en
Feedback
እስልምና እና ክርስትና

እስልምና እና ክርስትና

Open in Telegram

t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!

Show more
315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
99 የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፍል -7 ⓻ አል- ዓዚዝ {{ العزيز }} [[[[ አሸናፊ ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ <አል- ዓዚዝ> ሌላኛው የአላህ ስም ነው። አል ዓዚዝ ማለት "አሸናፊ " ማለት ሲሆን ፈፅሞ የማይሸነፍ፣ ሀያሉ፣ ብርቱው እንደማለት ነው። ብዙ ጊዜ ብዙ ሰዎች ልጆቻቸውን <አብዱል ዓዚዝ> (የአል-ዓዚዝ ባሪያ) በማለት ስም ሲሰይሙላቸው እንመለከታለን። ታድያ የአሸናፊው ጌታ ባሪያ ተብሎ መጠራትን በእርካታ የተሞላ ውስጣዊ ደስታ ይሰጣል፤ የብርቱነትና የአሸናፊነት መንፈስን ያጎናፅፋል። ✔ በቋንቋ ደረጃ <አል-ዓዚዝ> የሚለው ቃል በርካታ ትርጉሞች አሉት። ለምሳሌ፦ ሀ)"አል-ዓዚዝ" ማለት አንድም አቻ የሌለው ማለት ነው። 42፡11 #ليس كمثله شيء << የሚመስለው ምንም ነገር የለም።>> አረቦች "አል-ዓዚዝ " ማለት <የማይገኝ> ማለት ነው ይላሉ። ለምሳሌ የማይገኝ ልምድ ይላሉ። አላህ(ሱወ) አል-ዓዚዝ ነው ስንል አምሳያ የለውም፤ አጋር የለውም ማለታችን ነው። ለ) <አል-ዓዚዝ> ማለት አሸናፊና ፈፅሞ የማይሸነፍ ማለት ነው። - አንድ የሠው ልጅ ብዙ ጊዜ በሆነ ነገር እያሸነፈ ይኖርና ነገር ግን የሆነ ሰዓት ላይ ይሸነፋል። ለምሳሌ 1 ፦ የዘመናችን ምርጡ የአጭር ርቀት ሯጭ የነበረው ጃማይካዊው ቦልት በሩጫ ህይወቱ ሁሌም አሸናፊ ስለነበር ብዙ ክብረወሰኖችን የግሉ አድርጓል፤ ብዙ ውድድሮችን በተከታታይ ለአመታት አሸንፏል ነገር ግን የህይወቱን የመጨረሻውን ውድድር ሊያካሄድ ወደ ትራክ በገባበት ወቅት በአሜሪካዊው ሯጭ ተቀድሞ በውድድሩ ተሸንፎ ከሩጫ ዓለም ተሰናበተ።ስለዚህ እንደዚህ አይነት ያለው አካል <ዓዚዝ> ልንለው አይባልም ምክንያቱም የሠው ልጅ ተሸናፊ ከሆነ አሸናፊ ልንለው አይገባም። 12፡ 21 وقال الذي اشتراه من مصر لامرأته أكرمي مثواه عسى أن ينفعنا أو نتخذه ولدا ۚ وكذلك مكنا ليوسف في الأرض ولنعلمه من تأويل الأحاديث ۚ والله غالب على أمره ولكن أكثر الناس لا يعلمون <<... አላህም በነገሩ ላይ #አሸናፊ ነው፤ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም።>> ምሳሌ 2፦ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች እነ ሊቨርፑል፣ ሪያልማድሪድ፣ ባርሴሎና... የመሳሰሉት ሀያላን ክለቦች ለሁለት የውድድር ዘመን በአንድ ጨዋታ እንኳን ሳይሸነፉ ወጥ በሆነ አሸናፊነት በድል ሊጓዙ ይችላሉ። ነገር ግን በሶስተኛው አመት ሲሸነፉ ይታያል። ሌላም ምሳሌ፦ ሀያላን መንግስታት በተደጋጋሚ ጊዜ ለጦርነት በሚፋለሙበት ጊዜ ሁሌም ድል እያደረጉና እያሸነፉ ይኖሩና የሆነ ሰአት ላይ ይሸነፋሉ ፤በዚህም ወይ ይገደላሉ አሊያም ከስልጣን ይባረሩና የፓርቲያቸውም ድርጅት ተፈረካክሶ ይታያል። ለአብነትም ያክል የሩም፣የባቢሎን፣... ታድያ እነዚህ ክለቦችና ሀያላን መንግስታት ተሸናፊዎች ናቸውና <ዓዚዝ> ሊባሉ አይችሉም። በአንጻሩ አል ዓዚዙ አሏህ ግን፦ 3፡ 126 وما جعله الله إلا بشرى لكم ولتطمئن قلوبكم به ۗ وما النصر إلا من عند الله العزيز الحكيم << አላህም እርዳታውን ለእናንተ ብስራትና ልቦቻችሁ በእርሱ እንዲረኩ እንጂ ሌላ አላደረገም። #ድልም #መንሳት #አሸናፊ ጥበበኛ ከሆነው አላህ ዘንድ እንጂ ከሌላ አይደለም።>> ሐ) አል ዓዚዝ ያጠነክረናል፣ ተጨማሪ ሀይል ይሰጠናል፣ ያግዘናል፣ እንበረታ ዘንድ ድጋፍ ይሰጠናል። ለምሳሌ በያሲን ምዕራፍ ውስጥ አሏህ (ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 36፡ 14 إذ أرسلنا إليهم اثنين فكذبوهما فعززنا بثالث فقالوا إنا إليكم مرسلون << ወደነርሱ ሁለትን ሰዎች በላክንና ባስተባበሉአቸው ጊዜ፥ በሶስተኛም በአበረታናቸው>> ሌላም ምሳሌ እንመልከት ፦ መቼም የበድር ጦርነትን ሲራ ሲወራ በተደጋጋሚ ሰምተናልና ሙስሊሞች በቁጥር 303 የነበሩ ሲሆን ሁለት ፈረሶችም ነበሩ። ሙሽሪኮች ደግሞ 1000 ወታደሮች ሲያሰልፉ 200 ፈረሶች ነበሯቸው። ታድያ ያንን ሁላ የሙሽሪኮች የጦር ሰራዊትን ሲደመስስ የአሏህ እርዳታ መጥቶላቸውም ነበር። እናም በሺህ የሚቆጠሩ መላዒካዎች (74 ፡31 ይመልከቱ) ከሠማይ በመውረድ ነበር ሙሽሪኮችን የበረሃ ሲሳይ ያደረጓቸው።

99 የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፍል -6 ⓺ አል ሙሀይሚኑ المهيمنو } [[[ ባሮቹን ጠባቂው ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ▷ #አል #ሙሀይሚኑ ፦ ማለት ባሮቹን ጠባቂ የሆነ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የበላይ ሀያል የሚል ትርጉምም ይኖረዋል። ▷ አል-ሙሀይሚን በቁርዓን ውስጥ 59፡ 23 هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام المؤمن #المهيمن العزيز الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ #ባሮቹን #ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።>> ብዙውን ጊዜ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለደህንነታቸው ብለው body Guard ይቀጥሩና በየሄዱበት መሣሪያ ተሸክመው ሲከተሏቸው እናስተውላለን። ነገር ግን ይህ ጥበቃ የተሟላ ጥበቃ አይደለም። ለምሳሌ ከመኪና፣ ከአውሮፕላን መከስከስና ከሌሎችም...ይቅርና በአስተማማኝ ሁኔታ ከጠላት እንኳን የሚጠብቅ አይደለም። ነገር ግን የአሏህ ጥበቃ ከዚህ ይለያል፦ 22፡ 78 وجاهدوا في الله حق جهاده ۚ هو اجتباكم وما جعل عليكم في الدين من حرج ۚ ملة أبيكم إبراهيم ۚ هو سماكم المسلمين من قبل وفي هذا ليكون الرسول شهيدا عليكم وتكونوا شهداء على الناس ۚ فأقيموا الصلاة وآتوا الزكاة واعتصموا بالله هو مولاكم ۖ فنعم المولى ونعم النصير <<በአላህም ሃይማኖት ተገቢውን ትግል ታገሉ፡፡ እርሱ መርጧችኋል፡፡ በናንተም ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡ የአባታችሁን የኢብራሂምን ሃይማኖት ተከተሉ፡፡ እርሱ ከዚህ በፊት ሙስሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል፡፡ በዚህም (ቁርኣን)፤ መልክተኛው በእናንተ ላይ መስካሪ እንዲሆን እናንተም በሰዎቹ ላይ መስካሪዎች እንድትኾኑ (ሙስሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል)፡፡ ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፣ ዘካንም ስጡ፣ በአላህም ተጠበቁ፣ እርሱ ረዳታችሁ ነው፡፡ (እርሱ) ምን ያምር ጠባቂ! ምን ያምርም ረዳት! >> @AkeelComparative ይህን የአል-ሙሀይሚኑ አሏህ ጥበቃ ግን ከየትኛውንም ችግር የሚጠብቅ የሆነ የተሟላ ጥበቃ ነው። የአሏህ እውቀት ሁሉንም ያካበበ ዕውቀት ስለሆነ በጊዜ በቦታና በሁኔታ በማይገደበው ዕውቀቱም ከየትኛውንም ጉዳት ይጠብቀናል፤ በየትኛውንም ጠላት እንዳንጠቃ ያደርገናል። ለዚህም አላህ (ሱወ) እንዲህ በማለት ይናገራል፦ 4፡ 45 والله أعلم بأعدائكم ۚ وكفى بالله وليا وكفى بالله نصيرا "Allah has full knowledge of your enemies, and Allah is Sufficient as a Wali (Protector), and Allah is Sufficient as a Helper." << አላህም ጠላቶቻችሁን አዋቂ ነው። ጠባቂነትም በአላህ በቃ። ረዳትነትም በአላህ በቃ።>> ክፍል -7 ይቀጥላል t.me//AkeelComparative

ለ) ሁለተኛው ደግሞ አዱንያ ላይ ከቅጣት ያራቃቸው/የቀጣቸው ከሐዲዎችን በመጨረሻውም አለም ላይ በብርቱ ቅጣት የሚቀጣ የሆነ ሲሆን አማኞችን ግን ከቅጣቱ የሚያድናቸው የሆነ ጌታ ማለት ነው 39፡ 24 أفمن يتقي بوجهه سوء العذاب يوم القيامة ۚ وقيل للظالمين ذوقوا ما كنتم تكسبون << በትንሳኤ ቀን ክፉን ቅጣት በፊቱ የሚመክት ሰው (ከቅጣት እንደሚድን ነውን?) ለበዳዮችም <ትሠሩት የነበራችሁትን (ቅጣቱን) ቅመሱ> ይባላሉ።>> 3፡56 << እነዚያማ የካዱትን ሰዎች በቅርቢቱ አለምና በመጨረሻይቱ አለም ብርቱ ቅጣት እቀጣቸዋለሁ። ለእነርሱም ምንም ረዳቶች የሏቸውም።>> ✔ አል ሙዕሚን (ፀጥታን ሰጪው) ሌላኛው የአል-ሙዕሚን ትርጉም " #ፀጥታን #ሰጪው " የሚል ነው። 59፡ 23 هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام #المؤمن المهيمن العزيز الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ #ፀጥታን #ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።>> ▷ አል ሙዕሚን ማለት ትርጉሙ "ፀጥታን ሰጪው" ማለት ነው ሲል ምን ማለት ነው?? እስቲ አንድ ነገር እንመልከት ፦ ምሽት ከ4፡00 በኋላ ከቤት ወደ ውጪ ወጥተን የአካባቢያችንን ድባብ እንቃኝ!! ምንድነው Observe የምናደርገው?? ደምጽ፣ ሁከት፣ ጫጫታ፣ ረብሻ... የሌለበት ጸጥ ረጭ ያለ ሰላማዊ ምሽት አንመለከትም?? 6፡13 وله ما سكن في الليل والنهار وهو السميع العليم << በሌሊትና በቀንም ፀጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው። እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው።>> ይህ ነው እንግዲህ አል-ሙእሚን ማለት። ሌላው ደግሞ እስቲ ለደቂቃ እንኳን በምዕናባችን ከሀገራችን እንውጣና ጦርነት የበዛባቸውና በጦርነት የፈረሱ ሐገሮችን እንደነ ሶሪያ፣የመን፣ሊቢያ፣... የመሳሰሉትን ሐገሮች እንቃኝ!! ከነዚህ ሐገሮች አንጻር ሲታይ ወደቀዬአችን እንመለስና የኛን ሰላማዊ ኑሮ ስንመለከት ምንድ ነው ወደ አዕምሮአችን የሚመጣው? 29፡ 67 أولم يروا أنا جعلنا حرما آمنا ويتخطف الناس من حولهم ۚ أفبالباطل يؤمنون وبنعمة الله يكفرون << ሰዎቹ ከዙሪያቸው ሲነጠቁ እኛ አገራቸውን ፀጥተኛ ክልል ማድረጋችንን አያዩምን? በውድቅ ነገር ያምናሉን? በአላህም ፀጋ ይክዳሉን? >> ለፍጡራኖቹ ሰላምን የሚሰጥ ጌታ ማለት አላህ ነው እርሱም አል-ሙእሚን የሆነ ነው። ክፍል -6 ይቀጥላል

ክፍል -5 ⓹ አል- ሙዕሚኑ { المؤمنو } [[[ ከቅጣት የሚያድን/ ጸጥታን ሰጪው ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ▷ አል-ሙዕሚኑ ፦ ይኽኛው ስም ሌላኛው ከአሏህ 99 የመልካም ስሞች መካከል አንዱ ነው፤ ትርጉሙንም " #ከቅጣት #የሚያድን " ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ "ፀጥታን ሰጪው" ማለት ነው። ▷ አል- ሙዕሚን ከቅጣት የሚያድን ነው ብለን በምንልበት ጊዜ ይህም ሁለት አይነት ትርጉምን የተላበሰ ነው። ሀ) አሏህ(ሱ.ወ) ከሐዲዎችን አዱንያ ላይ እርሱ ከፈለገ ከቅጣት የሚያርቃቸው አልያም ደግሞ መሠረታቸውን የሚቆርጥ የሆነ ማለት ሲሆን አማኞችን ግን ከቅጣት የሚያድን የሆነ ማለት ነው። 2፡ 96 ولتجدنهم أحرص الناس على حياة ومن الذين أشركوا ۚ يود أحدهم لو يعمر ألف سنة وما هو بمزحزحه من العذاب أن يعمر ۗ والله بصير بما يعملون << ከሰዎችም ሁሉ ከእነዚያ (ጣኦትን) ካጋሩት ይበልጥ በህይወት ላይ የሚጓጉ ሆነው በእርግጥ ታገኛቸዋለህ። አንዳቸው ሺህ ዓመት እድሜ ቢሰጥ ይወዳል። እርሱም እድሜ መሰጠቱ ከቅጣት የሚያርቀው አይደለም። አላህም የሚሰሩትን ሁሉ ተመልካች ነው።>> 7፡ 72 فأنجيناه والذين معه برحمة منا وقطعنا دابر الذين كذبوا بآياتنا ۖ وما كانوا مؤمنين << እርሱንና እነዚያንም አብረውት የነበሩትን ከእኛ በሆነው ችሮታ ከቅጣት አዳንናቸው። የእነዚያንም በተአምራታችን ያስተባበሉትንና አማኞች ያልነበሩትን መሠረት ቆረጥን።>> ይህን (የ7፡72) ታሪክ ስንመለከት የነብዩላህ ሁድ(ዐሰ) እና የህዝቦቻቸውን ታሪክ ፍፃሜው ምን ይመስል እንደነበር ነው የሚገልፅልን። [[ 7፡65-72 ፣ 11፡50-60 ፣ 26፡123-140 ፣ 46፡21-26 እነዚህ ምዕራፎችን በማየት ሙሉ መረጃውን ያግኙ።]]] ታድያም በጊዜው ነብዩላህ ሁድ(ዐሰ) ለወገናቸው አላህን በብቸኝነት ተገዙ እኔም የአላህ መልዕክተኛ ነኝ ብለው አንድ አምላክን የመገዛት ጥሪ በሚያስተላልፉበት ወቅት ሠዎቹ ብዙ አማልክት እንጂ አንድ አላህን አንገዛም ብለው ነብያቸው ላይ አላገጡ። በዚህ ጊዜ አሏህ(ሱወ) የደመና ነፋስ እላያቸው ላይ ልኮባቸው ቅጣት አመጣባቸው፤ በዚህም እነዚህ ከሐዲዎችን አጠፋቸው ሙስሊሞችን ግን አዳናቸው። ለዚህም ደግሞ አሏህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦ 46፡ 24-25 { فلما رأوه عارضا مستقبل أوديتهم قالوا هذا عارض ممطرنا ۚ بل هو ما استعجلتم به ۖ ريح فيها عذاب أليم... } << ሸለቆዎቻቸውን ተቅጣጪ አግዳሚ ደመና ሆኖ ባዩትም ጊዜ <ይህ አዝናቢያችን የሆነ ደመና ነው> አሉ። (ሁድም) <አይደለም ፤ እርሱ ያ በእርሱ የተቻኮላችሁበት መዐት ነው። በውስጧ አሳማሚ ስቃይ ያለባት ነፋስ ናት። በጌታችሁ ትዕዛዝ አንዳችሁ ሁሉ ታጠፋለች > አላቸው። ከመኖሪያቸውም በስተቀር ምንም የማይታዩ ሆኑ። እንደዚሁ አመፀኞች ህዝቦች እንቀጣለን።>> በማለት ይናገራል። እናም አል-ሙዕሚን እዚህ አለም ላይ አመፀኞች ከሐዲዎችን በብርቱ የሚቀጣ አሊያም ለጊዜው የሚተው ሲሆን አማኞችን ግን ከቅጣት የሚያድን የሆነ ጌታ መሆኑን ይገልፃል።

⓸ አስ -ሰላም {{ السلآم }} [[[ የሰላም ባለቤት ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ አቡ ሁረይራ በዘገቡት ሐዲስ። የአላህ መልእክተኛም(ሰዐወ) "አላህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት ማለትም ለመቶ አንድ ሲቀር። እነርሱ ያወቀም ጀነት ይገባል" ብለዋል። (ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 3 , መፅሐፍ 50, ቁጥር 894 & ሀዲስ ቁጥር 419 ቅጽ 8) ታድያ እኛም እነዚህን 99 የአላህ መልካም ስሞች ጠንቅቀን ሙሉ በሙሉ አውቀን በዚህም ሰበብ ደግሞ ኢንሽ አላህ የጀነት በር እንዲከፈትልን እንትጋ!! ▷ አስ -ሰላም { السلام } ፦ ምን ማለት ነው? አስ -ሰላም ማለት የሰላም ባለቤት የሆነ ማለት ነው። አላህ(ሱወ) የሰላም ጌታ ሲሆን በፍጡራኖቹ ሁሉ ላይም ሰላም የሚያሰፍን የሆነ የሠላም አምላክ ነው። 59፡ 23 هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس #السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ #የሰላም #ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።>> አሏህ የሰላም ባለቤት ነው ሲባል በዚህ ዓለም ላይ ለሁሉም ፍጥረቱ ሰላም የሚሰጥ ነው ማለት ሲሆን በተለይ ለባሪያዎቹ ደግሞ ደህንነታቸው ጠብቆላቸው እንዲኖሩ ያደርጋል። የሰላም ባለቤቱ ጌታ ሁሉንም በእኩል የሚመለከት ሲሆን ሙስሊም ነው ክርስቲያን ነው አይሁድ ነው... ነው ብሎ አይመርጥም ለሁሉም የራሱ የሆነ ሠላም የሚችር ጌታ ነው። ለሙዕሚኖች ወይም እርሱን ለሚወዱት ደግሞ በተለየ መልኩ ሠላም ይሰጣል። ለምሳሌ አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 5፡ 16 يهدي به الله من اتبع رضوانه سبل السلام ويخرجهم من الظلمات إلى النور بإذنه ويهديهم إلى صراط مستقيم << አላህ ውዴታውን የተከተሉትን ሰዎች የሰላምን መንገዶች በእርሱ ይመራቸዋል። በፈቃዱም ከጨለማዎች ወደ ብርሃን ያወጣቸዋል። ወደ ቀጥተኛውም መንገድ ይመራቸዋል።>> ክፍል 5 ይቀጥላል

✔ ሌላው የክርስቲያኖች አሳዛኝ ንግግር ደግሞ ፈጣሪ ልጅ ይዟል፣ አምላክ በሰው መልክ ተወልዷል እና ሌሎችንም... መሠል ንግግሮችን ያለአንዳች እፍረት የሚቀጥፉት ቅጥፈት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ የጳውሎስ አስተምህሮን ብንመለከት - የሐዋርያት ስራ 8፥37 " እየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው።" - የሐዋርያት ስራ 9፥20 " ወዲያውም እርሱ የእየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በምኲራብ ሰበከ።" መቼም አምላካችን እንደ ሠው አይደለምና ለቅጣት አይቸኩልም። ነገር ግን እርሱ ያልወለደም ያልተወለደ ጌታ ነው። አል-ቁድዱስ የሆነው ፈጣሪያችን ከሁሉ የተብቃቃ ጌታ ነውና ምንም ነገር መፍጠር ሲፈልግ "ሁን" ብቻ ነው የሚለው ወዲያውም ይሆናል። ታድያ ይህ ጌታ የተብቃቃና ከጉድለት ሁሉ የጠራ ነው ከተባለም ልጅን መያዝ ምን ያደርግለታል? አላህ (ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 19፡ 35 ما كان لله أن يتخذ من ولد ۖ سبحانه ۚ إذا قضى أمرا فإنما يقول له كن فيكون << ለአላህ ልጅን መያዝ አይገባውም። (ከጉድለት ሁሉ) ጠራ። ነገርን በሻ ጊዜ ለርሱ የሚለው << ኹን >> ነው ወዲያውም ይሆናል። 10፡ 68 قالوا اتخذ الله ولدا ۗ سبحانه ۖ هو الغني ۖ له ما في السماوات وما في الأرض ۚ إن عندكم من سلطان بهذا ۚ أتقولون على الله ما لا تعلمون << "አላህ ልጅን ያዘ (ወለደ)" አሉ። (ከሚሉት) ጥራት ተገባው። እርሱ ተብቃቂ ነው። በሰማያትና በምድር ያሉው ሁሉ የእርሱ ነው። እናንተ ዘንድ በዚህ (በምትሉት) ምንም አስረጅ የላችሁም። በአላህ ላይ የማታውቁትን ትናገራላችሁ።>> ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative

⓷ አል- ቁድዱሱ ( القدوس ) [[[ ከጉድለት ሁሉ የጠራ ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ - በቋንቋ ደረጃ አል-ቁድዱስ ማለት ቀጥተኛ ትርጉሙ <ከጉድለት ሁሉ የጠራ> ማለት ነው። 59፡ 23 هو الله الذي لا إله إلا هو الملك #القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሱ፣ #ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሠላም ባለቤቱ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሀያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።>> ▷ ከ99 የጌታችን መልካም ስሞች መካከል አል-ቁድዱስ አንዱ ነውና ለመሆኑ የአል -ቁድዱስ ትርጉሙ " ከጉድለት ሁሉ የጠራ " ማለት ነው ሲባል እንዴት ነው! #ከጉድለት #ሁሉ #መጥራት ማለት ምን ማለት ነው! "ከጉድለት ሁሉ የጠራ" ነው ሲባል አላህ(ሱወ) በስራው፣ በባህሪው፣ በማንነቱ፣ በምንነቱ...ሁለመናው ከምንም አይነት እንከን የራቀ፣ ምንም አይነት ነውር የሌለበት ፣ ከምንም አሉባልታ የጸዳ ነው ለማለት ነው። ለምሳሌ፦ በአፈጣጠሩ ከጉድለት የጠራ ነው ማለት አሏህ (ሱወ) እያንዳንዱ ፍጥረት ለምን አላማ እንደሚፈጥረው ስለሚያውቅ በፈጠራቸው ፍጡራኖቹ አፈጣጠሩ ላይ መጀመሪያም ሲፈጥራቸው አሟልቶ ስለፈጠራቸው አዲስ ሞዴል ተብለው edit አይደረጉም ወይም ማሻሻያ አይደረግባቸውምና ምንም ጉድለት የለበትም፣ ለፍጡራኖቹ ቅርጽ በመስጠቱም ምንም ጉድለት የሌለበት ነው፣... ማለት ነው። በዚህም በአፈጣጠሩ ከጉድለት ሁሉ የጠራ አል-ቁድዱስ ነው ይባላል። #በክርስትና #እምነት #አስተምህሮ መሠረት የአምላክ ቅዱስነቱ ጉዳይ በጣም የሚያሳዝን መልኩ ነው የተገለጸው። በክርስቲያኖች ዘንድ በተለይም እንደ የመፅሐፍ ቅዱስ ፀሐፊዎች አባባል ከሆነ #እግዚአብሔር #አስቀድሞ #በሰራቸው #ስራዎቹም እንዲህ ነገር ለምን ሰራሁ በማለት #የሚፀፀትና #በስራው #የሚያዝን አምላክ እንደሆነ ይናገራል። ለምሳሌ፦ #የሠውን #ልጅ #በመፍጠሩ #ተፀፀተ ይላል፦ - ኦሪት ዘፍጥረት 6፥6 " እግዚአብሔር የሠውን ልጅ በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ፥ በልቡም አዘነ።" ▷ምሳሌ 2 #እግዚአብሔር #ነብይ #ስለላከ #ተፀፀተ!! - መፅሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 15፥35 "... እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ሳኦልን ስላነገሰ ተፀፀተ።" ይላል። ታድያ እነኚህ የሚያሳዩት እግዚአብሔር በስራው ላይ ጉድለት ያለበት አምላክ መሆኑ ነው ምክንያቱም የሠውን ልጅ ለምን አላማ እንደፈጠረውም ራሱ አያውቅምና ሰውን ስለፈጠረ ተፀፀተ እንዲሁም አዘነ። ይህ ደግሞ የታላቁን ጌታ ማንነት ማጉደፍ ሲሆን ስሙንም ማቅለል ፣ ማጣመም...ነው የሚሆነው። እግዚአብሔር ግን እንዲህ በማለት ይናገራል፦ - ኦሪት ዘሌዋውያን 22፥32 " የተቀደሰውንም ስሜ አታርክሱ..." ይላል። ይህንን በተመለከተ አሏህም (ሱወ)እንዲህ ይላል፦ 7፡ 180 ولله الأسماء الحسنى فادعوه بها ۖ وذروا الذين يلحدون في أسمائه ۚ سيجزون ما كانوا يعملون << ለአላህ መልካም ስሞች አሉት። (ስትጸይዩ) በእርሷም ጥሩት። እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው። ይሰሩት የነበሩትን በእርግጥ ይምመነዳሉ።>> በማለት ይናገራል።

. ከመፅሐፍ ቅዱስ እና ከቁርዓን ( 99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም) ክፍል 2 ⓶ አል-መሊክ (الملك ) [[[ ንጉስ ]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ - መሊክ ማለት ትርጉሙ ንጉስ ማለት ነው። ንጉስ ሲባልም የበላይ፣ የማይደፈር፣ መሪ... ሲሆን ብዙ አይነት ንጉስም ደግሞ አለ። ለምሳሌ የሰው ንጉስ ፤ የእንስሳት ንጉስ ... እንደ ኢትዮጵያ የታሪክ ጥናት መሠረት ሀገራችንን ከገዟት መሪዎች መካከል ንጉሰ ነገሰት ነኝ በማለት ኢትዮጵያን ከመሯት ውስጥም አፄ ሀይለ ስላሴ ይገኝበታል። ታድያ ይህ ሰው ስልጣን በእጁ እያለም ምን ነበር ያለው? <<ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስ>> ነበር ያለው። መጨረሻ ግን እንደ ውሻ አንጠልጥለው ነበር ከሀገር ይዘውት የወጡት። እስቲ አላህ የሚለንን እንስማ፦ 59፡23 هو الله الذي لا إله إلا هو #الملك القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሱ ከጉድለት ሁሉ የጠራው ፣ የሰላም ባለቤቱ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሀያሉ ፣ ኩሩው ነው። ከላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።>> - አል- መሊክ (ንጉስ) ማለት ይህ ነው። ምንም አይነት ነውር የሌለበት፤ ሁሌም አሸናፊ፣ ፀጥታን ሰጪ የሆነ... ይህን ሁሉ ባህርይ በአንድ ላይ የተላበሰ ስለሆነ ነው ከጉድለት ሁሉ የጠራ #ንጉስ የተባለው። ሀይለ ስላሴን ያነሳሁበት ምክንያት አለ። ሀይለ ስላሴ በየቦታው ሙስሊሞችን ይገድል ነበር፣ የድሀ ልጅ ትምህርት እንዳይማር አደረገ፣ መሬት ላራሹ ብሎ ድሀ እንዳይኖር አድርጓል... ታድያ በዚህ መሪ ጊዜ ህብረተሰቡ ውስጥ ሰላም የለም፣ ፀጥታ የለም፣ ጦርነትና ረሃብ ብቻ ሆነ... በዚህም መጨረሻው አወዳደቁ የከፋ ሆነ ፤አይሸነፉ አሸናነፍ ተሸነፈ። እርሱም ብቻ አደለም ሌሎች በጊዜያቸው ሀያልን የሚባሉ ታላላቅ መንግስታት መመልከት እንችላለን። ሁላቸውም እኔ ንጉስ ነኝ ይሉ ነበር። ሁላቸውም ደግሞ አወዳደቃቸው የከፋ ነበር። ለምሳሌ የሮም ንጉስ የነበረው፣ የግብፆች ንጉስ የነበረው(ፈርዖን)... የአሏህ ንጉስነት ግን ከእንደዚህ አይነት መልኩ የተለየ ነው እርሱ የማይሸነፍ የንጉሶች ሁሉ ንጉስ ነው። በሰማያትና በምድር ያሉት ሁሉ ለእርሱ አል - መሊክ ለሆነው አሏህ ያሞግሳሉ። 62፡1 << በሰማያት ያለው በምድርም ያለው ሁሉ ለአላህ ንጉስ ፣ ቅዱስ ፣ አሸናፊ፣ ጥበበኛ ለሆነው ያሞግሳል።>> 23፡ 116 فتعالى الله الملك الحق ۖ لا إله إلا هو رب العرش الكريم << የእውነቱም ንጉስ አላህ ከፍተኛነት ተገባው። ከርሱ ሌላ አምላክ የለም። የሚያምረው አርሽ ጌታ ነው።>> ያለፉት አምባገነን መንግስታት ሁሉ በጊዜያቸው ብዙ ችግርና መከራ በህዝብ ላይ እንዲደርስ አድርገዋል። ራሳቸውንም የበላይ ንጉስ በማድረግ ንጉሰ ነገስት እስከማለት ደርሰዋል። ይህ ደግሞ የአላህን ህልውና የሚጋፋ ነውና መጨረሻቸውና ማረፊያቸው የት እንደሆነ ዘንግተዋል። ማማር እንደተረከው ሃማም ቢን ሙነቢህ እንዲህ አሉ፦ " አቡ ሁረይራ የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል " በአላህ ፊት በትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ በጣም የተጠላው እና በጣም ጎስቋላው በእርሱ ዘንድ የተጠላው ማሊክ አል -አምላክ የተባለ ሰው ይሆናል። ከአላህ ሌላ ንጉስ የለምና።" ሶሒሕ ሙስሊም መፅሐፍ 38, ሐዲስ 15 ከአቡ ሁረይራ እንደተዘገበው ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- "በአላህ ዘንድ ከስሞች ሁሉ መጥፎው ማሊክ አል-አምላክ የተባለ ሰው ነው" ኢብኑ አቢ ሸይባህ በዘገባቸው ላይ "ከአላህ በስተቀር ሌላ ንጉስ የለም" ብለዋል። የተመሰገነና ከፍ ያለ ነው።" አል-አሻጅኢይ እንዲህ አለ፡- ሱፍያን እንዲህ አለ፡- “እንደ ሻሂን - ሻህ (“የነገሥታት ንጉሥ”ን የሚያመለክት የፋርስ ማዕረግ) ነው። [[(ሳሂህ ሙስሊም) መፅሐፍ 38, ሐዲስ ቁጥር 14]] ℹ #ከመፅሐፍ #ቅዱስ የእግዚአብሔር ስም #ንጉስ ተብሎ ከተጠቀሰባቸው መካከል #መዝሙረ ዳዊት 24፥10 " አምላክ እግዚአብሔር እርሱ የክብር ንጉስ ነው።" #መዝሙረ ዳዊት 95፥3 " እግዚአብሔር ታላቅ አምላክ ነውና፥ በአማልክትም ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉስ ነው።" #ትንቢተ ሚልኪያስ 1፥14 " እኔ ታላቅ ንጉስ ነኝ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። " ፨፨፨፨፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ክፍል -3 ይቀጥላል t.me//AkeelComparative

ይህ ከሀገራችን ወደ እስራኤል በስደት የሔደው መሶብ ከሰሞኑ እስራኤል ውስጥ በፈራረሱ ቤቶች መካከል ከፍርስራሽ ውስጥ የተገኘ ሲሆን ይህንም መሶብ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ
ይህ ከሀገራችን ወደ እስራኤል በስደት የሔደው መሶብ ከሰሞኑ እስራኤል ውስጥ በፈራረሱ ቤቶች መካከል ከፍርስራሽ ውስጥ የተገኘ ሲሆን ይህንም መሶብ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ አውጥታለች። በዚህም መግለጫ ላይ #ይህ #ስደተኛው #መሶባችን #በማርያም #ተዓምር #የተረፈው ብርቅዬውና ስደተኛው መሶባችን ነው ብለዋል!😆😆😆 t.me//AkeelComparative

ፍልስጥኤም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ "ፊልሥጢን" فِلَسْطِين ማለት "ፍልስጥኤም" ማለት ሲሆን በአንድ ወቅት የፍሊሥጢን ንጉሥ "ጃሉት" جَالُوت ማለትም "ጎልያድ" እና ሠራዊቱ ከጧሉት ማለትም ከሳኦል ሠራዊት ተዋግተዋል፦ 2፥249 ጧሉትም በሠራዊቱ ታጅቦ በወጣ ጊዜ፡- «አላህ በወንዝ ፈታኛችሁ ነው፥ ከርሱም የጠጣ ሰው ከእኔ አይደለም፡፡ ያልቀመሰውም ሰው በእጁ መዝገንን የዘገነ ሰው ብቻ ሲቀር እርሱ ከእኔ ነው» አለ፡፡ ከእነርሱም ጥቂቶች ሲቀሩ ከርሱ ጠጡ፡፡ እርሱ እና እነዚያም ከእርሱ ጋር ያመኑት ወንዙን ባለፉት ጊዜ፡- «ጃሎትን እና ሠራዊቱን በመዋጋት ለኛ ዛሬ ችሎታ የለንም» አሉት፡፡ እነዚያ እነርሱ አላህን ተገናኝዎች መኾናቸው የሚያረጋግጡት፡- «ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት፤ አላህም ከታጋሾች ጋር ነው» አሉ፡፡ فَلَمَّا فَصَلَ طَالُوتُ بِالْجُنُودِ قَالَ إِنَّ اللَّهَ مُبْتَلِيكُم بِنَهَرٍ فَمَن شَرِبَ مِنْهُ فَلَيْسَ مِنِّي وَمَن لَّمْ يَطْعَمْهُ فَإِنَّهُ مِنِّي إِلَّا مَنِ اغْتَرَفَ غُرْفَةً بِيَدِهِ ۚ فَشَرِبُوا مِنْهُ إِلَّا قَلِيلًا مِّنْهُمْ ۚ فَلَمَّا جَاوَزَهُ هُوَ وَالَّذِينَ آمَنُوا مَعَهُ قَالُوا لَا طَاقَةَ لَنَا الْيَوْمَ بِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ ۚ قَالَ الَّذِينَ يَظُنُّونَ أَنَّهُم مُّلَاقُو اللَّهِ كَم مِّن فِئَةٍ قَلِيلَةٍ غَلَبَتْ فِئَةً كَثِيرَةً بِإِذْنِ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ ከዚያም በጦርነቱ ተፋልመው ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ዳውድ ጃሉትን ገሎታል፦ 2፥250 ለጃሉት እና ለሠራዊቱ በተሰለፉም ጊዜ፡- «ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አንቧቧ፤ ጫማዎቻችንንም አደላድል፤ በከሓዲያን ሕዝቦችም ላይ እርዳን» አሉ፡፡ وَلَمَّا بَرَزُوا لِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ قَالُوا رَبَّنَا أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًا وَثَبِّتْ أَقْدَامَنَا وَانصُرْنَا عَلَى الْقَوْمِ الْكَافِرِينَ 2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ ቁርኣን ላይ ስለ ፍልስጥኤማውያን የሚናገረው እነዚህ አናቅጽ ላይ ነው። ሚሽነሪዎች፦ "ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም የምትባል አገር የላቸውም" እያሉ ባላነበቡት ነገር ይዘባርቃሉ። ፈጣሪ እስራኤልን ከግብጽ ምድር እንዳወጣ ሁሉ በጥንት ጊዜ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር አውጥቶ የራሳቸው ግዛት ሰቷቸዋል፦ አሞጽ 9፥7 እስራኤልን ከግብጽ ምድር፥ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር፥ ሶርያውያንንም ከቂር አላወጣሁምን? ኢዮኤል 3፥4 ጢሮስና ሲዶና የፍልስጥኤምም ግዛት ሁሉ ሆይ! ከእናንተ ጋር ለእኔ ምን አለኝ? በውኑ ብድራትን ትመልሱልኛላችሁን? "የፍልስጥኤምም ግዛት" የሚለው ይሰመርበት ፍልስጥኤም ግዛት ከነበረች ለምን መብቷ አይከበረም? እስራኤላውያን ቦታቸው መጥተው ሰፈሩባቸው እንጂ ጥንትም ቢሆን የእስራኤል ቅም አያት አብርሃም ከከላዳውያን ኡር በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀምጧል፦ ዘፍጥረት 21፥34 "አብርሃምም በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀመጠ"። ፍልስጥኤም መጤ ሳትሆን የራሷ ምድር ስለሆነ "በፍልስጥኤም ምድር" የሚል ኃይለ-ቃል ተጽፏል። ባይብል ላይ ብዙ ቦታ "የፍልስጥኤም ምድር" እያለ ይናገራል፦ ኤርምያስ 25፥20 የተደባለቀውንም ሕዝብ ሁሉ፥ የዖፅ ምድር ነገሥታትንም ሁሉ፥ "የፍልስጥኤም ምድር" ነገሥታትንም ሁሉ አስቀሎናንም ጋዛንም አቃሮንንም የአዞጦንንም ቅሬታ"። ዘጸአት 13፥17 እንዲህም ሆነ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ፥ ምንም ቅርብ ቢሆን እግዚአብሔር "በፍልስጥኤማውያን ምድር" መንገድ አልመራቸውም። ፍልስጥኤማውያን የራሳቸው አገር አላቸው፥ እስራኤላውያን የሰፈሩበት ከነዓን ሁሉ ሳይቀር የፍልስጥኤማውያን ምድር ነው፦ 2ኛ ነገሥት 8፥2 ሴቲቱም ተነሥታ እንደ እግዚአብሔር ሰው ቃል አደረገች፤ ከቤተ ሰብዋም ጋር ሄዳ "በፍልስጥኤም አገር" ሰባት ዓመት ተቀመጠች"*። ሶፎንያስ 2፥5 "የፍልስጥኤማውያን ምድር ከነዓን ሆይ"፥ የእግዚአብሔር ቃል በአንተ ላይ ነው። ዛሬ አገር እና ግዛት እንደሌላቸው እና መጤ እንደሆኑ ታይቶ እየተፈናቀሉ ነው፥ አሏህ ነስሩን ያቅርብላቸው! አሚን። ይህንን የምንለው ስለ ሐቅ እና ስለ ፍትሕ ነው፥ "ኢሥላም ሰም እና ወርቅ የያዘ ቅኔ ነው፥ ሰሙ ሐቅ ሲሆን ወርቁ ፍትሕ ነው" ስንል ዕውር ድንብ ጸለምተኛ ሙግት ይዘን ሳይሆን ጠቅሰንና አጣቅሰን በመሞገትና በመሟገት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ማሣሰቢያ!! ይህን 99 የአሏህ መልካም ስሞች ትርጉም በተከታታይ ክፍሎች በሰፊው የምንመለከትበት ፕሮግራም ነው። በዚህም ይህን አስተምህሮ ለሌሎች #ሼር እንዲያደርጉ በአላህ ስም እየጠየቅን በዚህ ቻናል ላይ ሌሎች ጓደኛዎትን #add ማድረግ የሚፈልግ ሰው ካለ @Akel1941 በማናገር admin ይደረጋል!! t.me//AkeelComparative

2) ቅዱስ ቁርዓን ሀያሉና የተከበረው ጌታችን አላህ ለባሪያዎቹ እጅግ አዛኝ የሆነ ጌታ ነው። በእዝነቱም ለባሪያዎቹ ከሰጣቸው ስጦታዎች መካከል ቅዱስ ቁርዓን ሌላኛው ውድ ስጦታ ነው። - ቁርዓን ሰዎችን ከጨለማ ወደ ብርሃን የምታወጣ የሆነች ልዩ ስጦታ ናት። ይህንን እውነት በ14፡1 ላይ ተገልጾ እናገኘዋለን። 14፡1 << አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ፤ ይህ ቁርዓን) ሰዎችን በጌታቸው ፈቃድ ከጨለማዎች ወደ ብርሃን አሸናፊ ምስጉን ወደ ሆነው ጌታ መንገድ ታወጣ ዘንድ ወዳንተ ያወረድነው መፅሐፍ ነው።>> - ቁርዓን ለሙዕሚኖች መድሐኒት ነው። ለዚህም አላህ (ሱወ) እንዲህ በማለት ይናገራል፦ 17፡ 82 وننزل من القرآن ما هو شفاء ورحمة للمؤمنين ۙ ولا يزيد الظالمين إلا خسارا << ከቁርዓንም ለምዕመናን መድሐኒትና እዝነት የሆነን እናወርዳለን። በዳዮችንም ከሳራን እንጂ ሌላን አይጨመርላቸውም።>> 10፡ 57 يا أيها الناس قد جاءتكم موعظة من ربكم وشفاء لما في الصدور وهدى ورحمة للمؤمنين << እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ በደረቶች ውስጥም ላለው {የመጠራጠር በሽታ} መድኃኒት ለምዕመናንም ብርሃንና እዝነት በርግጥ መጣላችሁ።>> 3) ጀነት አላህ(ሱ.ወ) ፍጥረተ አለሙን የከፈተው በእዝነት ነው። የአደም አፈጣጠር ብንመለከት በራሱ በእዝነት ነው የከፈተው አንነሳኢ በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዓ.ወ) " አላህ አደምን(ዐሰ) በፈጠረ ጊዜ ሩሕ በአደም ጭንቅላት በኩል ገባች። በዚህን ጊዜ አደም አስነጠሳቸው። መላዕክትም <አልሐምዱ ሊላህ >/ ምስጋና ለአላህ ይሁን /በል።> አሉት። አደምም <አልሐምዱ ሊላህ >አሉ። አላህም(ሱ.ወ) <የርሐምከላህ> /አላህ ይዘንልህ/ አላቸው። ይህችም አላህ (ሱ.ወ) ለአደም ያላት የመጀመሪያ ቃል ናት።" ተብሏል። አላህ ይዘንልህ ብሏቸው ነበርና አዝኖላቸውም ወደ ጀነት መለሣቸው። ምክንያቱም ጀነት እዝነቱ ናትና!! አጥጦበራኒ በዘገቡት ሐዲስ ነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) <<አንድም ሰው በአላህ እዝነት እንጂ ጀነት አይገባም። > አሉ። <አንቱም ቢሆኑ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! > አሏቸው። " አዎን እኔም ብሆን አላህ በእዝነቱ ውስጥ ቢነክረኝ እንጂ።" አሉ። ታድያ አላህ(ሱ.ወ) ጀነትን ረሕመት/እዝነት/ ብሎ ሰይሟታል። እንዲህ በማለት፦ 3 ፡107 وأما الذين ابيضت وجوههم ففي رحمة الله هم فيها خالدون << እነዚያም ፊቶቻቸው ያበሩትማ ፥ በአላህ ችሮታ (ገነት) ውስጥ ናቸው፤ እነርሱ በውስጧ ዘውታሪ ናቸው።>> ቡሓሪ በዘገቡት ሐዲስ አላህ (ሱ.ወ) ለጀነት <<አንቺ እዝነቴ ነሽ። ከባሮቼ መካከል የፈለግኩትን ባንቺ አማካይነት እዝነቴን እሰጠዋለሁ።>> ብሏል። ክፍል 2 ይቀጥላል

⓵ አር- ረሕማን አር- ረሒም ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ - ለመሆኑ ምን አይነት ሀብት አለህ? ምን አይነት ሀብትስ ትፈልጋለህ? በኳትሪሊየን የሚቆጠር G+99 ፎቅ መስራት ወይንስ በትሪሊየን የሚቆጠር V-8 መኪና ገዝቶ መንዳት? እነዚህ ካገኘህ ትደሰታለህን?????????? ወንድሜ ስማኝ፤ እህቴ ስሚኝ እኔ አሊም ባልሆንም ነገር ግን ከነዛ ፍርስራሽና ጠፊ ከሆኑት ፎቆችና መኪናዎች ሀብት በብዙ እጥፍ የበለጠ ፀጋ ልጠቁምህ/ ሽ? አልሐምዱሊላህ በል!!! ሙስሊም ላደረገን ጌታ!!! አምላካችን አር -ረሕማን አር - ረሒም( እጅግ በጣም ሩህሩህና አዛኝ) በመሆኑ በእጅጉ ደስ ይበለን። ምክንያቱም አላህ ሱ.ወ እንዲህ ይላል፦ 10፡ 58 قل بفضل الله وبرحمته فبذلك فليفرحوا هو خير مما يجمعون << በአላህ በችሮታና በእዝነቱ ይደሠቱ፥ በዚህም ምክንያት ይደሠቱ፥ እርሱ ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ነው፤ በላቸው።>> ታድያ ከዚህ የበለጠ ደስታ ምን አለ?? << ረሕመት>> እዝነት ማለት ሲሆን ለአንድ ፍጡር በሚጠቅመውና በሚያስደስተው ነገር መልካም መዋል ነው። ኡለሞች ይህንን ረሕማን ስለሚለው የአላህ መልካም ስም ሲናገሩ በእዝነቱ ሁሉም ነገር ያካበበ ከሁሉም ነገር የሠፋና ለፍጥረቱን ሁሉ ነው ብለዋል። ታድያ ሙስሊም ክርስቲያን ፣ አይሁድ፣ ቡድሃ፣ አመፀኛ፣ ጉልበተኛ.. አይልም ሁሉንም ያካትታል። #አል -አንቢያእ ፡42 << ከአር ረሕማን ቅጣት በቀንና በሌሊት የሚጠብቃችሁ ማነው?... በላቸው።>> በውነት በቀን ስንት ወንጀሎች እንሰራለን? ስንት ጊዜ ነው አላህ ላይ ያመፅነው? ታድያ አዛኝ በመሆኑ አዝኖልን ነው እንጂ ማን ነው ከቅጣቱ የሚጠብቀን? ✔ አር ረሕማን አር ረሒም ማለት ከአላህ 99 ስሞች ውስጥ ቀዳሚው ሲሆን ትርጉሙም እጅግ በጣም ሩህሩህና አዛኝ ማለት ነው። ✔ አር ረሒም የሚለው የአሏህ ሱወ ስም በእዝነቱ አማኞችን ብቻ የሚያካልልበት ሁኔታ ነው። ለዚህም ደግሞ ፦ Al-Ahzaab ፡ 43 هو الذي يصلي عليكم وملائكته ليخرجكم من الظلمات إلى النور ۚ وكان بالمؤمنين رحيما <<... ለአማኞችም በጣም አዛኝ ነው።>> አቡ ሑረይራ እንደዘገቡት አላህ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረ ጊዜ እርሱ ዘንድ አርሽ ላይ ከርሱ ዘንድ ባለው መፅሐፍ ላይ " እዝነቴ ቁጣዬን ቀደመች" ብሎ ፅፏል። Sahih Bukharin Vol 4, Book 54, Numbr 416 📚 በመፅሐፍ ቅዱስ - #መዝሙረ ዳዊት 86፥15 " አንተ ግን መሓሪና ሩሕሩሕ አምላክ ነህ።" - #መዝሙረ ዳዊት 145፥8 " እግዚአብሔር ሩሕሩህና መሓሪ ነው።" 👉 ሌላው በአምላክና በእየሱስ መካከል ያለው ልዩነትን አስመልክት አምላክ ሩህሩህ መሆኑን እየሱስ ሲናገር እንዲህ ይላል፦ #ሉቃስ ወንጌል 6፥36 " አባታችሁ ሩህሩህ ስለሆነ እናንተም ሩህሩህ ሁኑ።" በፍጥረተ አለሙ ውስጥ የእዝነቱ ተፅዕኖ አር ረሕማን አር ረሒም የሆነው ጌታችን እዝነትን በፈጠረ ጊዜ 99ኙን በራሱ ዘንድ አስቀምጦ አንዱን ብቻ ወደዚህ አለም ያደረጋት መሆኑን ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ተናግረዋል። ( ሶሒሕ ቡሓሪ vol 8 , book 73 & 76, number 29 & 476) ታድያ ይህ ሁሉም ፍጥረታት የሚንበሸበሹበት የሆነው የዱንያ ፀጋ ከመቶ አንድ እጁ በሆነው እዝነት ነው። የምንጠጣው ውሃ ከሰማይ መዝነቡ ፣ ምድርን አርሰን እንድንበላ መደረጉ፣ ሚስትና ልጆች ተሠጥቶን በፍቅር መኖር፣ ሙሉ ጤንነት ኖሮን አምሽተን እንድናነጋ፣ የሌሊትና ቀን መፈራረቅ... 28፡ 73 ومن رحمته جعل لكم الليل والنهار لتسكنوا فيه ولتبتغوا من فضله ولعلكم تشكرون << ከችሮታውም ለእናንተ ሌሊትንና ቀንን በውስጡ ልታርፉበት ፥ ከትሩፋቱም ልትፈልጉበት፥ አመስጋኞችም ልትሆኑ አደረገላችሁ።>> አስቡት እስቲ የዛሬን ሌሊት እስከ ቂያማ ቀን ድረስ አልነጋ ቢል? ምንድ ነው የሚውጠን? ፣ ከሠማይ የሚዘንበው ውሃ አላቋርጥ ብሎ ለ1000 አመት ዶፍ ቢዘንብ፣ የሚዘንበው ውሃ መርዛማ ቢሆንስ? 28፡ 71 قل أرأيتم إن جعل الله عليكم الليل سرمدا إلى يوم القيامة من إله غير الله يأتيكم بضياء ۖ أفلا تسمعون << አያችሁን? (ንገሩኝ) ፥ አላህ በናንተ ላይ ሌሊትን እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ዘውታሪ ቢያደርገው፥ ከአላህ ሌላ ብርሃን የሚያመጣላችሁ አምላክ ማነው? አትሰሙምን?> በላቸው።>> አዛኙ ጌታችን ሆይ! እንሰማሀለን!!!! እንገዛሀለን!!! የአንተ የአዛኙ ጌታ ባሪያ በመሆናችን ሠማያትና ምድርን የሚሞሉ ምስጋና ለአንተ ይሁን!!! አልሐምዱሊላህ!!!! ✔ በእዝነቱም ለባሪያዎቹ ከሠጣቸው ስጦታዎች አላህ እጅግ ከምናስበው በላይ አዛኝ የሆነ ጌታ ነው። እሱ በራሱ ላይ እዝነትን ፅፏል፤ እውቀቱ እና እዝነቱ ሁሉን ነገር አካቧል። ቁጣው ግን ሁሉንም ያካተተ አይደለም። አላህ እንዲህ በማለት ይናገራል፦ #አል-አንዓም ፡12 " በራሱ ላይ እዝነትን ፅፏል።" ታድያ ይህ አዛኙ ጌታ በእዝነቱም ለባሪያዎቹ ከሰጣቸው ስጦታዎች በጥቂቱ፦ 1ኛ) ነብዩ ሙሐመድን(ሰ.ዓ.ወ) አዛኙ አላህ ለባሪያዎቹ ከሠጣቸው ስጦታዎች መካከል አንዱ ነብዩን(ሰ.ዓ.ወ) መልዕክተኛ አድርጎ ለአለም መላኩን ከእዝነቱ ስጦታዎች ውስጥ ይገኝበታል። 21፡ 107 وما أرسلناك إلا رحمة للعالمين << (ሙሐመድ ሆይ!) ለአለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም።>> የቂያማ ቀን አላህ (ሱወ) ከዚህ በፊት ተቆጥቶ የማያውቀውን ቁጣ ክፉኛ ይቆጣና ፀሀይ በስንዝር ወደ አናት ቀርባ ሁሉንም ታጨናንቃለች። ነብያት እንኳን ሳይቀሩ ነፍስ ሁሉ ነፍሴ ነፍሴ ብሎ በሚጨነቅበት ጊዜ ህዝብ ሁሉ እፎይ የሚለው በረሱል(ሰ.ዓ.ወ) ሽምግልና ነት ነው። ይህ መላምት አደለም ሶሒሕ ሐዲስ ነው። ሙሉው refer ማድረግ ይቻላል ሶሒሕ ቡኻሪ Vol 6 Book 60 Number 336 ( አቡ ሑረይራ) Vol 6 Book 60 nuber 3 (Anas የዘገቡት) Vol 4 Book 55 number 556 ( አቡ ሑረይራ)

✅ የአላህ መልካም ስሞች አስገራሚነት በቁርዓን አላህ(ሱ.ወ) እሱንና መልካም ስሞቹን እናውቅ ዘንድ የሚነበብ ቁርዓንና የሚታይ ፍጥረተ ዓለሙን አድርጓል። - ልብ ብለን ያስተዋልን ከሆነ ቁርዓን የሚሽከረከረው በአላህ(ሱ.ወ) አንድነትና በመልካም ስሞቹ ዙሪያ ነው። ለዚህም እያንዳንዱ የቁርዓን ምዕራፍ የሚጀምረው፦ بسم الله الرحمن الرحيم << በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህና አዛኝ በሆነው።>> በሚለው አረፍተነገር ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜም የወረደው የቁርዓን አንቀፅ ደግሞ፦ 96፡1 اقرأ باسم ربك الذي خلق << አንብብ። በዚያ ( ሁሉን ነገር) በፈጠረው ጌታህ ስም።>> የሚለው ነው። በዚህ ምዕራፍ ላይ "አንብብ" ካለ በኋላ ወደ ታች ሲወርድ የሚቀጥለው ሀሳብ የሚሆነው አላህ ቸር አምላክ መሆኑንና እንዲሁም ደግሞ ሰዎችን የማያውቁትን ነገር በብዕር ያስተማረ መሆኑን ይናገራል። - ሌላው ከቁርዓን አስገራሚ አቀራረቦች መካከል ነገሮችን ይዘረዝርና ከዚያም ማሳረጊያውን በአላህ መልካም ስሞች ማድረጉ ነው። ለምሳሌ ፦ አላህ(ሱ.ወ) ሙታንን መልሶ እንዴት ህያው እንደሚያደርግ ከነብዩላህ ኢብራሂም(ዐ.ሰ) ጋር ያደረጉት ድንቅ ንግግርና አስገራሚ ታሪክ እንመልከት፦ 2፡ 260] وإذ قال إبراهيم رب أرني كيف تحيي الموتى ۖ قال أولم تؤمن ۖ قال بلى ولكن ليطمئن قلبي ۖ قال فخذ أربعة من الطير فصرهن إليك ثم اجعل على كل جبل منهن جزءا ثم ادعهن يأتينك سعيا ۚ واعلم أن الله عزيز حكيم << ኢብራሂምም ጌታዬ ሆይ! <ሙታንን እንዴት ህያው እንደምታደርግ አሳየኝ።> ባለ ጊዜ አስታውስ። (አላህም) <አላመንክምን?> አለው። <አይደለም አምኛለሁ። ግን ልቤ እንዲረጋ ነው።> አለ። አላህም< ከበራሪዎች (ከወፎች) አራትን ያዝ ፤ ወዳንተም ሰብስባቸው፤ ቆራርጣቸው፤ ከዚያም በየኮረብታው ሁሉ ላይ ከእነርሱ ቁራጭን አድርግ ፤ ከዚያም ጥራቸው ፈጥነው ይመጡልሀል።... ።>> ከዚያም የዚህ ታሪክ ማሣረጊያ የሆነው ምንድነው? <<እወቅ >> وأعلم أن ነው ያላቸው። ምንን? >> أن الله عزيز حكيم<< 2፡260 << አላህ በእርግጥም አሸናፊና ጥበበኛ መሆኑን እወቅ።>> ሌላም ተጨማሪ ምሳሌ ብንመለከት፦ 36፡ 38 والشمس تجري لمستقر لها ۚ ذلك تقدير العزيز العليم << ፀሀይም ለርሷ ወደሆነው መርጊያ ትሮጣለች። ይህ የአሸናፊው የአዋቂው አምላክ ውሳኔ ነው።>> - ማወቅ የሚገባንን ነገር ቆም ብለን ካላስተነተንን በቀር አሁን በምናነብበት መልኩ ቁርዓንን እያነበብን የአላህን መልካም ስሞች ፈፅሞ መረዳት የማንችል መሆኑን ነው። ታድያ <<አስማኡላህ አልሑስና>> (የአላህ መልካም ስሞች) በምንልበት ጊዜ "ሑስና" (መልካም) የሚለው ቃል ልብ ብለን ካስተነተነው ሁሉም ስሙ ያማረ፣ ምሉእ የሆነ፣ የተከበረና የላቀ ማለት ነው። እናም በሶሒሕ ቡኻሪ አቡ ሑረይራ(ረ.ዓ) በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ "ለመቶ አንድ ሲቀር ለአላህ 99 ስሞች አሉት። እነርሱን ጠንቅቆ ያወቀ ጀነት ገባ።" Sahih Bukhari Vol 3, Book 50, No 894 Vol 8, Book 75, No 419 Vol 9, Book 93, No 489

የአሏህ መልካም ስሞች ትርጉም [[ በመፅሐፍ ቅዱስ እና በቅዱስ ቁርዓን ]] 📝 በወንድም አቂል አክመል መቅድም በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህና በጣም አዛኝ በሆነው ምስጋና ለአላህ(ሱ.ወ) ይሁን። የአላህ(ሱ.ወ) እዝነትና ሰላም በታላቁ ነብይ ሙሐመድ ፣ በቤተሰቦቻቸው ፣ በሶሓቦቻቸውና በተከታዮቻቸው ላይ ሁሉ ይሁን። ይህ መፅሐፍ ይዘቱ ከሌሎች መፅሐፎች የተለየ ነው። ስለ ሀያሉና የተከበረው አሏህ (ሱ.ወ) በግልፅ እንነጋገርበታለን። ስለመልካም ስሞቹ ትርጉም ከመፅሐፍ ቅዱስና ከቅዱስ ቁርዓን እናወሳበታለን። አሏህ(ሱ.ወ) ማነው? በአምላክና በፍጡር መካከል በተለይም በክርስትና እምነት ዘንድ እንደ አምላክ ከሚመለኩት እየሱስ ጋር ያላቸው ሰፊ ልዩነቶች በመፅሐፍ ቅዱስና በቁርዓን ውስጥ በሰፊው እናወጋበታለን። ስለአምላካችን ማንነትና ምንነት ጠለቅ ያለ እውቀት እንጨብጥበታለን። የፀሐፊው ማስታወሻ ✅ አላህን የማወቅ እውቀት - ከእውቀቶች ሁሉ ትልቁ እውቀት አላህን ማወቅ ነው። - የዱንያን ጥቅም ስናሳድድ አላህን ልንረሳ እንችላለን። በዚህም መልካም ስሞቹን አስታውሰን ሀያሉንና የተከበረውን አላህን ማወቅ የጠፋ ህይወታችንን ለመመለስ የምንጠቀምበት አማራጭ የሌለው መንገድ ነው። - አላህን የሚያውቅና የማያውቅ ሰው በደረጃና በክብር ፈፅሞ ሊገናኙ አይችሉም። " አሏህን(ሱ.ወ) በስሙና በባህሪው ማወቅ በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ትርጉም ያለው ሕይወት ለመኖር የሚያነቃቃ የመንፈስ ምግብ ነው።" (ዶ/ር ዓምር ሐሚድ) 📚 ትንቢተ ሆሴዕ 6፥6 " ከመስዕዋት ይልቅ ምህረትን ፥ ከሚቃጠልም መስዕዋት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እወዳለሁና።" - አላህን የሚያውቅ ሰው ህያው ሲሆን የማያውቅ ደግሞ ህይወት ኖሮት በምድር ላይ የሚንቀሳቀስ ቢሆንም ሙት ነው። አሏህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦ 6፡ 122 أومن كان ميتا فأحييناه وجعلنا له نورا يمشي به في الناس كمن مثله في الظلمات ليس بخارج منها ۚ كذلك زين للكافرين ما كانوا يعملون << ሙት የነበረና ህያው ያደረግነው ለርሱም በሰዎች መካከል በርሱ የሚሄድበትን ብርሃን ያደረግንለት ሰው በጨለማዎች ውስጥ ከርሷ የማይወጣ እንዳልለ ቢጤ ነውን?...>> - በተመሣሣይ መልኩ እውነተኛው ፈጣሪ አምላክን በቅጡ አለማወቅና ከእርሱም መራቅ በቀትር ላይ እንደማያይ እውር ነው በማለት መፅሐፍ ቅዱስም ይናገራል። 📚 ዘዳግም 28፥29 " በቀትርም ጊዜ እውር በጨለማ እንደሚርመሰመስ ትርመሰመሳለህ፥ መንገድህም የቀና አይሆንም..." ሙሉውን መረጃ በተከታታይ ክፍሎች ለማግኘት t.me//AkeelComparative join ያድርጉ

. የክርስትና ሀይማኖት እና የእምነቱ መመሪያ የክርስትና ሀይማኖት መመሪያ መፅሐፍት በጣም በርካታ ቢሆኑም ከእነዚህም መፅሐፍት መካከልም በዋነኛነት ቅዱስና አምላካዊ ቃል ነው ተብሎ የሚታመንበት የእምነቱ መመሪያ መፅሐፍም ደግሞ በብዙዎች ዘንድ መፅሐፍ ቅዱስ እንደሆነም ይታመናል። ነገር ግን የትኛው መፅሐፍ ቅዱስ? @AkeelComparative መፅሐፍ ቅዱስ ✅ መፅሐፍ ቅዱስ በይዘት ረገድ ሠፊ ልዩነት ያላቸው ብዙ መፅሐፍ ቅዱሶች ይገኛሉ። ✅ መፅሀፍ ቅዱስ ከእትም እትም ይለያያል። ለምሳሌ፦ - የለንደን እትም - የሮማ እትሞች - የቤይሩት እትሞችና ሌሎችም ይገኛሉ። ✅ በአንድ ተመሣሣይ ቋንቋ የሚታተሙ እትሞች እንኳን ብዙ ልዩነቶች አሏቸው። ለምሳሌ፦ - ፕሮቴስታንቶች በባለ 39 መፅሐፍ ብሉይ ኪዳን ያምናሉ። - ኦርቶዶክሶች በብሉይ ኪዳን 46 + 35 በአዲስ ኪዳን በድምሩ 81 ምዕራፎች ያሉት መፅሐፍ ቅዱስ ያምናሉ። - ካቶሊኮች በፕሮቴስታንቶቹ ላይ ተጨማሪ 7 ምዕራፎች አሉት - የሠማርያውያን ብሉይ ኪዳን ደግሞ በ39/46 ፈንታ 5 ምዕራፎችን ብቻ ያካትታል። ✅ ከላይ እንደተገለፀው መፅሐፍ ቅዱስ በውስጡ አንድም ቦታ ላይ የመፅሐፉ መጠሪያ የሆነው ስሙ መፅሐፍ ቅዱስ ተብሎ አልተገለፀም። በአንፃሩ ግን የኢየሱስ አስተምህሮት የነበረው የእምነታቸው መመሪያ መፅሐፍ ወንጌል የሚባል የመፅሐፉ ስም ነበረው። - የሉቃስ ወንጌል 4 ፥ 17-20 " ኢየሱስም የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው ለድሆችም ወንጌል እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና... አለ። " የክርስትና ሀይማኖት መመሪያ መፅሐፍ የሆነው መፅሐፍ ቅዱስ በውስጡ የስሙን ስያሜ ካለመጠቀሱ አንፃር የእስልምና ሀይማኖት መመሪያ የሆነው ቅዱስ ቁርዓንን የተመለከትን እንደሆነ ቅዱስ ቁርዓን ✅ በቁርዓን ውስጥ የቅዱስ ቁርዓን ስም ከ130 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል። ✅ አረብኛ ቋንቋ ሆኖ መውረዱን ተገልጿል። 12፥2 " እኛ ፍቹን ታውቁ ዘንድ አረብኛ ቁርዓን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው። " ✅ በጠንካራና በተብራራ አንቀፅ መውረዱን 11፥1 " አሊፍ ላም ራ (ይህ) ቁርዓን አንቀፆቹ በጥንካሬ የተሰካኩ ከዚያም የተዘረዘሩ የሆነ መፅሀፍ ነው። ጥበበኛው ውስጠ አዋቂ ከሆነው ዘንድ (የተወረደ) ነው።" ✅ በአንድ ጊዜ ከሠማይ ተጠቅልሎ ዱብ ያለ ሳይሆን በተለያየ ጊዜ ተከፋፍሎ ተከፋፍሎ ለነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) በራእይ የወረደ መሆኑንና ለሠው ልጆችም መገሠጫነት የመጣ ነው። 53፥ 2- 4 " ነብያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም አልጠመመምም፤ ከልብ ወለድም አይናገርም። እርሱ(ንግግሩ) የሚወርድ ራእይ እንጂ ሌላ አይደለም።" 3 ፥ 3 "... ቁርዓንን ባንተ ላይ ከፋፍሎ በእውነት አወረደ። ተውራትንና ኢንጅልም አውርዷል።" 76፥23 " እኛ ቁርዓንን ባንተ ላይ ማውረድን እኛው አወረድነው። " 4፥174 " እናንተ ሰዎች ሆይ ከጌታችሁ ዘንድ በእርግጥ አስረጅ መጣላችሁ፤ ወደ እናንተም ገላጭ የሆነን ብርሃን ( ቁርዓን) አወረድን። " @AkeelComparative join ✅ ሌላው የመፅሐፍ ቅዱስ የስሙን ስያሜ የሠጡትም የእምነቱ ምሁራኖቹ ሲሆኑ በመፅሀፉ የተለያዩ ምዕራፎች ውስጥ የተለያዩ ግለሰቦች ተሳትፎ አድርገውበታል። በተለይም አዲስ ኪዳን ተብሎ በሚጠራው የመፅሐፉ ምዕራፎች ውስጥ የጳውሎስ የስራ ድርሻ እጅግ ከፍተኛ ነው። 👉 የመፅሐፍ ቅዱስ መለኮታዊ ራእዩ መለኮታዊ አስተምህሮቱ በተመለከተ መፅሐፍ ቅዱስ መነሻውን ወይም ማቆሚያውን የሚለይ መለኮታዊ ራዕይ የተላለፈበት አንቀፅ የለውም። የመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮት የሚጀምረው ከኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ቢሆንም መነሻ ሀሳቡ ግን አይታወቅም። እንዲሁ ማቆሚያም የለውም። ምክንያቱም - የዮሐንስ ራዕይ 22፥10 "... የዚህን መፅሀፍ ትንቢት ቃል በማህተም አትዝጋው። " ይላል ከዚህ አንፃር ቅዱስ ቁርዓንን የተመለከትን እንደሆነ፦ - ሲጀምር (መነሻው) << አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም።>> ( 96፥1) - መጨረሻውና ማጠቃለያው << ዛሬ ሃይማኖታችሁ ለእናንተ ሞላሁላችሁ፤ ፀጋዬንም በእናንተ ላይ ፈፀምኩ ፥ ለእናንተም ኢስላምን ከሀይማኖት በኩል ወደድኩ።" >> ( 5፥3) 👉 የመፅሐፍ ቅዱስ ቅዱስነቱ የመፅሐፍ ቅዱስን ቅዱስነቱ ጉዳይ ብዙም አጠያያቂ ነገር አይደለም። ምክንያቱም በብዙ ስህተቶችና አሉባልታዎች እንዲሁም በእርስ በርስ ግጭት የተሞላ ነው። ከእርስ በርስ ግጭቶቹ መካከል ለምሳሌ፦ - የማቴዎስ ወንጌል 5 ፥17 -20 " ኢየሱስም መልሶ " እኔ ህግና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ ልፈፅም እንጂ...።" - ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 ፥14 -15 " ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦ እየሱስ ሰላማችን ነው በአዋጅ የተነገሩትን የትዕዛዛትን ህግ ሽሮ በመካከል ያለውን...።" ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative

👉 #አስካሪ #መጠጥ (አልኮል) አልኮል በባህሪው የሠውን ልጅ አዕምሮ የሚያደነዝዝ ጎጂ የመጠጥ አይነት ሲሆን አስካሪ የአልኮል መጠጥ በተፈጥሮው ወንጀል ለመስራት የሚያደፋፍር ርኩስ የሆነ የሰይጣን ተግባር ነው። ለዚህም ደግሞ አላህ(ሱወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦ 5፡ 90 يا أيها الذين آمنوا إنما الخمر والميسر والأنصاب والأزلام رجس من عمل الشيطان فاجتنبوه لعلكم تفلحون እናንተ ያመናችሁ ሆይ! #የሚያሰክር #መጠጥ ቁማርም ጣዖታትም አዝላምም #ከሰይጣን #ሥራ #የኾኑ #እርኩስ #ብቻ ናቸው፡፡ (እርኩስን) ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡ 5፡ 91 إنما يريد الشيطان أن يوقع بينكم العداوة والبغضاء في الخمر والميسر ويصدكم عن ذكر الله وعن الصلاة ۖ فهل أنتم منتهون ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል አላህን ከማውሳትና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ (ከእነዚህ) ተከልካዮች ናችሁን (ተከልከሉ)፡፡ ✔ ስለአስካሪ መጠጥ በክርስትና ስለ አልኮል በኦሪት ህጎች ላይ በጥብቅ የተከለከለ ጉዳይ ሲሆን አስካሪ መጠጥ (አልኮል) አለመጠጣት ደግሞ #የዘላለም #ስርዓት እንደሆነ ተደንግጓል። በቅዱስ ቁርዓን 5፡90 ላይ እንደተገለፀው ሁሉ በኦሪትም ይህን የሚያደርግ (የሚጠጣ) ሰው #የርኩስነት መገለጫ መሆኑን ሲጠቅስ የሚጠጡ ሰዎች ርኩሶች፤ የማይጠጡ ሰዎች ደግሞ ቅዱሳኖች( ሙስሊሞች) እንደሆኑ ያስገነዝባል። - ኦሪት ዘሌዋውያን ምዕ. 10 9፤ እንዳትሞቱ ወደ መገናኛው ድንኳን ስትገቡ አንተና ልጆችህ #የወይን #ጠጅና #የሚያሰክርን #ነገር #ሁሉ #አትጠጡ፤ #ይህም #ለልጅ #ልጃችሁ #የዘላለም #ሥርዓት #ይሆናል፤ 10፤ በተቀደሰውና ባልተቀደሰው፥ #በርኩሱና #በንጹሑም #መካከል #ትለያላችሁ፤ ታድያ ይህ የሚለው #የኦሪት ህግ ነው እንጂ የክርስትናው ወንጌል አይደለም።ምክንያቱም በኦሪት ዘመን የክርስትና እምነት ምን እንደሆነ አይታወቅም ነበር። ሆኖም ክርስትና የተመሠረተው እየሱስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ነው፤ ይህንም እምነት የመሠረተው ጳውሎስ ሲሆን እርሱም በእየሱስ ስም አማካኝቶ ነበር የመሠረተው። ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦ - 1ኛ ቆሮንቶስ 3 ፥ 10-11 "... እንደ ብልሃተኛ የአናፂ አለቃ መሠረትን መሠረትኩ... እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።" - የሐዋርያት ስራ 11፥26 "... ለመጀመርያ ጊዜ በአንጾኪያ #ክርስቲያን ተባሉ።" አስካሪ መጠጥ አትጠጡ የሚለው የኦሪት ዘመን ህግ የሚቃወመውና በዚህ ኦሪትም የማይታወቀው እምነት ወይም የክርስትናን መስራቹ ጳውሎስ ወይንም ሆነ አጠቃላይ መጠጥ መጠጣትን እንደሚቻል ሲፈቅድ እንዲህ ይላል፦ - 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 9 3-4፤ ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን? 7፤ ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው? - 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5፥ 23 " ስለ ሆድህና ስለ በሽታህ ብዛት ጥቂት #የወይን #ጠጅ #ጠጣ እንጂ፥ ወደ ፊት ውኃ ብቻ አትጠጣ።" ✔ አስካሪ መጠጥ በኢስላም ነብዩ(ሰዐወ) መጠጥ የወንጀሎች ሁሉ እናት ነው በማለት የተናገሩ ሲሆን በዚህም በኢስላም በጥብቅ ተከልክሏል። - ኢብኑ ማጃህ ቅጽ 3, የአስካሪ መጠጦች ምዕራፍ 30, ተ.ቁ 3392 ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል" መጠኑ የበዛ የሆነ ማንኛውም አስካሪ መጠጥ ትንሽም ቢሆን ክልክል ነው" ብለዋል። - በሌላም ሐዲስ ኢብኑ ማጃህ ቅፅ 3, ምዕራፍ 30, ተ.ቁ 3371 ስካር ወይም መጠጥ የወንጀሎች ወይም የመጥፎ ስራዎች ሁሉ እናት ነው" ብለዋል። ከዚህ ከመጠጥ ጋር በተያያዘ 10 የማህበረሰብ ክፍሎች (ሰዎች) በአላህ ዘንድ የተረገሙ ናቸው - ኢብኑ ማጃህ ቅፅ 3, የአስካሪ መጠጦች ምዕራፍ 30, ቁጥር 3380 ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል፦ " አስር ሰዎች አላህ ዘንድ የተረገሙ ናቸው እነርሱም፦ 1) ለራሳቸው የሚጠምቁ 2) ለሌሎች የሚጠምቁ 3) ለሌሎች የሚያጓጉዙ 4) ለራሳቸው የሚያደርሱ 5) አገልግሎት የሚሰጡ 6) የሚሸጡ 7) ለሚገኘው ትርፍ የሚያመቻቹ 8) ከትርፉ የሚጠቀሙ 9) ለራሳቸው የሚገዙ 10) ለሌሎች የሚገዙ ሰዎች ናቸው ብለዋል።" ✔ የአስካሪ መጠጥ መፍትሔው በኢስላም ሶላት መስገድ ነው። 29፡45 اتل ما أوحي إليك من الكتاب وأقم الصلاة ۖ إن الصلاة تنهى عن الفحشاء والمنكر ۗ ولذكر الله أكبر ۗ والله يعلم ما تصنعون ከመጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀህ ስገድ፡፡ ሶላት ከመጥፎና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለችና፡፡ አላህንም ማውሳት ከሁሉ ነገር በላጭ ነው፤ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ያውቃል፡፡

✔ ዝሙትና መፍትሔው በኢስላም በኢስላም አስተምህሮ ውስጥ ዝሙትን ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የተለያዩ መፍትሔዎችን ተቀምጠዋል። ከእነዚህም መካከል 1ኛ) #ሚስት #ማግባትና #ጾም #መፆም የትዳርን ጣጣው ለቻለ ሰው ሚስት ማግባት ዝሙትን ለመከላከል አይነተኛ መፍትሄው ሲሆን ሌላው ፆም መፆም ነው። #ፆም የሠው ልጅ የፆታ ሀይልን የሚቀንስ የተፈጥሮ ባህሪይ በመሆኑም የተነሳ ማግባት ላልቻለ ሰው ደግሞ ፆም መፆም ዝሙት ከመፈፀም ይከላከላል። በዚህም ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መጽሐፍ 31 ቁጥር 129 በአልቃማ የተተረከ ከአብዱላህ ጋር እየተጓዝኩ ሳለ፡- እኛ ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ነበርን እና፡- ማግባት የሚችል ሰው ማግባት ስለሚረዳው #ወደ #ሌሎች #ሴቶች #ከማየት #እንዲቆጠብ እና #ብልቱን #እንዲታደግ #ይረዳዋል። ሌሎችን ሴቶች ከመመልከት ብልቱንም ከሕገወጥ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ያድን፤ ማግባት የማይችል ደግሞ #መጾም #የጾታ #ኃይሉን #ስለሚቀንስ #ይጾም። 2ኛ) ማግባትን ፈልጎ አቅም የሌለው #ሰራተኛውን ማግባት ዝሙት ለፈራ ሰው የሚሆን መፍትሔ ነው። 4፡ 25 ومن لم يستطع منكم طولا أن ينكح المحصنات المؤمنات فمن ما ملكت أيمانكم من فتياتكم المؤمنات ۚ والله أعلم بإيمانكم ۚ بعضكم من بعض ۚ فانكحوهن بإذن أهلهن وآتوهن أجورهن بالمعروف محصنات غير مسافحات ولا متخذات أخدان ۚ فإذا أحصن فإن أتين بفاحشة فعليهن نصف ما على المحصنات من العذاب ۚ ذلك لمن خشي العنت منكم ۚ وأن تصبروا خير لكم ۗ والله غفور رحيم ከናንተም ውስጥ ጥብቆች ምእምናት የኾኑትን ለማግባት ሀብትን ያልቻለ ሰው እጆቻችሁ ንብረት ካደረጓቸው ከምእምናት ወጣቶቻችሁ (ባሪያን ያግባ)፡፡ አላህም እምነታችሁን ዐዋቂ ነው፡፡ ከፊላችሁ ከከፊሉ (የተራባ) ነው፡፡ (ባሮችን) በጌቶቻቸውም ፈቃድ አግቡዋቸው፡፡ መህሮቻቸውንም በመልካም መንገድ ስጧቸው፡፡ ጥብቆች ኾነው ዝሙተኞች ያልኾኑ የስርቆሽ ወዳጆችንም ያልያዙ ሲኾኑ (አግቧቸው)፡፡በማግባት በተጠበቁም ጊዜ መጥፎን ሥራ ቢሠሩ በእነርሱ ላይ ከቅጣት በነጻዎቹ ላይ ያለው ግማሽ አለባቸው፡፡ ይህ (ባሪያን ማግባት) ከእናንተ #ዝሙትን #ለፈራ #ሰው #ነው። 3ኛ) ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት በኢስላም ከአንድ ሚስት በላይ ማግባት ሌላው ዝሙትን ከመፈፀም የሚከላከል የሆነ ምርጥ መፍትሔ ነው። ከአንድ በላይ ሚስት ለማግባት ፈልጎም ፍትሐዊ በሆነ መልኩና ሁሉንም በእኩል የማስተዳደር አቅም አለኝ የሚል ሙስሊም የሆነ ሰው እስከ አራት ሚስቶችን እንዲያገባ ተፈቅዶለታል። ሆኖም ግን ዝሙትን ሊፈራ ግድ እንደሚለው ሁሉ ሚስቶቹን በእኩል የማያስተዳድር ከሆነም ከተወሰነለት በላይ ከማግባት መታቀብም ይኖርበታል። 4፡ 3 وإن خفتم ألا تقسطوا في اليتامى فانكحوا ما طاب لكم من النساء مثنى وثلاث ورباع ۖ فإن خفتم ألا تعدلوا فواحدة أو ما ملكت أيمانكم ۚ ذلك أدنى ألا تعولوا በየቲሞችም (ማግባት) አለማስተካከላችሁን ብትፈሩ (ዝሙትንና ከተወሰነላችሁ በላይ ማግባትንም ፍሩ)፡፡ ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት ሦስት ሦስትም አራት አራትም አግቡ፡፡ አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡ በሀገራችንና በመላው አለም ላይ በሚገኙት የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተስተዋለ ለሚገኘው የዝሙት ተግባርም በዋነኛነት እንደ ምክንያት ከሚጠቀሱት መካከል በትዳር ውስጥ በፍላጎት ያለመጣጣም ጉዳይ ግንባር ቀደም ችግር ሲሆን በዚህም ባለቤታቸውን እቤት አስቀምጠው በየሆቴሎችና የመዝናኛ ስፍራዎች ላይ ሲማግጡ ይታያል። ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ደግሞ ለዚህ ችግር ወሳኝ መፍትሄ ነው። ታድያ በክርስትና እምነት ውስጥ እንኳንስ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ይቅርና ለስሜታዊ ፍላጎት ካልሆነ በቀር አንድ ሚስት ማግባትንም እንኳን ይከለክላል። በዚህም በቀላሉ ለዝሙት ይጋለጣሉ። ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦ - 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 7 8፤ ላላገቡና ለመበለቶች ግን እላለሁ። እንደ እኔ ቢኖሩ ለእነርሱ መልካም ነው፤ 9፤ #ነገር #ግን #በምኞት #ከመቃጠል #መጋባት #ይሻላልና #ራሳቸውን #መግዛት #ባይችሉ ያግቡ። 10-11፤ ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር ወይም ከባልዋ ትታረቅ፥ ባልም ሚስቱን አይተዋት ብዬ የተጋቡትን አዛቸዋለሁ፥ እኔ ግን አላዝም፥ ጌታ እንጂ። ----------------////--------- ክፍል 2 በአስካሪ መጠጦች ይቀጥላል

. ለችግሮች መፍትሔ ያለው እምነት እስልምና ነው? ወይንስ ክርስትና? ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ በዚህ በምንገኝበት አለም ላይ በተለይም በክርስትና እምነት ተከታዮች በኩል የሚስተዋሉ የተለያዩ የወንጀል አይነቶችንና መሠል ችግሮችን ይገኛሉ። ለምሳሌም ያክል እንደ ዝሙት፣ የአስካሪ መጠጥ መበራከት፣ ስርቆት፣ የአስገድዶ መድፈር፣ የግድያ፣ ሙስናና... ይገኛሉ። እነዚህንም ጨምሮ በእምነቱ ዘንድ መፍትሔ የሌላቸውም የሆኑ ሌሎች በርካታ ችግሮችና ወንጀሎች ይገኛሉ። ታድያ ለእነዚህም መፍትሔ ለሌላቸው ችግሮችም ችግሩን ለመፍታት በሚል በእምነቱ አስተምህሮ በኩል መፍትሄዎች ሲበጅላቸው ቢስተዋልም ነገር ግን ችግሩን ከስሩ የሚያስወግዱ የሆኑ መፍትሄዎች ግን መደንገግና መፍጠር አይችልም። የእስልምናን ሐይማኖት ከእንደነዚህ አይነቱ ችግሮች አንፃር የተመለከትነው እንደሆነ ኢስላም በራሱ ለችግሮች መፍትሔ ያበጀ #የመፍትሔ #እምነት መሆኑን እንገነዘባለን። 👉 ዝሙት በእርግጥ ስለዝሙት በክርስትና ዘንድ #አታመንዝር በሚል የተከለከለ ተግባር ሲሆን በተጨማሪም በዚህ እምነት አስተምህሮ ላይ #ማመንዘር የሚያረክስም እንደሆነ ተገልጿል። - የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 15 17፤ ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ እንዲጣል አትመለከቱምን? 18፤ ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው። 19፤ ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ #ምንዝርነት፥ #ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና። 20፤ ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው እንጂ፥ ባልታጠበ እጅ መብላትስ ሰውን አያረክሰውም። - የማቴዎስ ወንጌል 19፥18 " እርሱም። የትኞችን? አለው። ኢየሱስም። አትግደል፥ #አታመንዝር፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥" ታድያ #ዝሙት በክርስትና እምነት ዘንድ በእንደዚህ መልኩ ይከልከል እንጂ ችግሩን ከስሩ የሚቀርፍ የሆነ መፍትሔ ግን አልተቀመጠለትም። ✔ ዝሙት በኢስላም በእስልምና እምነት ውስጥ ዝሙት በጥብቅ የተከለከለ የወንጀል ተግባር መሆኑን አሏህ(ሱወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦ 17፡ 32 ولا تقربوا الزنا ۖ إنه كان فاحشة وساء سبيلا #ዝሙትንም አትቅረቡ፡፡ እርሱ በእርግጥ መጥፎ ሥራ ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ! ታድያ ይህንን የጌታችን ህግ ረስቶ ዝሙት የሚፈፅም የሆነን አንድ ሙስሊም ሰው ወንጀሉን በሚፈፅምበት ወቅት አማኝ እንዳልሆነ ተደንግጓል። ሁኔታውንም ነብዩ(ሰዐወ) ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 655 አቡ ሁረይራ በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “ #ዝሙተኛ ህገ ወጥ የሆነ #የግብረ #ሥጋ #ግንኙነት #ሲፈጽም #በወቅቱ #አማኝ #አይደለም፣ እየፈጸመው ነው፣ የአልኮል ጠጪም ከጠጣ በኋላ በሚጠጣበት ጊዜ አማኝ አይሆንም። ሌባ ሲሰርቅ ደግሞ በስርቆት ጊዜ አማኝ አይደለም፣ ዘራፊም ሲዘርፍ፣ ህዝቡም ሲያዩት እሱ በሚሰርቅበት ጊዜ አማኝ አይደለም።

👉 አይሁዶች እየሱስን አልሰማም ብለው እንደሚያምፁ ስላወቀ የእግዚአብሔር መንግስት ከእነርሱ እንደሚወሰድና ከእነርሱም ተወስዶ ለሌሎች እንደሚሰጥ እንዲሁም የካዕባውንም ድንጋይ ከእየሩሳሌም ወደ መካ እንደሚሄድ ተናግሯል። - የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 21 42፤ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን? 43፤ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች ፍሬዋንም ለሚያደርግ ሕዝብ ትሰጣለች። 44፤ በዚህም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ ድንጋዩ ግን የሚወድቅበትን ሁሉ ይፈጨዋል። ኦሪት ዘጸአት ምዕ. 28) ---------- 38፤ በአሮንም ግምባር ላይ ይሆናል፥ በእግዚአብሔርም ፊት ሞገስ እንዲሆንላቸው ቅጠል የሚመስለው ምልክቱ ሁልጊዜ በግምባሩ ላይ ይሁን። ... 43፤ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው እንዳይሞቱም፥ ወደ መገናኛው ድንኳን ሲገቡ በመቅደሱም ያገለግሉ ዘንድ ወደ መሠዊያው ሲቀርቡ በአሮንና በልጆቹ ላይ ይሆናል፤ ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ለዘላለም ሥርዓት ይሆናል።