en
Feedback
AACPPPDS

AACPPPDS

Open in Telegram

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዝና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

Show more
308
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በበጎነት ቀን የተከነወነ በጎ ተግባር ለመኖር ምቹ ካልነበረ ወደ ፅዱና የተዋበ መኖሪያ ቤት በበርካታ ሀገራዊና ማህበራዊ ተሣትፎዎቹ የሚታወቀው የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በኮልፌ ቀ
+3
በበጎነት ቀን የተከነወነ በጎ ተግባር ለመኖር ምቹ ካልነበረ ወደ ፅዱና የተዋበ መኖሪያ ቤት በበርካታ ሀገራዊና ማህበራዊ ተሣትፎዎቹ የሚታወቀው የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የሚገኙ የአምስት አባወራና እማወራ ቤተሠቦችን ቤት አድሶ ቁልፍ በማሥረከብ የተለመደ ኀላፊነቱን ተወጥቷል ። ይህ '' በበጎነት ቀን የተከናወነ በጎ ተግባር ነው '' ሲሉ የገለፁት የአገልግሎቱ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ አበበ ለነዋሪዎች ምቹ ከባቢና እና የተሻለ መኖሪያ መፍጠር አንዱ የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል ። ይህንን አቅጣጫ ተከትሎም እንደ መንግሰት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከዚህ ቀደም በፈራረሠ እና ለኑሮ ምቹ ባልነበሩ ቤቶች ውስጥ ሲኖሩ ለነበሩ አምስት አቅመ ደካማ ቤተሠቦች ከ 1.7 ሚልዮን በላይ ብር በመመደብ በአጭር ጊዜ ውስጥ እድሳት በማከናወን ለባለቤቶቹ ማሥረከብ መቻሉን ገልፀዋል ። በርክክቡ ወቅት በነዋሪዎቹ ላይ የተመለከትነው ደስታ የኛም ደስታ ነው ያሉት የፅ/ቤቱ ኃላፊ የህ ትልቅ እና የተቀደሠ ተግባር እውን እንዲሆን ከጎናችን ሆነው ድጋፍ ላደረጉ አካላት ከፍተኛ ክብር እና ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል ።

ኢትዮጵያ "በመስዋዕትነት የምትፀና ሀገር - ኢትዮጵያ በመስዋዕትነት ፀንታ የኖረች ፥ ወደፊትም በጀግኖች መስዋዕትነት የምትቀጥል ሀገር ናት። ሀገር እንድትፀና እና ትውልድ እንዲቀጥል መስዕዋትነት እና
+4
ኢትዮጵያ "በመስዋዕትነት የምትፀና ሀገር - ኢትዮጵያ በመስዋዕትነት ፀንታ የኖረች ፥ ወደፊትም በጀግኖች መስዋዕትነት የምትቀጥል ሀገር ናት። ሀገር እንድትፀና እና ትውልድ እንዲቀጥል መስዕዋትነት እና ህይወት መሥጠት መሣኝ ነው ። መሥዕዋትነት በህይወት መስዋዕትነት ብቻ አይወሰንም እያንዳንዱ ዜጋ ጊዜውን ፣ ጉልበቱን ፣ እውቀቱን እና ገንዘቡን ለሀገሩ እንዲሁም በደም እጥረት ለሚጎዱ ወገኖቹ ደሙን እንካችሁ ማለቱ ታላቅ መሥዕዋትነት ነው ። ይህንን የተቀደሠ ደም የመለገሥ ተግባር ደግሞ በየሦስት ወሩ እያከናወኑ የሚገኙት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዓመራርና ሠራተኞች በጳጉሜ 2 የመሥዕዋትነት ቀን አከናውነዋል ። በዕለቱ የደም ልገሳ ያደረጉት የተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ '' ኢትዮጵያ በመስዋዕትነት ፀንታ የኖረች ፥ ወደፊትም በጀግኖች መስዋዕትነት የምትቀጥል ሀገር ናት '' ብለው አክለውም ህይወታቸውን ሰውተው ያቆዩዋትን ኢትዮጵያ ፥ እኛም በዚህ ዘመን በያለንበት ሙያ እና አቅም የቻልነውን ሰጥተን ሀገርን ለትውልድ የማሻገር ኃላፊነት ተጭኖብናል እናም በምንችለው ሁሉ ትንሽ ዋጋ መክፈል አለብን ሲሉ አበክረው ገልፀዋል ። ደም መለገሥ ህይወት መለገሥ ነው !!! በመሥዕዋትነት የደመቀች ፤ በጀግንነት የታፈረች ፦ ኢትዮጵያ

'' ያለንን ማካፈል የአብሮነታችን ሚስጥር የበጎነት ማሣያ ነው '' በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ።
+2
'' ያለንን ማካፈል የአብሮነታችን ሚስጥር የበጎነት ማሣያ ነው '' በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ።

የጷግሜ ቀናት የመጀመሪያ ቀን ጷግሜ 1 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በድምቀት እና የአገልጋይነትን መንፈስ በተላበሠ መልኩ በድምቀት ተከበረ ። የዘንድሮውን የጷግሜ ቀናቶች ጷግሜን ለኢትዮጵያ በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ እሴቶችን በተላበሱ የተለያዩ መርኃ-ግብሮች እና አገልግሎትን ማእከል ባደረገ መልኩ ለማክበር ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ወደስራ የተገባ ሲሆን በዚህም አጠቃላይ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ባለሙያዎች እና አመራሮች እንዲሁም ዕለቱን አስመልክቶ የተገኙ በዓመት ዕረፍት ምክንያት ያልነበሩ ሰራተኞች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል። በኢትዮጵያ ህዝብ ብሔራዊ መዝሙር የተጀመረው መርሀ ግብሩ በተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ በእንኳን አደረሣችሁ እና ዕለቱን በተመለከተ አጠር ያለ መልዕክት በይፋ ተከፍቷል፡፡ በመቀጠልም ለዕለቱ በኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ ስለ አገልግሎት ምንነት እና አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ከተቋሙ ስለሚጠበቅ ድርሻና ሀላፊነት ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ፅሁፍ የቀረበ ሲሆን ። የእለቱ መርሀግብር አንዱ አካል የሆነው በስራ ገበታቸው ላይ በቅን አገልጋይነታቸው የተመሠከረላቸው ፣ በጥሩ ምግባራቸው ለሌላው አርኣያ የሚሆኑ ባለሙያዎችን የማመሥገን እና እውቅና የመሥጠት ስነስርዓትም ተከናውኗል ። በመጨረሻም ለቀጣዮ ቀን ማለትም ጷግሜ 2 የመሥዕዋትነት ቀን ለሚከናወን የደም ልገሳ ፕሮግራም ሀሣብ የማጥራት ፣ ለጋሽ የመለየት እና በፕሮግራሙ አተገባበር ላይ መግባባት ላይ በመድረሥ መልዕክት የማስተላለፍ ስራን በማከናወን እና ዕለቱን ታሣቢ ያደረገ ተቋማዊ አገልግሎትን በማስቀጠል መርሀግብሩ ተጠናቋል ። ዘገባው ።፦ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው ። ጷግሜ 01/2015

photo content
+3

በአዲስ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ንብረት ጨረታ ቁጥር 01/2016 ውጤት

አገራችን የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃና የመልማት ፍላጎት መሠረት ያደረገ የመልካም አገልግሎት አሰጣት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት
+1
አገራችን የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃና የመልማት ፍላጎት መሠረት ያደረገ የመልካም አገልግሎት አሰጣት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በትላንትናዉ ዕለት የመልካም አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችና የመፍትሔ ሐሳቦች ዙሪያ ዉይይት ያከናወነ ሲሆን የተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ መንግስቱ አጥናፉ እንደገለፁት ኢትዮጲያ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃና የመልማት ፍላጎት መሠረት ያደረገ የመልካም አገልግሎት አሰጣት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የመልካም አገልግሎት አስፈላጊነት ፣ የመልካም አገልግሎት ምንነት፣ሀገርንና ሕዝብን ማገልገል ማለት ምን ማለት ነው?ተገልጋዩ ሕዝብ ከአገልግሎት ሰጭው ምን ይፈልጋል? እና የመልካም አገልግሎት አሰጣጥ ችግር መንስኤዎችና መፍትሔዎቻቸው የሚሉት ዋና ዋና ጉዳዮች ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል ፡፡ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎትም በከተማ አስተዳደሩ ስር ከሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አንዱ እንደመሆኑ ቀልጣፋ እና ዘመናዊ እንዲሁም የደንበኛን እርካታ ማዕከል ያደረገ የመልካም አገልግግሎት ሰጪ ለመሆን ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ተገልፅዋል ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በቁጥር 01/2016 ዓ.ም የተቋማት ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች ላይ ተወዳድረው አንደኛ የወጡ ተጫራቾች ስም ዝርዝር

photo content

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች ተሽከርካሪዎች ጨረታ (ቁጥር 01/2016) አንደኛ የወጡ ተጫራቾች ስም ዝርዝር

በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮቻችንን በመቀላቀል የተለያዩ መረጃዎችን እና የጨረታ ማስታወቂያዎችን ይመልከቱ አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ! YouTube - https://www.youtube.com/@pppdstube Telegram - https://t.me/AACPPPDS Facebook - https://www.facebook.com/AAPPPDS Twitter - https://twitter.com/aapppds

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በ 2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻፀም ላይ ዉይይት ሊያከነዉን መሆኑ ተገለፀ፡፡ አገልግሎቱ ሀሙስ ነሀሴ 25-12-2015
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በ 2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻፀም ላይ ዉይይት ሊያከነዉን መሆኑ ተገለፀ፡፡ አገልግሎቱ ሀሙስ ነሀሴ 25-12-2015 ዓ.ም በ ግራንድ ኤሊያና ሆቴል ሊያከናዉን ባቀደዉ በዚህ የዉይይት መድረክ ላይ ጥሪ የተደረገላቸዉ አቅራቢዎች ፣ክፍለ ከተሞች፣ ሴክተር መስሪያ ቤቶች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙ ይጠበቃል ፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ክፍለ ከተሞች እና በስራቸዉ ላሉ ተቋማት የጋራ መገልገያ እና ስትራቴጂክ ጠቀሜታ ያለቸዉን እቃዎች በአለም እና ሀገር አቀፍ ደረጃ ጨረታዎችን በማዉጣት የማእቀፍ ስምምነት በመፈራረም ተቋማት ግዥ እንዲፈፅሙ በማስቻል እና በመንግስት ሃላፊነት ስር የሚገኙና እንዲወገዱ ዉሳኔ የተሰጠባቸዉን ንብረቶች በማስወገድ ገቢ በማስገኘት የሚታወቀዉ የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በዚህ በ2015 በጀት አመት እቅድ አፈፃጸም ሪፖርትን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ዉይይት የሚያከናዉን ሲሆን የተገኙ ዉጤቶችንም የጋራ እንደሚያደርግ እና የተስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት እና የገጠሙ ችግሮችን በመገምገም የተሻለ ተግባራትን ለመከወን ያስችል ዘንድ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል፡፡

የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሚና አዲስ አበባን ለማዘመን በሚደረግ እንቅስቃሴ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማና የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ ናት፡፡ብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችም ይገኙባታል፡፡ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ መዲናም ናት።ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የፌደራል ከተማነትን ማዕረግ ይዛለች።ከባሕር ጠለል በ2 ሺ 500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው አዲስ በ1999 ዓ.ም በተደረገው የህዝብ ቆጠራ ከ2 ሚሊዮን 739 ሺ 551 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ ትልቋ ከተማ ናት። የከተማዋ አስተዳደር ይህችን ከተማ እጅግ የዘመነች ከተማ የማድረግ ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ከተማዋን እየመሯት ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ወደ ስልጣን ከመጡ ጀምሮ ከተማይቱን በሁለንተናዋ በዓለም ካሉ የዘመኑ ከተሞች እኩል የማሳደግ ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ከሚበጅተው በጀት ከ70 በመቶ በላዩን የሚይዘው ግዢ ሲሆን ግዢው ለዚችው ከተማ ሁለንተናዊ ግንባታ ይውላል፡፡ይሄን የሚተግበሩ የቤት ሥራ የወደቀው ለከተማ አስተዳደሩና በአስተዳደር ውስጥ ላሉ መሥሪያ ቤቶች የተለያዩ ግዢዎች በሚፈጽመው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሲሆን ንብረት የማስወገድና ግዢ የመፈፀም ጥንድ ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ ለዛሬ ግዢው ላይ በማትኮር በተቋሙ የምክርና ሌሎች አገልግሎቶች ግዢ ቡድን መሪ አቶ ኤፍሬም አሩሲ የሰጡንን መረጃ እናካፍላችኋለን፡፡በመረጃው መሰረት ከተማዋን ማዘመን የሚያስችል 1 ቢሊዮን 441 ሚሊዮን 546 ሺ 702 የኢትዮጵያ ብር ወጪ የሆነበት ሰባት ትልልቅ ግዢ ፈጽሟል፡፡ ግዢዎቹ በመዲናዋ ባሉ የተለያዩ ተቋማት ሥራ ላይ ውለዋል፡፡በበጀት ዓመቱ ከከተማ አስተዳደሩ ከሚመነጨው በጀት ከ70 በመቶ በላዩ ለግዢ አገልግሎት ነው መዋሉን የሚያስታውሱት ኃላፊው ተቋማቸው በዚህ መሰረት ለግንባታውም ሆነ ለሌሎች ዘርፎች ግዢዎችን እንደሚፈጽምም ያነሳሉ፡፡ከነዚህ መካከል የጋራ መጠቀሚያ ግዢውች የሚላቸው ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ለአብነት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የጠረጴዛ፤ወንበርና የጽሕፈት መሣሪያ፤የደንብ ልብስና የጋራ መጠቀሚያ የተሰኙት ከሚፈጽሟቸው ግዢዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በየጊዜው ቢቀያየሩም የከተማ አስተዳደሩ ስትራቴጂክ ጠቀሜታ አላቸው ብሎ የሚያስባቸውን ግዢዎችም ይፈፀማል፡፡ለምሳሌ ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ከተማሪዎች ኢኒፎርምና ደብተር ጋር ተያይዞ የተፈፀመ ስትራቴጂክ ግዢ አለ፡፡ከዚህ ውጭ ያሉ ግዢዎች የሲስተም ግዢዎች እንደሆኑም አቶ ኤፍሬም ያነሳሉ፡፡እንደ ከተማ አስተዳደር የሚሰጡት አገልግሎቶች ዘመናዊ ፈጣንና ቀልጣፋ መሆን አለባቸው፡፡ዓለም ከደረሰበት ቴክኖሎጂ ጋር ሊሄድ የሚችል ከተማ በመገንባት የከተማ አስተዳደሩን ፍላጎት እውን ማድረግ የሚቻለውም በሲስተም ግዢዎችና በቴክኖሎጂዎች አማካኝነት ነው፡፡‹‹ለስማርት ሲቲ ግንባታ ቴክኖሎጂዎችና የሲስተም ግዢዎች በእጅጉ አስፈላጊ ናቸው››ይላሉም፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ተቋማቸው በ2015 በጀት ዓመት በርካታ የሲስተም ግዢዎች አከናውኗል፡፡ የሲስተም ግዥ ምን እንደሆነና ከሌሎች ግዢዎች በምን እንደሚለይ አስመልክተው እንደሰጡን መረጃ ግዢው እንደ ጠረጴዛ፤ወንበር፤ፈሳሽና ሌሎች ግዢዎች እንደሚከናወንባቸው ዓይነት አይደለም፡፡የምርምርና የቴክኖሎጂ ግዢነው፡፡እንደ ማዕቀፍ ግዢ በየሶስትና በየስድስት ወሩ እየታደሰ የሚሄድ የውል ይዘት የለውም፡፡ተቋሙ አንዴ ውል የሚዋዋልበት የአንድ ግዜ ግዢም ነው፡፡ዕቃውንና አገልግሎቱን የያዙ በመሆናቸው ከሌሎች ግዢዎች ይለያሉ፡፡አብዛኞቹ ከማቅረብ ጀምሮ የተለያዩ ሂደቶችን በማለፍ የሚከናወኑ ትልልቅና ከፍተኛ ገንዘብ የሚወጣባቸው ናቸው፡፡ለሦስትና ለሁለት ዓመት ይቆያሉም፡፡በአንዴ የሚፈፀሙ ቢሆኑም የግዢዎቹ ባህርይ ዕውቀትን፤ትልቅ ሙያና መልካም ስነምግባርን ይጠይቃል፡፡ትልልቅ ባለሙያዎችን ይፈልጋል፡፡የሚገዙት ዕቃዎች ወራንቲ፤ሜንቴናንስ (ጥገና)የሚሰጥበት ዓይነት ናቸው፡፡በግዢ ም ሆነ በግምገማ ሂደታቸውም ይለያሉ፡፡ሌሎቹ ግዢዎች ዝቅተኛ ዋጋ የተሰጠባቸው በመሆናቸው በጨረታ ሲለዩ እነዚህኞቹ በዋናነት ቴክኒካል ብቃታቸው ይታያል፡፡ዋጋው ተደምሮ በሁለቱ ድምር ውጤት አሸናፊዎች የሚለዩበት የግዢ ዓይነት ናቸው፡፡ግዢውም ተከናውኖ ወደ ተግባር ሲገባ ሥራውን የሚያከናውኑ ሰዎች በተገዙት ዕቃዎች ላይ ዕውቀት ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡ግዢው ተገዝቶ የሚተገበርበት ተቋም ውስጥ ያሉ ሰዎች ጉዳዩኝ እንዲረዱት ስልጠናም ይሰጣል፡፡ አሸናፊው ድርጀት ሥራውን ከሰራ በኋላ የሚያስረክበው ተቋሙ ላይ ላለ ለአይቲ የሥራ ክፍል ነው፡፡ክፍሉ አጠቃላይ ሥራዎችን መምራት የሚያስችል ዕውቀት፤ ግንዛቤ ያለው መሆን አለበት፡፡በመሆኑም የዕውቀት ሽግግርም ጭምር ያለባቸው የግዢ ዓይነት በመሆናቸው ከሌሎች ግዢዎች ይለያሉ፡፡ ‹‹ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሠጣጥ ትልቁ ፋይዳው ቅልጥፍናና ወጪ መቀነስ ነው››የሚሉት አቶ ኤፍሬም ከተማዋን በቴክኖሎጂ የታገዘች ዘመናዊ ከማድረግ አንፃር የተቋማቸውን አስተዋጾ ከፍተኛ እንደሆነ ያወሳሉ፡፡በከተማ አስተዳደሩ ከስማርት ሲቲ ግንባታጋር ተያይዞ የተያዘ ፕሮጀክት አለ››የሚሉት ኃላፊው ከዚህ አንፃር ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ለስማርት ሲቲው ግንባታ በርካታ የሲስተም ግዢ መግዛቱን ያነሳሉ፡፡ለአብነት ለአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር የኔትወርክ መሰረተ ልማት፤የዳታ ማዕከልና የሰርቪላንስ ግዢዎች ገዝቷል፡ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንም የኔትወርክ ኢንፍራስትራክቸር ዝርጋታ፤ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዲጂታል ቤተ መጽሐፍትና ማኔጅመንት ጋር የተያያዘ ግዢ ፈጽሟል፡፡ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዴሞክራሲ ግንባታ ከአጠቃላይ ተቋሙ ጋር ተያይዞ የመረጃ ፤ የሰው ኃይል፤የአደረጃጀት ጉዳዮችን የሚፈታ ግዢ ፤ለሌላ ተቋም የሲሲቲቪ ካሜራ (የቪዲዮ ካሜራ ሰርቪላንስ ሲስተም ግዢዎች ገዝቷል፡፡ለአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝምም ገዝቷ፡፡በሲስተም 1 ቢሊዮን 441 ሚሊዮን 546 ሺ 702 የኢትዮጵያ ብር ወጪ የሆነበት ሰባት ትልልቅ ግዢ ፈጽሟል፡፡ እንደሳቸው ግዢዎቹ ፋይዳ ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የተገዘ ከተማ ከመፍጠር አንፃር ጉልህ ፋይዳ አላቸው፡፡ግዢዎቹ በከተማ አስተዳደሩ ባሉ ተቋሞች ላይ ለውጥ ማምጣት ያስችላሉ፡፡ተገልጋዩን ያረካሉ፡፡የጉልበትና የጊዜ ብክነትን ይቀንሳሉ፡፡ጥራት ያለውና ተደራሽ እንደዚሁም ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት ያስችላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት ተቋማቸው ይሄንኑ የግዢ ሲስተም ሙሉ በሙሉ ከማነዋል በማላቀቅ ወደ ዘመነ ኤሌክትሮኒክስ የግብይት ሲስተም የማስገባት እቅድ አለው፡፡በከተማ አስተዳደሩ መተግበር ጀምሯል፡፡ግዢ የሚፈፀመው በአዋጅ፤በመመርያ፤በግዢ ማንዋል ስለመሆኑ ተቋማትና ሕብረተሰቡ ግንዛቤ የላቸውም፡፡አካላቱ ሰፋፊ ግዢ ከመፈፀሙ አኳያ የጥራት፤የቅልጥፍና እና የፍጥነት ቅሬታዎችም ያነሳሉ፡፡በመሆኑም ከግዢው ጎንለጎን እነዚህን ችግሮች ግንዛቤ በማስጨበጥ ለመፍታት የመሥራት ሀሳብ ሰንቋል፡፡

photo content

በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የአገልግሎቱ ዓመራሮችና ሠራተኞች ውይይት አካሄዱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳ
+1
በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የአገልግሎቱ ዓመራሮችና ሠራተኞች ውይይት አካሄዱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ውይይት ያካሔዱ ሲሆን በመድረኩም የውይይት መነሻ ሃሳብ በአገልግሎቱ አመራሮች ቀርቦ ሠፊ ውይይት ተከናውኗል ። ውይይቱ በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል እየተስተዋለ በሚገኘው የፀጥታ መደፍረስ ችግር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ። በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ሰራተኞች በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች ከሠሜኑ ጦርነት በመማር ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡ የጠየቁ ሲሆን አክለውም በሰላማዊ ውይይት እንጂ ከጦርነት ማንም የማያተረፍ መሆኑን በመገንዘብ እና የሰላም መደፍረስ ችግር መከሰቱ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በማንሳት መንግስት በአንድ በኩል ህግ የማስከበር ተልዕኮውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት እና ችግሩን በዘላቂነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትም ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋልም ብለዋል ። በመጨረሻም ሁሉም ዜጋ የሀገሩን ሠላም እና የህዝቡን ደህንነት የማስጠበቅ ግዴታውን እንዲወጣ በማሳሰብ የውይይት መድረኩ ተጠናቋል ። ዘገባው ፦ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፤ የተሸከርካሪ ጎማዎች፤ ቸርኬዎች፤ ባትሪዎች፤ ፍላፖች
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፤ የተሸከርካሪ ጎማዎች፤ ቸርኬዎች፤ ባትሪዎች፤ ፍላፖች፤ ከነመዳሪዎች፤ በርሜሎች፤ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች እና የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱ ባዶ የቶነር ካርትሌጆችን በሽያጭ ለማስወገድ ግልጽ ጨረታ ነሀሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከነሀሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሀሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቤክ የንግድ ማዕከል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት የጨረታ ሰነድ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ጨረታው ነሀሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይከፈታል፡፡

አገልግሎቱ በበጀት ዓመቱ የ 6.8 ቢሊየን ብር ግዢ ፈፅሟል በዚህም በማዕቀፍ ግዢዎችን በማከናወኑ ከሁለት ቢሊየን ብር በላይ ማዳኑን ታዉቋል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በከተማዋ በተበጣጠሰ መንገድ በተቋማት የሚፈጸመውን ግዢ በአንድ ማዕቀፍ በመከወኑ በበጀት ዓመቱ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መቀነሱን ገለጸ። የአገለግሎቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግሥቱ አጥናፉ ለኢፕድ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በአንድ ማዕከል ግዢን የመከወን ተገልጋይ ተቋማት ውልን አስሮ የማሳወቅ እና ግዢውን ማመቻቸት ላይ ይሰራል። እንዲሁም ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ ንብረቶችን በሽያጭ የሚወገዱትን በሽያጭ እንዲወገዱ ያደርጋል። ይህንንም ለመተግበር አስፈላጊውን የሰው ኃይል እና ተቋማዊ መዋቅር እንዲኖረው ተደርጎ የተቋቋመ ተቋም ነው። ተቋሙ ግዢዎቹን ለጠቅላላ አገልግሎት የሚውሉና ስትራቴጂክ ግዢዎችን የሚያከናውን ሲሆን በ2015 በጀት ዓመት ከተቋማት ጋር ውል በመተሳሰር 94 ዓይነት ግዢዎችን ለማካሄድ አቅዶ 84ቱን ለማሳካት ችሏል። በገንዘብ ደረጃ ስድስት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊየን ብር ያህል ግዢዎችን ለማከናወን አቅዶ ስድስት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር ግዢ መፈጸሙን ተናግረዋል። በዚህም 99 በመቶ ግዢውን ማሳካት የተቻለበት ሂደት መሆኑን ገልጸዋል። በ2014 ተመሳሳይ በጀት ዓመት ሁለት ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር ግዢ መፈጸሙን አስታውሰዋል። የዋጋ መናር፣ የሚገዙት እቃዎች አይነት እኔ ሌሎች ጉዳዮችን ጨምሮ በዚህ ዓመት በብዙ እጥፍ ከአምናው የተሻለ ግዢ ማሳካት የተቻለ ተችሏል። ግዢው በአንድ ማዕከል በመገዛቱ በተለይም ተቋማት በራሳቸው በተበጣጠሰ መንገድ ጨረታ አውጥተው ከመግዛት ይልቅ በማዕቀፍ በመገዛቱ ለከተማው ወደ ሁለት ነጥብ አንድ ቢሊየን ብር መቀነስ ተችላል ። በተለይም ከተማሪዎች ጋር የሚያያዙ ሰፋፊ ግዢዎች ደብተር ዩኒፎርም፤ ከተማውን ከማዘመን አኳያም ስትራቴጂክ የሆኑ በተለይም የቴክኖሎጂ፣ የሶፍትዌር፣ ተያያዥ የሃርድዌር እቃዎች፤ በተቋማት መገልገያ የሆኑ እቃዎችና ሼልፎችን እንዲሁም ለሰራተኞች ጥቅማጥቅም የሚውሉትን ያጠቃልላል። በዚህ ማዕቀፍ የሚገዛው አንዱም የተቋማት የመኪናዎች የመድን አገልግሎትና ተያያዥ የሆኑ ተሽከርካሪዎች አገልግሎትም በተቃሙ የሚገዛ ነው። ተቋማት በጋራ የሚጠቀሙባቸው ሰፊ ግዢዎችን የያዘው ማዕቀፉ ከ2014 በተሻለ ሂደት ግዢ ተፈጽሟል ብለዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ እንደገለጹት ለተቋሙ የተሰጠው የስራ ድርሻ አንዱ ያገለገሉ እቃዎችን በሽያጭ የሚወገዱትን በሸያጭ ማስወገድ ነው። በዚህም ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ እቃዎች ብረታ ብረት፣ ተሽከርካሪዎች፣ ጎማዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ የሆኑ እቃዎች በቀጥታ በተቋሙ የማስወገድ ሂደት የሚያልፉ ናቸው። ከዚያ ውጪ ያሉት ግን ተቋማት በራሳቸው ማስወገድ እንዲችሉ የተፈቀደላቸው አግባብ አለ። ተቋማት የአንድ ተናጥል ሽያጭ እስከ 50 ሺህ ፤ በጋራ ሲሆኑ ደግሞ እስከ 500 ሺህ ብር ያለውን በራሳቸው ያስወግዳሉ። ከዚህ በላይ ሲሆንም ወደ ተቋሙ ይመጣሉ። በአንድ ተቋም ውሰጥ በጣም የተከማቸ ፈርኒቸር ከ500 ሺህ ብር ግምት በላይ ከሆነ ወደ አገልግሎቱ የሚመጣ ሲሆን ከዛ በታች ከሆነም ተቋሙ ባራሱ ያስወግዳል። ነገር ግን ብረቶች፣ ተሽከርካሪዎች፣ ጎማ፣ ኤሌክትሮኒክስ የሆኑ ኮምውተር እና ተያያዥ የሆኑ እቃዎች ከአገልግሎቱ ጋር ውል የታሰረ በመሆኑ ግልጽ ጨረታ በማውጣት እና በማወዳደር ከፍተኛ ዋጋ ላቀረቡት የሽያጭ ሂደቱን በቀጥታ ያስኬዳል ብለዋል። አምና ብረት ላይ የማስወገድ ስራ በስፋት ያልተሄደበት መሆኑን ያስታወሱ ሲሆን ከፌደራል በወጣ ሰርኩላር ምክንያት አልሚ የሆኑ አገር ውስጥ ያሉ ብረትን የሚያቀልጡ ተቋማት ወስደው እንዲያቀልጡ እና ማምረት እንዲችሉ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ተቋሙ እነሱን ሲጠብቅ ቆይቷል ብለዋል። በተቋማትም በተለይ ብረትን ከማስወገደ አኳያ ሰፊ ቅሬታዎች አሉ። በበጀት ዓመቱም በከተማዋ ከሚወገዱ እቃዎች የሰነድ ሽያ ጨምሮ 100 ሚሊየን ብር ለማስገባት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ስድስት ጊዜ ጨረታዎች የወጡ ሲሆን 106 ሚሊየን ብር ለከተማ አስተዳደሩ ገቢ ማድረግ ተችሏል። ተቋሙ ሰፊ የመንግሥት ግዢን ከማዘመን አኳያ በ2022 አስተማማኝ እና ዘመናዊ የመንግስት ግዢ በመተግበር ከተማውን የበቃ የሀብት አጠቃቀም እንዲኖረው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ በመደረጉም በየቦታው ቦታ ይዘው ያሉ ብረታ ብረቶች ንብረቶች እንዲወገዱ ተደርገዋል። በተለይም ኤሌክትሮኒክስ ላይ ለረጅም ጊዜ ሳይወገዱ የቆዩ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በተሻለ ለማስወገድ ጥረት ተደርጓል። ጥቅም ላይ የማይውሉ ንብረቶችን በገንዘብ በመለወጥ ለከተማው ጥቅም እንዲያስገኝ ተደርጓል። በ2015 ተቋሙን መልሶ የማደራጀት እና ምቹ የስራ አከባቢ እንዲፈጠር ለማድረግ ስራዎች ሰርቷል። ግዚን አስመልክቶም ምን ያህል ተቋማት እርካታ ወይንም ቅሬታ እንዳላቸው ከተቋሙና በተለያዩ ተቋማት ባሉ ባለሙያዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት ተደርጓል። በውጤቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል። በጥናቱ የተገኘው ግበኣትም ለቅሬታ ምክንያት የሆኑ ግዢዎች ተቋማት በራሳቸው መግዛት የሚችሉትን እና ለከተማው በጀትን ይቀንስለታል የማይባሉትን እቃዎች በቀጣይ በ2016 በራሳቸው እንዲገዙ ለፋይናንስ ቢሮ ለማሳወቅ እና ተቋማት በራሳቸው እንዲያስኬዱ አቅጣጫ የተቀመጠበት ነው ብለዋል። እንዲሁም በጥናቱ የታየው ሌላው ግብኣት አቅራቢዎች በተፈለገው ፍጥነት ለተቋማት አገልግሎቱን የማቅረብ ችግሮች ምክንያት የጫረታ ጊዜ በጣም መራዘም እና የውሉ ጊዜ እስከ ሶስት ዓመት የሚቆይ መሆኑ ነው። በመሆኑም በቀጣይ በ2016 አንድ የታቀደው ጨረታዎችን እንደሁኔታቸው የአነድ ዓመትም፣ የሁለት ዓመትም ተደርገው ውል ሊታሰርላቸው የሚገባ መሆኑ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘም በአቅራቢዎች በየሶስት ወሩ የሚደረጉ የዋጋ ማሻሻያ በልዩ ሁኔታ ታሳቢ ለማድረግ መመሪያው በሚፈቅደው ሂደት መሰረት ለማየት ታቅዷል። ከብለሹ አሰራር እና ከሌብነት ጋር ተደጋግሞ ከሚፈረጁት ተቋማት አንዱ የሆነው ተቋሙ ይሄንን ከከንቲባ ጸህፈት ቤት፣ ከፋይናነስ ቢሮ፣ ከፍተህ ጽህፈት ቤት የተውጣጣ ቡድን ጥናት እንዲያካሄድ ተደርጓል። በዚህም የተቋሙ ውጫዊ አካላት ምን ይላሉ? የተቋሙ ሰራተኞች ምን ይላሉ? የሚለውን ሰፊ ዳሰሳ የተደረገበት ነው። ለዚሀ ተጋላጭ የሚሆነውም በተቃሙ ውስጠ ካሉተ ዘርፎችና የስራ አከባቢዎች ለሌብነት ምክንያት የሚሆኑ አሰራሮች ያሉት የቱጋር ነው በሚለው ላይ ሰፊ ዳሰሳ የተደረገበት ነው። ጥናቱ ተጠናቆ ለተቋሙ የተላከ ሲሆን ከባለድረሻ አካላት ጋር በቅርብ ውይይት የሚደረገበት መሆኑንም አመላክተዋል።

photo content

ግዥ ፈጻሚ መስሪያቤቶች በማእቀፍ ስምምነት የተገዙ እቃዎችን ጥራት አረጋግጠዉ መረከብ እንዳለባቸዉ ተገለፀ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የማእቀፍ እና ስትራቴጂክ ግዥዎችን ለከተማ
+2
ግዥ ፈጻሚ መስሪያቤቶች በማእቀፍ ስምምነት የተገዙ እቃዎችን ጥራት አረጋግጠዉ መረከብ እንዳለባቸዉ ተገለፀ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የማእቀፍ እና ስትራቴጂክ ግዥዎችን ለከተማ አስተዳደሩ መስሪያ ቤቶች የሚፈፅም ሲሆን ግዥዉ የሚፈፀምላቸዉ መስሪያቤቶች የተገዙላቸዉን እቃዎች በሚረከቡበት ወቅት የዕቃዉ ጥራት በፍላጎት መግለጫዉ መሰረት መሆኑን ሊያረጋግጡ ይገባል ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ የዕቃዎችን ጥራት በተመለከተ በተደጋጋሚ የሚነሱ ቅሬታዎችን እና የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመፍታት የቴክኒክ ጥራት ክትትል እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ቡድን ያዋቀረ ሲሆን ከአቅራቢና ግዥ ፈፃሚ ተቋማት ጋርም የዉዉይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አከናዉኗል፡፡ የመድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ እንደገለፁት የመድረኩ ዓላማ ከጥራት ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በተመለከተ በቀጣይ በጀት ዓመት መሰረታዊ መፍትሄ ማስቀመጥን እና አዲስ በተቋቋመዉ የቴክኒክ ጥራት ክትትል ቡድን በተከናወነ ሱፐርቪዥን ሪፖርት ዙሪያ ዉይይት ማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዉይይቱ ላይ የሱፐርቪዥኑን ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ዘላለም አብደላ እንዳብራሩት በ2016 በጀት ዓመት በከተማ አስተዳደሩ ሥር የሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች እና ክ/ከተሞች በማዕቀፍ ግዥ የሚገዙ እቃዎችን ማለትም የፈርኒቸር፣ የአይቲ እቃዎች፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የደንብ ልብስ፤ ጎማ፤ የጽዳት እቃዎች፤ የፕሪንተርና የፎቶ ኮፒ ቀለሞች እና አገራዊና ስትራተጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው ልዩ ግዥዎች ሲፈፀሙ በቀረቡ ናሙናዎች እና የፍላጎት መግለጫዎች መሰረት መሆን እንደሚገባ እና ይህንንም ተቋሙ የመከታተል እና የማረጋገጥ ስራ እንደሚያከናዉን ገልፀዋል፡፡

አገልግሎት የማይሰጡ የኮምፒዉተር እና ተያያዥ ዕቃዎች ከመወገዳቸዉ በፊት አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉባቸዉን ሁኔታዎች ማለፍ እንዳለባቸዉ ተገለፀ ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና
+2
አገልግሎት የማይሰጡ የኮምፒዉተር እና ተያያዥ ዕቃዎች ከመወገዳቸዉ በፊት አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉባቸዉን ሁኔታዎች ማለፍ እንዳለባቸዉ ተገለፀ ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የዋጋ ግመታ እና ማስወገድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጌቱ ተስፋዬ እንደገለፁት አገልግሎት የማይሰጡ የኮምፒዉተር እና ተያያዥ ዕቃዎች አወጋገድን አስመልክቶ በከተማ አስተዳደደሩ ስር የሚገኙ ተቋማት የኮምፒዉተር እና ተያያዥ ዕቃዎችን የይወገድልን ጥያቄ ከማቅረባቸዉ በፊት በባለሙያ የጎደለዉን ዕቃ በማሟላት ለአገልግሎት እንዲዉሉ ማድረግ ወይም ከአንዱ ኮምፒዉተር ወደሌላኛዉ የጎደሉ ዕቃዎችን በመቀያየር ገሚሱን አገልግሎት እንዲሰጥ ማስቻል ሌላዉ እና ሶስተኛዉ አማራጭ ለሌላ ተቋም በስጦታ ማስተላለፍ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም እነዚህን ደረጃዎች አልፈዉ ሊወገዱ የሚገባ ከሆነ አላስፈላጊነታቸዉ በባለሙያ ተፈትሾ እና በበላይ ኃላፊ ተረጋግጦ የይወገድልኝ ጥያቄ ሊቀርብልን ይገባል ብለዋል ፡፡