en
Feedback
AACPPPDS

AACPPPDS

Open in Telegram

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዝና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

Show more
308
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች የሆኑ ያገለገሉ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፣ የቤቶች
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች የሆኑ ያገለገሉ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፣ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች፣ ያገለገሉ ንብረቶች (የተሸከርካሪ ጎማዎች፣ ቸርኬዎች፣ ባትሪዎች፣ ፍላፖች፣ ከነመዳሪዎች) እና የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱ እና ተጠግነው አገልግሎት መስጠት የማይችሉ ኮምፒውተርና ተያያዥነት ያላቸው የኤሌክትሮኒክስ እና የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱ ባዶ የቶነር ካርትሬጆች በማሰባሰብ ፈጭተው መልሶ መጠቀም (Recycle) ለሚችሉ ሀገር በቀል የቶነር አምራች ፋብሪካዎች ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ በግልፅ ጨረታ ባሉበት በሽያጭ ለማስወገድ የጨረታ ማስታወቂያ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቷል፡፡ በዚሁ መሰረት መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቤክ የንግድ ማዕከል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት የጨረታ ሰነድ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ጨረታው ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይከፈታል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-86-71 ይደውሉ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሰት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

photo content

ጥራት ላይ ትኩረት ያደረገ የመንግስት ግዥ የመፍጠር ትጋት በመዲናችን አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች አብዛኞቹ በከተማ አስተዳደሩ በጀት የሚተዳደሩ ናቸው።የተለያዩ ዕቃዎችንና ስትራቴጅክ ግዥዎችን የሚፈጽሙትም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አማካኝነት ነው።አገልግሎቱ ለነዚህ መሥሪያ ቤቶች ባለፈው ዓመት ብቻ 6 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር የተለያዩ ዕቃዎችንና ስትራቴጂክ ግዢዎችን ፈጽሞላቸዋል።ይሄም ተቋማቱ ወጫቸውን እንዲቆጥቡና ጊዚያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከማስቻሉ ባሻገር ጥራታቸው የተጠበቁ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑምአድርጓል። አገልግሎቱ ይሄን ያህል በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ለሚፈስበት ግዥ ጥራት ወሳኝ መሆኑን በማመን የአገልግሎቱ የቴክኒክ ጥራት ማረጋገጥና ግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን መሪ አቶ በቀለ ተባባል ይናገራሉ።ቡድኑ ይሄው ታምኖበት በመጋቢት 2015 በአዲስ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም ያነሳሉ።ቡድኑ ከመቋቋሙ በፊትም አገልግሎቱ ከሚፈጽማቸው እጅግ ግዙፍ ስኬታማ ግዥዎች አንፃር እዚህ ግባ ባይባሉም ሳሙና፤ኮምፒውተር፤የቢሮ መገልገያ ጠረጴዛና ወንበሮች (ፈርንቸር) ግዥ ላይ ከጥራት መጓደል ጋር ተያይዞ በተጨባጭ የገጠሙ ጥቂት ችግሮች ነበሩ። “አቅራቢዎቻቸው የጥራት ደረጃቸውን አስተካክለው መልሰው እንዲያስገቧቸው ተደርጓል” የሚሉት አቶ በቀለ የጥራት ሱፐርቪዥን በየሩብ አመቱ በቋሚ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ እንደሚከናወንም ይጠቁማሉ። ቡድኑ የተቋቋመው በአስፈፃሚ አካላት መልሶ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 74/2014 ለአገልግሎቱ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሰረት መሆኑንም ይጠቅሳሉ። እንደሳቸው ይሄ የዘረጋው አዲስ አሰራር ‘የቴክኒክ ጥራት ክትትል እና የግንዛቤ መፍጠር የውስጥ አሰራር ማንዋል ቁጥር 01/2015’ ተብሎ በመጠቀስ በአገልግሎቱ ውስጥ እየተሰራበት እንደሚገኝም ይጠቁማሉ።እንደነገሩን ይሄ ማንዋል ቡድኑ የሚመራበትም ነው። “በዚህ መልኩ ጥራትን የመቆጣጠር ተግባራችን በቀላሉ የደንበኛ እርካታን ማረጋገጥ ያስችለናል” ይላሉ።ቡድኑ ጥራት ማስጠበቅና ግንዛቤ ማስጨበጥ ሁለት ተግባራት እንደሚያከናውንም ያወሳሉ።ሁለተኛው ተግባሩ ጥራት ነክ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራት ላይ ያተኩራል።ይሄው ቡድን ተጠሪነቱ ለአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ነውም ይላሉ።ቡድን መሪው ወደ ዝርዝር ተግባሩ ሲገቡ ሥራውን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር የቴክኒክ ጥራት ክትትል የስራ ክፍል ቋሚና ድንገተኛ የጥራት ሱፐርቪዥን የሚያከናውንበት ሁኔታ መኖሩን ያስረዳሉ። እንደማብራሪያቸው ለአገልግሎቱ በሚቀርቡ ጥራት ነክ ቅሬታዎች እና ጥቆማዎች ላይ በመመስረት ድንገተኛ የመስክ ምልከታ ይካሄዳል።በተለይ ውል በተገባባቸው ዕቃዎች ላይ የጥራት ፍተሻ በአቅራቢው የምርት ማከማቻ እና በተጠቃሚ መሥሪያ ቤቶች በአካል በመገኘት ይከናወናል።እንዳከሉት ሆኖም አገልግሎቱ በሚፈፅማቸው አንዳንድ ስትራቴጂክ ግዥዎች ላይ ከግዥዎቹ ልዩ ባህርይ የተነሳ በአገልግሎቱ ብቻ የጥራት ክትትል አይደረግባቸውም።አገልግሎቱ ታድያ በነዚህ ግዥዎች አፈጻጸም ዙሪያ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመተባበር የጥራት ሱፐርቪዥን (ቁጥጥርና ፍተሻ) የሚያከናውንበት ሁኔታ አለ። እንደ አስፈላጊነቱ ልዩ ሙያዊ ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው እቃዎች፤ምክርና ምክር ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶችና ልዩ ልዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ከሌሎች ተቋማት ድጋፍ የሚሰጡ ባለሙያዎች እንዲካተቱ የሚደረግበት አሠራርም ተመቻችቷል። ውል ከተገባ በኋላ የሚከናወን የጥራት ማረጋገጥ ተግባራትን አስመልክተውም ቡድን መሪው አቶ በቀለ በጨረታ ሰነድ ላይ በተገለፀው የጥራት መግለጫ (Specification) መሰረት እና ናሙና ገቢ መደረጉን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ይጠቅሳሉ።በዚህ ጊዜ አቅራቢው በጨረታ ሰነድ ላይ በተቀመጠው የፍላጎት መግለጫ መሰረት እያቀረበ መሆኑን ማረጋገጥ ግድ እንደሆነም ያነሳሉ።ከአገልግሎቱ ጋር ውል ገብተው አቅርቦት በሚፈፅሙ አቅራቢዎችና ተጠቃሚ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የጥራት ክትትል ሱፐርዥን በመደበኛ የጊዜ ሰሌዳ እና በልዩ ሁኔታ የሚከናወንበት አግባብም ውል ከተገባ በኋላ ያለውን የተግባር አፈፃፀም ይካተታል። እንደዚሁም ውል የተገባባቸው እቃዎች፤ምክርና ምክር ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶችንና ሌሎች ስራዎች ግዥዎችን የጥራት ሁኔታ በተለያዩ ዘዴዎች በመጠቀም ፍተሻ በማድረግ ጥራት ማረጋገጥ ውል ከተገባ በኋላ የሚከወን ነው።በተለያየ ወቅት በአቅራቢዎች የሚቀርቡ የሞዴልና የብራንድ ለውጥ ጥያቄዎችን ተቀብሎ ይመረምራል ውጤቱንም ለዋና ስ/አስኪያጅ ያሳውቃል ተገቢውን ምላሽም ያዘጋጃል።ከተጠቃሚ መስሪያ ቤቶች የሚቀርቡ ጥራትን የሚመለከቱ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ምላሽ መስጠትም ቡድኑ የግዥ ውል ከተገባ በኋላ የሚያከናውናቸው ተግባራት እንደሆኑ አቶ በቀለ ያብራራሉ። እንዳከሉት አገልግሎቱ በፈፀማቸው የተለያዩ ስትራቴጅክ ግዥዎች ርክክብ ወቅትም ሥራውን የሚሰራበት አግባብ አለ።በቴክኒክ መግለጫው መሰረት ፕሮጀክቱን ወይም ስትራቴጅክ ግዥውን ከሚመለከተው መሥሪያ ቤት ጋር በመተባባርም የጥራት ማረጋገጥ ስራ ማከናወኑ ማሳያ ነው።እንደ ቡድን መሪው አቶ በቀለ ማብራሪያ እነዚህ ለማሳያ ይጥቀሱ እንጂ ቡድኑ ጥራቱ የተረጋገጠ ግዥ እንዲፈፀም ለማስቻል በብዙ መልኩ የጥራት ፍተሻ እና ምርመራ ይከናወናል። ይሄም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት ሲሆን ቀዳሚው የደንበኞችን እርካታ በማረጋገጥ በ2015ዓ/ም ከነበረበት 73 በመቶ በ2016 ዓ/ም 80 በመቶ እና በላይ ማድረስ እና መንግስት እና የሚያገለግለው ህብረተሰብ ስትራቴጅካዊ ጠቀሜታ ማስገኘት ነው ። የውስጥ አደረጃጀት መልሶ በመከለስ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት ማስቻሉ ሌላው ሲሆን ግልጽ፣ ፍትሀዊ፣ ተደራሽ፣ ጥራትና ተጠያቂነት ያለው አገልግሎት መስጠት ማስቻሉም አንዱ ነው።በአጠቃላይ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተቀላጠፈ የግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የውስጥ አደረጃጀት የመፍጠር ጠቀሜታ ሰንቋል።ከጥራት ፍተሻው ጎን ለጎንም በቡድኑ ስር ወጥ የሆኑና በጥራት ዙሪያ የተፈጠሩ የግንዛቤ ክፍተቶችን በመለየት ድጋፍ የሚያደርግበት አሰራር ዘርግቶም የከተማ አስተዳደሩን የግዥ ስርዓት ለማሳለጥ እየተጋ መገኘቱን ገልፀዉ በቀጣይ አቅራቢቢቹም ሆነ ተጠቃሚ መ/ቤቶች የተከናወኑ ግዥዎችን ርክክብ በሚያደርጉበት ወቅት በተቀመጠው የውል አግባብ ጥራትን አረጋግጠው መሆን እንዳለበት በማሳሰብ ይህ ሳይሆን ቢቀርና በተለያዩ የክትትል መረሃ ግብሮች እነዚህ ችግሮች ሲገኙ በአቅራቢዎች የሚወሰደው የጥፋተኝነት እርምጃ እንደ ተጠበቀ ሆኖ ተጠቃሚ መ/ቤቶችም የሚጠበቅባቸውን ባለመወጣት ለወደፊት በሚዘጋጅ የቅጣት ማዕቀፍ የሚጠየቁ መሆኑን በማሳሰብ ሀሳባቸዉን ያሳርጋሉ።

የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በቁጥር 02/2016 ዓ.ም የተቋማት ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች ላይ ተወዳድረው 1ኛ የወጡ ተጫራቾች

የአገልግሎቱ ዓመራሮች እና ሠራተኞች 16ኛውን የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ 05/02/2016 ዓ.ም *አዲስ አበባ* በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት
+2
የአገልግሎቱ ዓመራሮች እና ሠራተኞች 16ኛውን የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ 05/02/2016 ዓ.ም *አዲስ አበባ* በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት '' የሠንደቅ አላማችን ከፍታ ለሕብረብሔራዊ አንድነታችንና ሉዓላዊነታችን ዋሥትና ነው '' በሚል መሪ ቃል 16ኛውን የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንን በድምቀት አክብሯል ። መርሀግብሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ዝሙር በጋራ በመዘመር የተጀመረ ሲሆን የሰንደቅ አላማ ቀንን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ መንግስቱ አጥናፉ እንደተናገሩት ሠንደቅ አላማ ታላቅ ሀገራዊ መስዕዋትነትን የከፈልንበት የሕብረ ብሔራዊነታችን መገለጫ፣ የአንድነታችን ምንጭ መሆኑ ገልፀው በተጨማሪም የኢትዮጵያዊነታችን መገለጫ ምልክት ነው ብለው አክለውም ልጆቿ በዘመናት ተጋድሎ ፀንታና ተከብራ የኖረች ሀገራችን ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ በክብርና በተሻለ የእድገት ደረጃ ለማሸጋገር፣ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በተሰለፈበት የሥራ መስክ ጠንክሮ መሥራትና ሀገራዊ አንድነትን የሚሸረሽሩ አፍራሽ ድርጊቶችን በጋራ መከላከል ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ በዕለቱ የሠንደቅ አላማ ቀንን እና የሠንደቅ አላማ ምንነትን አስመልከቶ ለውይይት የሚሆን ሠነድ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሠነድ ላይም ውይይት ተደርጓል ። ዘገባው፡- የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።

Tender Reference No.:- AAPPPDS/FA/NCB/PG/45/1/2016 Addis Ababa City Administration Public Procurement and Property Disposal Service (AAPPPDS) has funds with the procuring entity’s budget to be used for the Procurements Different types of Printer and Photocopy Machine Toners for Addis Ababa City Administration Budgetary Public Bodies with the framework agreement contract for Two Years starting from signing of the contact agreement. Therefore, AAPPPDS invites interested eligible bidders for the supply and delivery of the following goods & related services. Lot No. Lot- 1 Items - Different types of Printer and Photocopy Machine Toners Amount of Bid Security in ETB 500,000.00 1. A complete set of bidding documents in English shall be purchased by interested bidders upon payment of non-refundable fee of Birr 700.00 (Seven hundred Birr). 2. Documents will be issued at Addis Ababa City Administration Public Procurement and Property Disposal Service, Finance Directorate which is found at 6th floor, room no. 606, starting from October 12/ 2023 G.C from 8:30 AM to 5:30 PM. It will be floated for 20 /Twenty/ consecutive days. 3. Bid must be delivered on or before November 1/2023 G.C, 11:00 AM at 9th floor, Assembly Hall. 4. Bid will be closed on November 1/2023 G.C at 11:00 AM and will be opened at the same day; November 1/2023 G.C at 11:30 AM.at 9th floor, Assembly Hall. 5. AAPPPDS reserves the right to reject the bid partially or in full. 6. Address: Mexico Sengatera, behind St. Mary University College, located at Yobek Commercial center. Telephone: 251-0118- 26-62-35/ 251-0115-57-81-26 Addis Ababa, Ethiopia

photo content

የጨረታ መለያ ቁጥር፡ AAPPPDS/FA/NCB/PG/45/1/2016 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለአዲ ስአበባ ከተማ አስተዳደር ባለበጀት መስሪያ ቤቶች
የጨረታ መለያ ቁጥር፡ AAPPPDS/FA/NCB/PG/45/1/2016 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለአዲ ስአበባ ከተማ አስተዳደር ባለበጀት መስሪያ ቤቶች በማዕቀፍ ውል ስምምነት ግዥ የተለያዩ የፐሪንተርና የፎቶ ኮፒ ማሽኖች ቀለም (Different types of Printer and Photocopy Machine Toners) ዕቃዎች ግዥ ሀገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መፈጸም ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ከጥቅምት 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ድረስ ባሉት 20 ተከታታይ ቀናት ሰንጋ ተራ በሚገኘው ዩቤክ ኮሜርሻልሴ ሴንተር ህንፃ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በአካል በመቅረብ የማይመለስ 700 /ሰባት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ጨረታው ጥቅምት 21/2016 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት ከረፋዱ 5፡30 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት 9ኛ ፎቅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር+251- 11-557-81-26/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

የአዲስ.አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች የሆኑ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች በሽያጭ ለ
+5
የአዲስ.አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች የሆኑ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች በሽያጭ ለማስወገድ ጨረታ መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማዉጣቱ ይታወቃል ፡፡ በዚሁ መሰረት ጨረታው ጥቅምት 1 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ በመዝጋት በዕለቱ 4፡15 ላይ የመክፈት ስነስርዓት ተከናዉኗል ፡፡

NOTICE Addis Ababa city Administration Public Procurement and property Disposal Service floated international competitive bid
+1
NOTICE Addis Ababa city Administration Public Procurement and property Disposal Service floated international competitive bid with the objective of procuring supply of different types of stationary items with framework agreement for three (9) budget year on the behalf of on the consumption of public bodies . Therefore the Financial Bid Evaluation result of the bidders is attached below .

በአገልግሎት ምንነት፣ የደንበኛ አያያዝና አገልግሎት ስታንዳርድ ዙሬያ ስልጠና ተሰጠ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በርካታ አገልግሎት ሰጪ ከሆኑ ተቋማት ዉስጥ አንዱ የሆነዉ የመንግስት ግዥ
+1
በአገልግሎት ምንነት፣ የደንበኛ አያያዝና አገልግሎት ስታንዳርድ ዙሬያ ስልጠና ተሰጠ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በርካታ አገልግሎት ሰጪ ከሆኑ ተቋማት ዉስጥ አንዱ የሆነዉ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ነዉ፡፡ ተቋሙ የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻሻለ የመጣ ሲሆን ስልጡን ዘመናዊና የተገልጋዮችን እርካታ ማዕከል ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት በርካታ ተግባራትን እያከናወነም ይገኛል ፡፡ ስልጠናዉም የዚሁ እንቅስቃሴ አንድ አካል መሆኑ ተጠቅሷል ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልገሎት ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ከተገልጋዩ ህብረተሰብ ጋር መልካም ግንኙነት መፍጠር፣ይቻል ዘንድ የአገልግሎት ምንነት፣ ደንበኛ አያያዝና አገልግሎት በተመለከተ ለተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች የግናዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናን አከናዉኗል፡፡ ስልጠናዉ በአገልግሎት ምንነት፣ በደንበኛ አያያዝ ፣ በደንበኞች አገልግሎት መርሆዎች እና መሰል ፅንሰ ሀሳቦች ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን ፡፡ በስልጠናዉ ተቋሙ ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ከተገልጋዩ ህብረተሰብ ጋር መልካም ግንኙነት መፍጠር፣ ተገልጋዮችን እንደ ባህሪያቸው ማስተናገድ፣ ከተገልጋይ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ትኩረት ሰጥቶ መፍታት፣ ቀጣይነት ያለው መሻሻል ሊያመጣ የሚችል ስልት መዘርጋት ወይም መተግበር እና በየደረጃው የሚገኙ ሰራተኞች ስራ መስራት የሚያስችል ስልጣን፣ ልምድ፣ ብቃት እና ድጋፍ የሚያገኙበት አሰራር መፍጠር አስፈላጊ መሆኑ ተወስቷል፡፡ ተቋማትም የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በምን መልክና ሁኔታ ለተገልጋዩ ማድረስ እንደሚችሉ የሚያመለክት ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ለተገልጋዮች እሴት የሚጨምር መሆኑን በመድረኩ ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት ለተለያዩ ዓላማዎች ሲባል ይከናወናል።በተለይ ሀገራችንን ጨምሮ ዓለማችን በምጣኔ ሀብት መዋዠቅና በዋጋ ግሽበት አጣብቂኝ ውስጥ በገባችበት በአሁኑ ሰዓት ለብዙ ዓላማ ሲባል ሊደረግ እንደሚችል የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ። በኢትዮጵያ በንግዱ ማህበረሰብ ዘንድ በቅርብ የተደረገ አንድ ጥናት እንደሚጠቁመው በተለይ በዚህ ዓይነቱ አጣብቂኝ ወቅት ዝቅተኛውን ሕብረተሰብ ከዋጋ ግሽበት ለመታደግ ሊደረግ የሚችልበት አጋጣሚ አለ። ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ይከናወናል።እየተከናወነ የሚገኘው ለተለያየ ዓላማ መሆኑን ከአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የአገልግሎቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የገበያ ጥናትና ማስወገድ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ በአገልግሎቱ ወቅታዊ የገበያ ጥናት በዋነኝነት ለተለያዩ የግዥና ሽያጭ ሥራዎች ዓላማ ሲባል የሚከናወንበት ሁኔታ እንዳለ ይናገራሉ።በተጨማሪም የግዥ ጣሪያ ወይም ገደብን ለማስቀመጥ፤ ለፋይናንስ ግምገማና የዋጋ ማሻሻያ ውሳኔዎችን ለመወሰን እንደሚካሄድ ያክላሉ። ኃላፊዋ ስለ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት አሰራር ሂደት ሲያብራሩም የተለያዩ ዕቃዎችን፤ አገልግሎቶችን፤ የግንባታ ግብዓቶችን ተንተርሶ ሊሰራ ይችላል ይላሉ።እንደሳቸው የሚሰራው በየወቅቱ በተለያዩ የገበያ ቦታዎች በመገኘት ዋጋቸው ምን ያህል መሆኑን መረጃ በመሰብሰብና በመተንተን ነው።ሥራው ጨረታ በወጣ ቁጥር የሚካሄድም ነው። ጨረታው ደግሞ በዓመት አራቴና ስድስቴ ሊወጣ ይችላል።በጥቅሉ የሚሰራው እንደ አለው ወቅታዊ የሥራ እንቅስቃሴ ሲሆን ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የግድ የገበያ ጥናት መካሄድ አለበት ሲሉም ያስረዳሉ። እንደ ኃላፊዋ የገበያ ጥናት ሲሰራ የሚያስፈልጉ ዝርዝር መረጃዎችን ይዞ መሄድ ይጠይቃል።ለሽያጩ ወይም አገልግሎት ሰጪው የሚሰጥ ደብዳቤ አንዱ ነው።በመሆኑም አገልግሎቱ ይሄንኑ በመያዝ አዲስ አበባ ከተማ ላይ 12 ያህል እየተዘዋወረ ገበያ የሚያጠናባቸው አካባቢዎች ይተማል።ለአብነት ፒያሳ አካባቢና ሜክሲኮ እንደ አንድ የገበያ ቦታ በመውሰድ እየሰራባቸው ካሉት ይጠቀሳሉ። መርካቶና ተክለሐይማኖት አካባቢ እየሰራባቸው ካሉ ሌሎቹ የገበያ ቦታዎች ይካተታሉ።እንደዚሁም ሌሎች አገልግሎቱ የገበያ ጥናት እያካሄደባቸው የሚገኝ የገበያ ቦታዎች አሉ። በጥናቱ ወቅት የሚፈልገውን መረጃ የሚጠይቃቸው አካላት የጅምላ እና የችርቻሮ ነጋዴዎችን እንደሆነም ያነሳሉ። በገበያው የሚጠይቁት ዋጋ በዛው መረጃውን እየሰበሰቡ ባሉበት ዕለት ያለውን እንደሆነም ያክላሉ።አሁን በሀገራችን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የገበያ ዋጋ በፍጥነት የሚለዋወጥበት ሁኔታ አለ። በዚህ ወቅት ደግሞ የተረጋጋ ዋጋ ማግኘት ያስቸግራል። ኃላፊዋ ቢሆንም መሰረቱን ስለማይለቅ ብዙም የሚያመጣው ልዩነት እንደማይኖር ይናገራሉ።ምክንያቱ ደግሞ 11 የገበያ ቦታ ተደራሽ አድርጎ ከሰበሰበው የተወሰኑት ትክክለኛ የገበያ ዋጋ መረጃ ሊሰጡት ይችላሉና ነው።ታድያ ይሄን ወደ ቀመር አስገብቶ ትክክለኛውን ዋጋ በመስራት ሊፈጠር የሚችለውን ችግር ቀድሞ ይከላከላል። ሆኖም አንድ ብር የሚሸጠውን ዕቃ ዝርዝሩን በሙሉ ማንበብ ሰልችቶት አምስት ብር ነው ብሎ የሚሞላ ሰው ሊኖር ይችላል።አገልግሎቱ ይሄን ግዜ አይ አምስት ብር ከሆነ ዋጋው አንድ ብር መሸጡ ወይም አንድ ብር ሆኖ ዋጋው አምስት ብር መሸጡ ልክ አይደለም ብሎ ጨረታ ሊሰርዝ የሚችልበት ሁኔታ ይፈጥራል።መጓተቶች ሊመጡ የሚችሉበትም ይከሰታል። ጨረታ በአብዛኛው ሊሰረዝ የሚችለው ትክክለኛ መረጃ ባለማግኘት ነውም ይላሉ። ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት ለማድረግ የሚያሰችለውን ሕጋዊ ደብዳቤ ለንግድ ድርጅቱ ወይም ለአገልግሎት ሰጪው ተቋም የሚሰጥበት ሁኔታ መኖሩን ያስታውሳሉ። በዚህ ወቅት ታድያ ቀና ትብብር አለማድረግ፤የመታከትና በወቅቱ ያለውን ዋጋ ያለመስጠት ችግር እንደሚስተዋልም ይገልፃሉ። በምሳሌ እንደሚያስረዱት በገበያው አገልግሎቱ የሚፈልጋቸው ዕቃዎች ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ። ሆኖም ዕቃዎቹ የዋጋ ዝርዝራቸው የተለያየ ይሆናል። ለአብነት ላፕቶፕን ብንወስድ ኮራይ3 እና ኮራይ5 የተለያዩ ናቸው።አንዳንዴ ታድያ አገልግሎቱ ከንግዱ ማህበረሰብ ላፕቶፕ መሆኑን ብቻ እንጂ የትኛው ዓይነት ላፕቶፕ እንደሆነ በዝርዝር ማየት ላይ ችግር ያጋጥመዋል።ትክክለኛውን መረጃ መስጠት ላይም ብዙ ክፍተቶች ይገጥማሉ። ትክክለኛ መረጃ አለመስጠት፤ቀና ትብብር አለማድረግና መረጃ ሰብሳቢው አካል ተመልሶ እንዳይመጣባቸው ዓይነት የሚመስል የተሰላቸ የውሸት መረጃ መስጠት ከሚገጥሟቸው ይጠቀሳሉ። ነገር ግን ትክክለኛ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት ብዙ ፋይዳዎች እንዳሉት መረዳት እንደሚያስፈልግም ያወሳሉ። ‹‹በአገልግሎቱ በርካታ የመንግስት ግዥዎች ይፈፀማሉ።ወደ እዚህ ግዥ ከመገባቱ በፊት የግድ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት መካሄድ እንዳለበትም ይጠቅሳሉ።የሚሰበሰበው እና የሚተነተነው ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ውሳኔዎችን ለመወሰን እንደሚረዳም ያስገነዝባሉ። እንዳከሉት ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መረጃ የመሰብሰብም ሆነ የመተንተን ስራ በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ መከናወን ያለበት ተግባር ነው።በመሆኑም ለዚህ ተግባር የሚያገለግል መረጃ ነጋዴዎች ሲጠየቁ በከፍተኛ የትብብር እና የኃላፊነት መንፈስ ትክክለኛውን ወቅታዊ መረጃ ሊሰጡ ይገባል። መረጃው በግዴለሽነት እና በተሳሳተ መልኩ መሰጠቱ ብዙ ችግሮችን እንደሚያስከትልም ያነሳሉ። ይሄ ዓይነቱ መረጃ ለነጋዴውም ሆነ ለአገር ከፍተኛ የውሳኔ መዛባት ችግር ያስከትላል ይላሉ።የጉልበት፤የጊዜና የኃብት ብክነት በማስከተል በእያንዳንዱ ዜጋ ላይ ጫና የሚፈጥር እንደሆነም ያስረዳሉ። በመሆኑም ‹‹አገልግሎቱ እያገለገለ ያለው ሕዝብን ነው››የሚሉት ኃላፊዋ ወይዘሮ መቅደስ የንግዱ ማህበረሰብ ትክክለኛውን የዕቃዎች ዋጋና መረጃ በኃላፊነት ስሜት የመስጠት ዜግነታዊና ህሊናዊ ኃላፊነትና ግዴታ እንዳለበት ያሳስባሉ።ትክክለኛውን የዋጋ መረጃ በትክክለኛው ወቅት እንዲሰጥና ለመስጠትም ቀና ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን በማስተላለፍ ያካፈሉንን ሀሳብ ቋጭተዋል።

የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያዎች ጨረታ የፋይናንስ መክፈቻ ስነ-ስርዓት
+3
የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያዎች ጨረታ የፋይናንስ መክፈቻ ስነ-ስርዓት

በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተከናወነ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክ
+1
በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተከናወነ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለለተቋሙ አመራሮች እና አጠቃላይ ሰራተኞች በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አከናወነ፡፡ መርሀ ግብሩ የአገልገሎቱ ም/ስራ አስኪያጅ በሆኑት አቶ መርቆ ብርሌው የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በንግግራቸዉም እንደ ጠቆሙት ሙስና እና ብልሹ አሰራር ሁሉንም የሚነካ፣ የመፈፀሚያ መንገዱም የሚለዋወጥ እና እየተቀያየረ የሚሄድ ልንታገለዉ የሚገባ ወንጀል ነው ብለዋል ፡፡ በዕለቱ ስልጠናዉን የሰጡት በስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳ/ሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘላለም አብደላ እንደገለፁት በ2016 በጀት ዓመት እንደ ተቋም ለሙስናና ብልሹ አሰራር ሊያጋልጡ የሚችሉ የአሰራር ስርዓቶችን በማጥናት የመፍትሄ እርምጃዎች የሚወሰዱ መሆኑን ያብራሩ ሲሆን ስልጠናው በአዋጅ ቁጥር 75/2014 እንዲሁም በሙስና ፅንሰ ሀሳብና መከላከያ ስልቶች ላይ ግንዛቤ መፍጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት አስቀድሞ ለመከላከል እንዲቻል እንዲሁም በጋራ መስራት፤ ራስን ከሙስናና ብልሹ አሰራር ማራቅና ሙስናን የማይሸከም ሹመኛ አመራር፣ ኃላፊና ሰራተኛ መፍጠርን ዓላማ ያደረገ መሆኑን አክለዉ ገልፀዋል ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የ Supply, Installation, and Implementation ERP Platform System ግዥ የቅድመ ጨረታ ው
+1
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የ Supply, Installation, and Implementation ERP Platform System ግዥ የቅድመ ጨረታ ውይይት መድረክ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮቻችንን በመቀላቀል የተለያዩ መረጃዎችን ፣ የጨረታ ማስታወቂያዎችን የጨረታ ዉጤቶችን እ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮቻችንን በመቀላቀል የተለያዩ መረጃዎችን ፣ የጨረታ ማስታወቂያዎችን የጨረታ ዉጤቶችን እና የጨረታ አሸናፊዎችን ዝርዝር ይመልከቱ ! አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ! YouTube - https://www.youtube.com/@pppdstube Telegram - https://t.me/AACPPPDS Facebook - https://www.facebook.com/AAPPPDS Twitter - https://twitter.com/aapppds

የንግዱ ማህበረሰብ በተቋማችን ለሚከናወኑ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናቶች ትክክለኛዉን የዕቃዎች ዋጋና መረጃ በኃላፊነት ስሜት ሊሰጡ እንደሚገባ ተጠቆመ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት የተለያዩ እቃዎችን ፣ አ
የንግዱ ማህበረሰብ በተቋማችን ለሚከናወኑ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናቶች ትክክለኛዉን የዕቃዎች ዋጋና መረጃ በኃላፊነት ስሜት ሊሰጡ እንደሚገባ ተጠቆመ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት የተለያዩ እቃዎችን ፣ አገልግሎቶችን እና ግንባታዎች ወይም የግንባታ ግብዓቶች በየወቅቱ በተለያዩ የገበያ ቦታዎች በመገኘት ዋጋቸው ምን ያህል መሆኑን መረጃ በመሰብሰብና በመተንተን የሚሰራ ነው ሲሉ የገለፁት የአገልግሎቱ ም/ስ/አስኪያጅና የገበያ ጥናት እና ማስወገድ ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ አክለዉም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናት ለተለያዩ ዓላማዎች የሚከናወን ሲሆን በዋነኝነት በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለተለያዩ የግዥና ሽያጭ ስራዎች የግዥ ጣሪያ ወይም ገደብን ለማስቀመጥ ፣ለፋይናንስ ግምገማ እና ለዋጋ ማሻሻያ ውሳኔዎችን ለመወሰን የሚረዳ በጥናት የተደገፈ መረጃ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ የሚሰበሰበው እና የሚተነተነው ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ውሳኔዎችን ለመወሰን የሚረዳ በመሆኑ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መረጃ የመሰብሰብም ሆነ የመተንተን ስራ በከፍተኛ የሓላፊነት መንፈስ መከናወን ያለበት ተግባር በመሆኑ ለዚህ ተግባር የሚያገለግል መረጃ ነጋዴዎች ሲጠየቁ በከፍተኛ የትብብር እና የሃላፊነት መንፈስ ትክክለኛውን ወቅታዊ መረጃ ሊሰጡ እንደሚገባ በመግለፅ መረጃው በግዴለሽነት እና በተሳሳተ መልኩ የሚሰጥ ከሆነ ለነጋዴውም ሆነ ለአገር ከፍተኛ የውሳኔ መዛባት ችግር በመፍጠር የጉልበት፤ የጊዜና የሃብት ብክነት በማስከተል በእያንዳንዱ ዜጋ ላይ ጫና የሚፈጥር ነውም ተብሏል ፡፡ ስለሆነም የንግዱ ማህበረሰብ በዚህ ዙሪያ ለሚከናወኑ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ጥናቶች ትክክለኛዉን የዕቃዎች ዋጋና መረጃ በኃላፊነት ስሜት ሊሰጡ እንደሚገባ ጠቁሟል

photo content

ኢትዮጵያ የመደጋገፍ ፣ የመረዳዳት እና የመተዛዘን ምሳሌ ናት ! በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የበጎነትን ቀንን በመረዳዳት እና በመደጋገፍ መንፈስ በበ
+2
ኢትዮጵያ የመደጋገፍ ፣ የመረዳዳት እና የመተዛዘን ምሳሌ ናት ! በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የበጎነትን ቀንን በመረዳዳት እና በመደጋገፍ መንፈስ በበርካታ ተግባራት አሳለፉ ። ጳጉሜ 3 የበጎነት ቀንን አስመልክቶ መርሀ ግብሩን በእንኳን አደረሳችሁ አጭር ንግግር የከፈቱት የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ በንግግራቸው እንደጠቆሙት ኢትዮጵያውያን ዘመን የተሻገረ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን ገልፀው ያለንን ማካፈል የአብሮነታችን ሚስጥር የበጎነት ማሣያ ነው '' ሀገራችንም የዚህ በጎ ተግባር ምሳሌ ናት ብለዋል ። '' ዕለቱንም ከ 30 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች እና የተለያዩ ዝቅተኛ የገቢ ምንጭ ላላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የገንዘብ እና የምግብ ግብዓቶችን በመለገስ አክብረውት አልፈዋል ። በመጨረሻም ዋና ስራ አስኪያጁ በጎነት ለአንድ ቀን የሚከናወን ተግባር ሳይሆን እለት ተዕለት ልንፈፅመው የሚገባ የተቀደሰ ተግባር ነው ሲሉ ጠቁመው መጪው አዲስ አመትም የበለጠ የምንተሳሰብበት የምንረዳዳበት እና እንዲሁም የሠላም እና የብልፅግና ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል ።