AACPPPDS
Open in Telegram
308
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
308
' የምስጋና የምስክር ወረቀት ''
በአረንጓዴ አሻራ ውጤታማ የችግኝ መትከል ተግባር
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በ 5ኛ ዙር በ2105 ዓ.ም ላከናወነው ዉጤታማ የችግኝ መትከል እንቅስቃሴ እና ደማቅ የአረንጓዴ አሻራን የማኖር ተግባር አከናዉኗል።
ለዚህም ተግባሩ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ከወረዳው ውበት እና አረንጓዴ ልማት ፅ/ቤት የምስጋና የምስክር ወረቀት ከታላቅ አክብሮት ጋር ተበርክቶለታል።
ዘገባዉ - የኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለበለጠ መረጃ 0115-557-622
308
ነገን ዛሬ እንትከል
በአገር አቀፍ ደረጃ ለአምስተኛ ዙር 6.5 ቢሊየን ለመትከል እና በአዲስ አበባ ከተማ 17 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አርዓያነት ‹ነገን ዛሬ እንትከል!› በሚል መሪ ቃል በተለያዩ አካላት አረንጓዴ አሻራን የማሳረፍ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል።
አምና በእንጦጦ ፓርክ 5 ሺህ ችግኞችን በመትከል አሻራዉን ያኖረዉና በተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች ላይ እና በክረምት የበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ በንቃት በመሳተፍ የሚታወቀዉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በዘንድሮውም የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በመጀመሪያ ምዕራፍ 5000 ሺህ ችግኞችን የመትከል ስራ አከናዉኗል።
በችግኝ የመትከል መርሃ ግብርሩ ላይ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ዓመራር እና ሰራተኞች ፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ነዋሪዎች የተሳተፉ ሲሆን አሻራቸዉንም ለትዉልድ ያኖሩበት እንደነበር ታውቋል።
በስፍራዉም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዓመራሮች እንዳስገነዘቡት የተተከሉትን ችግኞች በኃላፊነት የመንከባከብ እና የመጠበቅ ተግባር ይደር የማይባል ቀጣይነት ያለው ግዴታችን ነው ብለዋል።
ዘገባዉ :- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
308
በሀገር ሽማግሌዎች እና እናቶች ምርቃት የታጀበ በመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አመራሮች እና ሰራተኞች ደማቅ የችግኝ መትከል መርሀ ግብር ።
'' ነገን ዛሬ እንትከል ''
308
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወነው የችግኝ መትከል መርሀ ግብር ላይ የተለመደ አሻራዉን ለማኖር ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በወረዳ 03 የሚገኘዉን የቀለበት መንገድ አካፋይ የችግኝ መትከያ ቦታ ተረክቧል።
308
የአዲስ.አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች የሆኑ የተለያዩ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፣ ማለትም የተሽከርካሪ ጐማዎች፣ ቸርኬዎች፣ ባትሪዎች፣ ፍላፖች፣ ከነመዳሪዎች፣ በርሜሎችና የቢሮ መገልገያ ፈርኒቸሮች በሽያጭ ለማስወገድ የጨረታ ማስታወቂያ ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቷል፡፡
በዚሁ መሰረት መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቤክ የንግድ ማዕከል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት የጨረታ ሰነድ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ጨረታው ሰኔ 30 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይከፈታል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-86-71 ይደውሉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሰት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት
308
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በጨረታ ቁጥር AAPPPDS/SA/2015/ICB/PIS/30/04/2015 ባወጣው የ Supply, Design, Installation, Implementation and Support of 87 primary and secondary School-net Project Phase-1 የፋይናንስ ሰነድ የመክፈት ስነስርዓት ተከናወነ
308
በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ የመንግሰት ት/ቤቶች የ 2016 ዓ.ም የተማሪዎች ደብተር እና የደንብ ልብስን በወቅቱ ተደረሽ ለማድረግ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ የመንግሰት ትምህርት ቤቶች የመማሪያ ቁሳቁስ እና የደንብ ልብስ እንዲሁም ለመምህራን ጋዎን በግልፅ ጨረታ ግዥ በመፈፀም በነፃ ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወቃል።
በ 2016 ዓ.ም የመማር ማስተማር ዘመንም ይህንኑ ተግባር ወቅቱን ጠብቆ ይፈፀም ዘንድ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ፣ ምገባ ኤጀንሲ ፣ የፋይናስ ቢሮ ፣ ምክር ቤት ፅ/ቤት ፣ እና የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በጋራ ትኩረት ሰጥተዉ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል ።
የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅትም ጥራታቸዉን የጠበቁ የተማሪዎች የደንብ ልብስ እና የመምህራን ጋዎን ለማቅረብ በሚደረገዉ ጥረት የተለየ ትኩረት በመስጠት የበኩሉን ሚና እየተጫወተ መሆኑንም መረዳት ተችሏል ።
በዚህም 997.461 ያህል ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች እና 39.969 መምህራን ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።
308
በግዥ ምንነት እና ፅንሰ ሀሳብ ፣ በጨረታ ሰነድ ዝግጅት ፣ በግዥ እና የጨረታ ሒደት እና ግምገማ ፣ በውል አስተዳደር ፣ በባንክ እና ኢንሹራንስ አገልግሎት ዙሪያ ።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት እና በኢትዮጵያ የንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የግዥና ማማከር አገልገሎት ዘርፍ ለግዥ ባለሙያዎች እና አመራሩ በጋራ ሲከናወን የቆየዉ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ ።
308
ለግዥ ባለሙያዎች እና አመራሩ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ
ስልጠናዉን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ እንደጠቆሙት ስራን በዕውቀት በማጀብ የተገል ጋይን እርካታ ለማረጋገጥ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ያለቸው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል ።
ስልጠናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት እና በኢትዮጵያ የንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የግዥና ማማከር አገልገሎት ዘርፍ በጋራ የሚከናወን ሲሆን መሰጠት የጀመረው የአቅም ግንባታ ስልጠናም ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።
ስልጠናው በግዥ ምንነት እና ፅንሰ ሀሳብ ፣ በጨረታ ሰነድ ዝግጅት ፣ በግዥ እና የጨረታ ሒደት እና ግምገማ ፣ በውል አስተዳደር ፣ በባንክ እና ኢንሹራንስ አገልግሎት ዙሪያ ትኩረት እንደሚያደርግም ተጠቅሷል።
308
የጨረታ ቁጥር፡- AAPPPDS/SA/2015/NCB/PIS/03/07/2015
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ግዥ ለመግዛት በአገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ የአይሲቲ እቃዎች እና ተዛማጅ አገልግሎቶች ግዥ በልዩ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ህጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
መግለጫ
supply, design, installation, commissioning and testing of Wi-Fi network infrastructure.
የጨረታ ማስከበሪያ በብር 500,000 Birr
1. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በመክፈል ከመጋቢት 22/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለ20 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ስለሆነ ከጥዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 የጨረታ ሰነድ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ከ6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 መግዛት ይችላሉ፡፡
2. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከመጋቢት 22/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለ20 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ይሆናል፡፡
3. ጨረታው ቅዳሜ ሚያዚያ 21/2015 ዓ.ም ከጥዋቱ 5፡00 ተዝግቶ በዚያው ዕለት ከረፋዱ 5፡30 በአገልግሎቱ 9ኛ ፎቅ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
4. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ሚክሲኮ ሰንጋ ተራ ከቅድስት ማርያም ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ጀርባ ዮቤክ የንግድ ማዕከል።
ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት በስልክ ቁጥር
• +25115-573170/40 ከ2፡30 እስከ 11፡30 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
