንዶች በመሆናቸው
4ኛ) ብዙ ሴቶች በህጻንነት የመሞት አደጋን ከወንዶች ይልቅ የመቋቋም ተፈጥሮ ስላላቸውና ወዘተ...
- የሴቶች የእርጠት ሁኔታን
ሴት ልጆች ከወንድ ልጆች አንጻር ስለእድሜአቸው አብዝተው ይጨነቃሉ። ወንድ ልጅ እድሜው ቢገፋም ልጅ የመውለድ አቅም በአብዛኛው አያጡም። የሴቶች ማህፀን ግን ከ35 አመት በላይ ልጅ የመሸከም ችሎታው እየመነመነ ይሄዳል። ስለዚህ በህይወትዋ አጋማሽ ገደማ ባል ማግኘት ያልቻለች ሴት ምንግዜም የምትመኘው ልጅ ወልዶ የመሳም እድል ሊያልፋት ይችላል። በዚህም ጊዜ አባት ልጅ ወልዶ መሣም ያምረዋልና ለዚህም ደግሞ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባትን አይነተኛው መፍትሄ ስለሆነ ሌላ ተጨማሪ ሚስት አግብቶ ልጅ የማግኘት እድሉ ያሰፋል። ነገር ግን በክርስትና እምነት አስተምህሮ መሠረት ከሆነ ይህ ጉዳይ የማይታሰብ ስለሆነ በባለትዳሮቹ መካከልም ፍቅር ጠፍቶ ፀብ ይፈጠራል በዚህም ምክንያት የግድ ለፍቺ ሲዳረጉ ይስተዋላል።
ታድያ ባሏን የሞተባትና በልጅ እጦት ምክንያትም ሆነ በሌላ ትዳሯን የፈረሰባት የሆነች አንዲት ክርስቲያን ሴት የመጀመሪያዋን ባል ከፈታች በኋላ ሌላ ባል አግብታ ትዳር ለመመስረት ቤተ-ክርስቲያን አይፈቅድላትም።
- #ኦሪት በዘሌዋውያን 21፥14
" #ባልዋ #የሞተባትን፥ ወይም #የተፋታችውን፥ ወይም ጋለሞታይቱን አያግባ፤ ነገር ግን ከሕዝቡ ድንግሊቱን ያግባ።"
- #ሕዝቅኤል 44፥22
"... የተፈታችውን አታግቡ።
- #1ኛ ቆሮ 7
፥10-11
"...ሴት ከባሏ አትፋታ፤ ከተፋታች ግን ሳታገባ ትኑር እንጂ አታግባ ወይም ትታረቅ
፥27 "...በሚስት ካልታሠርክ አታግባ።
፥38 "... ድንግል ያገባ መልካም አደረገ፤ ነገር ግን ያላገባ የተሻለ አደረገ።"
- በመጨረሻም
ሴቶችን የብቸኝነት ኑሮ እንዲገፉ የሚያደርግ ህግና ሐይማኖት ሰብዓዊ መብታቸውን መግፈፍ ነውና ሊኮነን ይገባል። እንዲሁም የአንድን ግለሠብ ተፈጥሯዊ አባት የመሆን ፍላጎቱ የሚነፍግ የሰብአዊ መብት ድንጋጌን በመጣሱ መወቀስ ይኖርበታል።
✔ እናም ፓስተር አብረሃም የሴቶችን መብት የሚጋፋው የእስልምና ሐይማኖት ነው ወይስ የክርስትና?
ክፍል - 7 ይቀጥላል
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት
(ኢስላም v/s ክርስቲያን) የሚለውን ቻናል ተቀላቀሉ t.me//AkeelComparative
ክፍል - 5
✔ መስፈርት
ከአንድ ሚስት በላይ ለማግባት ቁርዓን የሠጠው መስፈርት የገንዘብ መትረፍረፍን ሳይሆን በሚስቶች መካከል ሚዛናዊነት(ማስተካከል) እና ፍትህን ነው።
ይህም ማለት ሁሉም ሚስቶች በእኩል ማስተዳደር ማለት ለምሳሌ፦ ለሁላቸውም እኩል አስቤዛ፣አልባሳት፣ቤት፣መኪና፣ ጌጣጌጥ... ያለ አድሎ ማቅረብና ማከፋፈል ይኖርበታል።
ያ ካልሆነ ግን ሁለት ፣ ሶስት ፣ አራት ማግባት የሚሉት ነገር ከባድ ስለሆነና ከፍተኛም የሆነ አደጋ ስላለው አለማሰብ ነው የሚሻለው። ነገር ግን ሁሉንበም እኩል ደረጃ ማፍቀር ሊከብድ ይችላል። ለዚህም ደግሞ በሴቶች መካከልም ፍቅርን እኩል በሆነ መንገድ ለመስጠት አዳጋች መሆኑን በቁርዓን ተገልጿል።
4፡ 129
ولن تستطيعوا أن تعدلوا بين النساء ولو حرصتم ۖ فلا تميلوا كل الميل فتذروها كالمعلقة ۚ وإن تصلحوا وتتقوا فإن الله كان غفورا رحيما
በሴቶችም መካከል ምንም እንኳ ብትጓጉ (በፍቅር) ለማስተካከል አትችሉም፡፡ እንደ ተንጠለጠለችም አድርጋችሁ ትተዋት ዘንድ (ወደምትወዷት) መዘንበልን ሁሉ አትዘንበሉ፡፡ ብታበጁም ብትጠነቀቁም አላህ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡
ይህም ማለት አንዷ ጋር በፍቅር በመክነፍ ሌላዋን በአየር ላይ እንደምትንሳፈፍ ፊኛ አታድርጓት ነው። ስሜትህን ገታ አድርገህ ሁለቱንም ጋር ለማስተካከል መጣር ነው ያለብህ እንጂ ከአንደኛዋ ጋር አለምህን እየቀጨህ ሌላኛዋን ችላ በማለት ዞር ብለህ ማታያት ከሆነ አደጋ ውስጥ ነው ያለኸው። ለዚህም ነው "ብታበጁም ብትጠነቀቁም አላህ መሀሪ አዛኝ ነው "ያለን።
እንዲህ ማድረግን ወይም ማስተካከልን አይሆንልኝም በማለት የፈራ ሰው ግን በተከታዩ የቁርዓን አንቀፅ ተገልጿል፦
4፥ 3
>>... ۖ فإن خفتم ألا تعدلوا فواحدة أو ما ملكت أيمانكم ۚ ذلك أدنى ألا تعولوا
"...አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡"
ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ፦
" አንድ ሰው ሁለት ሚስቶች ቢኖሩትና ወደ አንደኛዋ ይበልጥ ቢያዘነብል(ቢያደላ) በትንሳኤ ቀን ከፊል አካሉ በድን ሆኖ ይነሳል።"
✔ ከአንድ በላይ የማግባት ጉዳትና ጠቀሜታው፦
- እስከ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ከአንድ በላይ ማግባት በአውሮፓ የተለመደ እና ቤተ- ክርስቲያንም ምንም ተቃውሞ ሳታሰማ ቆይታለች። ከዚያ በኋላ ግን ቤተ-ክርስቲያን በግዛቷ ስር የነበሩትን አገሮች ከአንድ በላይ ሚስት ያገቡ ወንዶችን አንዲት ብቻ በማስቀረት ሌሎቹን እንዲፈቱ የሚያሳስብ አዋጅ አወጣች። (Lari,Mujtaba, Western Civilizatation through Muslim Eyes, P.112) ይህ ውሳኔ የተፈፃሚነት አግኝቷል። ነገር ግን ሴቶችን ህጋዊ ወዳልሆነ ፈቃደ ስጋና ከዚያም ወደ ዝሙት በመጨረሻም ወደ ሴተኛ አዳሪነት አዘቅጥ ውስጥ እንዲዘፈቁ አድርጓቸዋል።
- ተፈጥሯዊ ወደሆነው የወንድና የሴት ግንኙነት ማለትም (ፖሊጋሜ) መመለስ ለሴተኛ አዳሪነት ፣ ለአባላዘር በሽታዎች፣ ለውርጃ ፣ ህጋዊ ያልሆኑ ልጆች ስለሚደርስባቸው ሰቆቃ ፣ ከፆታ አለመመጣጠን የተነሳ የተፈጠረው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ያላገቡ ሴቶች ችግር ፣ ለዝሙት ፣ ለቅናትና ለመሳሰሉት ማህበራዊ መሠናክሎች ይዳርጋልና ከአንድ በላይ ማግባት ለነዚህና ለሌሎችም ችግሮች አይነተኛ መፍትሄ ነው።(Islam an Introduction, Bawany, P.192)
ክፍል - 6 ይቀጥላል
ክፍል- 4
ምነው ታድያ ከቀደምት ነቢያት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ከአንድ በላይ የማግባት ህግ ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሲደርስ አራት ማግባትን መፈቀዱ በክርስትና እምነት ዘንድ እንዲህ ወንጀልና አስነዋሪ ጉዳይ ሆነ? ለመሆኑ እየሱስ ከመጣ በኋላ የድሮውን ህግ ተሽሯልን? ወይንስ ነቢያት ተሽረዋል? ለመጥፋትና ለመጠመድ ነው እንጂ እየሱስማ ህግ ለመሻር አልመጣሁም ይላል፦
- #የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 5
17፤ #እኔ #ሕግንና #ነቢያትን #ለመሻር #የመጣሁ #አይምሰላችሁ፤ #ልፈጽም #እንጂ #ለመሻር #አልመጣሁም።
18፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ #ከሕግ #አንዲት #የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ።
19፤ እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት #ትእዛዛት #አንዲቱን #የሚሽር #ለሰውም #እንዲሁ #የሚያስተምር #ማንም #ሰው #በመንግሥተ #ሰማያት #ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል።
እየሱስ መጥቶ ካረገ በኋላ የክርስትናን እምነት (እንደብልሀተኛ አናጺ መሠረትን መሠረትሁ የሚለው (1ኛ ቆሮ 3፥10)) ጳውሎስ ከእግዚአብሔር ትዕዛዝ ውጪ በራሱ ስልጣን ካወጣቸው የተለያዩ ህጎች መካከልም ስለዚህኛው የትዳር ጉዳይ ከብዙዎች አዋጆቹ ውስጥ አንዱ ሲሆን ለክርስትና ሐይማኖት ተከታዮችም እንኳንስ ከአንድ በላይ ማግባት ይቅርና ጭራሽ ሳያገቡ እንዲኖሩ እንዲህ በማለት ያዛቸዋል።
- #1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 7
6፤ ዳሩ ግን ይህን #እንደ #ፈቃድ #እላለሁ #እንጂ #እንደ #ትእዛዝ #አይደለም።
7፤ ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁና፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ።
8፤ ላላገቡና ለመበለቶች ግን እላለሁ። #እንደ #እኔ #ቢኖሩ #ለእነርሱ #መልካም ነው፤
9፤ ነገር ግን #በምኞት #ከመቃጠል #መጋባት #ይሻላልና #ራሳቸውን #መግዛት #ባይችሉ ያግቡ።
ለዚህም ነው በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆኑ ሴት እህቶቻችን ሳያገቡና ትዳር ሳይመሠርቱ የወጣትነት እድሜያቸውን ያለትዳር ቆርጥመውት ወደ እርጅና የሚያመሩት ።
ክፍል -5 ይቀጥላል
ክፍል -3
በመጀመሪያ ደረጃ ሰባት ሴት ይፈቀዳል ያልከው አሉባልታና መሠረት የሌለው ወሬ በራሱ ስህተት ነው። ምክንያቱም ከአራት በላይ ማግባት እንደማይቻል በሐዲስ ተረጋግጧል። ይኸውም፦
1) ኸይላን ሰቀፍይ አስር ሚስቶች የነበሩት ሲሆን ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ከአስሩ አራቱን ብቻ እንዲመርጥ አዘውታል።
2) በተመሣሣይ ሁኔታ ሀሪስ ኢብን ቀይስም ከስምንት ሚስቶቹ ጋር በሠለመበት ወቅት አራቱን መርጦ እንዲያስቀር በነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ታዟል።
ከአንድ እስከ አራት ሴቶች ማግባት እንደሚፈቀድ ደግሞ በቁርዓን እንዲህ ተገልጿል ፦
4፡ 3
وإن خفتم ألا تقسطوا في اليتامى فانكحوا ما طاب لكم من النساء مثنى وثلاث ورباع ۖ فإن خفتم ألا تعدلوا فواحدة أو ما ملكت أيمانكم ۚ ذلك أدنى ألا تعولوا
በየቲሞችም (ማግባት) አለማስተካከላችሁን ብትፈሩ (ዝሙትንና ከተወሰነላችሁ በላይ ማግባትንም ፍሩ)፡፡ ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት ሦስት ሦስትም አራት አራትም አግቡ፡፡ አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡
- ጄ.ኤ.ክሌር <<ዘ ኬዝ ፎር ፖሊጋሜ>> በተሰኘው መፅሐፋቸው እንደጻፉት " ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ከማህበራዊ ግንኙነት ፣ ከግብረ ገብነትም ሆነ ከሐይማኖት አንጻር ስንመለከተው የሠው ልጅ ካለበት የስልጣኔ ደረጃ ተጻራሪ አለመሆኑን በተጨባጭ ማሳየት ይቻላል። ከአንድ በላይ ማግባት ለተቸገሩና ትዳር ለሌላቸው ሴቶች አይነተኛ መድሐኒት ነው። ይህን ካልተቀበልን ግን ያለው ምርጫ የሴተኛ አዳሪዎችን ፣ የጎዳና ወይዛዝርትን ፣ የእቁባቶችን(ውሽማ) ፣የጋለሞታዎችንና የሴተ ላጤዎችን አሀዝ መጨመር ነው።" ብለዋል።
ታድያ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት በቁርዓን ህግ ብቻ የተፈቀደ ሳይሆን ከነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) በፊት በነበሩ አያሌ ነቢያት ህግጋትም የፀደቀ ነበር። ለብዙዎች ነቢያትም ከሁለት በላይ ሚስቶች ነበሯቸው። ለአብነትም ያክል
- ለሰለሞን = 700 ሚስቶችና 300 ቁባቶች ነበሩት
- ለአብረሀም = 2 ሚስቶች ነበሩት
- ለዳዊት = 2 ሚስቶች ነበሩት
- ለሮብዓም = 18 ሚስቶችና 60 ቁባቶች ነበሩት
- ለአብያም = 14 ሚስቶች ነበሩት
- #መፅሐፈ ነገስት ቀዳማዊ 11፥3
" ለእርሱም(ለሰለሞን) ወይዛዝር የሆኑ #ሰባት #መቶ (700) ሚስቶች #ሦስት #መቶም (300) ቁባቶች ነበሩት፤ ሚስቶቹም ልቡን አዘነበሉት። "
- #ዘፍጥረት 16፥3
" አብረሐምም ሳራና ግብጻዊት የሆነችና ስሟንም አጋር የተባለች #ሁለት #ሚስቶች ነበሩት።
- #መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 25፥43
" ዳዊትም ደግሞ ኢይዝራኤላዊቱን አኪናሆምን ወሰደ፤ #ሁለቱም ሚስቶች ሆኑለት።"
- #መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 11፥21
" ሮብዓምም ከሚስቶቹና ከቁባቶቹ ሁሉ ይልቅ የአቤሴሎምን ልጅ መዓካን ወደደ፤ አሥራ ስምንትም (18) ሚስቶችና ስድሳ ቁባቶች ነበሩት፥ ሀያ ስምንት ወንዶችና ስድሳ ሴቶች ልጆች ወለደ።"
- #መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 13፥21
" አብያም ጸና፥ #አሥራ #አራትም (14) ሚስቶች አገባ፥ ሀያ ሁለትም ወንዶች ልጆችንና አሥራ ስድስት ሴቶች ልጆችን ወለደ። "
ክፍል - 4 ይቀጥላል
ክፍል -2
- እኔም፦ የእስልምናን አስተምህሮ ለምን ጠላኸው? እስልምናን እንድትጠላው ያደረገህ ምክንያትህ ምንድ ነው? አልኩት።
- ፓስተሩም ፦ እስልምናን እንድጠላው ያደረገኝ ሁለት ምክንያቶች አሉኝ" አለ
1ኛ) በእስልምና ሰባት ሴቶችን ማግባት ይፈቀዳል
2ኛ) ሴቶች ተሸፋፍነው እንጂ ተገልጠው እንዲሄዱ አይፈቅድም።ስለዚህ የሴቶችን መብት ይጋፋል" አለኝ።
- እኔም ፦ ሌላስ አልኩት።
- ፓስተሩም፦ ሌላ ነገሩ እንኳን አያስጠላኝም ነገር ግን ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየኝ ምንም ነገር የለም" አለኝ።
- እኔም ፦ እርግጠኛ ነህ በነዚህ ሁለት ምክንያት ብቻ ነው እስልምናን የምትጠላው? አልኩት።
- ፓስተሩም ፦ " አዎ እነዚህ በቂ ምክንያቶቼ ናቸው፤ ከነዚህ የበለጠ ምክንያት ምን አለ? አንድ ወንድ እንዴት ሰባት ሴት ያገባል?" አለኝ።
- እኔም፦ በጣም ገርሞኝ የሱረቱል ካፍን የመጀመሪያው አንቀጽ ትዝ ብሎኝ ቀራሁት።
18፡ 1
بسم الله الرحمن الرحيم الحمد لله الذي أنزل على عبده الكتاب ولم يجعل له عوجا ۜ
"ምስጋና ለአላህ ለዚያ መጽሐፉን በውስጡ መጣመምን ያላደረገበት ሲሆን በባሪያው ላይ ላወረደው ይገባው፡፡"
የቁርዓኑን ትርጉም ከነገርኩት በኋላ፦ አየህ አብርሽ! እስልምና ልተቸው ብትል እንኳን መተቸት አትችልም፤ እስልምና ለመተቸት ራሱ አይመችም። ቁርዓን ውስጥ ምንም አይነት የርስ በርስ የሐሳብ ግጭት፣ የትርጉም መጣመም፣... ልታገኝ አትችልም። ብዙዎች እስልምናን በመጥላት ሐይማኖቱን ለመተቸት ብለው ቁርዓን ማንበብ ይጀምሩና በዚያው ሰልመው ይቀራሉ። አንድም ነገር እንድትጠላው አያደርግህም። በአንጻሩ በመፅሐፍ ቅዱሳችሁ ውስጥ ያለው የሐሳብ መጋጨት ግን አካል ኖሮት ቢንቀሳቀስ ኖሮ ምድራችን አልቆለት ነበር።
ወደ አንተዎቹ ጥላቻዎች ልመለስና እስልምና ሰባት ሴት ማግባት ስለሚፈቅድ እምነቱን እጠላዋለሁ ብለሀል።
ክፍል-3 ይቀጥላል
.
ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት
( እስልምና v/s ክርስትና )
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አብረሐም ይባላል የአንድ ሰፈር ልጆችና አብሮ አደጎችም ነን። ፓስተር አብረሐም ሻኪሶ በሚባል ክፍለ ሀገር ላይ የክርስትና እምነት አስተማሪ ወይም ሰባኪ ነው እናም ከተገናኘን ረጅም ጊዜ ሆኖናል።
ታድያ አጋጣሚ ሆነና እሱ ለመስቀል በዓል አገር ቤት በገባበት እኔ ደግሞ ለጉዳዬ በሄድኩበት በአጋጣሚ ተገናኝተንም ለአንድ ሳምንት ያክል አብረን ነበርንና ከእለታት አንድ ቀን "እየሱስ አምላክ ነው ብለህ እንድታምነውና እንድታመልከው ያስቻለህ ጉዳይ ምን እንደሆነ በመፅሐፍ ቅዱስ ከእየሱስ አንደበቶች ንገረኝ" ስል ጠየቅኩት። ያው የሁላቸውንም ምላሽ በተለመደው መልኩ "እኔና አብ አንድ ነን፣እውነትም መንገድም እኔ ነኝ..." ብሎ የተናገራቸውን ንግግሮች አነሳልኝ። እኔም የሱን ማብራሪያዎችና እየሱስ አምላክ እንዳለሆነም የሚጠቁሙ ብዙ መረጃዎች አቀረብኩለት። ማመን አልፈለገም እንጂ በመረጃዎቹ ተሸንፏል ታድያ እኔ ደግሞ አስተማሪ እንደመሆኑም ጀነራል ወደሆነ ነገር ልውሰደው ብዬ "ወደ ፍጥረታት አፈጣጠር"
መራሁትና
- እኔም፦ ሰማይና ምድር፣ መላዕክት ፣ እንስሳት...ማን ፈጠራቸው? አልኩት።
- ፓስተሩም፦ ሰማይና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት እየሱስ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሁሉን ስለእርሱ ተፈጥረዋል። ( ወደ ቆላስይስ 1፥15-16) አለኝ።
-እኔም፦ መልሼ እየሱስ እኮ የተወለደው የዛሬ 2000 አመት አካባቢ ነው፤ እንደ አንተ አባባል ከሆነ እየሱስ ፍጥረታትን ከፈጠረ በኋላ ወደ ማህፀን ውስጥ ገብቶ ነው ድጋሚ የተወለደው? አልኩት። ፓስተሩ ግራ ገብቶት መልስ ከየት ያምጣ
- እኔም፦ በዚህ ጊዜ ትንቢተ.ኢሳያስ 44፥24ን አነሳሁለት።
✔ ትንቢተ ኢሳያስ 44፥24
"... ሁሉን የፈጠርሁ፤ ሰማያትን ለብቻ የዘረጋሁ ምድርንም ያፀናሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ ፤ከእኔ ጋር ማን ነበረ? ይላል እግዚአብሔር።
ስለዚህ እግዚአብሔር ብቸኛው ፈጣሪ እኔ ነኝ ከኔ ጋር ማንም አልነበረም ይላልና ራስህን ፈልገህ እንድታገኝ ከቁርዓን አንዳንድ ነገሮች ብነግርህ ፈቃደኛ ነህ ወይ? አልኩት።
- ፓስተሩም ፦ "በእየሱስ ስም! መቼም ቢሆን የእስልምናን አስተምህሮ ማወቅ አልፈልግም " አለኝ።
.
#ጳውሎስ #ለአምላክ #የማይታዘዝና
#ለፍጡራን #የሚገዛ ሰው መሆኑን
@@@@@@@@@@@@@@@@
ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
ሀ) እግዚአብሔርን የሚታዘዝ አዕምሮ
እንዲፈርስ አደርጋለሁ!
ለ) ፅድቅ የሚገኘውና መዳን የሚገኘው
እግዚአብሔርን ባለመታዘዝ ነው!
ከዚህ ቀደም ክፍል ላይ ስለ ስግደት፣ መታዘዝና የጣኦት ትርጉም ምን እንደሆነ እንደሆነ እንዲሁም ጳውሎስ ጣኦት አምላኪ ሰው መሆኑን አይተን ነበር። ቀጥሎም በዚህ ክፍል ጳውሎስ ለአምላክ የማይታዘዝ ነገር ግን ለፍጡራን የሚታዘዝና እነርሱንም የሚገዛ ሰው መሆኑን እንመለከታለን።
ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረውና ሁሉን አስተናባሪ የሆነው ፈጣሪ አምላክ በብቸኝነት ሊመለክ የሚገባው አምላክ ነውና ከዚህ ውጪ የሚመለኩት ደግሞ በሙሉ ጣኦታት ናቸው።
ጣኦታት ሲባሉም ደግሞ በባህርያቸው አንዳች ሲሳይ ሊሰጡ የማይችሉ እንዲሁም ምንንም ነገር ሊፈጥሩ የማይችሉ የሆኑ ፍጡራኖች ናቸው።
ለዚህም አላህ(ሱ.ወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦
16፡ 73
ويعبدون من دون الله ما لا يملك لهم رزقا من السماوات والأرض شيئا ولا يستطيعون
ከአላህም ሌላ ከሰማያትም ከምድርም ምንንም ሲሳይ የማይሰጧቸውን (ምንንም) የማይችሉትንም ይግገዛሉ፡፡
22፡ 73
يا أيها الناس ضرب مثل فاستمعوا له ۚ إن الذين تدعون من دون الله لن يخلقوا ذبابا ولو اجتمعوا له ۖ وإن يسلبهم الذباب شيئا لا يستنقذوه منه ۚ ضعف الطالب والمطلوب
እናንተ ሰዎች ሆይ! አስደናቂ ምሳሌ ተገለጸላችሁ፡፡ ለእርሱም አድምጡት፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትግገዟቸው (ጣዖታት) ዝንብን ፈጽሞ አይፈጥሩም፡፡ እርሱን (ለመፍጠር) ቢሰበሰቡም እንኳን (አይችሉም)፡፡ አንዳችንም ነገር ዝንቡ ቢነጥቃቸው ከእርሱ አያስጥሉትም፡፡ ፈላጊውም ተፈላጊውም ደከሙ፡፡"
ታድያም በጳውሎስ የአምልኮ ስርዓት ውስጥ ለዚህ ለሀያሉ ፈጣሪ አምላክ ከመታዘዝ ይልቅ ምንም ሊጠቅሙና ሊጎዱ የማይችሉትን ግኡዝ አካላት መታዘዝን እንደ #ጽድቅ #አምልኮ #ይቆጠራል። እንዴት የሚለውን ቀጥሎ እንመልከት
1.1 የጳውሎስ የአለመታዘዝ አምልኮ
ሀ) መታዘዝ ማለት ለአንድ ፈጣሪ አምላክ ራስን ማስገዛት ማለት ሲሆን አለመታዘዝ ማለት ደግሞ ፈጣሪ አምላክን በመካድ ሁለመናን ለፍጡራን ወይም ለጣኦታት መስጠት ማለት ነው። እናም ጳውሎስ #እግዚአብሔርን #የሚታዘዝ #አዕምሮ #እንዲፈርስ #አድርጌ #ሰዎች #ክርስቶስ #ብቻ #እንዲታዘዙ #አደርጋለሁ፥ ከዛም ደግሞ #አንታዘዝም ይላል፦
- 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፥ 5-6
" የሰውንም ሀሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሳውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አዕምሮን ሁሉ እንማርካለን፥ መታዘዛችሁም በተፈፀመች ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ልንቀበል ተዘጋጅተናል።"
ለ) በማስከተልም ፅድቅና ምህረት የሚገኘው #እግዚአብሔርን #ባለመታዘዝ #ነው ሲል #መዳን #የሚፈልግ #ሰው #ካለ #አለመታዘዝን #መምረጥ አለበት እንዲሁም ደግሞ የማይታዘዝ ሰው ሹመት ሊያገኝ ይገባል በማለት ጳውሎስ ይናገራል። ለዚህም ደግሞ ይህ ሰው እንዲህ ይላል፦
- ወደ ሮሜ ሰዎች 11፥ 30-32
" እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር እንዳልታዘዛችሁ አሁን ግን ካለመታዘዛችሁ የተነሳ ምህረት እንዳገኛችሁ፥ እንዲሁ በተማራችሁበት ምህረት እነርሱ ደግሞ ምህረትን ያገኙ ዘንድ እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም። እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን ባለመታዘዝ ዘግቶታል።
- ወደ ቲቶ 1፥6
" ስለ አለመዳራትም ወይም ስለ አለመታዘዝ የማይከስ ማንም ቢኖር ሹመው።"
- ወደ ዕብራውያን 2፥2
" መተላለፍና አለመታዘዝም ሁሉ የፃድቃን ብድራት ከተቀበለ፥ እኛስ እንዲህ ያለውን ታላቅ መዳን ቸል ብንለው እንዴት እናመልጣለን? " በማለት ይናገራል!!።
✔ እናም ጳውሎስ ለአምላክ ታዛዥ ስላልሆነ ይህን ይበል እንጂ እግዚአብሔር ግን እርሱን ስለመታዘዝ በተመለከተ እንዲህ ይላል፦
- ትንቢተ ኢሳያስ 1፥19
" እሺ ብትሉ እኔንም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ።"
- ኦሪት ዘዳግም 27፥10
" ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ቃል ታዘዝ፥ ዛሬም የማዝህን ትዕዛዙና ስርዓት አድርግ።"
- መፅሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 15፥ 22
" መታዘዝ ከመስዕዋት ይበልጣል።" ይላል!!
በዚህም መሠረት ጳውሎስ ለአምላክ የማይገዛና የማይታዘዝ ሰው ነበረ ማለት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative
7፡138
وجاوزنا ببني إسرائيل البحر فأتوا على قوم يعكفون على أصنام لهم ۚ قالوا يا موسى اجعل لنا إلها كما لهم آلهة ۚ قال إنكم قوم تجهلون
<< የእስራኤልም ልጆች ባህሩን አሻገርናቸው፥ ለእነርሱ በሆኑ ጣኦታት (መገዛት) ላይ በሚዘወትሩ ህዝቦች ላይ አለፉም። < ሙሳ ሆይ፦ ለእነርሱ (ለሰዎቹ) አማልክት እንዳላቸው ለእኛም አምላክን አድርግልን> አሉት። እናንተ የምትሳሳቱ ህዝቦች ናችሁ > አላቸው።
የዚህ ነገር ጉዳዩም እንዲህ ነበር፦ ሙሴ ወይም ሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦቻቸውን ከግብፅ ምድር ከፊራኦን እጅ አውጥተው ወደ ሀገራቸው በመሄድም ላይ ሳሉ በመንገዳቸው ጥልቅ የተንጣለለ የባህር ውሃ ገጠማቸው። የፊራኦን ሰራዊት ከኋላቸው ይከተላቸው ስለነበረ በጣም ተጨነቁ፤ በዚህም ጊዜ አላህ(ሱ.ወ) ለሙሳ(ዓ.ሰ) በያዝከው በትር ባህሩን ምታው ሲላቸው ሙሳም(ዓ.ሰ) በያዙት በትር ባህሩን ሲመቱት ያንን ተንጣልሎ የተኛውን ባህር መሀል ለመሀል ተገመሶም ተከፈለ። በዚህም ጊዜ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች በተከፈለው ባህር ውስጥ ሊሻገሩ ገቡ፤ የፊራኦንንም ሰራዊት በሙሉ እነርሱንም ተከትለው በተከፈለው ባህር ውስጥ ገቡ።
ታድያ በዚህም ጊዜ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች ሁሉንም ባህሩን አቋርጠው ጨርሰው እንደወጡና እንዲሁም የፊራኦንንም ሰራዊት ሁሉንም ጨርሰው በተከፈለው ባህር ውስጥ ከገቡም በኋላ መሀል ለመሀል ተከፍሎ እንደ ተራራ በግራና በቀኝ ቆሞ የነበረውን የባህር ውሃ ቀድሞ ወደነበረበት ቦታ ተመለሠ። ያኔም ፊራኦን፣ ባለስልጣናቱ( እነ ሀማንና ሌሎቹንም ጨምሮ) እንዲሁም የፊራኦንን ሰራዊት በሙሉ በባህሩ ውስጥ ሰጥመው የባህር ውስጥ ስጋ ተመጋቢ ፍጡራን ሲሳይ ሲሆኑ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች ግን ከዚህ ጉድ በተዓምር ተርፈውም ወደ አገራቸው ጉዞ ቀጠሉ።
ከረጅም ጉዞ በኋላም በጡር ተራራ ጎንም በሰፈሩ ጊዜ ለሙሳ(ዓ.ሰ) አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ሊፆሙ ከአላህ ዘንድ ለቀጠሮ ተጠሩ። ታድያ ህዝቦቹ ለሙሳ(ዓ.ሰ) ከግብፅ ያወጣን አምላክህ አንድ አይደለምና ለእኛም ሌሎች አማልክት ስራልን በማለት ይነዘንዟቸው ነበር። እናም ሙሳ(ዓ.ሰ) ከአላህ(ሱ.ወ) ጋር ሊነጋገሩ ወደ ተራራው በወጡ ጊዜ እነዚያ የሙሴ ህዝቦች ግን ለአንድ ሳምራዊ አማልክት ስራልን አሉት። እርሱም የወርቅ፣ የብርና ሌሎችም ጌጣጌጦችን ሰብስባችሁ አምጡልኝ አላቸው፥
እነርሱም የጆሮና የእጅ የተለያዩ ጌጣጌጦቻቸውን ሰብስበው ለሳምራዊው አመጡለት። አንድ ላይ አድርገው እሳት ውስጥም ጨመሩት። በዚህም ጊዜ ጥጃ የሚመስል መልክ ያለው ነገር ከእሳቱ ወጣላቸው። እነዚያንም ሰዎች ከግብፅ ያወጡን አማልክቶቻች እነዚህ ናቸው በማለት ጣኦት ማምለክ ጀመሩ። ለዚህም ሙሉ ማስረጃ ፦
ከቅዱስ ቁርዓን ፦ 2፥ 49-57 ፣ 7፥ 103-155 ፣ 20፥ 77- 98 ፣ 28፥ 6-50 ከብዙ በጥቂቱ
ከመፅሐፍ ቅዱስም ፦ የሐዋርያት ስራ 7፥20-46፣ ኦሪት ዘዳግም 9&10, ዘፀአት 13፥ 18-22, 14፥ 1-31, 15፥ 4-27 ፣ ኦሪት ዘሀልቅ 21፥ 4-20 ከብዙ በትንሹ
እናም ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ ሲል
ኑፋቄ ማለት " የዋጃቸውን ጌታ ክደው ፈጥኖ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ" መባሉን መረሣት የለበትምና (ይህም ማለት በጣኦት ማመን ማለት ነው) እንዲሁም ከግብፅ ምድር የወጡት የጳውሎስ ቀደምት አባቶች ከሙሳ አምላክ ውጪ የሆነን ባዕድ አካል ማምለካቸውን ይታወሳልና በዚህም ደግሞ እነርሱ ያመለኩት አካልም ጳውሎስ ያመልከዋል ማለት ነው።
- ትንቢተ ሆሴዕ 13፥2
" በብራቸው ለራሳቸው ቀልጦ የተሠራውን ምስል፥ እንደጥበባቸውም ጣኦታት ሰርተዋል። ሁሉንም የሠራተኛ ስራ ናቸው፤ ስለእነርሱም የሚሰው ሰዎች እምቦሳውን ይሳሙ ይላል።"
ከዚህ ጋር ተያይዞ አንድ ክርስቲያን <<አይ ይህ ነገር ልክ አይደለም ጳውሎስ እየሱስን ነው የሚያመልከው>> ሊል ይችላል። ነገር ግን እንዲህም ቢሆን እንኳን የጳውሎስ አምልኮ ያው ነው አይለወጥም።ለዚህም ደግሞ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
- 1ኛ ወደቆሮንቶስ ሰዎች 10፥ 1-4
" ወንድሞች ሆይ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባህር መሀከል ተሻገሩ፥ ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመና በባህር ተጠመቁ፥ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፥ ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ አለት ጠጥተዋልና ያም አለት #ክርስቶስ #ነበረ ።"
ታድያም የጳውሎስ አባቶች ያመልኩት እንደነበረው በኑፋቄ መንገድ ማምለክም ሲባል በጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ጳውሎስም እነርሱ እንዳመለኩ እንዲሁ ያመልካልና በዚህም ጳውሎስ ጣኦት አምላኪ ሰው ነው ማለት ነው።
ቀደምት ነቢያት ግን አንድ አምላክ(አሏህን) ያመልኩ የነበረ ሙስሊም ነበሩ እንጂ ማናቸው ቢሆን ክርስቲያንም ይሁን አይሁድ አልነበሩም። ለዚህም ደግሞ አሏህ(ሱወ) በቁርዓን 2፡140 ላይ ይናገራል።
