en
Feedback
እስልምና እና ክርስትና

እስልምና እና ክርስትና

Open in Telegram

t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!

Show more
315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
" የእግዚአብሔርም ማኅተም በግምባራቸው ከሌለባቸው ሰዎች በቀር በምድር ያለውን ሣር ቢሆንም ወይም ማናቸውንም የለመለመ ነገር ወይም ማናቸውንም ዛፍ እንዳይጐዱ ተባለላቸው።" (የዮሐንስ ራእይ 9:4) 👉 በወንጌል ላይ ስለ የፊት ኑሩ የትንቢት ምልክት እና ስለሙስሊሞቹም ጉዳይ በቁርዓን እንደተገለፀው ሁሉ እየሱስ #አትክልት #በተከለ #ገበሬ #አስመስሎ በምሳሌ የተናገረ ሲሆን እርሱም እንዲከተሉ ወይም እየሱስ ተልኮላቸው የነበሩት አይሁዶችም ስለከዱት ነበር በምሳሌ እንዲህ ብሎ የተናገረው ፦ - የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 21) 33፤ ሌላ ምሳሌ ስሙ። የወይን አትክልት የተከለ ባለቤት ሰው ነበረ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 34፤ የሚያፈራበትም ጊዜ ሲቀርብ፥ ፍሬውን ሊቀበሉ ባሮቹን ወደ ገበሬዎች ላከ። 35፤ ገበሬዎቹም ባሮቹን ይዘው አንዱን ደበደቡት አንዱንም ገደሉት ሌላውንም ወገሩት። 36፤ ደግሞ ከፊተኞች የሚበዙ ሌሎች ባሮችን ላከ፥ እንዲሁም አደረጉባቸው። 37፤ በኋላ ግን። ልጄንስ ያፍሩታል ብሎ ልጁን ላከባቸው። 38፤ ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ እርስ በርሳቸው። ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ፥ እንግደለውና ርስቱን እናግኝ ተባባሉ። 39፤ ይዘውም ከወይኑ አትክልት አወጡና ገደሉት። 40፤ እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ በሚመጣ ጊዜ በእነዚህ ገበሬዎች ምን ያደርግባቸዋል? 41፤ እነርሱም። ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፥ የወይኑንም አትክልት ፍሬውን በየጊዜው ለሚያስረክቡ ለሌሎች ገበሬዎች ይሰጠዋል አሉት። - የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 13) 24፤ ሌላ ምሳሌ አቀረበላቸው እንዲህም አለ። መንግሥተ ሰማያት በእርሻው መልካም ዘርን የዘራን ሰው ትመስላለች። 25፤ ሰዎቹ ሲተኙ ግን ጠላቱ መጣና በስንዴው መካከል እንክርዳድን ዘርቶ ሄደ። 26፤ ስንዴውም በበቀለና በአፈራ ጊዜ እንክርዳዱ ደግሞ ያን ጊዜ ታየ። 27፤ የባለቤቱም ባሮች ቀርበው። ጌታ ሆይ፥ መልካምን ዘር በእርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን? እንክርዳዱንስ ከወዴት አገኘ? አሉት። 28፤ እርሱም። ጠላት ይህን አደረገ አላቸው። ባሮቹም። እንግዲህ ሄደን ብንለቅመው ትወዳለህን? አሉት።

. #በመፅሐፍ_ቅዱስ የሙስሊሞቹ #የፊት #ኑር ትንቢት ለሙሐመድ(ሰዐወ) እና ለተከታዮቻቸው ስለመነገሩ ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ ሶላት በመስገድም(በሰጋጅ ሙስሊሞች) ላይ የሚታየው የፊት ኑርን በተመለከተ በኦሪት እና በወንጌል የተነገረ ትንቢት ሲሆን ይህም ደግሞ ስለነብዩ ሙሐመድ(ሰዐወ) መምጣትና ስለተከታዮቻቸው ሙስሊሞችም ፀባይ የተነገረ ድንቅ የምልክት ትንቢት ነው። ምልክቱም በግምባራቸው ይሆናል ይላል፦ - የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 22 3፤ ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ #ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ ፊቱንም ያያሉ፥ 4፤ #ስሙም #በግምባሮቻቸው #ይሆናል። 5፤ ከእንግዲህም ወዲህ ሌሊት አይሆንም፥ ጌታ አምላክም በእነርሱ ላይ ያበራላቸዋልና የመብራት ብርሃንና የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም፤ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣሉ። በኦሪትና በወንጌል መፃህፍት ላይ ስለዚህ የሙስሊሞች የፊት ኑር ጉዳይ ትንቢት ስለመነገሩ በቁርዓን እንዲህ ተገልጿል ፦ 48፡ 29 محمد رسول الله ۚ والذين معه أشداء على الكفار رحماء بينهم ۖ تراهم ركعا سجدا يبتغون فضلا من الله ورضوانا ۖ سيماهم في وجوههم من أثر السجود ۚ ذلك مثلهم في التوراة ۚ ومثلهم في الإنجيل كزرع أخرج شطأه فآزره فاستغلظ فاستوى على سوقه يعجب الزراع ليغيظ بهم الكفار ۗ وعد الله الذين آمنوا وعملوا الصالحات منهم مغفرة وأجرا عظيما የአላህ መልክተኛ ሙሐመድ እነዚያም ከእርሱ ጋር ያሉት (ወዳጆቹ) በከሓዲዎቹ ላይ ብርቱዎች በመካከላቸው አዛኞች ናቸው፡፡ አጎንባሾች፣ ሰጋጆች ኾነው ታያቸዋለህ፡፡ ከአላህ ችሮታንና ውዴታን ይፈልጋሉ፡፡ #ምልክታቸው #ከስግደታቸው #ፈለግ #ስትኾን #በፊቶቻቸው #ላይ #ናት ፡፡ ይህ በተውራት (የተነገረው) ጠባያቸው ነው፡፡ በኢንጂልም ውስጥ ምሳሌያቸው ቀንዘሉን አንደአወጣ አዝመራና፣ (ቀንዘሉ) እንዳበረታው፣ እንደወፈረምና፣ ገበሬዎቹን የሚያስደንቅ ኾኖ በአገዳዎቹ ላይ ተስተካክሎ እንደ ቆመ (አዝመራ) ነው፡፡ (ያበረታቸውና ያበዛቸው) ከሓዲዎችን በእነርሱ ሊያስቆጭ ነው፡፡ አላህም እነዚያን ያመኑትንና ከእነርሱ በጎዎችን የሠሩትን ምሕረትንና ታላቅ ምንዳን ተስፋ አድርጎላቸዋል፡፡ ታድያ የዚህ ጉዳይ በመፅሐፍ ቅዱስ በምን መልኩ ተጠቅሷል? የሚለውን እንመልከት፦

📝በኢስላም መሠረታዊ ክንውኖች አምስት መስፈርቶች ተቀምጧል። 1) ፈርድ (ግዴታ) መፈፀም ብቻ 2) ሙስተሀድ ( የሚወደድ) 3) ሙባህ ( በምርጫ የሚወሰድ) 4) መክሩም (የሚጠላ) 5) ሐራም ( የተከለከለ) ✅ ፈርድ (ግዴታ) - ይህ ማለት አንድ ሰው ፈርድ የሆነን ነገር መፈፀም ግዴታው ሲሆን ቢያከናውን ሚንዳ ያገኝበታል ፤ ነገር ግን ባያከናውን ይቀጣበታል። ✅ ሙስተሐድ (የሚወደድ) - አንድን የሆነ ነገር ቢያከናውን ሚንዳ ያገኝበታል፤ ባያከናውን አይቀጣም። ✅ ሙባሕ (በምርጫ የሚወሰድ) - አንድ ነገር ቢያከናውንም ባያከናውንም አይመነዳም አይቀጣም። ✅ መክሩሕ (የሚጠላ) - ባያከናውን ሚንዳ ያገኝበታል ቢያከናውን ግን አይቀጣም። ✅ ሐራም (የተከለከለ) - ባያከናውን ሚንዳ ያገኛል(ይመነዳበታል)፤ ቢያከናውን ይቀጣበታል። በዚህም መሠረት፦ 1ኛ) መውሊድ ማክበር ፈርድ ነው ወይ? - መልሱ = #አይደለም ምክንያቱም አልታዘዝንምና ብናከብር እንቀጣለን። 2ኛ) መውሊድ ማክበር ሙስተሐድ(የሚወደድ) ነው ወይ? - መልሱ = #አይደለም ምክንያቱም ሊያስቀጣ ይችላል። 3ኛ) መውሊድ ማክበር ሙባሕ(በምርጫ የሚወሰድ) ነው ወይ? - መልሱ = #አይደለም ምክንያቱም ካከበርነው ሊያስቀጣን ስለሚችል ሙባህ ውስጥ አይገባም። 4ኛ) መውሊድ ማክበር መክሩሕ(የሚጠላ) ነው ወይ? - መልሱ = #አይደለም ምክንያቱም ብናከብረው ሊያስቀጣን ይችላልና መክሩሕ ውስጥ አይመደብም። 5ኛ) መውሊድ ማክበር ሐራም(የተከለከለ) ነው ወይ? - መልሱ = #አዎ ሐራም ነው ምክንያቱም ብናከብረው እንቀጣለን ባናከብረው እንመነዳበታለን።

አንድ አዲስ የማናውቀው ነገር በሚገጥመን ሰዓት ወደ ቁርዓንና ወደ ሐዲስ እንሂድና እውነቱን እናጣራ፤ እንዲሁም ደግሞ በሐዲስና በቁርዓን የምናውቀው ነገር ከሆነ ኪታብ ጋር የሚጋጭ ከሆነ የቁርዓኑንና የሐዲሱን ነው መከተል ያለብን። ከዚህ ውጪ ግን እነ ሼህ እገሌ በኪታባቸው እንዲህ ብለዋል የሚለውን ጉዳይ መተው ነው ነገር ግን ሼሆቹን ማክበር ይጠበቅብናል። 4፡ 115 ومن يشاقق الرسول من بعد ما تبين له الهدى ويتبع غير سبيل المؤمنين نوله ما تولى ونصله جهنم ۖ وساءت مصيرا ቅኑም መንገድ ለእርሱ ከተገለጸ በኋላ መልክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከምእምኖቹ መንገድ ሌላ የኾነን የሚከተል ሰው (በዚህ ዓለም) በተሾመበት (ጥመት) ላይ እንሾመዋለን፤ ገሀነምንም እናገባዋለን፡፡ መመለሻይቱም ከፋች! 7፡ 30 فريقا هدى وفريقا حق عليهم الضلالة ۗ إنهم اتخذوا الشياطين أولياء من دون الله ويحسبون أنهم مهتدو ከፊሉን ወደ ቅን መንገድ መራ፡፡ ከፊሎቹም በእነሱ ላይ ጥመት ተረጋግጦባቸዋል፡፡ እነርሱ ሰይጣናትን ከአላህ ሌላ ረዳቶች አድርገው ይዘዋልና፡፡ እነርሱም (ቅኑን መንገድ) የተመራን ነን ብለው ያስባሉ፡፡ አንድ ነገር ግን ግልፅ ማድረግ እፈልጋለሁ። ኢማሞችን አንከተል ከእነርሱ እውቀት አንውሰድ ማለቴ አይደለም ነገር ግን የምናውቅ ከሆነ የአንዳንድ ኢማሞች አስተምህሮ ከቁርዓንና ከሐዲስ ይጋጫሉና እውነቱን ለማረጋገጥ በቁርዓንና በሐዲስ እንመርምረው ነው። ኢማሞችን መከተል ደግሞ #ተቅሊድ ይባላል። ደግሞም ኢማሞችም እንደኛው ሰዎች ናቸውና በሸይጧን ጉትጎታ ተሳስተው አዲስ እተምህሮ ሊፈጥሩና ለሰዎችም ሊያስተምሩ ይችላሉ። ረሱል(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መጽሐፍ 46 ቁጥር 705 አቡ ሁረይራ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “በተከታዮቼ ልብ ውስጥ የሚያንሾካሾከውን ነገር በተግባር እስካላደረጉት ወይም እስካልተናገሩት ድረስ አላህ ይቅር እንዲለው ልመናዬን ተቀብሎታል። ****************** እናም መውሊድ ስለማክበር በቁርዓንና በሐዲስ የተገለፀ ነገር አለ ወይ? ረሱል(ሰዐወ) አክብሩልኝ ብለዋል ወይ? ሶሐቦችስ አክብረዋል ወይ? ከተባለ መልሱ ሁሉም የሚስማማበትን #የለም እና #አላሉም ነው። ነገር ግን ከየት መጣ? ነብዩ(ሰዐወ) የእሳቸው መመሪያና ሶሐቦቻቸውን እንድንከተል አዘውናል ከዚያም በመቀጠል ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 3፣ መጽሐፍ 48፣ ቁጥር 819 & 820 በዘህዳም ቢን ሙድራብ የተተረከ ኢምራን ቢን ሁሴን (ሰ.ዐ.ወ) ሲናገሩ ሰማሁ፡- “ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “በኔ ትውልድ ውስጥ የሚኖሩ፣ ከዚያም ከእነሱ በኋላ የሚመጡት፣ ከዚያም በኋላ የሚመጡት (ሁለተኛው ትውልድ) ናቸው። ኢምራን እንዲህ አለ "ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ከአሁኑ ትውልድዎ በኋላ ሁለት ወይም ሶስት ትውልዶችን እንደጠቀሱ አላውቅም። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) አክለውም "ከአንተ በኋላ አንዳንድ ሰዎች ይኖራሉ እነሱም ታማኝ የማይሆኑ እና ያለ ምንም ምስክር (ማስረጃ) የሚመሰክሩ ናቸው። ይመሰክሩማል፥ ስእለትም ይሳላሉ፥ ስእለታቸውንም አይፈጽሙም፥ በመካከላቸውም ስብ ይታያል። ********************* ነብዩ(ሰዐወ) ምርጡ ትውልድ የሶሐቦች ነው አሉ ፤ ከዚያም የሚቀጥለው ትውልድ (ተኣቢዎች) ነው አሉ፤ ከዚያም የሚቀጥለው ትውልድ (የተኣቢ ተኣቢዎች) ነው አሉ። እናም በእነዚህ ምርጥ በተባሉት ሶስት ትውልዶችም ላይ ቢሆን #መውሊድን #አልተከበረም ። ታድያ ምን ተሻለ? የሚለውን ለማየትና የተሻለውንም አማራጭ ለመውሰድ በርዕሱ ላይ የተቀመጡትን በአምስቱ የኢስላም መሠረታዊ ክንውኖች እንፈትሸው።

. መውሊድ ማክበር ፈርድ ነው? ሐራም ነው? ሙባህ ነው ? መክሩም ነው? ወይስ ሙስተሐድ? .፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። እንደሚታወቀው መውሊድ ማክበር ቢዳኣ ነው ወይም ደግሞ ቢዳኣ አይደለም በሚል ብዙ ውዝግብ የሚነሳበት ጉዳይ ሲሆን የኡማውን አንድነት ከሚከፋፍሉ ጉዳዮችም መካከል አንዱ ነው። ታድያ የዚህ መውሊድን የማክበርና ያለማክበር ጉዳይ ምን ይሆን? የእስልምና ህግ (ሸሪአው) ስለዚህ ምን ይላል? ኢስላም የአላህ የተፈጥሮ መንክር ነው፤ እስልምና ምንም አይነት ነገር ያልጎደለው የተሟላ ዲን ነው። ለዚህም አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 5፡3 "... ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡..." ችግራችን የመገንዘብና ያለመገንዘብ ጉዳይ ሆኖ ነው እንጂ ዲኑማ በዚህ መልኩ ሙሉ ተደርጓል። እናም አላህ መልካም የሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋልና አምላካችን የመረጠውና ሙሉ ያደረገው እስልምናም ለተገነዘበ ሰው እያንዳንዱ እንቅስቃሴው ለርሱ ግልፅ ነው። እንኳንስ በመውሊድ ጉዳይ ግራ መጋባትና መወዛገብ ይቅርና ምንም አይነት ጉዳይ ቢያጋጥመው እንኳን ለእርሱ በብርሃን እንደሚጓዝ ሰው ነው። ምክንያቱም በኢስላም መመሪያ ውስጥ አንዳችም ያልተብራራና ያልተገለፀ ሚስጥር የለም። አላህ እንዲህ ይላል፦ 6፡ 59 وعنده مفاتح الغيب لا يعلمها إلا هو ۚ ويعلم ما في البر والبحر ۚ وما تسقط من ورقة إلا يعلمها ولا حبة في ظلمات الأرض ولا رطب ولا يابس إلا في كتاب مبين የሩቅ ነገርም መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው፡፡ ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም፡፡ በየብስና በባሕር ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ ከቅጠልም አንዲትም አትረግፍም የሚያውቃት ቢኾን እንጅ፡፡ ከቅንጣትም በመሬት ጨለማዎች ውስጥ የለም #ከእርጥብም #ከደረቅም #አንድም #የለም #ግልጽ #በኾነው #መጽሐፍ ውሰጥ (የተመዘገበ) ቢኾን እንጅ፡፡ ታድያ ግልፅም ይሁን ድብቅ ሁሉን አዋቂው አላህ በእውቀቱ፣ በጥበቡና በችሎታው ሙሉ አድርጎትም በመመሪያው መፅሃፉ ውስጥ እያንዳንዱን ጉዳይ በግልፅ ከገለፀው ዲን ሸሸት ብሎ ሌላን የራስ አማራጭ መከተል የአላህን እውቀት፣ ጥበብና ማንነት እንደማሳነስ ነው። ምክንያቱም እሱ ሙሉ አድርጎት ቀጥተኛ ያደረገውን እምነት እኔ ጎዶሎ ነው ብዬ መከተልን ብተውና አንድ አዲስና መጤውንም መርጬ የፈጠራ ተግባርን ከፈፀምኩ ይህ ተግባር በግልፅ ጥመት ነው። ለዚህም አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 6፡ 153 وأن هذا صراطي مستقيما فاتبعوه ۖ ولا تتبعوا السبل فتفرق بكم عن سبيله ۚ ذلكم وصاكم به لعلكم تتقون «ይህም ቀጥተኛ ሲኾን መንገዴ ነው፤ ተከተሉትም፡፡ (የጥመት) መንገዶችንም አትከተሉ፡፡ ከ(ቀጥተኛው) መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና፡፡እነሆ ትጠነቀቁ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ፡፡» ይህን ግልፅ የሆነውን መመሪያ ብቻ ተከተሉ ከተባልን ወደድንም ጠላንም ቁርዓንና ሐዲስ ብቻ መከተል ነው እንጂ ሌላ ተጨማሪ የሰው ፈጠራ የሆኑ ኪታቦችን እንድንከተል አልታዘዝንም። 7፡ 203 وإذا لم تأتهم بآية قالوا لولا اجتبيتها ۚ قل إنما أتبع ما يوحى إلي من ربي ۚ هذا بصائر من ربكم وهدى ورحمة لقوم يؤمنون በተዓምርም ባልመጣሃቸው ጊዜ (በራስህ) «ለምን አትፈጥራትም» ይላሉ፡፡ ከጌታዬ ወደኔ የተወረደውን ብቻ እከተላለሁ፡፡ ይህ (ቁርኣን) ከጌታችሁ ሲኾን ለሚያምኑ ሕዝቦች መረጃዎችና መምሪያ እዝነትም ነው በላቸው፡፡ 6፡ 157 أو تقولوا لو أنا أنزل علينا الكتاب لكنا أهدى منهم ۚ فقد جاءكم بينة من ربكم وهدى ورحمة ۚ فمن أظلم ممن كذب بآيات الله وصدف عنها ۗ سنجزي الذين يصدفون عن آياتنا سوء العذاب بما كانوا يصدفون ወይም «እኛ መጽሐፍ በእኛ ላይ በተወረደ ኖሮ ከእነሱ ይበልጥ የተመራን እንኾን ነበር» እንዳትሉ ነው፡፡ ስለዚህ ከጌታችሁ ግልጽ ማስረጃ፣ መምሪያም፣ እዝነትም በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ በአላህም አንቀጾች ካስተባበለና ከእርሷም ከዞረ ሰው ይበልጥ በዳይ ማን ነው እነዚያን አንቀጾቻችንን የሚተውትን ይተውት በነበሩት ምክንያት ብርቱን ቅጣት በእርግጥ እንቀጣቸዋለን፡፡

- ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 45 18፤ ሰማያትን የፈጠረ እግዚአብሔር፥ እንዲህ ይላል። እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም በቀር ሌላ የለም። 20፤ እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፥ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ፤ #የተቀረጸውን #የምስላቸውን #እንጨት #የሚሸከሙና #ያድን #ዘንድ #ወደማይችል #አምላክ #የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም። 👉 በአመት በሶስት በዓላት ብቻ እንዲደሰቱ፣ ከጣኦታት እንዲርቁ እና እግዚአብሔርን በብቸኝነት እንዲያመልኩት ሙሴ በህግ የተደነገገላቸው የሆኑት እነዚያ እስራኤላውያን ግን እየዋሉ እያደሩ ለባሪያዎቹ ፈጥኖ ደራሹ ባለውለታቸው አምላክ ከዱ፤ በጥበቡና በችሎታው ባህር ከፍሎ ስላሻገራቸው ለመታሰቢያነት የተሰጠው የበዓል ህግ በመናቅና ህጉንና በዓላቱን ሻሩ ፤ ይህንንም ከአምላክ የተሠጠው በዓልና ህግ ሽረውም የራሳቸው የሆነ የጣኦታት በዓላት መሠረቱ፤ ጣኦታትም አመለኩ፤ ለዛሬው የደመራና የመስቀል በዓል መፈጠር ምክንያት ሆኑ፤ - መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 74 4፤ #ጠላቶችህ #በበዓል #መካከል #ተመኩ፤ #የማያውቁትንም #ምልክት #ምልክታቸው #አደረጉ። 8፤ አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ #የእግዚአብሔርን #በዓሎች #ከምድር #እንሻር #አሉ ። 9፤ ምልክታችንን አናይም #ከእንግዲህ #ወዲህም #ነቢይ #የለም፤ እስከ መቼ እንዲኖር የሚያውቅ በኛ ዘንድ የለም። አሉ። - መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ምዕ. 14 15፤ በዚያ ጊዜም ሸምበቆ በውኃ ውስጥ እንደሚንቀሳቀስ እግዚአብሔር እንዲሁ እስራኤልን ይመታል፤ #እግዚአብሔርንም #ያስቈጡ #ዘንድ #የማምለኪያ #ዐፀድ #ተክለዋልና ለአባቶቻቸው ከሰጣቸው ከዚች ከመልካሚቱ ምድር እስራኤልን ይነቅላል፥ በወንዙም ማዶ ይበትናቸዋል። 23፤ እነርሱም ደግሞ ከፍ ባለው ኮረብታ ሁሉ ላይ፥ #ቅጠሉ #ከለመለመ #ዛፍ #ሁሉ #በታች #መስገጃዎችንና #ሐውልቶችን #የማምለኪያ #ዐፀዶችንም #ለራሳቸው ሠሩ። - መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ ምዕ. 17 14፤ ነገር ግን አምላካቸውን እግዚአብሔርን እንዳላመኑ እንደ አባቶቻቸው አንገት አንገታቸውን አደነደኑ እንጂ አልሰሙም። 15፤ ሥርዓቱንም ከአባቶቻቸውም ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን፥ ያጸናላቸውንም ምስክሩን ናቁ፤ ከንቱ ነገርንም ተከተሉ፥ ምናምንቴዎችም ሆኑ፥ እግዚአብሔርም እንደ እነርሱ እንዳይሠሩ ያዘዛቸውን በዙሪያቸው ያሉትን አሕዛብን ተከተሉ። 16፤ የአምላካቸውንም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሁሉ ተዉ፥ ቀልጠው የተሠሩትንም የሁለቱን እንቦሶች ምስሎች አደረጉ፥ #የማምለኪያ #ዐፀድንም #ተከሉ፥ ለሰማይም ሠራዊት ሁሉ ሰገዱ፥ #በኣልንም #አመለኩ። 👉 የተናቀው እግዚአብሔር ግን ይህንን ድርጊታቸው አይቶ ዝም አላላቸውም። ይልቁንም እነርሱ የፈጠሯቸውን በዓላት ጠላቸው፤ ተፀየፋቸውም፣ አመት በዓላቸውንም ወደ ለቅሶ ቀየረባቸው፣ በጉባኤያቸውንም ተከፋ፣ ያቀርቡት የነበረው ቁርባንና መስዕዋትም ተወው... - ትንቢተ አሞጽ ምዕ. 5 21፤ #ዓመት #በዓላችሁን #ጠልቼዋለሁ #ተጸይፌውማለሁ፤ የተቀደሰውም ጉባኤአችሁ ደስ አያሰኘኝም። 22፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕታችሁና የእህሉን ቍርባናችሁን ብታቀርቡልኝም እንኳ አልቀበለውም፤ ለምስጋና መሥዋዕት የምታቀርቡልኝን የሰቡትን እንስሶች አልመለከትም። 23፤ የዝማሬህንም ጩኸት ከእኔ ዘንድ አርቅ፤ የመሰንቆህንም ዜማ አላደምጥም። - ትንቢተ አሞጽ 8፥10 " ዓመት በዓላችሁንም ወደ ልቅሶ፥ ዝማሬአችሁንም ወደ ዋይታ እለውጣለሁ፤ ማቅንም በወገብ ሁሉ፥ ራስ መንጨትንም በሁሉ ላይ አመጣለሁ፤ እንደ አንድያ ልጅም ልቅሶ፥ ፍጻሜውንም እንደ መራራ ቀን አደርገዋለሁ።" 👉 ለአምላክ በስተቀር ለሌላ የሚከወን የትኛውንም አምልዕኮ (ለታቦት መስገድ፣ የገና በዓል ማክበር ፣ የገና ዛፍ ማጌጥ ፣ ለመስቀል፣ ደመራ ማቀጣጠል ፣ እንቁጣጣሽ፣ ለሠማይ መላዕክት መስገድ፣ ለማሪያም ማጎብደድ፣ እየሱስን ማምለክ...) ሁሉንም ለጣኦት ነው። ምክንያቱም ፦ - ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 16፥26 " የአሕዛብ አማልክት ሁሉ ጣዖታት ናቸው፤ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።" 👉 ስለዚህ እግዚአብሔር እነዚህ ተግባሮቻቸውን እንዲህ አድርጉባቸው ይላል፦ - ዘዳግም 7፥5 " ነገር ግን እንዲህ አድርጉባቸው፤ መሠዊያቸውን አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም ቍረጡ፥ የተቀረጸውን ምስላቸውንም በእሳት አቃጥሉ። " - ዘዳግም 12፥3 " መሠዊያቸውንም አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም በእሳት አቃጥሉ፥ የአማልክቶቻቸውንም የተቀረጹ ምስሎች አንከታክቱ፤ ከዚያም ስፍራ ስማቸውን አጥፉ።"

ደመራ እና የመስቀል በዓል የጣኦት አምልዕኮ
ደመራ እና የመስቀል በዓል የጣኦት አምልዕኮ

👉 ታድያም አጀንዳችን #ደመራ እና #መስቀል #የጣኦታት በኣላት ናቸው የሚል ነውና ወደዚሁ ርዕስ መለስ እንበል፦ ከላይ እንደተመለከትነው እግዚአብሔር ከከለከላቸው የበዓላት ህጎች መካከልም ከዛፍ የማምለኪያ አፀደ አለመትከልና እንጨት ከምሮ አለማቃጠልም አንዱ ሲሆን ይህን ማድረግ ደግሞ ጣኦትን የማምለክ አስተምህሮ መሆኑን በትንቢተ ኤርምያስ 10፥8 ላይ ተገልጿል። - ትንቢተ ኤርምያስ ምዕ. 10 3፤ የአሕዛብ ልማድ ከንቱ ነውና፤ ዛፍ ከዱር ይቈረጣል፥ በሠራተኛም እንጅ በመጥረቢያ ይሠራል። 4፤ በብርና በወርቅ ያስጌጡታል፥ እንዳይናወጥም በችንካርና በመዶሻ ይቸነክሩታል። 5፤ እንደ ተቀረጸ ዓምድ ናቸው እነርሱም አይናገሩም፤ መራመድም አይቻላቸውማን ይሸከሙአቸዋል። ክፉ መሥራትም አይቻላቸውምና፥ ደግምም መልካም ይሠሩ ዘንድ አይችሉምና አትፍሩአቸው። 8፤ #ጣዖታት #የሚያስተምሩት #የእንጨት #ነገር #ብቻ ነው።" ይላል!!! 👉 እዚህ ላይ እንጨትና ጣኦት ምን አገናኛቸው ልንል እንችል ይሆናል። ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩት 5 ነጥቦችን ለምሳሌ እንመልከት፦ 1ኛ) #ታቦት መጀመሪያ ከግራርና ከተለያዩ እንጨቶች ከተሠራ በኋላ ነው በወርቅ፣ በብር ፣ በነሐስ ተለብጦ የሚመለከውና የሚሰገድለት!! 2ኛ) ፋሲካ ሲከበር የገና ዛፍን በመስቀል ነው የሚመለከው!! 3ኛ) የእየሱስ፣ የማሪያም ፣ የገብሬል... ፎቶዎች የሚቀረፁት አብዛኛውን ጊዜ ከእንጨት ውጤቶች ሲሆን ከወርቅና ከብርም እንደአስፈላጊነቱ ይቀርፃሉ!! 4ኛ) መስቀል ከእንጨት፣ ከወርቅ፣ ከብር... ውጤቶች ተቀርፆ ነው በክርስቲያኖች ዘንድ እንደ መዳኛ የሚመለከው!! 5ኛ) አይሁዶች እየሱስን የሰቀሉት በእንጨት ላይ እንደሆነ ክርስቲያኖች ያምናሉ። ያንንም እየሱስ ተሰቅሎበት የነበረውን መስቀልም ለማግኘት ከጊዜ በኋላ በንግስት እሌኒ አማካኝነት የስቅላት ቦታው ተቆፍሮ መስቀሉ እንደተገኘና እንዲሁም የመስቀል በዓልም የሚከበረውም ከዚህ የመስቀሉ መገኘት አንፃር እንደሆነ ነው። በአጠቃላይ የዚህ የእንጨት አስተምህሮ ጉዳይ የጣኦት አምልኮ መሆኑን መፅሐፍ ቅዱስ ጠቅለል አድርጎ እንዲህ በማለት ይገልፀዋል ፦ - ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 44 13፤ ጠራቢውም ገመድ ይዘረጋል በበረቅም ያመለክተዋል በመቅረጫም ይቀርጸዋል በመለኪያም ይለካዋል፤ በቤትም ውስጥ ይቀመጥ ዘንድ በሰው አምሳልና በሰው ውበት ያስመስለዋል። 15፤ ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። 17፤ የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ። አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። 18፤ አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። 19፤ በልቡም ማንም አያስብም። ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም።

ደመራ እና መስቀል የጣኦት አምልዕኮ
ደመራ እና መስቀል የጣኦት አምልዕኮ

. ደመራ እና መስቀል የጣኦታት በኣል ስለመሆናቸው °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ለዘላለም የመታሰቢያ ስርዓት እንዲሆንላቸው በሚል #ፋሲካን እንዲያደርጉ በአመት ውስጥ ሶስት አይነት በዓላትን ብቻ እንዲያከብሩ ደንግጎላቸው ነበር። እነርሱም #የቂጣ በዓል፣ #የሰባቱ #ሱባኤ በዓል እና #የዳስ በዓል ናቸው። - ኦሪት ዘፀአት 23፥14 " በዓመት ሦስት ጊዜ በዓል ታደርግልኛለህ።" ታድያ ይህ የሆነበት ምክንያትም ደግሞ በሙሴ ዘመን የነበሩት እነዚያ በግብፅ ምድር ላይ በፊራኦን የባርነት ቀንበር ውስጥ ጣኦታትን በማምለክ ይማቅቁ የነበሩትን እስራኤላውያን እግዚአብሔር ባህርን ከፍሎ በድንቅ ተዓምር ከግብፅ ምድር ካወጣቸው በኋላ እግዚአብሔር ከእርሱ ሌላ አምላክ እንደሌለ አውቀው እርሱን ብቻ በብቸኝነት እንዲያመልኩ፤ ለእርሱም እንዲሠው እንዲሁም ደግሞ ያንንም ተዓምር በወደፊት ትውልዶች እንዲዘከር ታስቦ የተደነገጉ በዓላት ነበሩ። - ኦሪት ዘጸአት ምዕ. 12 12፤ እኔም በዚያች ሌሊት በግብፅ አገር አልፋለሁ፥ በግብፅም አገር ከሰው እስከ እንስሳ ድረስ በኵርን ሁሉ እገድላለሁ፤ በግብፅም አማልክት ሁሉ ላይ እፈርድባቸዋለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ። 13፤... እኔም የግብፅን አገር በመታሁ ጊዜ መቅሰፍቱ ለጥፋት አይመጣባችሁም። 14፤ #ይህም #ቀን #መታሰቢያ #ይሁናችሁ፥ #ለእግዚአብሔርም #በዓል #ታደርጉታላችሁ፤ ለልጅ ልጃችሁ #ሥርዓት #ሆኖ #ለዘላለም ታደርጉታላችሁ። 15፤ ሰባት ቀን ቂጣ እንጀራ ትበላላችሁ፤ በመጀመሪያም ቀን እርሾውን ከቤታችሁ ታወጣላችሁ፤ ከመጀመሪያውም ቀን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው ቀን እርሾ ያለበትን እንጀራ የሚበላ ነፍስ ከእስራኤል ተለይቶ ይጥፋ። 16፤ በመጀመሪያውም ቀን የተቀደሰ ጉባኤ እንዲሁም በሰባተኛውም ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ይሆንላችኋል። ከሚበላው በቀር በእነርሱም ምንም አትሠሩም፥ ይህንም ብቻ ታደርጉታላችሁ። 17፤ በዚህም ቀን ሠራዊታችሁን ከግብፅ አገር አውጥቼአለሁና የቂጣውንም በዓል ጠብቁት፤ እንግዲህ ይህን ቀን ለልጅ ልጃችሁ ለዘላለም ሥርዓት ትጠብቃላችሁ። - ኦሪት ዘዳግም ምዕ. 16 16፤ በዓመት ሦስት ጊዜ፥ በቂጣ በዓል፥ በሰባቱ ሱባዔም በዓል፥ በዳስም በዓል ወንዶችህ ሁሉ በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት እርሱ በመረጠው ስፍራ ይታዩ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ባዶ እጃቸውን አይታዩ። እናም እነዚህ ሶስት በዓላት ሲፈፀሙ ለየራሳቸው የተፈቀዱ የሆኑ መስፈርቶች የተቀምጠውላቸው (ገብቶ መመልከት) ሲሆን በዓላቶቹ በሚከበሩበት ወቅትም ሆነ በሌላ ጊዜ ህዝቦቹ ፍፁም እንዳይከውኑት የሚያግዱ የሆኑ የተከለከሉ ህጎችም ተደንግገዋል። ከእነዚህ ህጎችም መካከል ደግሞ #የማምለኪያ #ዛፍን #መትከል(የገና ዛፍን አምልዕኮ) ፣ እንጨት ከምሮ ማቃጠል(ደመራ)፣ ሐውልት ማቆምን፣ ተጨማሪ በዓላትን ማክበርና... ይገኙበታል። - ዘዳግም 16 21፤ ለአንተ በምትሠራው በአምላክህ በእግዚአብሔር መሠዊያ አጠገብ ከማናቸውም ዛፍ #የማምለኪያ #ዐፀድ #አድርገህ #አትትከል። 22፤ አምላክህ እግዚአብሔርም የሚጠላውን ሐውልት ለአንተ አታቁም።

ደመራ እና መስቀል የጣኦት አምልዕኮ
ደመራ እና መስቀል የጣኦት አምልዕኮ

ይልማ ደሬሳ ስለክርስቲያኑ ጦር ብዛት እንዲህ ሲሉ ፅፈዋል፦ " የሠራዊቱ ብዛትና የመሪዎቹ ጀግንነት የእስላምን ሰራዊት ልብ ትር ትር ማሰኘቱ አልቀረም። አህመድ ኢብራሂም ግን በልቡ ቆራጥነትና በነፍጦቹ ተመክቶ ይህ መዓት የሆነ ሰራዊትን ሳያወላውል ለመግጠም ተዘጋጅቶ ቆየ።" ( #ምንጭ ፦ ይልማ ደሬሳ ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ፣ በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን ፤ ሁለተኛ እትም 1999 ፤ አዲስ አበባ ፤ ገጽ 65) - ሙስሊሙን ሲጨፈጭፍ የነበረው የአፄው ጦርና ኢማሙ ሊገጥሙ ተፋጠዋል፤ ጂሐዱ ሊጀምር ነው። የኢማሙ ጦር የዳዕዋ ክፍል ሙስሊሙን ማነሳሳት ጀመረ።የቁርዓን አስተማሪው ሼህ አቡበክር ቢን ነስረዲን ቢን ሙሐመድ( አርሹናእ) ለሙስሊሙ ጦር ስለ ጂሐድ ዳዕዋ አደረገ። ስለ ጀነት ታላቅነትና ለኢስላም ሲሉ በፅናት መዋጋት እንዳለባቸው መከረ። ሸሒድ (መስዕዋት) ስለመሆን በማስታወስ ሙጃሒዱን አስለቀሰ፤ የጂሐድ ወኔና ስሜታቸውን አነሳሳ። በመጨረሻም ከቁርዓን ምዕራፍ 9፡111 እንዲህ ሲል አነበበላቸው ፦ 9፡ 111 إن الله اشترى من المؤمنين أنفسهم وأموالهم بأن لهم الجنة ۚ يقاتلون في سبيل الله فيقتلون ويقتلون ۖ وعدا عليه حقا في التوراة والإنجيل والقرآن ۚ ومن أوفى بعهده من الله ۚ فاستبشروا ببيعكم الذي بايعتم به ۚ وذلك هو الفوز العظيم <<አላህ ከምእምናን ነፍሶቻቸውንና ገንዘቦቻቸውን ገነት ለእነሱ ብቻ ያላቸው በመኾን ገዛቸው፡፡ በአላህ መንገድ ላይ ይጋደላሉ፡፡ ይገድላሉም፤ ይገደላሉም፡፡ በተውራት በኢንጅልና በቁርኣንም (የተነገረውን) ተስፋ በእርሱ ላይ አረጋገጠ፡፡ ከአላህም የበለጠ በኪዳኑ የሚሞላ ማነው በዚያም በእርሱ በተሻሻጣችሁበት ሽያጫችሁ ተደሰቱ፡፡ ይህም እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡>> - ጦሩ የጂሐዱ ስሜቱ ተቀጣጠለ፤ ለኢስላም ሲል ለመሞት ቆረጠ። ኢማሙ << ቦታችሁን ያዙ ፤ እነርሱ መጋደል እስኪጀምሩ ድረስ ጥቃት አትጀምሩ፤ ጦራችሁን በተጠንቀቅ ያዙ፤ ከቆዳ የተሰራውን የጦር መከላከያ ልብስም ልበሱ። አላህን እያስታወሳችሁ ቢሆን እንጂ ለአንዲት እርምጃ እንኳን እግራችሁን አታንቀሳቅሱ።>>ሲል አዘዘ።( #ምንጭ ፦ Futuh Al-Habaša, P.80) ኢማሙ ከዚህም አስከትሎ <<አላህ ሆይ! ሁላችንንም ታጋሽና ለሃይማኖትህ አሸናፊዎች አድርገን> ሲል አላህን ለመነ።( #ምንጭ ፦ Ibid, P.74) - እንደተለመደው አፄው ሙስሊሙ ላይ ጥቃት ሰነዘረ፥ በዚህ ጊዜ ጦርነቱን ተጀመረ። ሁለቱ ሰራዊቶች ተገናኙ ፤ የቀስተኞች ፍላፃ አየሩን ሞላው፤ ሰይፍ ከሰይፍ ተጋጨ። የፈረሶች ኮቴ ያስነሳው አቧራ ወደ ሰማይ ተበትኖ እንደ ደመና ፀሀይን ጋረዳት ፤ የአፄ ልብነ ድንግል ጦር ጥቃቱን አፋፋመ፤ ወደ ማሸነፍ ተቃረበ። በግራ በኩል የሱማሌያውን ጦር ነበር የተሠለፈው። በዚህ ብርጌድ የጊሪ ጎሳ፣ መራይሃን፣ ይቤሪ ፣ ሃርቲ ፣ ጀራን ፣ መዛር ፣ እና ባርሱስ ጎሳዎች ሁሉም በጎሳው አለቃ መሪነት ተሰልፈዋል። ጦርነቱ ሲያይል ከግራው ሱማሌ ብርጌድ ሶስት ሺህ ሙስሊሞች ተሰው። የተቀሩት መሸሽ ጀመሩ። ሆኖም ዋና ታላላቅ የጎሳ መሪዎቹ እነ መታን ቢን ዑስማን ፣ አህመድ ጊሪና ዐሊ ገራድ (የመታን ወንድሞች)፣ የበሻራ ወንድም፣ ዐሊ ማድ ጂራ፣ ሑሴን ሙሳ ቢን አብደላህ ማኪዳ እና ዩሱፍ ለተሂያ ንቅንቅ ሳይሉ በአስደናቂ ሁኔታ ተጋደሉ። ( #ምንጭ ፦ Ibid, P.82) - በተለያየ አቅጣጫ ሙጃሒዶች መሰዋታቸውን እየበዛ ሄደ ነገር ግን ማፈግፈግም ሆነ መሸሽ ሚሉት ነገር የለም። ጦርነቱ በረታ፤ አቧራ አየሩን ሞላው፤ ጦሩ የራሱን ወገን መለየት ሁሉ አቃተው። <<አላሁ አክበር!>>... <<የሙሐመድ ጦር ፅኑ!>>... << ላ ኢላህ ኢለላህ!>>... <<ድል የኢስላም ነው!>> እና መሠል መፈክሮች በተደጋጋሚ በሙጃሒዶች መካከል እዚያም እዚያም ይሰማሉ። ሙጃሒዶች ንቅንቅ ሳይሉ መጋደሉን ቀጠሉ። - የአፄ ልብነ ድንግል እና የኢማሙን ጦር ብዛት ስናነፃፅር ልዩነቱ ሰፊ ነበር( 216,000 ለ12,560)። ይህም ማለት 1 የሙስሊም ወታደር 17 የክርስቲያን ወታደሮችን ነበር የጠመው። - ከቀኑ 9፡00 አካባቢ ሙስሊሞች የበላይነቱን ተቆጣጠሩ፤ የኢማሙ ጦር ማሳደድና መማረክን ተያያዘው፤ ከአፄ ልብነ ድንግል ጦር ታላላቅ መሪዎች ተገደሉ፤ የተረፈው ግን እግሬ አውጪኝ ብሎ ሸሸ። በዚህም ጦርነት 10,000 ወታደሮች ተገደሉ። ታሪኩን በጦርነቱ ላይ በመገኘት በዐረብ ፊቅህ <<ፉቱህ አል ሐበሻ>> በተሰኘው መፅሐፍ እንደተረከው 5,000 ሙስሊሞች ተሰውተዋል። ( #ምንጭ ፦ Ibid, Pp.84-85) ይልማ ደሬሳ የሟቾችን ቁጥር ከፍ ያደርጉታል። እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፦ << በዚህች ቀን ሽምብራ ኩሬ ላይ የሞቱት የኢትዮጵያ ሰዎች ከክርስቲያኑ ሰራዊት 12,000 ሲሆን ከእስላሞች ደግሞ 6,000 የሚበልጡ ወታደሮችና መኮንኖች ናቸው ሲል ታሪክ መዝግቧል።... ሽምብራ ኩሬ የኢትዮጵያ ታሪክ መንገድ የለወጠችበት ቀንና ቦታ ነች።>> ( #ምንጭ ፦ የኢትዮጵያ ታሪክ ከአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን፤ ገፅ 66) - የሽምብራ ኩሬው ጦርነት በዚህ መልኩ በኢማም አህመድ በተመራው የሙስሊሙ ጦር የበላይነት ሲጠናቀቅ የክርስቲያኑ መሪ የልብነ ድንግል ሰራዊት ግን የሽንፈትን ፅዋ ተጎንጭቶ፣ አንድነቱን ተበታትኖ ወኔውንም በከፍተኛ ሁኔታ ተንኮታኩቶ በመሸሽ አመለጠ። ከዚህም የሙስሊሞች ድል በኋላ ለጊዜውም ቢሆን ለዘመናት የክርስቲያኑ መንግስት ወደ ደቡብ በመዝመት በሙስሊሞች ላይ ያሻውን ይፈፅም የነበረበትን ሂደት አስቀርቶታል። በጊዜው የሐይልና የጦርነቱ ሚዛን ወደ ሙስሊሞች ያጋደለ ስለነበር በሙስሊሞች ግዛት ይካሄድ የነበረውን ጦርነት በአፄው ግዛት ውስጥ መካሄዱን ቀጠለ።

. ስለመግደል የሚያስተምረው እምነት ( እስልምና? ወይስ ክርስትና?) ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ ከቀደሙት የኢትዮጵያ ነገስታት የግድያ ታሪክ የቀጠለ 👉 #ኢማሙ_አህመድ vs #አፄ_ልብነ_ድንግል ክፍል 11 ⓭ - #አፄ_ልብነ_ድንግል አፄ ልብነ ድንግል የአጼ ናኦድ ልጅ ሲሆን አባቱ አፄ ናኦድ በ1508 ሲሞት በ11 ዓመቱ እንዲነግስ ተደረገ። የአፄ ዘርዓያዕቆብ ሚስት የነበረችው ንግስት እሌኒ ሙሐመድ ሞግዚት ተደረገች። ንግስት እሌኒ የሐድያው ንጉስ ሙሐመድ ልጅ የነበረች ሲሆን ዘርዓያዕቆብ በጦርነት ወቅት ይዟት በመሄድ ክርስትና አነሰነስቶ አገባት። በጸረ ኢስላም አስተሣሠብ እንድትጠመቅ ተደረገች። በኋላም ላይ በክርስቲያኑ መንግስት ውስጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰው ሆነች። - #አፄ #ልብነ #ድንግል በነገሠ በዓመቱ በ1509 ንግስት እሌኒ <<ኢስላምን ለማጥፋት እንተባበር>> ስትል ለፖርቹጋሉ ንጉስ ዶም ማኑኤል (ዶም ዮሐንስ 3ኛ) ደብዳቤ ላከች። ነገር ግን እጅግ ዘግይቶ ነበር በ1520 የዚህ ደብዳቤ ምላሽ የመጣው። - አፄ ልብነ ድንግል በ1517 ኢማም ማህፉዝን ለማጥቃት ጦር አዘጋጅቶ ወደ አዳል ዘመተ። ከኢማም ማህፉዝ ጦርም ጋር ውጊያው ተጀመረ። እንደ ተክለ ፃድቅ መኩሪያ ገለፃ "አባ ገብረ እንድርያስ" በተሰኙ መነኩሴ የኢማሙ አንገት ተቀልቶ ተገደሉ። ( #ምንጭ ፦ ዝኒ ከማሁ) የክርስቲያኑ ጦር አዳልን ተቆጣጠረ በዘንከር የሚገኘውን የሱልጣኑን ቤተመንግስት አወደመ፤ ከተማውንም አቃጠለ። - አፄ ልብነ ድንግል በፋጣጋርና በአዳል መካከል በሙስሊሞች ላይ ጦሩን አዘመተ። 12 ሺህ ገደማ ሙስሊሞችንም ጨፈጨፈ። ሌሎች ወደ ተራራ ቢሸሹም ተከበቡ። በዚያው በርካቶች በረሃብ አለቁ። ( #ምንጭ ፦ ኢትዮጵያ ወል ወሩባህ ወል ኢስላም ዐብረ ታሪኽ ፤ ጥራዝ 2 ፣ ገጽ 65) ኢማም ማህፉዝም ተሰው። አንገታቸውም በዓፄ ልብነ ድንግል ጦር ተቆርጦ ተወሰደ። - የአፄ ልብነ ድንግል ደገልሃን የተሰኘው አማች በ1525 አዳልን አጠቃ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ ከሐረር በስተደቡብ ምዕራብ በሚገኘው አማሬሳ ወንዝ አቅራቢያ አንድ ኢማም ጦሩን እያዘጋጀ ይገኛል። ታድያ ክርስትና በኢትዮጵያ መስፋፋት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ በ1189 በዛጉዌ ስርወ መንግስት የላሊበላ ገዢ እስከነበረው ገ/መስቀል ድረስ ከዚህም በመቀጠል እስከ ኢማም ማህፉዝ በልብነ ድንግል እስከተሰውበት 1520 ድረስ ለዘመናት እንደ በግ ሲያርዱ የኖሩት የክርስቲያን መሪዎች ጭካኔያቸው እስከዚህ በ1525 አዳል እስካጠቃበት ዘመን ድረስ ዘለቀ። ነገር ግን እዚህ አካባቢ ላይ በአሁኑ ዘመን ባሉት ክርስቲያኖች ትውልድ ፊት እንኳ ስሙ የማይጠራ የሆነ ኢማም አለ። በዚህም ኢማም የተደራጀው ጦር ያንን በ1525 አዳልን ሊያጠቃ የመጣው የአፄ ልብነ ድንግል አማች ከሆነው ከደገልሃን ጦር ጋር <<ዲር >> በተሰኘ ስፍራ (የዛሬዋ ድሬዳዋ አቅራቢያ) ላይ ተገናኙ። በጦርነቱም የልብነ ድንግል ጦር ውጥንቅጡ ወጥቶ እንዳልነበር ሆኖ በኢማሙ ጦር ተደመሠሠ። በዚህም ኢማሙ ድል አደረገ፤ በርካታ ሰራዊትም ማረከ። ኢማሙም የመጀመሪያን ዘመቻ በድል ጀመረ። የዚህም ኢማም ስም ኢማም አህመድ ይባላል(አህመድ ግራኝ ይሉታል እነ እገሌ) - ከ1525 -29 ባሉት አራት አመታት ውስጥ ተበታትነው የነበሩት ሙስሊሞችን ኢማሙ አሰባስቧቸውና አንድ አድርጓቸው ጠንካራ ሰራዊት የመሠረተ ሲሆን ከዚህ ቀደም በአፄ ልብነ ድንግል ተይዘው የነበሩትን የሙስሊም ግዛቶች ለማስመለስም ከፍተኛ ትግል አድርገዋል። በዚህም ደግሞ ደዋሮንና ሌሎችም ግዛቶች ከአፄው ሰራዊት በማስለቀቅ የክርስቲያኑ ጦር ወደመጣበት እንዲሸሽ አድርጓል። - የክርስቲያኑ ጦር ሙስሊሙን ለማጥቃት ሲመጣ መመከቱ እንደሚያስጠቃ የተረዳው ኢማም አህመድ ከመከላከል ይልቅ የማጥቃት ስትራቴጂን ተከተለ። በዚህም ደግሞ ጦርነቱ በአፄው ግዛት እንዲደረግ በማሠብ ጦሩ ወደ ክርስቲያኑ አገር ሄዶ እንዲያጠቃ አዘዘ። ባለቤቱ ባቲ ድል ወንበሯ ከዚህ ጦር ጋር አብራ ለመዝመት ተዘጋጀት። ጦሩ ግን በርሷ መዝመት ደስተኛ ስላልነበረ በዚህም የመጀመሪያው ዘመቻ ወቅት እስከ ኢፋት ድረስ ሸኝታቸው ተመለሠች። ( #ምንጭ ፦ Ibid, P.32) - የኢማሙን አይበገሬነት ያሳየው ታላቁ ጦርነትም #የሽምብራ_ኩሬው ጦርነት ነበር። ኢማሙ ከዚህ ጦርነት በፊት የተለያዩ ድሎችን ቢያስመዘግብም #ሽምብራ_ኩሬ ግን ወሳኙና የአፄውን ጦር ወኔ ያላሸቀ ነበር። - ሽምብራ ኩሬ በአዳማና ቢሾፍቱ መካከል በሞጆ ወንዝ አቅራቢያ ነበር የተካሄደው። ኢማም አህመድ ጦሩን አደራጅቶ ከጨረሰ በኋላ ከዝቋላ ወደ ሞጆ ወንዝ አቅራቢያ ተጓዘ። በማርች 7-1529 ኢማሙ ስትራቴጂያዊ በሆነው የሽምብራ ኩሬ መንደር ጦሩን አሠፈረ። የአፄ ልብነ ድንግል ጦር ኢማሙ ዝቋላን ለቆ መሄዱን ተመለከተ፤ ወደ ሞጆ ተከተለው። የሽምብራ ኩሬ ጦርነት ሊጀመር ነው-ማርች 11-1529። - ልብነ ድንግል 16,000(16 ሺህ) ፈረሰኞችና 200,000(200 ሺህ) እግረኛ ጦር አሰልፏል። - ኢማም አህመድ በበኩሉ 560 ፈረሰኞችና 12,000( 12 ሺህ) እግረኞች ያሉት ሰራዊት አሰልፏል። ( #ምንጭ ፦ Merid Wolde Aregay, A Reappraisal of the impact of Fire arms in the History of Warefare in Ethiopia C. 1500-1800, Joumal of Ethiopian Studies, Vol. XIV, AAU, 1980, P.101)

ከሶሒሕ ቡኻሪ አምድ ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 627 ኢብኑ ዑመር ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) “በቂያማ ቀን ጭቆና ጨለማ ይሆናል” ብለዋል። * ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 628 ኢብኑ አባስ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሙዓዝን ወደ የመን ላኩና፡- “በእርሱ(በተበዳይ) እና በአላህ መካከል መጋረጃ ስለሌለ ከተጨቆኑ ሰዎች እርግማን ፍራ። * ቅፅ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 632 ሰኢድ ቢን ዘይድ ዘግበውታል። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹የሰውን መሬት ያለ አግባብ የነጠቀ ሰው አንገቱ በርሷ በሰባት ምድር ይከበራል።(በትንሣኤ ቀን)። * ቅፅ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 633 አቡ ሰላማ ዘግበውታል። በእሱና በአንዳንድ ሰዎች (በአንድ መሬት ላይ) ክርክር ነበር. ስለ ጉዳዩ ለዓኢሻ (ረዐ) በነገራቸው ጊዜ፡- “አቡ ሰላማ ሆይ! ምድሪቱን ያለ አግባብ ከመውሰድ ተቆጠብ፤ ነቢዩም እንዲህ ብለዋል፡- “የአንድን ሰው መሬት አንድ ስንዝር እንኳ የቀማ አንገቱ በሰባቱ ምድር ይከበራል። ." * ቅፅ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 637 በአኢሻ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “አላህ ዘንድ በጣም የተጠላ ሰው በጣም ጠበኛ ነው። * ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 643 በአል-አራጅ ተረከ አቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፡- “የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ፡- ማንም ጎረቤቱን በግድግዳው ላይ የእንጨት ችንካር ከማስተካከሉ የሚከለክለው የለም። አቡ ሁረይራ (ለባልደረቦቻቸው) "ለምን ተጸየፋችኁ አገኛችኋለሁ በአላህ እምላለሁ በእርግጥ እነግረዋለሁ" አላቸው። * ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 645 በአቡ ሰኢድ አል-ኩድሪ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) "ተጠንቀቁ በመንገድ (መንገዶች) ላይ ከመቀመጥ ተቆጠብ" አሉ። ሰዎቹም “እነዚህ የምንወያይባቸው የመቀመጫ ቦታዎች በመሆናቸው መውጫ የለንም። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) "እዚያ መቀመጥ ካለብህ የመንገዱን መብት ጠብቅ" አሉ። እነሱም "የመንገድ መብት ምንድን ነው?" እነሱም ዓይኖቻችሁን ዝቅ ማድረግ (በሕገ-ወጥ መንገድ መመልከትን)፣ ሰዎችን ከመጉዳት መቆጠብ፣ ሰላምታን መመለስ፣ በመልካም መምከርና ከመጥፎ መከልከል ናቸው። * ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 653 አቡ ሁረይራ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) በመሬቱ ላይ ክርክር በተፈጠረ ጊዜ ሰባት ክንድ ለሕዝብ መንገድ እንዲቀር ፈረደ። * ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 654 አብደላህ ቢን ያዚድ አል-አንሷሪ ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዘረፋን (ያለ ፈቃዳቸው የሌሎችን መውሰዳቸውን) ከልክለዋል እንዲሁም አካልን ማጉደልን (ወይም የአካል ጉዳትን) ከልክለዋል። * t.me//AkeelComparative

. አላህ ማነው!? ።።።።።።።።።።።። አላህ እርሱ ያ፦ 2፡ 29 هو الذي خلق لكم ما في الأرض جميعا ثم استوى إلى السماء فسواهن سبع سماوات ۚ وهو بكل شيء عليم <<እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡>> 7፡ 54 إن ربكم الله الذي خلق السماوات والأرض في ستة أيام ثم استوى على العرش يغشي الليل النهار يطلبه حثيثا والشمس والقمر والنجوم مسخرات بأمره ۗ ألا له الخلق والأمر ۗ تبارك الله رب العالمين ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ ከዚያም (ስልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ፡፡ (አላህ) ሌሊትን በቀን ፈጥኖ የሚፈልገው ሲኾን ይሸፍናል፡፡ ፀሐይንና ጨረቃንም ከዋክብትንም በትእዛዙ የተገሩ ሲኾኑ (ፈጠራቸው)፡፡ ንቁ! መፍጠርና ማዘዝ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ የዓለማት ጌታ አላህ (ክብሩ) ላቀ፡ 14፡32 الله الذي خلق السماوات والأرض وأنزل من السماء ماء فأخرج به من الثمرات رزقا لكم ۖ وسخر لكم الفلك لتجري في البحر بأمره ۖ وسخر لكم الأنهار አላህ ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ከሰማይም ውሃን ያወረደ በእርሱም ከፍሬዎች ሲሳይን ለእናንተ ያወጣ መርከቦችንም በፈቃዱ በባሕር ላይ ይንሻለሉ ዘንድ ለናንተ የገራ ወንዞችንም ለናንተ የገራ ነው፡፡ 21፡ 33 وهو الذي خلق الليل والنهار والشمس والقمر ۖ كل في فلك يسبحون <<እርሱም ሌሊትንና ቀንን፣ ፀሐይንና ጨረቃንም የፈጠረ ነው፡፡ ሁሉም በፈለካቸው ውስጥ ይዋኛሉ፡፡ 25፡ 54 وهو الذي خلق من الماء بشرا فجعله نسبا وصهرا ۗ وكان ربك قديرا <<እርሱም ያ ከውሃ ሰውን የፈጠረ፣ የዝምድናና የአማችም ባለቤት ያደረገው ነው፡፡ ጌታህም ቻይ ነው፡፡>> 32፡ 7 الذي أحسن كل شيء خلقه ۖ وبدأ خلق الإنسان من طين <<ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው የሰውንም ፍጥረት ከጭቃ የጀመረው ነው፡፡ 43፡ 12 والذي خلق الأزواج كلها وجعل لكم من الفلك والأنعام ما تركبون <<ያም ዓይነቶችን ሁሉ የፈጠረ ለእናንተም ከመርከቦችና ከቤት እንስሳዎች የምትጋልቧቸውን ያደረገላችሁ ነው፡፡>> 46፡ 33 أولم يروا أن الله الذي خلق السماوات والأرض ولم يعي بخلقهن بقادر على أن يحيي الموتى ۚ بلى إنه على كل شيء قدير <<ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ እነርሱንም በመፍጠሩ ያልደከመው አላህ ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ መኾኑን አላስተዋሉምን? (በማስነሳት) ቻይ ነው፡፡ እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና፡፡>> 67፡ 2-3 الذي خلق الموت والحياة ليبلوكم أيكم أحسن عملا ۚ وهو العزيز الغفور الذي خلق سبع سماوات طباقا ۖ ما ترى في خلق الرحمن من تفاوت ۖ فارجع البصر هل ترى من فطور <<ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡ ያ ሰባትን ሰማያት የተነባበሩ ኾነው የፈጠረ ነው፡፡ በአልረሕማን አፈጣጠር ውስጥ ምንም መዛነፍን አታይም፡፡ ዓይንህንም መልስ፡፡ «ከስንጥቆች አንዳችን ታያለህን?» t.me//AkeelComparative

. የእግዚአብሔር እና የእየሱስ ልዩነቶች ክፍል 3 ⓶ የመፍጠር ልዩነት 2.1 የእግዚአብሔር ፈጣሪነት!! - ሁሉንም ፍጥረታት ያለቢጤ የፈጠረ የሆነው አንድ አምላክ ብቻ ሲሆን እግዚአብሔርም ደግሞ ይህንኑ አስመልክቶ የፍጥረታት ብቸኛ ፈጣሪ መሆኑን እና ከርሱም በስተቀር ሌላ እንደሌለ ይናገራል። - ትንቢተ ኢሳያስ 44፥24 " ሁሉን የፈጠርሁ ሠማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያፀናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ? " - ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 44 6፤ የእስራኤል ንጉሥ እግዚአብሔር፥ የሚቤዥም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። #እኔ #ፊተኛ #ነኝ #እኔም #ኋለኛ #ነኝ፥ #ከእኔ #ሌላም #አምላክ የለም። 7፤ እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ይነሣና ይጥራ ይናገርም፤ ከጥንት የፈጠርሁትን ሕዝብ ያዘጋጅልኝ፥ የሚመጣውም ነገር ሳይደርስ ይንገሩኝ። 8፤ አትፍሩ አትደንግጡም፤ ከጥንቱ ጀምሬ አልነገርኋችሁምን? ወይስ አላሳየኋችሁምን? እናንተ ምስክሮቼ ናችሁ። #ከእኔ #ሌላ #አምላክ #አለን? #አምባ #የለም፤ #ማንንም #አላውቅም። - ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 45 12፤ እኔ ምድርን ሠርቻለሁ ሰውንም በእርስዋ ላይ ፈጥሬአለሁ፤ እኔ በእጄ ሰማያትን ዘርግቼአለሁ፥ ሠራዊታቸውንም ሁሉ አዝዣለሁ። 18፤ ሰማያትን የፈጠረ እግዚአብሔር፥ እርሱም ምድርን የሠራና ያደረገ ያጸናትም፥ መኖሪያም ልትሆን እንጂ ለከንቱ እንድትሆን ያልፈጠራት አምላክ፥ እንዲህ ይላል። እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም በቀር ሌላ የለም። እንግዲህ ብጤ የሌለውና ፍጥረታትን ለብቻው የፈጠረ የሆነው የሁሉ ፈጣሪው አምላክ ፍጥረታትን ስለመፍጠሩ እንዚህህ በማለት ተናግሯል። ይህ መፍጠር ሌሎች ሊጋሩት የማይገባና ለእርሱ ብቻ የተገባ የሆነም የእርሱ ስልጣን ነው። ታድያ ይህን መፍጠር ከቁርዓን አንፃር እንዴት ይታያል? 31፡25 ولئن سألتهم من خلق السماوات والأرض ليقولن الله ۚ قل الحمد لله ۚ بل أكثرهم لا يعلمون ሰማያትንና ምድርንም የፈጠረ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ አላህ ነው ይላሉ፡፡ ምስጋና ለአላህ ይገባው በላቸው፡፡ ይልቁንም አብዛኛዎቹ አያውቁም፡፡ 39፡ 62 الله خالق كل شيء ۖ وهو على كل شيء وكيل አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ 7፡ 54 إن ربكم الله الذي خلق السماوات والأرض في ستة أيام ثم استوى على العرش يغشي الليل النهار يطلبه حثيثا والشمس والقمر والنجوم مسخرات بأمره ۗ ألا له الخلق والأمر ۗ تبارك الله رب العالمين ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ ከዚያም (ስልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ፡፡ (አላህ) ሌሊትን በቀን ፈጥኖ የሚፈልገው ሲኾን ይሸፍናል፡፡ ፀሐይንና ጨረቃንም ከዋክብትንም በትእዛዙ የተገሩ ሲኾኑ (ፈጠራቸው)፡፡ ንቁ! መፍጠርና ማዘዝ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ የዓለማት ጌታ አላህ (ክብሩ) ላቀ፡፡ ክፍል 4 ይቀጥላል ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ይህንን ቻናል ይቀላቀሉ @AkeelComparative

1.2) ለእየሱስ ብዙ አምሳያዎች አሉት! እየሱስ ከአምላክ ወይም ከእግዚአብሔር በተለየ መልኩ ብዙ አምሳያዎች እንዳሉትና በብዙ ነገሮችም ተመስሎ ተገልጿል። ከነዚህም መካከል በድንጋይ ፣ በሰው ፣ በመንፈሳዊ አለት ፣ በእግዚአብሔር ጥበብ፣ በአማላጅነት ፣... 👉 #በሰው ተመስሏል፦ - የሐዋርያት ስራ 2፥22 " የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም #ከእግዚአብሔር #ዘንድ #ለእናንተ #የተገለጠ #ሰው ነበረ ፤" 👉 #በአለት ተመስሏል፦ - 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10፥4 " ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ዓለት ጠጥተዋልና፥ #ያም #ዓለት #ክርስቶስ #ነበረ ።" 👉 #በእግዚአብሔር ሀይልና ጥበብ ተመስሏል፦ " ለተጠሩት ግን፥ አይሁድ ቢሆኑ የግሪክ ሰዎችም ቢሆኑ፥ የእግዚአብሔር ኃይልና የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:24) 👉 #በእውነተኛ #አምላክ ተመስሏል፦ " የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 5:20) 👉 #በእግዚአብሔርና #በሰው #መካከል እንደሚኖር #ሰው ተመስሏል፦ " አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:5) 👉 #በድንጋይ ተመስሏል፦ " በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:20) 👉 #አማላጅ ተደርጎ ተመስሏል፦ " የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 8:34) ✔ ሌላው መነሳት ያለበት ነጥብ ቢኖር እግዚአብሔር #ሰውን በመልኩና #በአምሳሉ ፈጠረው የሚባለው ተረት ጉዳይ ማንሳት ያስፈልጋል። ይህን የሚለው - #ዘፍጥረት 1፥26 " ሰው በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር" ብሏል በማለት ይናገራል። ✔ታድያም ከላይ እግዚአብሔር "በማን #ትመስሉኛላችሁ? እንመሳሰል ዘንድ ከማን ጋር ታስተያዩኛላችሁ?" ብሎ ነበር እዚህ ቦታ ላይ ደግሞ #ሰው #በእግዚአብሔር #አምሳያ #ተፈጠረ ይለናል። ቀጥሎም ከታች ደግሞ፦ - መፅሃፍ ኩፋሌ 4፥3 እግዚአብሔርም ለኛ እንዲህ አለን ፦ #እንደ #እርሱ #ያለ #ረዳትን #እንፍጠርለት #እንጂ #አዳም ብቻውን ይኖር ዘንድ አግባብ አይደለም አለ... - ትንቢተ ሆሴዕ 11፥9 "እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሠው አይደለሁምና..."ይላል። ስለዚህ አዳም ረዳቱ ሔዋንን የመሠለ ከሆነና እግዚአብሔር ደግሞ እንደ ሰው ያልሆነ ከሆነ ሰው የእግዚአብሔር አምሳያ ነውን? በጭራሽ!! ክፍል 3 ይቀጥላል @AkeelComparative

. የእግዚአብሔር እና የእየሱስ ልዩነቶች [[ በመፅሐፍ ቅዱስ ]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በዚህ የእግዚአብሔር እና የእየሱስ ልዩነቶች በሚል በቀረበው ጉዳይ ላይ የእነዚህን (የእግዚአብሔርና የእየሱስ) የግል ልዩነቶችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ምን እንደሚመስል የምንዳስስበት ርዕስ ይሆናል። ታድያ ስለ አንድነትና ልዩነት በንፅፅር የሚወራው ሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ የተለያዩ ማንነቶች፣ ምንነቶችና በአጠቃላይ አንድ ባልሆኑ በተለያዩ አበይት ጉዳዮች ስለሆነ ነውና የሚነፃፀረው የእግዚአብሔር እና የእየሱስም ልዩነቶች እንደዚሁ ነው የምንመለከተው። እንደሚታወቀው በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ነው እየሱስም ደግሞ አምላክ ነው። ሆኖም ግን ሁለት የተለያዩ ማንነቶች ያሏቸው የሆኑት እነዚህ እግዚአብሔርና እየሱስ መንፈስ ቅዱስንም ጨምሮ በአካል ሶስት በመለኮት ግን አንድ አምላክ ናቸው በማለት ያምናሉ። ይህንንም የተሳሳተ አመለካከታቸው እንዲገነዘቡት ሲባል ይህን ወሳኝ ርዕስ ለመዳሰስ ፈልጌያለሁ። በዚህም መሠረት የሚከተሉትን ነጥቦች በማንሳት ልዩነቶቻቸውን ተራ በተራ እንመለከታለን፦ ⓵ የአምሳያ ልዩነት 1.1 እግዚአብሔር አምሳያ የለውም! - አምላክ ሁሉን የፈጠረ የፍጥረታት ባለቤት ነው ከተባለ ለእርሱ ከፍጥረቱ #አምሳያ #ሊኖረው አይገባም። ይህ ማለት አምላክ የሚመስል፣ በስልጣን እርሱን የሚጋራ፣ በመልክም ሆነ በማንነት ከፍጡራኑ ጋር መመሳሰል የሌለበት... ሲሆን በተጨማሪም በምንነቱም ሆነ በማንነቱ ፈጣሪ አምላክ የሚመስል #ፍጡር #የለም ፤ #ወደፊትም #አይኖርም ሊኖር አይገባም። ለዚህም ደግሞ እግዚአብሔር ሲናገር እንዲህ ይላል፦ -ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 46 5፤ #በማን #ትመስሉኛላችሁ? ከማንስ ጋር ታስተካክሉኛላችሁ? #እንመሳሰል #ዘንድ #ከማን #ጋር #ታስተያዩኛላችሁ? - ትንቢተ ኢሳይያስ 45፥21 " ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ፤ ከጥንቱ ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማን ነው? ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ እኔ ጻድቅ አምላክና መድኃኒት ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም።" - ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 46 9፤ እኔ አምላክ ነኝና፥ ሌላም የለምና የቀድሞውን የጥንቱን ነገር አስቡ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ #እንደ #እኔም #ያለ #ማንም የለም። 10፤ በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ። - ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 43 10፤ ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ እኔም እንደሆንሁ ታስተውሉ ዘንድ፥ እናንተ የመረጥሁትም ባሪያዬ ምስክሮቼ ናችሁ ይላል እግዚአብሔር፤ #ከእኔ #በፊት #አምላክ #አልተሠራም #ከእኔም #በኋላ #አይሆንም። 11፤ እኔ፥ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ #ከእኔ #ሌላም #የሚያድን #የለም። ይህን እውነት አላህ(ሱወ) በቅዱስ ቁርዓንም እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፦ 112፡ 4 ولم يكن له كفوا أحد "And there is none co-equal or comparable unto Him." «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» ........... ///........ ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ @AkeelComparative .............///........... ክፍል 2 ይቀጥላል

ት እየሱስ ለደቀመዛሙርታቸው በአህዛብ መንገድ አትሂዱ ብለዋቸው ስለነበር። - የማቴዎስ ወንጌል 10፥5 " ወደ ጠፉት የእስራኤል በጎች ቤት እንጂ በአህዛብ መንገድ አትሂዱ.." - ስለዚህ እየሱስ ለደቀመዛሙርታቸው ወደ አህዛብ አትሂዱ ነው ያሉአቸው እንጂ ወደ አህዛብ ሄደው በአብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቁ አላዘዙኣቸውም። እናም እየሱስ ስለክርስትና እምነት ምንም ያሉት ጉዳይ ከሌለ ታድያ የክርስትና እምነት መሥራቹ (አናፂው)ማነው? የዚህ ሀይማኖትም የእምነቱ መሠረት የጣለና እምነቱንም የመሠረተው አናፂ ጳውሎስ ራሱ እንደሆነ እንዲህ በማለት ይናገራል፦ - 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3፥10-11 " የእግዚአብሔር ፀጋ እንደተሠጠኝ መጠን እንደ ብልሀተኛ የአናፂ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ። ሌላውም በላዩ ያንፃል፥ ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልም እርሱም እየሱስ ክርስቶስ ነው።" በዚህ መልኩ ጳውሎስ የክርስትናን እምነት እየሱስ ላይ መሠረት አድርጎ እንደ የአናፂ አለቃ መሠረትን መስርቷል። በመቀጠልም ስለ እምነቱ መለኮታዊ አስተምህሮዎች ሲደነግግ እንዲህ ይላል፦ - 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፥ 2-5 " የምትድኑበት ወንጌል አሳስባችኋለሁ፥ እኔ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ ፥ እንዲህ ብዬ መፅሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለሀጢአታችን ሞተ በሶስተኛውም ቀን ተነሳ።" - ወደ ዕብራውያን 6፥1-2 " የክርስቶስን ነገር መጀመሪያ የሚናገረውን ቃል ትተን ወደ ፍጻሜው እንሂድ መሠረትን ደግመን እንመስርት እርሱም ከሞተ ስራ ንስሀና በእግዚአብሔር እምነት ስለጥምቀቶችና እጆችንም ስለመጫን ስለሙታንም ትንሳኤ ስለዘላለም ፍርድም ትምህርት ነው።" አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራችሁ! ለእኛም ፅናቱን ይስጠን። ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀላሉ

. የክርስትና እምነት ( የሐይማኖቱ) አመሠራረት 👉 ክርስትና #የት ፣ #መቼና በማን# ተመሠረተ ክርስትና የዛሬ 2016 አመት አካባቢ በቤተክርስቲያን ሰዎች አማካኝነት የተመሠረተ በሰው የተፈጠረ እምነት ሲሆን በአንጻሩ እስልምና ግን ሰዎች የተፈጠሩበት አምነት ነው። 30፡ 30 فأقم وجهك للدين حنيفا ۚ فطرت الله التي فطر الناس عليها ۚ لا تبديل لخلق الله ۚ ذلك الدين القيم ولكن أكثر الناس لا يعلمون <<ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን (ሃይማኖት ያዟት)፡፡ የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም፡፡ ይህ ቀጥተኛ ሃይማኖት ነው፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም፡፡>> 1.1) ክርስትና የት ተመሠረተ? ክርስትና የተመሠረተው አሁን ላይ ሶሪያ ተብላ በምትጠራው ሀገር ላይ ሲሆን አንጾኪያ በሚባል ቤተክርስቲያንም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ መመሥረቱን ተጠቅሷል። - የሐዋርያት ስራ 11፥26 " ጳውሎስና በርናባስ በአንፆኪያ ቤተክርስቲያን ብዙ ህዝብን አስተማሩ ፥ ለመጀመሪያ ጊዜም #ክርስቲያን ተባሉ።" 1.1) መቼ ተመሠረተ? ክርስትና የተመሠረተው እየሱስ ካረጉ በኋላም ከ3- 14 ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ ነበር። ይህም ጳውሎስ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ እየሩሳሌም ወጥቶ እያለም ህግን እየተቃወመ እየሱስን በሚሰብክበት ወቅት ከእየሩሳሌም እንዲወጣ ተደረገና ከከተማው ሲባረርም ወደ ጠርሴስ ሰደዱት። በዚህም ጊዜ በርናባስ ወደ ጠርሴስ ሄዶ ጳውሎስን ወደ አንጾኪያ ወሰደውና በዚያም የክርስትናን ሀይማኖት መሠረተ።ለዚህም ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦ - ወደ ገላትያ ሰዎች 1፥ 17-18 " ከኔም በፊት ሀዋርያ ወደነበሩት እየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ አረብ ሀገር ሄድኩ እንደገናም ወደ ደማስቆ ተመለስኩ፤ ከ3 አመት በኋላም ኬፋን ልጠይቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ እየሩሳሌም ወጣሁ፤ በዚያም 15 ቀናት ኖርኩ።" ይላል - የሐዋርያት ስራ 9፥1-43 " ከዚያም ጳውሎስ ከእየሱስ ደቀመዛሙርት ጋር ሊተባበር ፈለገ፥ እነርሱ ግን ሀዋርያ እንዳልሆነ ስላወቁ ፈሩት። ህግን እየተቃወመ እግዚአብሔርን ያመልካል በማለት ክስ መስርተውበት ከእስራኤልም አባረሩት፤ እርሱም ደግሞ ወደ ቂሳሪያ ጠርሴስ አመራ። " - የሐዋርያት ስራ 11 ፥ 25-26 " በርናባስም ጳውሎስን ሊፈልግ ወደ ጠርሴስ ሄደ አግኝቶትም ወደ አንጾኪያ ወሰደው። በዚያም ብዙን ህዝብ አስተማሩ፤ በአንጾኪያ ቤተክርስቲያንም ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቲያን ተባሉ።" ℹ እናም ጳውሎስ ከእስራኤል ከተባረረና በአንፆኪያም ሲኖር የክርስትናን እምነት መሥርቶ ህዝቡን ካስተማረ ወዲህም ዳግም ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እየሩሳሌም የወጣውም ከ14 ዓመታት በኋላ ነበር። - ወደ ገላትያ ሰዎች 2፥1 " ከዚያ ወዲያ ከ14 አመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ይዤ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እየሩሳሌም ወጣሁ።" ይላል የዚህ ተቃራኒ የሆነው እስልምና ግን የመጀመሪያዎቹ ነቢያትም የተላኩበት እምነት መሆኑን እንዲህ ተጠቅሷል ፦ 42፡13 شرع لكم من الدين ما وصى به نوحا والذي أوحينا إليك وما وصينا به إبراهيم وموسى وعيسى ۖ أن أقيموا الدين ولا تتفرقوا فيه ۚ كبر على المشركين ما تدعوهم إليه ۚ الله يجتبي إليه من يشاء ويهدي إليه من ينيب <<ለእናንተ ከሃይማኖት ያንን በእርሱ #ኑሕን ያዘዘበትን ደነገገላችሁ፡፡ ያንንም ወዳንተ ያወረድነውን ያንንም በእርሱ ኢብራሂምን ሙሳንና ዒሳንም ያዘዝንበትን ሃይማኖትን በትክክል አቋቁሙ በእርሱም አትለያዩ ማለትን (ደነገግን)፡፡ በአጋሪዎቹ ላይ ያ ወደርሱ የምትጠራቸው ነገር ከበዳቸው፡፡ አላህ የሚሻውን ሰው ወደእርሱ (እምነት) ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደርሱ ይመራል፡፡ 1.3 የክርስትና ሀይማኖት በማን ተመሠረተ? ብዙዎች የእምነቱ ተከታዮች የክርስትናን ሀይማኖት የመሠረተው እየሱስ ነው በማለት በልበ ሙሉነት ይናገራሉ። ታድያም አማኞቹ በይሆናል ምኞት ይህን ይበሉ እንጂ እየሱስ ግን አንድም ቦታ ላይ የክርስትናን ስም አንስተውም ተናግረውም አያውቁም። ይህም ብቻ አይደለም ከሀይማኖቱ መሠረታዊ ጉዳዮችና ከእምነቱ መለኮታዊ አስተምህሮዎች መካከልም አንድ እንኳን እንዲህ ነው በማለት ያስተማሩት ነጥብ የለም። ሐይማኖቱንም የተመሠረተው #በጳውሎስ አማካኝነት ነው። እኛ ሙስሊሞች ለክርስቲያን ወገኖቻችን እየሱስ ስለክርስትና ሀይማኖት ያስተማሩት ምንም ነገር የለም በምንላቸው ጊዜ እነርሱ የሚያነሱት አንድ ነጥብ አለ ይህም ስለ ሶስቱ ስላሴ በማቴዎስ ወንጌል አስተምሯል በማለት ይናገራሉ። የዚህ ጉዳይ ነገር ግን እንደሚከተለው ነው፦ - የማቴዎስ ወንጌል 28፥ 19-20 " እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ በአብ በወልድ መንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀመዛሙርት አድርጓቸው። እነሆም እኔ እስከ አለም ፍፃሜ ድረስ ሁልጊዜ ከናንተ ጋር ነኝ።" ይላል!! እየሱስ ስለ ሶስቱ ስላሴ አስተምሯል ብለው የሚሟገቱበት ነጥብ ይህን ነው። ታድያም ይህ ንግግር ለእነርሱ እውነትም የእየሱስ ንግግር ይምሰላቸው እንጂ እውነቱን ግን ሌላ ነው። ይህ የማቴዎስ ወንጌል 28፥19-20 የእየሱስ አስተምህሮ አለመሆኑን ነፍ ማረጋገጫዎች አሉ። እኔ ግን ሁለት ምክንያቶችን ብቻ አቀርባለሁ 1ኛ) ምክንያት በመጀመሪያ ደረጃ ይህን ንግግር የተናገረው ሰውዬ እየሱስ አይደሉም። ምክንያቱም፦ ሀ) እንደነርሱ አባባል ከሆነ ይህ ንግግር በተነገረበት ወቅት እየሱስ ሞቶ ነበር እንጂ በህይወትና በስብከት ስራ ላይ አልነበረም፤ እንዲሁም ደግሞ መቃብሩም ጋር ሲመጡ እየሱስ አልነበረም። ለ) ይህ የተናገረው እየሱስ ነው የምትሉ ከሆነ ደቀመዛሙርቱ ግን እየሱስ እንዳልሆነ አውቀው ነበር፦ - የማቴዎስ ወንጌል 28፥16- 18 " ለአስራ አንዱም ደቀመዛሙርት እየሱስ እንዳዘዛቸው ወደ ገሊላ ተራራ ሄዱ። ባዩትም ጊዜ ተጠራጠሩት።" - ስለዚህ ደቀመዛሙርቱ እየሱስን አያውቁትም ነበር ወይስ ለምን ተጠራጠሩ? ምክንያቱ ግልፅ ነው ሰውዬው እየሱስ ስላልሆነ ነው። ሐ) እየሱስ ወደ አምላካቸው የሚሄዱበት ሰዓት መድረሱን ባወቁ ጊዜ ለደቀመዛሙርትም ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም ወደ አብ እሄዳለሁ ብለዋቸው ነበር። - የዮሐንስ ወንጌል 16፥17 " ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ ታዩኛላችሁ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ አታዩኝም፥ ወደ አብ እሄዳለሁና።" - የዮሐንስ ወንጌል 8፥23 " እናንተ ከዚህ አለምና ከታች ናችሁ፥ እኔ ግን ከዚህ አለም አይደለሁም ከላይ ነኝ።" ብለው ነበር። እናም ስለ ሶስቱ ስላሴ የተናገረው እየሱስ ነው ስለሚሉት ሰውዬ ጋር ልምጣና ይህ ሰው እዛው ንግግሩ ላይ በማቴዎስ 28፥19-20 ".... እስከ አለም ፍፃሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ" ብሏል። - ስለዚህ ስለ ስላሴው የተናገሩት እየሱስ ከሆኑና እስከ አለም ፍጻሜ ከእነርሱ ጋር ከሆኑ እየሱስ ቃላቸው የማይጠብቁ ውሸታም ናቸው ማለት ነው? አይደለም ተናጋሪው እየሱስ አይደሉም ነው። 2ኛ) ምክንያት ይህን የማቴዎስ ወንጌል 28፥19-20 ንግግር የተናገሩት እየሱስ አይደሉም። ምክንያቱም ደግሞ ይህ ንግግር ከእየሱስ የወንጌል አስተምህሮታቸው ጋር ስለሚጋጭ። ይህም ማለ