en
Feedback
AACPPPDS

AACPPPDS

Open in Telegram

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዝና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

Show more
308
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር_የመንግስት_ግዥና_ንብረት_ማስወገድ_አገልግሎት_የተለያዩ_ሴክተር_መቤቶች.docx0.49 KB

photo content

photo content

የመንግስትን ንብረት በጥንቃቄ መያዝ ፣መጠቀም እና ህግን ተከትሎ ማስወገድ እንደሚገባ ተገለፀ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የመንግስት ንብረት አወጋገድን አስመልክቶ ባዘጋጀዉ የግንዛቤ ማስቸበጫ የዉይይት መድረክ ላይ እንደተገለፀዉ የመንግስትን ንብረት በጥንቃቄ መያዝ ፣መጠቀም እና ማስወገድም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ህግን ተከትሎ ማስወገድ እንደሚገባ ተገልጿል ፡፡ የመንግስት ንብረት አወጋገድን አስመልክቶ የሚስተዋሉ የግንዛቤ ክፍተቶችን መሙላት እና ለሚገጥሙ ተግዳሮቶችም መፍትሄ መስጠትን ዓላማ ባደረገዉ በዚህ መድረክ ላይ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ እና ተወካዮች ፣ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ኃላፊ እና ተወካዮችን ጨምሮ የአስራ አንዱም ክፍለ ከተማ የንብረት አስተዳደር ፅ/ቤት ሃላፊዎች እና የሚመለከታቸዉ አካላት የታደሙበት ነበር፡፡ በዕለቱ የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የዋጋ ግመታ እና ማስወገድ ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ተስፋዬ እንደገለፁት ተቋማት ንብረት ማስወገድ የሚገባቸዉ በምን ምክንያት እንደሆነ ሲገልፁ ንብረቱ ለመስሪያ ቤቱ የማያስፈልግ ሲሆን ፣ ንብረቱን ይዞ መቀጠል የሚያስከትለዉ ወጪ ከፍተኛ ሆኖ ሲገኝ ፣ በተለያየ ምክንያት ንብረቱ አገልግሎት የማይሰጥ ሲሆን፣ ንብረቱ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት እንደማይችል ሲረጋገጥ እና መስሪያ ቤቱ ከሚኖረዉ የመካከለኛ እና ረጅም ጊዜ እቅድ አንጻር ትርፍ መሆኑ ሲታመን ነዉ ብለዋል፡፡ አክለዉም በአገልግሎቱ ያለ ዋጋ ጣሪያ/Threshold/ የሚወገዱ ንብረቶች ተሽከርካሪ ፣የተሽከርካሪ (ጎማ፣ባትሪ፣ከነመዳሪያ፣ፕላፕ፣ቸርኬ)፣ቁርጥራጭ ብረታ ብረት ኮሚፒውተርና ተያዥነት ያላቸው የኤሌክትሮኒከስ ዕቃዎች እና ባዶ ቶነር ካርትሬጅ ሲሆኑ ሌሎች ንብረቶች በአገልግሎቱ የሚወገዱት በነጣላ ዋጋ 50,000 ብር በላይ እና ጠቅላላ ዋጋ 500,000 ብር በላይ የሆኑ ናቸዉ ብለዋል ፡፡ በመድረኩም ንብረት አወጋገድን አስመልክቶ ተቋማት ንብረት ማስወገድ ሲፈልጉ ያለአገልግሎት የተከማቹ ንብረቶችን መለየትና የመስሪያ ቤቱ የበላይ ሃለፊ እንዲወገዱ ወሳኔ መስጠት፣ ያለ አገልግሎት የተከማቹ ንብረቶች በራሳቸውን የሚወገዱ የንብረት ዋጋ ገማችና አስወጋጅ ኮሚቴ በማቋቋም �እንዲሁም በአገልግሎቱ በኩል የሚወገዱትን መረጃዎችን አደራጅተው መላክ፣ ለሚወገዱ ንብረቶች ልዩ ጥበቃ ማድረግ፣ በማዕከል የሚወገዱ ንብረቶች ላይ ከአገልግሎቱ ጋር መተማመኛ መፈረም፣ የሚወገዱ ንብረቶች ለተጫራቾች ማሳየትና ከተሸጡ በኋላም ለአሸናፊ ድርጅቶች በአግባቡ ማስረከብ እንዳለባቸዉ ተገልጿል፡፡

photo content
+1

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ መ/ቤቶችና ተቋማት ንብረቶች የሆኑ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ መ/ቤቶችና ተቋማት ንብረቶች የሆኑ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፣ የተሸከርካሪ ጎማዎች፣ ቸርኬዎች፣ ባትሪዎች፣ ፍላፖች፣ ከነመዳሪዎች፣ ጀነሬተር፣ በርሜሎች፣ ያገለገሉ የቢሮ መገልገያ ፈርኒቸሮች እና ያገለገሉ የህክምና ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ ማስታወቂያ የካቲት 16 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቷል፡፡ በዚሁ መሰረት መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከየካቲት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቤክ የንግድ ማዕከል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት የጨረታ ሰነድ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ጨረታው መጋቢት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይከፈታል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-86-71 ይደውሉ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሰት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

ለመንግሥት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰራተኞች በሙሉ የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የመፅሀፍ ንባብ እና የ ዉሰት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን እየገለጸ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆ
+2
ለመንግሥት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰራተኞች በሙሉ የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የመፅሀፍ ንባብ እና የ ዉሰት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን እየገለጸ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ይገልፃል

በተማከለ የመንግስት ንብረት አወጋገድ ዙሪያ ጥናት ሊከናወን መሆኑ ተገለፀ በጥናቱ በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጥያቄ መሰረት የሚከናወን ሲሆን በአዲስ አበባ አመራር ዓካዳሚ የሚከ
+2
በተማከለ የመንግስት ንብረት አወጋገድ ዙሪያ ጥናት ሊከናወን መሆኑ ተገለፀ በጥናቱ በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጥያቄ መሰረት የሚከናወን ሲሆን በአዲስ አበባ አመራር ዓካዳሚ የሚከናወን መሆኑም ተገልጿል፡፡ በዚህ የጥናቱ ማስጀመሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና መግባቢያ መድርክ ላይ የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን የጥናት እና ምርምሩ ዓላማም የተማከለ የመንግስት ንብረት አወጋገድ እያስገኘ የሚገኘዉን ጠቀሜታ እና የሚያጋጥመዉን ተግዳሮት ለይቶ ማስቀመጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በዚህ ጥናትም 16 ሴክተር መስሪያ ቤቶች ፣ 4 ክፍለ ከተሞች 36 ወረዳዎች እና 2 ሆስፒታሎች እንደሚካተቱ የተጠቀሰ ሲሆን ይህም ሁሉንም የአስተዳደር እርከኖች ከግምት ያስገባ ነዉ ተብሏል፡፡ በመድረኩም የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ም/ስራ አስኪያጅ እና የማስወገድ እና ገበያ ጥናት ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጎርጊስ እንዳብራሩት ስራዎች የሚኖራቸዉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ እና ሀገራዊ ጠቀሜታ በሳይንሳዊ ጥናት እና ምርመምር ማስደገፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለዉ አስቀምጠዉ ተቋማት ለጥናቱ ቀና ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡

photo content

+1
የመንግስት ሰራተኞች የስራ ምደብ ማስታወቂያ

የሰራተኞች ድልድል መመሪያ