እስልምና እና ክርስትና
Open in Telegram
t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!
Show more315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም
( በመፅሐፍ ቅዱስ እና በቁርዓን)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ክፍል - 9
⓽ አል-ኻሊቅ (الخلاق )
[[[ ፈጣሪ ]]]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
- #አል_ኻሊቅ ማለት ትርጉሙ የሁሉም ነገር ፈጣሪ፣ የሁሉም ነገር ጀማሪ፣ የሁሉም ነገር አስገኝ ማለት ነው። መፍጠር ማለት አንድን ያልነበረ ነገር ማስገኘት ማለት ነው። አል-ኻሊቁ አላህ ሁለመናው ፈጣሪ ስለመሆኑ ሲናገር እንዲህ ይላል፦
15፡ 86
إن ربك هو الخلاق العليم
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) #ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
39፡ 62
الله خالق كل شيء ۖ وهو على كل شيء وكيل
አላህ #የነገሩ #ሁሉ #ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡
40፡62
ذلكم الله ربكم خالق كل شيء لا إله إلا هو ۖ فأنى تؤفكون
ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ #የነገሩ #ሁሉ #ፈጣሪ ነው፤ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ (ከእምነት) ወዴት ትመለሳላችሁ፡፡
✔ ሁለት አይነት እውቀት አለ
1) በአላህ(ሱወ) መኖር ማመን። ይህንን እውቀት ሁሉም የሰው ልጆች(ሙስሊሙም፣ ክርስትያኑም፣ ሌላውም) በአንድነት ይጋሩታል። ነገር ግን እኛ ሙስሊሞች አላህ ብቸኛ ፈጣሪ መሆኑን ብናምንም ሌሎች ግን ይህንን አይቀበሉም። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦
31፡25
ولئن سألتهم من خلق السماوات والأرض ليقولن الله ۚ قل الحمد لله ۚ بل أكثرهم لا يعلمون
ሰማያትንና ምድርንም የፈጠረ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ አላህ ነው ይላሉ፡፡ ምስጋና ለአላህ ይገባው በላቸው፡፡ ይልቁንም አብዛኛዎቹ አያውቁም፡፡
2) አላህ(ሱወ) የመውደድ እና ከሱ ሐያዕ የማድረግ እውቀት። እሱ ፈጥሮናልና ከሱ ሐያዕ እናደርጋለን። በሱ ከማመፅ እንጠነቀቃለን። የዚህ አይነቱ እውቀት የአምልኮ እውቀት ሲሆን በዚህም አላህን በብቸኝነት ማምለክና የተፈጠርንበት አላማ ከግብ ማድረስ ነው።
- አል-ኻሊቅ የፈጠረን አምላካችንን የሚያስታውሰን ስም ነው። እርሱ ፍጥረታትን በሙሉ በብቸኝነት የፈጠረ ጌታ ነው።
አላህ ከሱ ውጪ ፈጣሪ የለም። ይህን በሌላ የቁርዓን አንቀጽ ውስጥ ደግሞ ያረጋግጥልናል። እንዲህ በማለት፦
7፡54
إن ربكم الله الذي خلق السماوات والأرض في ستة أيام ثم استوى على العرش يغشي الليل النهار يطلبه حثيثا والشمس والقمر والنجوم مسخرات بأمره ۗ ألا له الخلق والأمر ۗ تبارك الله رب العالمين
ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ ከዚያም (ስልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ፡፡ (አላህ) ሌሊትን በቀን ፈጥኖ የሚፈልገው ሲኾን ይሸፍናል፡፡ ፀሐይንና ጨረቃንም ከዋክብትንም በትእዛዙ የተገሩ ሲኾኑ (ፈጠራቸው)፡፡ ንቁ! መፍጠርና ማዘዝ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ የዓለማት ጌታ አላህ (ክብሩ) ላቀ፡፡
#መፅሐፍ_ቅዱስ ( አል-ኻሊቅ)
የክርስትና እምነት በሚስጥረ ስላሴ ሚስጥር ውስጥ ፈጣሪ አምላክ ሶስት እንደሆኑ ይደነግጋል። ይህም ማለት ህዝበ ክርስትያኖች ፈጣሪ አምላክ በአካል ሶስት በመለኮት አንድ ናቸው በማለት ያምናሉ። ታድያ ከዚህ ከሚስጥረ ስላሴ ፅንሰ ሀሳብ አንጻር በመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ላይ የፈጣሪ አምላክ ሶስትነት እንዴት ይታያል?
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት
t.me//AkeelComparative ይቀላቀሉ
አብርሃም ሦስት ጊዜ መጠራቱ አብርሃም ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? መልክአ ኢየሱስ የሚባለው የኦርቶዶክስ መጽሐፍ ላይ ኢየሱስን ሦስት ጊዜ “ኢየሱስ፥ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ” ይለዋል፦
*“ኢየሱስ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ”* ክርስቶስ ዘሰረጽከ እመቤተ ሌዊ ኮሬባዊ መለኮታዊ ቃል ሰማያዊ እም ድንግል ተወለደ።
ኢየሱስ የሚለው ቃል ሦስት ጊዜ መደገሙ ከድንግል የተወለደው ኢየሱስ ሦስት አካላት ነውን? ዘፍጥረት ላይ ደግሞ አብርሃም ሁለቴ ስሙ ተደግሟል፦
ዘፍጥረት 22፥11የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። *“አብርሃም፥ አብርሃም”* አለው።
አብርሃም ሁለት አካል ነውን? ኢየሱስን ሁለት ጊዜ “ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ” ይሉታል፦
ማቴዎስ 7፥21 *“ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ”* የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።
ኢየሱስ ሁለት አካል ነውን? ሙሴ ሁለት ጊዜ “ሙሴ ፥ ሙሴ” ተብሏል፦
ዘጽአት 3፥4 “እግዚአብሔር ከቁጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ፦ *ሙሴ፥ ሙሴ ሆይ አለ*።
ሙሴ ሁለት አካል ነውን? እንዳትሰክሩ ብለን እንጂ ማስረጃ በቁና ሰፍረን መስጠት እንችላለን። አይሁዶች በሥላሴ አያምኑም፥ ታዲያ ለምን አንድ ጉዳይ ሶስት ጊዜ ተደጋገመ? ለሚለው መልሳቸው “አንድ ስም ከአንድ በላይ ጊዜ መጠራት ጉዳዩን አጽንዖትና አንክሮት ለመስጠት እንጂ ያንን ስም ብዙ አካል አያደርገውም” ይላሉ። አንዱ አምላክ “ቅዱስ” ተብሏል፥ እንደ እርሱ ያለ ቅዱስ የለም፦
1ኛ ሳሙኤል 2፥2 “እንደ ያህዌህ ቅዱስ የለምና”።
1ኛ ሳሙኤል 2፥2 "ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም"።
ራእይ 15፥4 “አንተ ብቻ ቅዱስ” ነህና"።
“አንተ” የሚለው ነጠላ ተውላጠ-ስም አንድ ነጠላ ማንነት ብቻ ቅዱስ እንደተባለ ፍትውና ቁልጭ አድርጎ ያስረዳል፥ ሦስት ማንነትቶች ቢሆኑ ኖሮ “እናንተ” ተብሎ ይቀመጥ ነበር። “ከእናንተ” በቀር ቅዱስ የለም” ቢል ኖሮ ለሦስት አካላት ያዋጣ ነበር፥ ቅሉ ግን “አንተ ብቻ ቅዱስ ነህ” ተብሏል። እርሱ ቅዱስ የተባለው ፍጡራን በተባሉበት ስሌትና ቀመር አይደለም፥ ለምሳሌ ሰው እና መላእክት ቅዱሳን ተብለዋል፦
ዘሌዋውያን 11፥45 *እንግዲህ “እኔ ቅዱስ ነኝ እና እናንተ ቅዱሳን”* ሁኑ።
ኢዮብ 15፥15 እነሆ፥ *በቅዱሳኑ ስንኳ አይታመንም*፤ ሰማያትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም።
እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ "ኤሎሂም" የተባሉት መላክእት ስለሆኑ ግሪክ ሰፕቱጀንት እና የዕብራውያን ጸሐፊም ጭምር "መላእክት" ብለው በግልጽ አስቀምጠዋል። ስለዚህ አዳም ዛፉን ሲበላ መልካም እና ክፉውን በማወቅ እንደ መላእክት ከሆነ ያህዌህ ደግሞ መልካምና ክፉ ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ የሚለው እነዚህን አማልክት ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፦
ሆሴዕ 12፥4 በጕልማስነቱም ጊዜ “ከአምላክ” ጋር ታገለ፤ “ከመልአኩም” ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም “ከእኛ” ጋር ተነጋገረ"።
ያዕቆብ የተነጋገረው ከመልአኩ ጋር እና ከያህዌህ ጋር ነው፥ ያህዌህ መልአኩን ጨምሮ “ከእኛ” እንዳለ አንባቢ ልብ ይለዋል። አይ ያህዌህ እኛ የሚለው ሥላሴን ያሳየል ከተባለ ዕውዱ ላይ ስለ ሥላሴ የሚያሳይ ኃይለ-ቃል ፈልቅቆ ማሳየት ይጠበቅባችኃል! ወይም "ይህ አንቀጽ ስለ ሥላሴ ያወራል" ብሎ የተናገረ ነብይ ወይም ሐዋርያ ጠቅሳችሁና አጣቅሳችሁ መሞገትና መሟገት ይጠበቅባችኃል።
በባይብል አንድ ማንነት "ኑ" ብሎ ሲያዝ ከእርሱ ውጪ ከሆኑ ማንነቶች ጋር እየተነጋገረ እንደሆነ ስሙር እና ዕሙር ነው፦
ዘፍጥረት 11፥3 እርስ በርሳቸውም፦ "ኑ" ጡብ "እንሥራ"።
ዘፍጥረት 37፥20 አሁንም "ኑ" እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው"።
ዘኍልቍ 14፥4 እርስ በርሳቸውም፦ "ኑ" አለቃ ሾመን ወደ ግብፅ "እንመለስ" ተባባሉ።
1ኛ ሳሙኤል ቀዳማዊ 11፥14 ሳሙኤልም ሕዝቡን፦ "ኑ" ወደ ጌልገላ "እንሂድ"፥ በዚያም መንግሥቱን "እናድስ" አላቸው።
ሰዎች ለሰዎች "ኑ" ብለው በትእዛዛዊ ግስ ማዘዛቸው የደረጃ መግዛትን"functical subordination" ሲያመለክት "እንሥራ" "እንግደለው" "እንጣለው" "እንመለስ" "እንሂድ" "እናድስ" የሚለው የንግግር መመላለስ እንዳለ አመላካች ነው። በአንድ ወቅት ያህዌህ ለእስራኤል ሕዝብ፦ "ኑ እንዋቀስ" ብሏቸው ነበር፦
ኢሳይያስ 1፥18 "ኑ" እና "እንዋቀስ" ይላል ያህዌህ"።
ያህዌህ አንድ ከሆነ ይህ አንድ ያህዌህ በሁለተኛ መደብ "ኑ" በማለት የሚያዘው እና "እንዋቀስ" በሚል በብዜት ግስ የሚያናግረው ከእርሱ ውጪ ያሉትን ፍጡራን እንደሆነ ቅቡል ነው፥ "ኑ" የሚለው ትእዛዛዊ ግስ በራሱ የኑባሬ መግዛትን"ontological subordination" ያሳያል። በተመሳሳይ ሰዋስው አንዱ አምላክ ያህዌህ ከእርሱ ውጪ ለሆኑ ፍጡራን "ኑ"
ዘፍጥረት 11፥ ያህዌህም አለ፦
ዘፍጥረት 11፥7 "ኑ" "እንውረድ" አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ "እንደባልቀው"።
የሚያጅበው አንዱ ያህዌህ "ሃባህ" הָ֚בָה የሚለው ከሁለት ማንነት የሆኑ ማንነቶችን ነው፥ እነዚህ ማንነቶች መላእክት መሆናቸውን በ 1952 ድኅረ-ልደት AD በቁምራን ዋሻ የሙት ባህር ጥቅል የተገኘው ጁብልይ በአገራችን መጽሐፍ ኩፋሌ ይናገራል፦
ግዕዙ፦
ኩፋሌ 10፥13 "ወይቤለነ እግዚአብሔር አምላክነ ለነ፤ ናሁ ሕዝብ አሐዱ፤ መወጠነ ይግበር፤ ወይእዜኒ ኢናኀርቅ እምኔሆሙ ንዑ ንረድ ወንከዐው ልሳናቲሆሙ።
ዐማርኛ፦
ኩፋሌ 10፥13 "ፈጣሪአችን እግዚአብሔር እኛን እንዲህ አለን፦ አንድ ቋንቋ የሆነ ወገን ግንብ ይሰሩ ጀመር "ኑ" ወርደን በቋንቋ እንለያቸው"።
"ፈጣሪአች" የሚሉት መላእክት ስለመሆናቸው ከዚህ በፊት አይተናል፥ "ኑ" ያለውም ለመላእክት እንደሆነ ይህ ትውፊት አስረጂ ነው። የአይሁድ ኮመንታርይ ባጠቃላይ ያህዌህ "ኑ" "እንውረድ" ለመላእክት እንደሆነ አንዳች ልዩነት የላቸው።
በተጨማሪም አንድ ያህዌህ አለ፥ ይህ አንድ ያህዌህ መላእክትን ጨምሮ "እኛ" ይላል፦
ዘዳግም 6፥4 "እስራኤል ሆይ ስማ! "አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው"። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד.
ዘፍጥረት 3፥22 "ያህዌህ አምላክም አለ፦ "እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ"። וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, הֵן הָאָדָם הָיָה כְּאַחַד מִמֶּנּוּ, לָדַעַת, טוֹב וָרָע; וְעַתָּה פֶּן-
“እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦
“እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦
ነጥብ አንድ
“እንደ አንዱ”
“ከ-አሐድ” כְּאַחַ֣ד ማለት “እንደ አንዱ”as one of” ማለት ነው፤ ያ ማለት በከፊል መመሳሰልን ያሳያል፦
1ኛ ሳሙኤል 17፥36 *እኔ ባሪያህ “አንበሳ እና ድብ” መታሁ፤ ይህም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያውን አምላክ ጭፍሮች ተገዳድሮአልና “ከእነርሱ እንደ አንዱ” ይሆናል*። גַּם אֶת-הָאֲרִי גַּם-הַדֹּב, הִכָּה עַבְדֶּךָ; וְהָיָה הַפְּלִשְׁתִּי הֶעָרֵל הַזֶּה, כְּאַחַד מֵהֶם, כִּי חֵרֵף, מַעַרְכֹת אֱלֹהִים חַיִּים.
“ከ-አሐድ ሜሄም” כְּאַחַד מֵהֶם ማለት “ከእነርሱ እንደ አንዱ”as one of them” ማለት ሲሆን ፍልስጥኤማዊ ጎልያድ በዳዊት በመገደል ደረጃ “እንደ አንበሳ እና ድብ” ይሆናል ማለት ነው እንጂ ጎልያድ አውሬ ይሆናል ማለት አይደለም፥ “እንደ” የሚለው ተውሳከ-ግስ የተወሰነን መመሳሰል ለማመልከት የሚገባ ነው። ልክ እንደዚሁ አደም መልካምና ክፉ በማወቅ እንደ እንደ እነርሱ ሆኗል፥ ለዛ ነው “ከ-አሐድ ሜንሁ” כְּאַחַ֣ד מִמֶּ֔נּוּ ማለትም “ከእኛ እንደ አንዱ”as one of us” የሚለው። ያህዌህ ታዲያ ማንን ጨምሮ ነው “እኛ” የሚለው?
ነጥብ ሁለት
“እኛ”
ያህዌህ “እኛ” የሚለው ማንን ጨምሮ ነው? የሚለው ለመረዳት እዚሁ ዐውድ ላይ አዳም ከእኛዎቹ እንደ አንዱ የሚሆነው “መልካምንና ክፉን ለማወቅ” እንደሆነ ይሰመርበት! እዛው ዐውድ ላይ አዳም ቢበላ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የሚያውቁ” እንደሆነ ተነግሯል፦
ዘፍጥረት 3፥5 "ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ” ያህዌህ ስለሚያውቅ ነው እንጂ"። כִּי, יֹדֵעַ אֱלֹהִים, כִּי בְּיוֹם אֲכָלְכֶם מִמֶּנּוּ, וְנִפְקְחוּ עֵינֵיכֶם; וִהְיִיתֶם, כֵּאלֹהִים, יֹדְעֵי, טוֹב וָרָע.
የግዕዙ ዕትም፦
ዘፍጥረት 3፥5 “ዘይቤ ከመ ኢትኩኑ አማልክተ ወኢታምሩ ሠናየ ወእኩየ”።
የኢንግሊሹ ዕትም፦
For God doth know that in the day ye eat thereof, then your eyes shall be opened, and "ye shall be as gods, knowing good and evil".(KJV)
የግሪክ ሰፕቱአጀንት”LXX”፦
ዘፍጥረት 3፥5 ᾔδει γὰρ ὁ Θεός, ὅτι ᾗ ἂν ἡμέρᾳ φάγητε ἀπ᾿ αὐτοῦ, διανοιχθήσονται ὑμῶν οἱ ὀφθαλμοὶ καὶ ἔσεσθε ὡς "θεοί", γινώσκοντες καλὸν καὶ πονηρόν.
የግዕዙ ዕትም ላይ “አማልክት” ብሎ እንዳስቀመጠው አስተውል! “ኤሎሂም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ማለት “አማልክት” ማለት ነው፥ ይህ ቃል ለነጠላ ማንነት ወይንም ለብዙ ማንነት ይውላል። ግን እዚህ አንቀጽ ላይ ግን ለብዙ መባሉን በግሪክ ሰፕቱጀንት ላይ “ቶኢ” θεοί ማለትም “አማልክት” ብሎ በብዙ ቁጥር አስቀምጦታል፥ ልብ አድርግ የቴኦ ነጠላ “ቴኦስ” Θεὸς ነው። “ቴኦስ” ብሎ በነጠላ አለማስቀመጡ ለብዙ ማንነቶች መሆኑን ያሳያል፥ በኢንግሊሹም ደግሞ በብዙ ቁጥር “gods” መባሉን አስተውል። በብሉይ ደግሞ ብዙ ቦታ አማልክት የተባሉት መላእክት ናቸው፦
መዝሙር 97፥7 ”አማልክትም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ስገዱለት።
መዝሙር 8፥5 *“ከአማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים እጅግ ጥቂት አሳነስኸው"።
መዝሙር 138፥1 ”በአማልክት כֵּֽאלֹהִ֔ים ፊት እዘምርልሃለሁ"።
የሥላሴ አማንያን፦ "አይ ያህዌህ እኮ በብዜት የተጠቀሰው በስም መደብ "ኤሎሂም" ተብሎ ብቻ ሳይሆን በብዜት በግስም መደብ ጭምር ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ዘፍጥረት 20፥13 "ኤሎሂምም ከአባቴ ቤት "ባወጣኝ" הִתְע֣וּ ጊዜ አልኋት"።
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባወጣ" ለሚለው የገባው የዕብራይስጥ ቃል "ሂትኡ" הִתְע֣וּ ሲሆን ቃል በቃል ሲተረጎም "ባወጡ" ነው፥ "አወጣ" ለማለት ነጠላ ቃል "ታህ" תָּעָה መሆን ነበረበት። እና ምን ለማለት ፈልጋችሁ ነው? ስንላቸው "ሦስት አካላትን ያሳያል" ይሉናል ይህ ውኃ የማይቋጥር ስሑት አካሄድ ነው፥ በባይብል አንድ ነገር ሦስትነት ሳይኖረው ብብዜት ግስ መቀመጥ የተለመደ ነው፦
ዘጸአት 32፥4 "ከእጃቸውም ተቀብሎ በመቅረጫ ቀረጸው፥ ቀልጦ የተሠራ ጥጃም አደረገው፤ እርሱም፦ እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር "ያወጡህ" הֶעֱל֖וּךָ አማልክትህ ናቸው" አላቸው"።
ጥጃው አንድ ሆኖ ሳለ በነጠላ "አለህ" עָלָה ማለትም "ያወጣ" በማለት ፋንታ በብዙ የግስ መደብ "ሂልኡ" הֶעֱל֖וּ ማለትም "ያወጡ" በማለት መጠቀሙ ጥጃው ሦስት አካል አሊያም ሥላሴ መሆኑን ያሳያልን?
ፍልስጤማውያን ያህዌህ ሥላሴ መሆኑን አያምኑም፥ ግን ስለ ያህዌህ ሲናገሩ፦ "እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት የመቱ ናቸው" ብለዋል፦
1ኛ ሳሙኤል 4፥8 "ወዮልን ከእነዚህ ከኃያላን አማልክት እጅ ማን ያድነናል? እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት "የመቱ" ናቸው"።
ፍልስጤማውያን ያህዌህን በብዙ ቁጥር "የመቱ" ስላሉ ያህዌህ ሦስት አካል መሆኑ ገብቷት ነውን?
ሳሙኤል አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ሲወጡ" በሚል በብዙ የግስ መደብ ተቀምጧል፦
1 ሳሙኤል 28፥13 ሴቲቱም ሳኦልን፦ "አማልክት ከምድር "ሲወጡ" አየሁ" አለችው።
1 ሳሙኤል 28፥14 "እርስዋም፦ ሽማግሌ ሰው "ወጣ" መጐናጸፊያም ተጐናጽፎአል" አለች። ሳኦልም ሳሙኤል እንደ ሆነ አወቀ፥ በፊቱም ተጐነበሰ፥ በምድርም ላይ እጅ ነሣ"።
ሴትየዋ ሳሙኤልን በብዙ ቁጥር "ሲወጡ" ስላለች ሳሙኤል ሦስት አካል መሆኑ ገብቷቸው ነውን?
ከላይ የዘረዘርነው የሙግት ነጥብ እና አካሄድ ኤሎሂም ለሥላሴ አስተምርሆት እንዳልሆኑ በቂ ማሳያ ነው፥ እንደውም እኮ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ፦ "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር" ይለናል፦
ገድለ ተክለ ሃይማኖት ገጽ 8 ቁ. 24 "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር"፡፡
ታዲያ "የብሉይ ኪዳን ሰዎች ብዜትን የሚጠቀሙት ለሥላሴ ነው" መደምደም እንዴት ይቻላል?
የብዜት የስም መደብ በተመለከተ የሚያጅበው እኮ “አዶን” אָד֖וֹן በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶን” በሚለው ቃል ላይ “ኢም” ים የምትለዋ ስትጨመር “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים ትሆናለች፥ የአዶን አገናዛቢ ዘርፍ “አዶኒ” אדֹנִ֗י ማለትም “ጌታዬ” ማለት ነው፥ የአዶኒም አገናዛቢ ዘርፍ ደግሞ በብዜት “አዶናይ” אֲדֹנָ֥י ነው።
ኤሎሂም
“ኤሎሃ” אלוהּ ለሚለው ቃል ብዜት “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ቃል በቃል ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ነው፥ “ኤሎሂም” אלהים የሚለው ቃል ለአንድ ቅዋሜ ማንነት ግርማ፣ ሞገስ፣ ሉዓላዊነት፣ ልዕልና፣ ገናናነት ሆኖ ይመጣል፦
ዘፍጥረት 1፥1 "በመጀመሪያ “ኤሎሂም אלהים ሰማይንና ምድርን ፈጠረ"።
በዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም በእግሊዝኛ ላይ "God" አሊያም በግሪኩ ሰፕቱጀንት "ቴኦስ" Θεὸς ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ምሁራን ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙት ብዙ ቁጥር ለማመልከት "እግዚአብሔሮች" ወይም "Gods" አሊያም "ቴኦኢ" θεοί በማለት ፋንታ በነጠላ የመተርጎማቸው ምክንያት ቃሉ ብዜት ሳይሆን ግርማን፣ ሞገስን፣ ሉዓላዊነትን፣ ልዕልናን፣ ገናናነትን ስለሚያመለክት ነው፥ ለምሳሌ ግሪግ ሰፕቱጀንት ላይ ተመልከት፦
ዘፍጥረት1፥1 ἐν ἀρχῇ ἐποίησεν ὁ θεὸς τὸν οὐρανὸν καὶ τὴν γῆν.
እውን ዘፍጥረት 1፥1 ላይ “ኤሎሂም”אלהים መባል ሥላሴ "አማልክት" ለመሆናቸው እንደ ማስረጃ መቅረቡ በራሱ ዐበይት ክርስትና የመድብለ-አማልክት ትምህርት"Polytheism" አራማጅ መሆኑን አያሳብቅምን?
ሲቀጥል ዘፍጥረት 1፥1 ላይ ቃል በቃል ብንወስድ እንኳን "አማልክት" አለ እንጂ ሦስት አካላት ወይም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳይ ምንም ፍንጭ እና ሽታው የለውም።
ሢሠልስ “ኤሎሂም” אלהים የተባለ አንድ ማንነት በውስጥ ሦስት ማንነቶችን ያሳያል ከተባለ የመረባት አምላክ ተብሎ የሚታመነው ዳጎን "ኤሎሂም” אלהים ተብሏል፦
መሳፍንት 16፥23 “ለአምላካቸው” אֱלֹהֵיהֶ֖ם ለዳጎን ታላቅ መሥዋዕት ይሠዉ ዘንድ ደስም ይላቸው ዘንድ ተሰበሰቡ"።
የፍልስጥኤምም መኳንንት ዳጎንን "አንድም ሦስትም ነው" ብለው አያምኑም፥ የመሳፍንት ጸሐፊም ዳጎን "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ብሎ አያምንም።
የሴም አምላክ ተብሎ የሚታመነው በኣል "ኤሎሂም” אלהים ተብሏል፦
1ኛ ነገሥት 18፥27 "በቀትርም ጊዜ ኤልያስ “ኤሎሂም” אלהים ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ! ምናልባት አሳብ ይዞታል ወይም ፈቀቅ ብሎአል ወይም ወደ መንገድ ሄዶአል፥ ወይም ተኝቶ እንደ ሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል" እያለ አላገጠባቸው"።
ኤልያስ በኣልን በሽሙጥ እና በለበጣ “ኤሎሂም” ሲለው "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ማለቱ አልነበረም። ቀጣይ ሌሎች ሙግቶችን እንመልከት፦
መዝሙር 45፥6 “ኤሎሂም” אלהים ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘላለም ነው፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው።
እንደ አይሁዳውያን ማብራሪያ ይህ አንቀጽ የሚናገረው ስለ ንጉሥ ሰልሞን ነው፥ የዕብራውያንን ጸሐፊ መሠረት በማድረግ ሥላሴአዋያን ይህንን ጥቅስ ለወልድ ነው" ይላሉ።
ወልድ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ወልድ እራሱ ሦስት ማንነት ነውን? ያህዌህ ሙሴን በፈርዖን ላይ “ኤሎሂም” אלהים አርጎታል፦
ዘጸአት 7፥1 ያህዌህም ሙሴን አለው፦ እይ! እኔ ለፈርዖን “ኤሎሂም” אלהים አድርጌሃለው"።
ሙሴ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ሦስት ማንነት ነውን? በዕብራይስጥ ቃላት ውስጥ የብዜት ቃላት ለክብር መምጣት የተለመደ ነው፦
መኃልይ ዘሰሎሞን 5፥16 "አፉ" እጅግ “ጣፋጭ” מַמְתַקִּים ነው፥ እርሱም ፈጽሞ “ያማረ” מַחֲמַדִּים ነው"።
ሱናማይቱ ልጃገረድ የንጉሥ ሰልሞንን አፍ “ጣፋጭ” ነው ትለናለች፥ “ጣፋጭ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “ሙተቅ” מֹתֶק ሳይሆን በብዜት “መምተቂም” מַמְתַקִּים ማለትም “ጣፋጮች” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ያማረ” ነው ትለናለች፥ “ያማረ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “መኽመድ” מַחְמַד ሳይሆን በብዜት “መኽመዲም” מַחֲמַדִּים ማለትም “ያማሩ” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? እስቲ እንቀጥል፦
ኢሳይያስ 19፥4 "ግብጻውያንንም በጨካኝ “ጌታ” אֲדֹנִ֣ים እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌህ"።
“አዶን” אָדוֹן ደግሞ በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ የአሦር ንጉሥ አስራዶን በ 670 ቅድመ-ልደት የተነሳ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים ስለተባለ አስራዶን ሦስት ማንነት ነውን? ሙግታችንን እንቀጥል፦
ዘፍጥረት 21፥7 "ደግሞም ሣራ “ልጆችን” בָנִ֖ים እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና" አለች*።
“ባኒም” בָנִ֖ים በብዜት ሲሆን “ልጆች” ማለት ሲሆን በነጠላ “ቤን” בֵ֖ן ነው፥ ይስሐቅ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “ባኒም” בָנִ֖ים እንደተባለ አስተውል! ሳራ ያጠባችው ልጅ ይስሐቅ “ልጆች” ስለተባለ ይስሐቅ ሥላሴ ነውን?
ኤሎሂም
“ኤሎሃ” אלוהּ ለሚለው ቃል ብዜት “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ቃል በቃል ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ነው፥ “ኤሎሂም” אלהים የሚለው ቃል ለአንድ ቅዋሜ ማንነት ግርማ፣ ሞገስ፣ ሉዓላዊነት፣ ልዕልና፣ ገናናነት ሆኖ ይመጣል፦
ዘፍጥረት 1፥1 "በመጀመሪያ “ኤሎሂም אלהים ሰማይንና ምድርን ፈጠረ"።
በዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም በእግሊዝኛ ላይ "God" አሊያም በግሪኩ ሰፕቱጀንት "ቴኦስ" Θεὸς ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ምሁራን ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙት ብዙ ቁጥር ለማመልከት "እግዚአብሔሮች" ወይም "Gods" አሊያም "ቴኦኢ" θεοί በማለት ፋንታ በነጠላ የመተርጎማቸው ምክንያት ቃሉ ብዜት ሳይሆን ግርማን፣ ሞገስን፣ ሉዓላዊነትን፣ ልዕልናን፣ ገናናነትን ስለሚያመለክት ነው፥ ለምሳሌ ግሪግ ሰፕቱጀንት ላይ ተመልከት፦
ዘፍጥረት1፥1 ἐν ἀρχῇ ἐποίησεν ὁ θεὸς τὸν οὐρανὸν καὶ τὴν γῆν.
እውን ዘፍጥረት 1፥1 ላይ “ኤሎሂም”אלהים መባል ሥላሴ "አማልክት" ለመሆናቸው እንደ ማስረጃ መቅረቡ በራሱ ዐበይት ክርስትና የመድብለ-አማልክት ትምህርት"Polytheism" አራማጅ መሆኑን አያሳብቅምን?
ሲቀጥል ዘፍጥረት 1፥1 ላይ ቃል በቃል ብንወስድ እንኳን "አማልክት" አለ እንጂ ሦስት አካላት ወይም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳይ ምንም ፍንጭ እና ሽታው የለውም።
ሢሠልስ “ኤሎሂም” אלהים የተባለ አንድ ማንነት በውስጥ ሦስት ማንነቶችን ያሳያል ከተባለ የመረባት አምላክ ተብሎ የሚታመነው ዳጎን "ኤሎሂም” אלהים ተብሏል፦
መሳፍንት 16፥23 “ለአምላካቸው” אֱלֹהֵיהֶ֖ם ለዳጎን ታላቅ መሥዋዕት ይሠዉ ዘንድ ደስም ይላቸው ዘንድ ተሰበሰቡ"።
የፍልስጥኤምም መኳንንት ዳጎንን "አንድም ሦስትም ነው" ብለው አያምኑም፥ የመሳፍንት ጸሐፊም ዳጎን "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ብሎ አያምንም።
የሴም አምላክ ተብሎ የሚታመነው በኣል "ኤሎሂም” אלהים ተብሏል፦
1ኛ ነገሥት 18፥27 "በቀትርም ጊዜ ኤልያስ “ኤሎሂም” אלהים ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ! ምናልባት አሳብ ይዞታል ወይም ፈቀቅ ብሎአል ወይም ወደ መንገድ ሄዶአል፥ ወይም ተኝቶ እንደ ሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል" እያለ አላገጠባቸው"።
ኤልያስ በኣልን በሽሙጥ እና በለበጣ “ኤሎሂም” ሲለው "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ማለቱ አልነበረም። ቀጣይ ሌሎች ሙግቶችን እንመልከት፦
መዝሙር 45፥6 “ኤሎሂም” אלהים ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘላለም ነው፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው።
እንደ አይሁዳውያን ማብራሪያ ይህ አንቀጽ የሚናገረው ስለ ንጉሥ ሰልሞን ነው፥ የዕብራውያንን ጸሐፊ መሠረት በማድረግ ሥላሴአዋያን ይህንን ጥቅስ ለወልድ ነው" ይላሉ።
ወልድ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ወልድ እራሱ ሦስት ማንነት ነውን? ያህዌህ ሙሴን በፈርዖን ላይ “ኤሎሂም” אלהים አርጎታል፦
ዘጸአት 7፥1 ያህዌህም ሙሴን አለው፦ እይ! እኔ ለፈርዖን “ኤሎሂም” אלהים አድርጌሃለው"።
ሙሴ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ሦስት ማንነት ነውን? በዕብራይስጥ ቃላት ውስጥ የብዜት ቃላት ለክብር መምጣት የተለመደ ነው፦
መኃልይ ዘሰሎሞን 5፥16 "አፉ" እጅግ “ጣፋጭ” מַמְתַקִּים ነው፥ እርሱም ፈጽሞ “ያማረ” מַחֲמַדִּים ነው"።
ሱናማይቱ ልጃገረድ የንጉሥ ሰልሞንን አፍ “ጣፋጭ” ነው ትለናለች፥ “ጣፋጭ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “ሙተቅ” מֹתֶק ሳይሆን በብዜት “መምተቂም” מַמְתַקִּים ማለትም “ጣፋጮች” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ያማረ” ነው ትለናለች፥ “ያማረ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “መኽመድ” מַחְמַד ሳይሆን በብዜት “መኽመዲም” מַחֲמַדִּים ማለትም “ያማሩ” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? እስቲ እንቀጥል፦
ኢሳይያስ 19፥4 "ግብጻውያንንም በጨካኝ “ጌታ” אֲדֹנִ֣ים እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌህ"።
“አዶን” אָדוֹן ደግሞ በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ የአሦር ንጉሥ አስራዶን በ 670 ቅድመ-ልደት የተነሳ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים ስለተባለ አስራዶን ሦስት ማንነት ነውን? ሙግታችንን እንቀጥል፦
ዘፍጥረት 21፥7 "ደግሞም ሣራ “ልጆችን” בָנִ֖ים እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና" አለች*።
“ባኒም” בָנִ֖ים በብዜት ሲሆን “ልጆች” ማለት ሲሆን በነጠላ “ቤን” בֵ֖ן ነው፥ ይስሐቅ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “ባኒም” בָנִ֖ים እንደተባለ አስተውል! ሳራ ያጠባችው ልጅ ይስሐቅ “ልጆች” ስለተባለ ይስሐቅ ሥላሴ ነውን?
👉 አላህ(ሱወ) ፍጥረታትን የፈጠረው ለሰው ልጅ ጥቅም ሲሆን ሰውና ጋኔን ግን እርሱን በብቸኝነት ሊገዙ እንደፈጠራቸው በ51፡56 ላይ ተናግሯል። ታድያም ይህ ፈጣረውን ሊገዛ የተፈጠረ የሆነው የሰው ልጅ ኩራት ከራሱ ላይ አንስቶ አምላኩን (አላህን) በብቸኝነት መገዛት እንዳለበትና ኩራተኛም ሰው የተጠላ መሆኑን አል- ሙተከቢር (ኩሩው) የሆነው አላህ(ሱወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦
4፡36
واعبدوا الله ولا تشركوا به شيئا ۖ وبالوالدين إحسانا وبذي القربى واليتامى والمساكين والجار ذي القربى والجار الجنب والصاحب بالجنب وابن السبيل وما ملكت أيمانكم ۗ إن الله لا يحب من كان مختالا فخورا
አላህንም ተገዙ፡፡ በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ በየቲሞችም፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በሩቅ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ንብረት ባደረጓቸው (ባሮች)፣ መልካምን (ሥሩ)፤ አላህ ኩራተኛ ጉረኛ የኾነን ሰው አይወድም፡፡
57፡23
لكيلا تأسوا على ما فاتكم ولا تفرحوا بما آتاكم ۗ والله لا يحب كل مختال فخور
(ይህ ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑ አላህም በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው፡፡ አላህም ኩራተኛን ጉረኛን ሁሉ አይወድም፡፡
👉 የኩራት መጀመሪያው ጥፋት መጨረሻው ደግሞ እሳት ነው። ለዚህም የፈርዖንን ሁኔታ በቁርዓን መመልከት በቂ ነው።
23፡ 46-48
إلى فرعون وملئه فاستكبروا وكانوا قوما عالين
فقالوا أنؤمن لبشرين مثلنا وقومهما لنا عابدون
فكذبوهما فكانوا من المهلكين
ወደ ፈርዖንና ወደ ጭፍሮቹ (ላክናቸው)፡፡ ኮሩም፡፡ የተንበጣረሩ ሕዝቦችም ነበሩ፡፡ «ብጤያችንም ለኾኑ ሁለት ሰዎች ሕዝቦቻቸው ለእኛ ተገዢዎች ኾነው ሳሉ እናምናለን» አሉ፡፡ አስተባበሉዋቸውም፡፡ ከጠፊዎቹም ኾኑ፡፡
👉 ስለ ኩራተኛ ሰው ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦
ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 7
መጽሐፍ 72 ቁጥር 680
አቡ ሁረይራ ዘግበውታል።
ነብዩ (ወይም አቡል ቃሲም) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹አንድ ሰው ሁለት ልብስ ለብሶና ፀጉሩ በደንብ ተላጥጦ እየኮራ ሲሄድ በድንገት አላህ ምድር ውስጥ እንዲሰምጥ አድርጎት ወደ ውስጥ እየሰመጠ ይሄዳል። እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ።
*********************
ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 7
መጽሐፍ 72 ቁጥር 683
አብደላህ ቢን ዑመር ዘግበውታል።
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “ከኩራትና ከኩራት የተነሣ ልብሱን (በምድር ላይ) የሚጎተት አላህ በትንሳኤ ቀን አይመለከተውም።
አላህ ከኩራት ይጠብቀን!!
ይህንና ሌሎች ንፅፅሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative
99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ክፍል -9
⓽ አል ሙተከቢሩ { المتكبار}
[[[[ ኩሩው ]]]]]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
- አል-ሙተከቢር ፦ ማለት ትርጉሙ #ኩሩ ማለት ነው። ታድያ ብቸኛው ፣ንጉስ፣ ከጉድለት የጠራው፣ ሃያሉ፣ጥበበኛው... ከሆነው ጌታችን አላህ(ሱወ) የመልካም ስሞች መካከልም ይህ #አል_ሙተከቢር የሚለው ስም ሌላኛው የባህሪያቱ መገለጫውና የመጠሪያው ስሙ በመሆን ይታወቃል። እናም ይህ አል-ሙተከቢር ( ኩሩ) የሆነው ጌታም በቁርዓን ሲናገር እንዲህ ይላል።
59፡ 23
هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار #المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون
<< እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ #ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ!።"
ራሱን ቻይና የተብቃቃ የሆነው ጌታ ኩራት የርሱ ልብሱ ነው። ለዚህም ረሱል(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦
በሀዲስ ቁዱስ ላይ አቡ ሁረይራ (ረዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ሃያሉ የተከበረው ጌታ እንዲህ ብሏል፦ ኩራት ካባዬ፤ ታላቅነት መታጠቂያዬ ነው። ከእነሱ ከአንደኛው እንኳ ከእኔ ጋር የሚፎካከረውን ወደ ጀሐነም እሳት እወረውረዋለሁ።" በማለት ተናግሯል።
✔ ኩራት የአላህ(ሱወ) ብቻ መገለጫ ሲሆን #አል_ሙተከቢሩ (ኩሩው) የሚለው የአላህ ስም በቁርዓን ውስጥ ሁኔታውን ስንመለከተው አብዛኛውንም ጊዜ ከሀዲዎች ከአላህ ውጪ የሆነን ባዕድ አካል በማምለካቸው እና በዚህም በመኩራታቸውም ምክንያት ከመጨረሻው ዓለም ጋር ያላቸው ቁርኝት ጋር ተያይዞ ምን እንደሚመስል ተጠቅሶ እናገኘዋለን። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦
45፡ 36-37
فلله الحمد رب السماوات ورب الأرض رب العالمين وله الكبرياء في السماوات والأرض ۖ وهو العزيز الحكيم
ምስጋናም ለአላህ ለሰማያት ጌታ ለምድርም ጌታ ለዓለማት ጌታ የተገባው ነው፡፡
ኩራትም በሰማያትም በምድርም ለእርሱ ብቻ ነው፡፡ እርሱም አሸነፊው ጥበበኛው ነው፡፡
16፡22-23
إلهكم إله واحد ۚ فالذين لا يؤمنون بالآخرة قلوبهم منكرة وهم مستكبرون
لا جرم أن الله يعلم ما يسرون وما يعلنون ۚ إنه لا يحب المستكبرين
አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እነዚያም በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት ልቦቻቸው ከሓዲዎች ናቸው፡፡ እነሱም የኮሩ ናቸው፤ (አያምኑም)፡፡ አላህ የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ሁሉ የሚያውቅ ለመኾኑ ጥርጣሬ የለበትም፡፡ እርሱ ኩሩዎችን አይወድም፡፡
የሙሳ እናትም በወህዩ መሠረት ልጇን ወደ ባህር ወረወረችው። አይኗ እያየ ልጇን ባህር ይዞባት ሄደ!! ሱብሃን አሏህ!!! አሁን ይህች እናት የቀራት ነገር ቢኖር ፈጣሪዋ ላይ ተስፋ ማድረግን ብቻ ነበር። የጥበበኛው አላህ ጥበብ በጣም የሚገርም ነውና በባህር የተወረወረው ልጅ በመጨረሻም የፊርአውን ሚስት ባህር ውስጥ ታገኘውና ከባህሩ አውጥታ የአራጁ የፊርአውን ቤት አስገባችው። ነገር ግን ልጁ እንዳይታረድ ከልክላው እዛው ቤት ሞግዚት ተቀጥሮለት እንዲያድግ ተወሰነ። ከዚያም ሞግዚት ፍለጋ ቀጣይ አጀንዳ ሆነና ሞግዚት(አሳዳጊ) ተፈልጎ ተገኘ። ሞግዚቷ ደግሞ ማን ብትሆን ጥሩ ነው!?? ወልዳ ልጇን በባህር የወረወረችው የሙሳ የራሳቸው እናት አሳድጊ ተብላ ተቀጠረች። አሏህ አክበር!!!!!!!!
ከዚያም አሏህ እንዲህ ይላል፦
28፡ 13
فرددناه إلى أمه كي تقر عينها ولا تحزن ولتعلم أن وعد الله حق ولكن أكثرهم لا يعلمون
<< ወደናቱም ፥ አይንዋ እንድትረጋ ፥ እንዳታዝንም ፥ የአላህም የተስፋ ቃል እርግጥ መሆኑን እንድታውቅ መለስነው፤ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም።"
በዚህ መልኩ አልጀባሩ አላህ ወዳጆቹን ይጠግናል።
✔ #በአል_ጀባር እና #አል_ሙንተቂም መካከል ያለው ልዩነት
* አል- ሙንተቂም ከበዳዮች ጋር ብቻ የተያያዘ ነው።
* አል-ጀባር ግን በዋንኛነት ከተበዳዮች ጋር የተያያዘ ስም ነው። ስለሆነም የተበዳዮችን ሐቅ ለማሟላት በዳዮችን መበቀል የግድ ነው።
ታድያም አንዳንድ ጊዜ ሰዎችን እንበድልና በሰዎች ላይ በሰራነው ግፍ የተነሳ አላህ(ሱወ) ይህንን ሰው ለመጠገን ብሎ ይሰብረናል። በዚህም ጊዜ ህመሙ ይሰማንና አላህ ሆይ ጠግነኝ፣ፈውሰኝ በማለት ወደ አል-ጀባር እንመለሳለን። አላህም እኛን የሰበረበት ነገር ወደ ጸጋ ይለውጥልናል።
በአንድ ወቅት ነብዩ ሙሳ(ዐሰ) ግብፅ በነበሩበት ጊዜ አንድን ሰውዬ ይመቱትና ድንገት ሰውዬው ይሞታል። በዚህም ምክንያት ሙሳ(ዐሰ) ግብፅን ለቀው ተሰደዱ። ይህ በርግጥም ኋላ ላይ ወደ ከፍተኛ ፀጋ የተለወጠ ትልቅ ስብራት ነበር። በዚህን ጊዜ በስደት በቆዩበት 10 ዓመታት አላህ(ሱወ) ለነብይነት ያዘጋጃቸው ጊዜ ነበር።
- #አል_ሙንተቂም ግፈኛና በደለኛን ብርቱ አያያዝ በመያዝ ለተበዳዮችና ለተጨቋኞች የሚበቀልላቸው የሆነ ማለት ነው።
ጭቆና በጣም አስከፊና የመጨረሻው ውጤቱንም እልቂት ሲሆን የሚጨቆኑ ሰዎችም በቂም በጥላቻ ተነሳስተው አላስፈላጊ ተግባር ውስጥ ተዘፍቀው እናገኛቸዋለን። በተለያየ ጊዜ በሰዎች ጭቆና የመጣ ዘር ማጥፋትና ብሄርተኝነት ይፈጠራል፤ ፅንፈኝነት፣ አሸባሪነትና ሌላም ሌላም ቡድኖች የሚፈጠሩት በዚህ በጭቆና ምክንያት ነው።
ኢብኑ ኡመር በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ (ሰዐወ) " በቂያማ ቀን ጭቆና (ለባለቤቱ(የሙስሊም ዘገባ)) ጨለማ ይሆናል" ብለዋል።
[ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መጽሐፍ 43 ቁጥር 627
- አል-ሙንተቂም ማለት በዚህ መልኩ ከተበዳዮች ጎን የሚቆም ማለት ነው።
በሌላ ኢብኑ አባስ በዘገቡት ሐዲስ
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሙዓዝን ወደ የመን ላኩና፡- “በእርሱ(በተበዳይ) እና በአላህ መካከል መጋረጃ ስለሌለ ከተጨቆኑ ሰዎች እርግማን ፍራ" ብለዋል።
*****
[ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መፅሐፍ 43 ቁጥር 628 ]
ክፍል -9 ይቀጥላል
t.me//AkeelComparative
99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ክፍል- 8
⓼ አል ጀባር { الجبار }
[[[[ ሀያል ]]]]]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
" #አል_ጀባር " የሚለው ስም በቁርዓን ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ ነው የተጠቀሰው ይኸውም፦
59፡ 23
هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز #الجبار المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون
<< እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ #ሃያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ!።"
✔ "አል-ጀባር" ማለት በቋንቋ ደረጃ ሁለት ተቃራኒ ትርጉም አለው። የመጀመሪያው ትርጉሙ " #ሀያሉ ፣ ትዕቢተኞችን በሀያልነቱ የሚሰብር" ማለት ሲሆን ሌላኛው ትርጉሙ ደግሞ " #ጠጋኝ ፣ የተጎዱትን የሚጠግን፣ ጉዳታቸውን የሚያብስና የሚፈውስ " ማለት ነው። መቼም የሚጠገን ካለ የሚሰበር ስላለ ነውና ነው።
መሠበር ሁለት አይነት አለው። የአካል መሠበርና የቀልብ መሠበር ናቸው።
- የሠው ልጅ(ሐኪሞች) የተሰበረን አካል በአላህ ፈቃድ ሊጠግኑ ይችላሉ።ይህም ሲባል አጥንት አያይዞና አስሮ ወደ ቦታ ይመልስ ይሆናል ነገር ግን የአጥንቱ የደም ስሮችና ሌሎችንም እንደገና ስራቸውን እንዲጀምሩ የሚያደርገው #አል #ጀባሩ አላህ ነው።
- ሐኪሞች የተሠበረን ቀልብ መጠገን አይችሉም።
- አል-ጀባሩ አላህ ግን ሁለቱም ስብራቶች የሚጠግን #ጠጋኝ የሆነ ጌታ ነው። የቀልብ ስብራትን ጥገናን በተመለከተ ደግሞ #አልጀባሩ አላህ ብቸኛው የዚህ ሙያ ባለቤት ነው።
ከነብዩ(ሰዐወ) ዱዓዎች መካከል "ያ ጃቢረ ኩልለ ከሲር.. ይገኝበታል።
ትርጉሙንም "የተሰበረውን ሁሉ የምትጠግን ሆይ!" ማለት ነው።
በየ ስራ ቦታችን አካባቢ ግፈኛ የሆነ ሐላፊ ኖሮብንም በሆነም ባልሆነም ምክንያት ቀልባችንን የሚሰብርብን ከሆነ " ያ ጀባር!!!" እንበለው ከእርሱ ውጪ ሌላ ጠጋኝ ስለሌለ በእርግጠኝነት ይጠግነናል።
@AkeelComparative
እስቲ አንድ ታሪክ ላስታውስ! በፊርአውን ዘመን ልጅ ሲወለድ የተወለዱት ወንዶች ከሆኑ ህፃናቶቹ ያርዳቸው ነበር። እናም የሙሳ(ዐሰ) እናት ወንድ ልጅ(ሙሳን) ወለዱና ያርድብኛል ብላ ክፉኛ ሰጋች። አል ጀባሩ አሏህ(ሱወ) ግን ወደሷ ወህይ አደረገ።
28፡7
وأوحينا إلى أم موسى أن أرضعيه ۖ فإذا خفت عليه فألقيه في اليم ولا تخافي ولا تحزني ۖ إنا رادوه إليك وجاعلوه من المرسلين
<< ወደ ሙሳም እናት <አጥቢ፤ በርሱም ላይ በፈራሽ ጊዜ በባህሩ ውስጥ ጣይው፤ አትፍሪም፤ አትዘኝም፤ እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልዕክተኞቹም አድራጊዎቹ ነንና> ማለትን አመለከትን።>>
የሙሳ እናት ልቧ ምን ያክል ተሰብሮ እንደነበር ለአፍታ ያህል እናስተውል!! 9 ወር በሆዷ ተሸክማ የወለደችው ልጇን አይኗ እያየ ሊታረድ መሆኑን ስታስበው እንዴት እንደተረበሸችና በሌላም በኩል ደግሞ ወደ ባህር ስትወረውረው!!
ከዚህ ጭንቀት በኋላም ግን ጠጋኝ የሆነው አልጀባር ቀልቧን ጠገነው። "አትፍሪም አትዘኝም እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልዕክተኞቹም አድራጊዎች ነንና" በማለት አረጋጋት
.....
የዚህን ሙሉ መረጃና ሌሎችም ንፅፅሮችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative
✔ ከቁርዓንና ከሐዲስ በስተቀር ሌሎች ኪታቦችን መከተልና ቢድአ መፍጠርን የማይገባ መሆኑን
ሶሒሕ ቡኻሪ ቅጽ 3 መጽሐፍ 30 ቁጥር 94
በአሊ የተተረከ
እኛ ከአላህ ኪታብ እና ከዚህ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የተጻፈ ወረቀት በስተቀር ምንም የለንም። ወይም በውስጧ ለእንዲህ ዓይነቱ #ቢዲአ #ፈጣሪ #መጠጊያ #መስጠት #የአላህን፣ የመላእክትንና የሰዎችን ሁሉ እርግማን ያስከትላል፣ #የትኛውም #አስገዳጅ #ወይም #አማራጭ #የሆነ #መልካም #ኢባዳ #ተቀባይነት #አይኖረውም። እና ማንኛውም ሙስሊም የሚሰጠው ጥገኝነት (ጥገኝነት) በሌሎቹ ሙስሊሞች ዘንድ የተጠበቀ (መከበር) አለበት። በዚህ ረገድ ሙስሊምን አሳልፎ የሰጠ የአላህ፣ የመላእክቱ፣የሰዎችም ሁሉ እርግማን አለበት።ከዚህም ውጭ የሆነ የግዴታም ሆነ አማራጭ የሆነ መልካም ስራው ተቀባይነት የለውም። ከነፍሰ ገዳይዎቹ ያለፈቃዳቸው የአላህን፣ የመላእክትንና የሰዎችን ሁሉ እርግማን ያስከትላሉ፣ እናም የትኛውም አስገዳጅ ወይም አማራጭ የሆነ #መልካም #አምልኮ #ተቀባይነት #አይኖረውም።
*********************
✅ ተርሚዚ 131 እና 2643 ላይ እንደተጠቀሰው ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) የእስራኤል ልጆች፣ አይሁዶችና ክርስቲያኖች ለ72 መንገድ ተከፍለዋል የኔንም ኡማ ለ73 መንገድ ይከፈላል። አንዱ ሲቀር ሁሉም የእሳት ናቸው።ብለዋል ሶሃቦችም እነማናቸው የሚተርፉት ብለው ጠየቋቸው። ረሱልም (ሰ.ዓ.ወ) #እኔና #ሶሀቦንቼ የተከተሉ። በማለት መልሰውላቸዋል።
ታድያ ነብዩ(ሰዐወ) እኔና ሰሐቦቼን የተከተሉ ብለዋል። ነገር ግን እኔ 3 ጥያቄዎች አሉኝ
1) ነብዩ(ሰዐወ) ራሳችሁን #ሰለፊይ ብላችሁ ጥሩ ብለዋልን?!!
2) ነብዩስ(ሰዐወ) ሰለፊይ ነበሩ??
3) ሶሐቦችም ቢሆኑ የኛ ተከታዮች ሰለፊይ ተብለው ይጠሩ ብለዋልን? ካለ ይጠቁመንና እንከተል!!
እኔ እንደውም ራሴን ሰለፊይ ብዬ ከምጠራ ሙሐመዲይ ብዬ ብጠራ ይሻለኝ ነበር ምክንያቱም እኔን ተከተሉ ስላሉኝ!! ነገር ግን ቢድአ ነውና አልፈልግም!!
ታድያም የኡማቸውን ሁኔታ የሚያስጨንቃቸውንም ነብይ ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ ይላሉ፦
✅ በሱና አቡዳውድ ሐዲስ 4579 እና 4580 ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) አይሁዶች ለ71 እና ለ72 እንዲሁም ክርስቲያኖች ለ71 እና ለ72 ቦታ እንደተከፈሉት ሁሉ ሙስሊሞችም ለ73 ይከፈላሉ ብለዋል።
✅ በቡኻሪ በ3ኛ መፅሐፍ ላይ 2652 ነብዩ (ሰ.ዓ.ወ) ምርጡ ትውልድ የኔው ትውልድ ነው፤ ከዛም የሚቀጥለው ከዛም የሚቀጥለው ብለዋል።
ℹ ነብዩ ምርጡ ትውልድ የሶሐቦች ከዛም ታቢዎች(ሶሐቦችን ያዩ) ከዛም የተአቢ ተከታዮች እነዚህ ሰለፉነ ሷሊሂን ይባላሉ። ሰለፍ ማለት ቀደምት መሪዎች (ቀደምት አባቶቻችን) ማለት ነው።
እኛ ግን ኸለፍ ነን እንጂ ሰለፎች አይደለንም። በመጨረሻም ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል፦
ሶሒሕ ቡኻሪ ጥራዝ 3 ተ.ቁ 4565
" የሙስሊሙን ኡማ የሚከፋፍል ሰው ካለ በሰይፍ ምቱት እምቢ ብሎም ከድርጊቱ አልቆጠብም ካለ ግደሉት" ብለዋል።
እና የትኛውን እንከተል? የትኛውንም አንከተልም ምክንያቱም እኛ ሙሥሊምና ሙሥሊሞች ብቻ ነን። ለዚህም አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦
አላህ ሱወ እንዲህ በማለት ይናገራል፦
22፡78
وجاهدوا في الله حق جهاده ۚ هو اجتباكم وما جعل عليكم في الدين من حرج ۚ ملة أبيكم إبراهيم ۚ هو سماكم المسلمين من قبل وفي هذا ليكون الرسول شهيدا عليكم وتكونوا شهداء على الناس ۚ فأقيموا الصلاة وآتوا الزكاة واعتصموا بالله هو مولاكم ۖ فنعم المولى ونعم النصير
<<... የአባታችሁ የኢብራሂምን ሀይማኖት ተከተሉ። እርሱ ከዚህ በፊት ሙስሊሞች ብሎ ሰይሞአችኋል፤ በዚህም ቁርዓን መልክተኛው በናንተ ላይ መስካሪ እንዲሆን እናንተም በሰዎች ላይ መስካሪዎች እንድትሆኑ ሙስሊሞች ብሎ ሰይሞአችኋል።>>
✔ ከቁርዓንና ሐዲስ ውጪ ያሉ ፍልስፍናዎችን በተመለከተ
ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 9፣ መጽሐፍ 92፣ ቁጥር 382
በአብደላህ የተተረከ
በላጩ ንግግር (ንግግር) የአላህ ኪታብ (ቁርኣን) ሲሆን በላጩ መንገድ የመሐመድ መንገድ ነው፡ ከሁሉ የከፋው ደግሞ መናፍቃን (እነዚያ አዲስ ነገሮች ወደ ሃይማኖት የገቡ) ናቸው። የምትስፈራሩትም ሁሉ በእርግጥ ይፈጸማል። እናንተም አታመልጡም።
*********************
ታድያ ብዙ ሙስሊሞች የሶሀቦች ተከታይ ሰለፍይ ነኝ በማለት ይናገራሉ። ለመሆኑ በየትኛው ሶሒሕ ሐዲስ ውስጥ ነው ሰለፍይ ሁኑ የሚል የረሱል(ሰ.ዓ.ወ) ንግግር የሚገኘው? ይህንን አስመልክቶ አንድ ሶሒሕ ሐዲስ ማምጣት የሚችል ሰው ካለ ይጠቁመንና እንከተለው። በርግጥ አንድ ሐዲስ እንዲህ ተብሎ ተጠቅሷል ፦
በሶሒሕ ሓዲስ 2405 ላይ ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) ለልጃቸው ፋጢማ(ረ.ዓ)፦ " እኔ ለአንቺ የተመረጥኩ ሰለፍ ነኝ" ብለዋል። አረብኛ ትርጉሙ ደግሞ በሐይማኖት የተምሳሌት አባት ነኝ ማለታቸው ነው። እና ለመሆኑ ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) ለእኛ አባት መሆን ይችላሉን? መልሱ አይችሉም ነው ምክንያቱም ደግሞ በቁርዓን ውስጥ (33፥40) ላይ በግልፅ ተቀምጧል።
የሠለፊዝም ፅንሰ ሀሳብ የሚጀምረው ከየት? መቼና ከማን ነው የሚነሳው?
ሼህ ነስረዲን አልባኒ ሰለፍይ ፈርድ ነው ብለው የሚያምኑ ሼህ ናቸው። አላህ ይርኸማቸውና እኚህ ሼህ በትውልድ አልባኒያዊ ሲሆኑ ( Aug 16, 1914 - Oct 2, 1999 የነበሩ) በእስልምና እውቀታቸውም አንቱ የተባሉ ታዋቂ ሼህ ናቸው። ሼህ አልባኒ መጀመሪያ አካባቢ ወህሃቢዝምን
ከመሩና ከደገፉ ሰዎች አንዱ ሲሆኑ የአለም ሀገራት በቡድን ቡድን ተከፋፍለው ጦርነት ባካሄዱበት ማግስትም ማለትም በሀያኛው ሴንቸሪ የመጀመሪያዎቹ አካባቢ ሰለፊዝምን የመሠረቱ ሼህ ናቸው።
የሼህ አልባኒ የግል ታሪካቸውን ጥቂት ልበል፦ ሼህ አልባኒ በኢስታንቡል የፊቅህ አስተማሪ ከነበሩ ከአንድ የሀነፊ ተከታይ አባት በ1914 አልባኒያ ውስጥ ተወለዱ። ሼሁ ቤተሰባቸው እጅግ ድሃ ስለነበሩ መጀመሪያ አካባቢ ቤት ሰሪ አናፂ ነበሩ ከዚያም ከአባታቸው ከተቀላቀሉ በኋላ watchmaker (ሰዓት ሠሪ) ሆኑ። ከአባታቸውም ቁርዓን ተጅዊድና አል ነህዋን አጠኑ ቀጥለውም ብዙ ኪታቦችን ሙህተሳር አል ቀድሪና ሐነፊ ፊቅህን እንዲሁም ሌሎችም የእስልምና እውቀት ከቀሠሙ። የሁለተኛው የአለም ጦርነት ከተገባደደ በኋላም ሰለፊዝምን መሠረቱ። በመጨረሻም oct 2, 1999 ጆርዳን ውስጥ ህይወታቸው አልፏል። መረጃውን Wikipedia ላይ Al Albani ብለው በመግባት መሉ የህይወት ታሪካቸውን ማግኘት ይችላሉ። እናም ሼህ አልባኒ አላህ ይርኸማቸውና እንወዳቸዋለን እናከብራቸዋለን ነገር ግን እሳቸውን ተቅሊድ ማድረግ አይገባንም። ተቅሊድ ማለት ኢማሞችን መከተል ማለት ነው።
ስለዚህ አልባኒን አንከተልም። የሌሎችንም ግሩፖች ደግሞ በሌላ ጊዜ እናየዋለን።
በጣም የሚያሳዝነው ነገር የሁሉም ግሩፕ ተከታዮች የኔ ይበልጣል የኔ ይበልጣል በማለት በጎሪጥ መተያየትና አንዱን ለአንዱ ካፊር በማለት ይሰዳደባሉ። ሰለፍዮች ከአህለል ሱና እኛ እንበልጣለን ይላሉ አህለል ሱናዎችም እንደዛው ሌላኛው ከሌላው እንደዚሁ እኔ እበልጣለሁ ይላል።
በዚህም ሙስሊም ተብሎ መጠራትን የመሠለ ምርጥ መጠሪያ እያለ እኔ እንዲህ ነኝ እኔ እንዲህ ነኝ እያለ አንዱን ከሌላው የሚለያይበት የሆነ ሁኔታ ተፈጥሯል። ታድያ ይህ ለምን ሆነ ብለህ ሰለፊዮችን ስትጠይቃቸው ከዚህ ከነሱ መንገድ ውጪ ሌላ መንገድ ያለ አይመስላቸውም። ነገር ግን ስለእናንተው ግሩፕ ሁኔታ ወይም በዚህ ስም ተጠሩ የሚል ነገር ከሶሒሕ ሐዲስ አሳዩኝ ስትላቸው መልስ የለም። እና እንዴት እንከተላቸው? ደግሞስ ሰለፊይም ቢሆን ቁጡቢይ ሰለፊይ፣ መድኸሊይ ሰለፊይና ሱሩሪ ሠለፊይ በመባል ይከፋፈላሉ። ታድያ የትኛው ሰለፊይ እንከተል? አህለል ሐዲሶችም ቢሆኑ እንዲሁ ናቸው። እነርሱም ጉርቢያተል አህለል ሐዲስና ጃሚአተል አህለል ሐዲስ በመባል ይከፋፈላሉ። እና የትኛውን እንከተል?
የኡማውን አንድነት የሚከፋፍል ሰው ይገደል!!
ነብዩ ሙሐመድ(ሰዐወ)
#ሰለፊይ ምን አይነት መንገድ ነው?
▷▷▷▷▷▷▷▷▷
ቢስሚላህ
የአላህ ሰላም የነቢያትም ሁሉ መደምደሚያ በሆኑት ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዓ.ወ) ላይ እና በባልደረቦቻቸው፣ በሁሉንም የአላህ መልዕክተኞች እንዲሁም የእውነት መንገድ በተከተሉት ሁሉ ላይ ይውረድ።
እንደሚታወቀው በአለማችን ላይ ብዙ ተከታይ ካሏቸው ሀይማኖቶች መካከል እስልምና ቁጥር አንድ ሀይማኖት ቢሆንም በዚህ ቅዱስ ሀይማኖት ውስጥም ብዙ የክፍፍል ቡድኖች እንደሚገኙም ይታወቃል። ከነዚህም ክፍፍል ግሩፖች መካከልም ሐነፊይ፣ ሰለፍይ፣ ሱንይ፣ አህለል ሀዲስ፣ ወህሃብይ፣ አህለል ሱና፣ ቁጡቢይ፣ መድኸሊይ፣ ሱሩሪይ፣ ጉርቢያተል አህለል ሀዲስ፣ ኢህዋንይ፣ ጃሚአተል አህለል ሀዲስ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊእይ፣ ... በመባል ተከፋፍለዋል።
ታድያ እነዚህ ግሩፖች ከየት መጡ? እንዴት ተመሠረቱ? በቅዱስ ቁርዓንና በሶሒሕ ሐዲስ ውስጥ ይታወቃሉ ወይ??
አሏህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦
30፡ 32
من الذين فرقوا دينهم وكانوا شيعا ۖ كل حزب بما لديهم فرحون
<< ከእነዚያ ሀይማኖታቸውን ከለያዩትና ክፍፍሎችም ከሆኑት (አትሁኑ)። ህዝብ ሁሉ እነሱ ዘንድ ባለው ነገር ተደሳቾች ናቸው።>>
4፡ 125
ومن أحسن دينا ممن أسلم وجهه لله وهو محسن واتبع ملة إبراهيم #حنيفا ۗ واتخذ الله إبراهيم خليلا
<< እርሱ ከመልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን ለአላህ ከሠጠና የኢብራሂምን መንገድ ቀጥተኛ ሲሆን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ያማረ ማነው? አላህም ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ አድርጎ ያዘው።>> ይላል።
እዚጋ أسلم " አስለም "የተባለው ለአላህ የታዘዘ ለማለት ነው ይህም "ኢስላም "إسلم ከሚል ቃል derive የተደረገ ነው። ኢስላም ማለት የታዘዘ/ታዛዥ ማለት ነው።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት t.me//AkeelComparative join ያድርጉ
ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ" ብሏል። የጳውሎስ አምልኮ ይህ ከሆነ ታድያ አባቶቹ እነማን ናቸው? እነርሱስ ያመልኩት የነበረው ማንን ነው??
እሱ አባቶች ያላቸው ነብያትንና የቀደምት እስራኤላውያን ሰዎችን ነው። ታድያ ነብያት ከአንድ አምላክ ውጪ ሌላ ጣኦታት አምልከዋልን?? የለም አላመለኩም። ቀደምት እስራኤላውያን አባቶቹ ግን ጣኦታትን አምልከዋል። ለዚህም ደግሞ የሙሴ ህዝቦች በግብፅና ከግብፅ ከወጡ በኋላ የተከሠተው ክስተት እንደ አንኳር ነጥብ ማንሳት ይቻላል።
- መፅሐፈ እያሱ ወልደነዌ 24፥ 14
" እግዚአብሔርን ፍሩ፥ በእውነተኛም በፍጹም ልብ አምልኩ፥ #አባቶቻችሁ #ከወንዝ #ማዶ #በግብፅም #ውስጥ #ያመለኩአቸውን #አማልክት #ከእናንተ #አርቁ፥ እግዚአብሔርም አምልኩ።"
ቁርዓንንም ይህንን እውነት እንዲህ በማለት ይተርከዋል፦
7፡138
وجاوزنا ببني إسرائيل البحر فأتوا على قوم يعكفون على أصنام لهم ۚ قالوا يا موسى اجعل لنا إلها كما لهم آلهة ۚ قال إنكم قوم تجهلون
<< የእስራኤልም ልጆች ባህሩን አሻገርናቸው፥ ለእነርሱ በሆኑ ጣኦታት (መገዛት) ላይ በሚዘወትሩ ህዝቦች ላይ አለፉም። < ሙሳ ሆይ፦ ለእነርሱ (ለሰዎቹ) አማልክት እንዳላቸው ለእኛም አምላክን አድርግልን> አሉት። እናንተ የምትሳሳቱ ህዝቦች ናችሁ > አላቸው።
የዚህ ነገር ጉዳዩም እንዲህ ነበር፦ ሙሴ ወይም ሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦቻቸውን ከግብፅ ምድር ከፊራኦን እጅ አውጥተው ወደ ሀገራቸው በመሄድም ላይ ሳሉ በመንገዳቸው ጥልቅ የተንጣለለ የባህር ውሃ ገጠማቸው። የፊራኦን ሰራዊት ከኋላቸው ይከተላቸው ስለነበረ በጣም ተጨነቁ፤ በዚህም ጊዜ አላህ(ሱ.ወ) ለሙሳ(ዓ.ሰ) በያዝከው በትር ባህሩን ምታው ሲላቸው ሙሳም(ዓ.ሰ) በያዙት በትር ባህሩን ሲመቱት ያንን ተንጣልሎ የተኛውን ባህር መሀል ለመሀል ተገመሶም ተከፈለ። በዚህም ጊዜ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች በተከፈለው ባህር ውስጥ ሊሻገሩ ገቡ፤ የፊራኦንንም ሰራዊት በሙሉ እነርሱንም ተከትለው በተከፈለው ባህር ውስጥ ገቡ።
ታድያ በዚህም ጊዜ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች ሁሉንም ባህሩን አቋርጠው ጨርሰው እንደወጡና እንዲሁም የፊራኦንንም ሰራዊት ሁሉንም ጨርሰው በተከፈለው ባህር ውስጥ ከገቡም በኋላ መሀል ለመሀል ተከፍሎ እንደ ተራራ በግራና በቀኝ ቆሞ የነበረውን የባህር ውሃ ቀድሞ ወደነበረበት ቦታ ተመለሠ። ያኔም ፊራኦን፣ ባለስልጣናቱ( እነ ሀማንና ሌሎቹንም ጨምሮ) እንዲሁም የፊራኦንን ሰራዊት በሙሉ በባህሩ ውስጥ ሰጥመው የባህር ውስጥ ስጋ ተመጋቢ ፍጡራን ሲሳይ ሲሆኑ የሙሳ(ዓ.ሰ) ህዝቦች ግን ከዚህ ጉድ በተዓምር ተርፈውም ወደ አገራቸው ጉዞ ቀጠሉ።
ከረጅም ጉዞ በኋላም በጡር ተራራ ጎንም በሰፈሩ ጊዜ ለሙሳ(ዓ.ሰ) አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ሊፆሙ ከአላህ ዘንድ ለቀጠሮ ተጠሩ። ታድያ ህዝቦቹ ለሙሳ(ዓ.ሰ) ከግብፅ ያወጣን አምላክህ አንድ አይደለምና ለእኛም ሌሎች አማልክት ስራልን በማለት ይነዘንዟቸው ነበር። እናም ሙሳ(ዓ.ሰ) ከአላህ(ሱ.ወ) ጋር ሊነጋገሩ ወደ ተራራው በወጡ ጊዜ እነዚያ የሙሴ ህዝቦች ግን ለአንድ ሳምራዊ አማልክት ስራልን አሉት። እርሱም የወርቅ፣ የብርና ሌሎችም ጌጣጌጦችን ሰብስባችሁ አምጡልኝ አላቸው፥
እነርሱም የጆሮና የእጅ የተለያዩ ጌጣጌጦቻቸውን ሰብስበው ለሳምራዊው አመጡለት። አንድ ላይ አድርገው እሳት ውስጥም ጨመሩት። በዚህም ጊዜ ጥጃ የሚመስል መልክ ያለው ነገር ከእሳቱ ወጣላቸው። እነዚያንም ሰዎች ከግብፅ ያወጡን አማልክቶቻች እነዚህ ናቸው በማለት ጣኦት ማምለክ ጀመሩ። ለዚህም ሙሉ ማስረጃ ፦
ከቅዱስ ቁርዓን ፦ 2፥ 49-57 ፣ 7፥ 103-155 ፣ 20፥ 77- 98 ፣ 28፥ 6-50 ከብዙ በጥቂቱ
ከመፅሐፍ ቅዱስም ፦ የሐዋርያት ስራ 7፥20-46፣ ኦሪት ዘዳግም 9&10, ዘፀአት 13፥ 18-22, 14፥ 1-31, 15፥ 4-27 ፣ ኦሪት ዘሀልቅ 21፥ 4-20 ከብዙ በትንሹ
እናም ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ ሲል
ኑፋቄ ማለት " የዋጃቸውን ጌታ ክደው ፈጥኖ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ" መባሉን መረሣት የለበትምና (ይህም ማለት በጣኦት ማመን ማለት ነው) እንዲሁም ከግብፅ ምድር የወጡት የጳውሎስ ቀደምት አባቶች ከሙሳ አምላክ ውጪ የሆነን ባዕድ አካል ማምለካቸውን ይታወሳልና በዚህም ደግሞ እነርሱ ያመለኩት አካልም ጳውሎስ ያመልከዋል ማለት ነው።
- ትንቢተ ሆሴዕ 13፥2
" በብራቸው ለራሳቸው ቀልጦ የተሠራውን ምስል፥ እንደጥበባቸውም ጣኦታት ሰርተዋል። ሁሉንም የሠራተኛ ስራ ናቸው፤ ስለእነርሱም የሚሰው ሰዎች እምቦሳውን ይሳሙ ይላል።"
ከዚህ ጋር ተያይዞ አንድ ክርስቲያን <<አይ ይህ ነገር ልክ አይደለም ጳውሎስ እየሱስን ነው የሚያመልከው>> ሊል ይችላል። ነገር ግን እንዲህም ቢሆን እንኳን የጳውሎስ አምልኮ ያው ነው አይለወጥም።ለዚህም ደግሞ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
- 1ኛ ወደቆሮንቶስ ሰዎች 10፥ 1-4
" ወንድሞች ሆይ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባህር መሀከል ተሻገሩ፥ ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመና በባህር ተጠመቁ፥ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፥ ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ አለት ጠጥተዋልና ያም አለት #ክርስቶስ #ነበረ ።"
ታድያም የጳውሎስ አባቶች ያመልኩት እንደነበረው በኑፋቄ መንገድ ማምለክም ሲባል በጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ጳውሎስም እነርሱ እንዳመለኩ እንዲሁ ያመልካልና በዚህም ጳውሎስ ጣኦት አምላኪ ሰው ነው ማለት ነው።
ቀደምት ነቢያት ግን አንድ አምላክ(አሏህን) ያመልኩ የነበረ ሙስሊም ነበሩ እንጂ ማናቸው ቢሆን ክርስቲያንም ይሁን አይሁድ አልነበሩም። ለዚህም ደግሞ አሏህ(ሱወ) በቁርዓን 2፡140 ላይ ይናገራል።
✔ #የታዘዙ ፦ ማለት < اسلم > / < አስለም> ሲሆን < مسلم > /
< ሙስሊም> ከሚለው ስርወ ግንድ የተገኘ ቃል ነው።
ስለዚህ ኢስላም ማለት በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነተኛው መንገድ ወይም ሀይማኖት ሲሆን ሙስሊም ማለት ደግሞ ለአምላኩ የሚታዘዝ ፣ የታዘዘውን የሚፈፅም (የአምልዕኮ ክንውኖችን ለአምላኩ የሚያደርግ ( የሚሰግድ፣ የሚፆም፣...) ነው። ታድያ ጳውሎስ ለማን ነው የሚታዘዘው? ለማነው የሚሰግደው? በመጀመሪያ ደረጃ ስግደት ማለት ምን ማለት ነው?
✔ #ስግደት ፦ ማለት ለአንድ አካል መስገድ ማጎብደድ፣ ማምለክ፣ መታዘዝ.. ማለት ሲሆን
ስግደት በሁለት ይከፈላል፦ እነርሱም #የአምልኮ #ስግደት እና #የአክብሮት #ስግደት ናቸው።
1) የአምልኮ ስግደት፦ ይህ ስግደት ለፈጣሪ አምላክ በብቸኝነት መስገድ ፤ የአምልኮ ክንውኖችን ለአንድ ፈጣሪ ማድረግ ማለት ነው።
- ኦሪት ዘዳግም 10 ፥ 12-13
" እግዚአብሔር አምላክህን በፍፁም እውነት በፍፁም ልብህ አምልክ።"
41፡37
ومن آياته الليل والنهار والشمس والقمر ۚ لا تسجدوا للشمس ولا للقمر واسجدوا لله الذي خلقهن إن كنتم إياه تعبدون
ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ አትስገዱ፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው #አላህ #ስገዱ፡፡ #እርሱን #ብቻ #የምትግገዙ እንደ ኾናችሁ ( #ለሌላ #አትስገዱ)፡፡
2) የአክብሮት ስግደት፦ ይህ ስግደት ከአምላክ ውጪ ላሉት ለባዕድ ነገሮች (ለጣኦታት) መስገድ ፣ ማምለክ... ማለት ነው።
✔ #ጣኦት ማለት ምን ማለት ነው?
ከአንድ ፈጣሪ አምላክ ውጪ ሌላ የሚመለክና የሚሰገድለት ማንኛውንም አካል ካለ እርሱ ጣኦት ይባላል። ለዚህም
29 ፥ 17
<< ከአላህ ሌላ የምትግገዙት ጣኦት ብቻ ነው። ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ...። >>
#ጣኦት በሁለት ይከፈላል፦ #አስናም እና #አውሳን በመባል።
- አስናም ማለት ከእንጨት ፣ ከወርቅ፣ ከብር ፣ ከነሀስ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው።
- ትንቢተ ዳንኤል 5፥ 4 & 5፥23
" የወይን ጠጅም እየጠጡ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከነሀስና ከእንጨት የተቀረፁትን ጣኦታት አመሠገኑ።"
#ከቁርዓን ደግሞ 6፥74 መመልከት
- አውሳን ማለት ደግሞ ፦ ከድንጋይ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው።
- ኦሪት ዘሌዋውያን 26፥ 1
" እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ፥ ለእናንተ ጣኦት አታድርጉ፥ የተቀረፀ ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፥ ትሰግዱለትም ዘንድ ምድራችሁ ላይ ከድንጋይ የተቀረፀ አታኑሩ።"
#ከቁርዓን ደግሞ 29፥17ን ማየት
ታድያ ጳውሎስ እንዴትና በምን መልኩ ነው ጣኦት አምላኪ ሰው ነው ሊባል የቻለው??
.
#ኑፋቄ
(የጳውሎስ በጣኦት አምልኮ መንገድ)
******************************
#ኑፋቄ ማለት ራሱን የቻለ የአምልኮ ሁኔታ ሲሆን ይህም ደግሞ ጳውሎስ አምላኩን የሚያመልክበት የሆነ የክርስት ሐይማኖት መንገድ ነው። ጳውሎስ የአምልኮ ሁኔታዬን ለሚመረምሩኝ ሰዎች መልሴ ይህ ነው ይላል፦
- የሐዋርያት ስራ 24፥14
" ነገር ግን ይህን እመሰክርልሃለሁ፤ በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ #ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ፤"
በማለት ይናገራል።
ጳውሎስ የሚያመልከው የአምልኮ አይነት ይህን ይመስላል። ታድያ ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው በሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ" ይላልና ለመሆኑ ኑፋቄ ማለት ምን ማለት ነው? በዚህ መንገድ ማምለክ ሲባልስ እንዴትና በምን አይነት መንገድ ማምለክ ማለት ነው?
1.1 ኑፋቄ ምንድ ነው?
#ኑፋቄ ማለት ጥሬ ቃሉ ወይም ፍቺው መንፈቅ ፣ መክፈል፣ መግመስ፣ መቅደድ... ማለት ነው።
ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ ማምለክ የማለት ትርጉሙም፦ የአንድን ነገር እውነት ላይ ቀዳዳ በማበጀትና የሀሰት ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሁም እውነተኛውን ሀሳብ ላይ የራስ ፈጠራዎችን በማካተት እውነተኛውን ሀሳብ ከእውነታው እንዲርቅ የሚያደርግ የአምልዕኮ ተግባር ነው። በሌላ አባባል በዚህ በኑፋቄ መንገድ ማምለክ ማለት እውነተኛውን አምላክ በመካድ የሚያጠፋ የሆነን ጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ይህም ደግሞ እውነተኛውን ሀይማኖት በመተው አዲስና መጤ እምነትን መከተል ማለት ነው። ለዚህም ደግሞ፦
- 2ኛው የጴጥሮስ መልዕክት 2፥ 1 - 15
"... ነገር ግን ሀሰተኞች ነቢያት ደግሞ በህዝቡ መካከል ነበሩ እኝዲሁም በመካከላቸው ደግሞ ሀሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ። እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳን ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው እየሳቡ የሚያጠፋ #ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ። ብዙዎች በመዳራታቸው ይከተሏቸዋል፥ በእነርሱም #ጠንቅ #የእውነት #መንገድ ይሰደባል።... #ቅንን #መንገድ #ትተው #ተሳሳቱ።" ይላል!!
ስለዚህ የኑፋቄ ትርጉምና ኑፋቄ በሚሉት መንገድ ማምለክ ማለት ትርጉማቸው ይህ ከሆነ ለመሆኑ የጳውሎስ አባቶች(ነቢያት) መንገድ ምን ነበር? እንዲሁም በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነት መንገድ የትኛው ነው? የሚዋጅ ጌታስ ማነው?
የእነዚህን ጥያቄዎች መልስ በተመለከተ አሏህ(ሱወ) በቁርአን እንዲህ ይላል፦
3፡ 83
أفغير دين الله يبغون وله أسلم من في السماوات والأرض طوعا وكرها وإليه يرجعون
በሰማያትና በምድር ያሉ ሁሉ፤ በውድም በግድም ለርሱ የታዘዙ ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ (ከሓዲዎች) ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን
3፡84
قل آمنا بالله وما أنزل علينا وما أنزل على إبراهيم وإسماعيل وإسحاق ويعقوب والأسباط وما أوتي موسى وعيسى والنبيون من ربهم لا نفرق بين أحد منهم ونحن له مسلمون
«በአላህ አመንን፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም (በቁርኣን)፣ በኢብራሂምና በኢስማዒልም፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው (አመንን)፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል፡፡
3፡85
ومن يبتغ غير الإسلام دينا فلن يقبل منه وهو في الآخرة من الخاسرين
ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡
3: 13
<<(የበድር ቀን) በተጋጠሙት ሁለት ጭፍሮች ለናንተ በእርግጥ ተዓምር አልለ፡፡ አንደኛዋ ጭፍራ በአላህ መንገድ ትጋደላለች፡፡ ሌላይቱም ከሓዲ ናት፡፡ ከሓዲዎቹ (አማኞቹን) በዓይን አስተያየት እጥፋቸውን ኾነው ያዩዋቸዋል፡፡ አላህም በርዳታው የሚሻውን ሰው ያበረታል፡፡ በዚህ ውስጥ ለማስተዋል ባለቤቶች በእርግጥ መገሰጫ አለበት፡፡>>
3፡123
በበድርም እናንተ ጥቂቶች ሁናችሁ ሳለ አላህ በእርግጥ ረዳችሁ። አላህም ታመሠግኑት ዘንድ ፍሩት።>>
#አል - #ዓዚዝ በቁርዓን ውስጥ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
✔ <አል- ዓዚዝ> የሚለው የአሏህ ስም በቁርዓን ውስጥ 95 ቦታ ላይ ተጠቅሷል።
✔ <አል-ዓዚዝ የሚለው የአሏህ ስም በቁርዓን ውስጥ ከአራት(4) የአሏህ ስሞች ጋር በመጣመር ተወስቷል። ለምሳሌ፦
- "አል-ሐኪም" ከሚለው ጋር አርባ ሰባት(47) ጊዜ
- "አር-ረሒም" ከሚለው ጋር አስራ አራት(14) ጊዜ
- "አል-ቀዊይ" ከሚለው ጋር አንድ(1) ጊዜ
- " አል-አሊም" ከሚለው ጋር አንድ (1) ጊዜ
▷ #አዚዙን #ሐኪም (ሐያል/አሸናፊ እና ጥበበኛ)፦ አላህ(ሱወ) ሐያል አሸናፊና ጥበበኛ ጌታ ነው። የዚህ አይነቱ ባህሪ በአንድ ላይ መላበስ ከሠው ልጅ ላይ የማይታሰብ ነገር ነው። ምክንያቱም የሠው ልጅ ሐያልነት ወደ ጉልበትና ደመነፍሳዊነት ስሜት ይመራል። በዚህም ጥፋት ሊከተል ይችላል። አላህ(ሱወ) ግን ሐያልና አሸናፊ ነው፥ ከዚህም ጋር ጥበበኛ ነው።
▷ #አዚዙን #ረሒም (ሐያል/አሸናፊ እና አዛኝ) ፦ የሠው ልጅ ብርቱ፣ ሐያልና አሸናፊ በሚሆንበት ጊዜ በአብዛኛውም የእዝነት ስሜት አይታይበትም። በዚህም ጨካኝና አምባገነን ነው የሚሆነው። ለምሳሌ በጦርነት ወቅት አሸናፊዎቹ ህዝብን ጨፍጭፈው ነው ድል የሚቀዳጁት። አላህ(ሱወ) ግን ተቃራኒ ባህሪዎችን አንድ ላይ ይዟልና ሐያል አሸናፊና አዛኝ የሆነ ጌታ ነው። ሱብሀን አሏህ!!!!!
▷ #አዚዙን #አሊም እና #ቀዊይዩን #አዚዝ ፦ ይህም አሸናፊነት ከሱ ነው። ብርቱነት የሱ ባህሪ ነው። እሱ የሐይልና የአሸናፊነት ባለቤት ነው። ይህ ሀያሉና አሸናፊነቱ ደግሞ እውቀትን ያዘለ ነው። ማለት ነው።
22፡ 40
الذين أخرجوا من ديارهم بغير حق إلا أن يقولوا ربنا الله ۗ ولولا دفع الله الناس بعضهم ببعض لهدمت صوامع وبيع وصلوات ومساجد يذكر فيها اسم الله كثيرا ۗ ولينصرن الله من ينصره ۗ إن الله لقوي عزيز
<<... አላህም ሀይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል። አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና።>>
58 ፡21
<< አላህ ፦ " እኔ በእርግጥ አሸንፋለሁ፥ መልዕክተኞቼም (ያሸንፋሉ)" ሲል ፅፏል። አላህ ብርቱ ፥ አሸናፊ ነውና።>>
አንድ ሰው በ"አል-ዓዚዝ" አሸናፊነት ፤ የበላይነት ይጠራጠር ይሆናል። ሰዎችም በ"አል-ዓዚዝ" እርዳታ ሳይሆን በራሳቸው ጥረት ከትልቅ ደረጃ የሚደርሱ የሚመስላቸው አሉና በዚህም ለሀብታም ሲተናነሱና
ሲያጎበድዱ ይታያል። ታድያም ይህ ታሪክ የኛ ማንነት ከሆነ የአሸናፊው ጌታ ባሪያ መሆናችንን የረሳን ሲሆን ሀብትና ዝና ላለው ሰው በማጎብደዳችንም የአሸናፊው አላህ ክብር አሳንሰናል ማለት ነው። ለዱንያዊ ጥቅም ብለን ለባለሀብቶች የምናጎበድድ ከሆነ ለኛ የበታችነትና ዝቅተኝነቱ ላይታየን ይችላል። ይህ በርግጥ ትልቅ ፈተና ነው።
ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ "ለሀብቱ ብሎ ለሀብታም የተናነሰ ሰው የሀይማኖቱ ሁለት ሶስተኛ ሄደ።" ብለዋል። ነብዩ(ሰዐወ) በሌላም ሐዲሳቸው "ከሰዎች ስትፈልጉ በተከበራችሁበት መልኩ ይሁን። ነገሮች ሁሉ የሚከናወኑት በቀድር ነውና።" ብለዋል።
✔ ለአል ዓዚዝ ራሳችንን እናስተናንስ፣ ዝቅ እንበል፣እንዋረድለት እርሱ ከፍ ያደርገናል፤ ክብርን ያጎናፅፈናል።
---------------------///----------------
ክፍል -8 ይቀጥላል
የ99ኙንም ሙሉ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀላሉ! ለሌሎችም ሼር ያድርጉ t.me//AkeelComparative
