en
Feedback
WeMind Ethiopia

WeMind Ethiopia

Open in Telegram

Comprehensive Mental Health Resources Across Ethiopia

Show more
1 193
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1030 days
Posts Archive
የዶ/ር ግርማ ትምህርቶች 01 ዶ/ር ግርማ ስለሱስ የተናገሩት ■ ማንም ሰው ሱሰኛ ለመሆን አቅዶ ሱስ አልጀመረም! ■ ሱስ መጥፎ ነው -- የሚያሳይህ የሚያብረቀርቀውን ነው፡፡ ■ የሱስ አደገኝነቱ እየ
የዶ/ር ግርማ ትምህርቶች 01 ዶ/ር ግርማ ስለሱስ የተናገሩት ■ ማንም ሰው ሱሰኛ ለመሆን አቅዶ ሱስ አልጀመረም! ■ ሱስ መጥፎ ነው -- የሚያሳይህ የሚያብረቀርቀውን ነው፡፡ ■ የሱስ አደገኝነቱ እየገደለህ እንኳን ክፋቱን እንዳታይበት ያደርግሀል፡፡ ■ ሱስ አእምሮህን ይቆጣጠረህና ለእኔ ብቻ ቅድሚያ ስጠኝ ይልሀል፡፡ ■ “ሰቀለ” ሲባል ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? … ልብስ መስቀያን አስቡት፡፡ አንድ ቀጭን ብረት ወይም እንጨት ላይ ልብሳችሁን ትሰቅሉበታላችሁ፡፡ አንድ ሱሰኛ “ሰቀለ” የሚባለው በሱሱ ምክንያት ከስቶ ከስቶ በአጥንት እና ቆዳ ብቻ ሲቀር ነው፡፡ ልብስ መስቀያ፡፡ አንድ እንዲሁ “ሰቃይ” የተባለለት ደንበኛዬ እንዲህ አለኝ፡፡ “‹ሰቀለ› መባል አሪፍነት ይመስለኝ ነበር፡፡ አሁን ሲገባኝ አሪፎቹስ የማይጠቀሙት ነበር”…. (ወረድ ባለ ድምጽ) የሚያሳዝነው ይህ ደንበኛዬ ከባነነ በኋላ ብዙ አብሮኝ መቆየት አልቻለም (አረፈ) ■ አእምሮህ የሱስ ጊዜያዊ ጥቅሙን ሊያስታውስ ይችላል፡፡ አንተ ግን ጉዳቱን አስብ፡፡ አንድ የምትወደው ምግብ ቀርቦልህ ቆሻሻ ብታገኝበት ትጥለዋለህ፡፡ ሱስን ከጊዜያዊ ጥቅሙ ይልቅ ቆሻሻነቱን አስታውስ፡፡ የተፋኸውን ምራቅ መልሰህ አትውጠውም፡፡ ያወጣኸውን ሱስ መልሰህ እንዳትገባበት፡፡ ■ ሱስን መውሰድ ያለብህ እንደ አለርጂ ነው- ከነካኸው ይቀሰቀስብሀል፡፡ አየህ ማኖ መንካት የለብህም፡፡ በተቻለ መጠን ራስህን ሱስ በሚገኝባቸው ቦታዎች እያዞርክ ራስህን አትፈታተነው፡፡

ጥቂት ወንበሮች ቀርተዋል በ0955346528 ወይም https://forms.gle/TVLJScFMPbf9MYG97 ቶሎ ይመዝገቡ መግቢያ #በነጻ
ጥቂት ወንበሮች ቀርተዋል በ0955346528 ወይም https://forms.gle/TVLJScFMPbf9MYG97 ቶሎ ይመዝገቡ መግቢያ #በነጻ

ራስህን አክብር ራስህን ካላከበርክ ማንም ሰው እንደማያከብርህ እወቅ፡፡ ራስህን ማክበርህን ለማወቅ ስለ ራስህም ሆነ ስለ ሃገርህ ሰዎች፣ ስለ ወገኖችህ የምትናገረውን ንግግር አጢነው፡፡ ራስህን ሳታከብ
ራስህን አክብር ራስህን ካላከበርክ ማንም ሰው እንደማያከብርህ እወቅ፡፡ ራስህን ማክበርህን ለማወቅ ስለ ራስህም ሆነ ስለ ሃገርህ ሰዎች፣ ስለ ወገኖችህ የምትናገረውን ንግግር አጢነው፡፡ ራስህን ሳታከብር ወገንህን ልታከብር አትችልም፡፡ ወገኑን የናቀ ሰው በቅድሚያ የናቀው ራሱን ነው፡፡ በሌላ ጎኑ፣ አለባበስህ፣ ለራስህ የምትሰጠው ትኩረት፣ የምትገኝባቸው ስፍራዎች፣ የምትመርጣቸው የጓደኛ አይነቶች ለራስህ የሰጠኸው ዋጋ ምልክቶች ናቸው፡፡ ንጹህ ነኝ ብለህ እያሰብክ ቆሻሻ ቦታ ራስህን ልታገኘው አትችልም፡፡ ጨዋ ነኝ ብለህ እያሰብh ራሳቸውን ከተራ ነገር ለማውጣት ከማይፈልጉ ሰዎች ጋር ማሳለፍ አትችልም፡፡ የምታደርጋቸው ነገሮች ሁሉ ለራስህ የሰጠኸው ዋጋ ነጸብራቆች ናቸው፡፡ “ለራሳችን ያለንን ክብር አሳልፈን ካልሰጠናቸው በስተቀር ሰዎች ሊወስዱብን አይችሉም” - Mahatma Gandhi ይህንን አትዘንጋ፡- ሰዎች ከሰጠሃቸው መብት የበለጠ ምንም አይነት መብት በአንተ ላይ ሊኖራቸው አይችልም፡፡ እንዳይንቁህ ማድረግ አትችልም፣ ራስህን በማhበር ግን ንቀታቸውን ቦታ ልታሳጣው ትችላለህ፡፡ ስለአንተ ክፉ እንዳያወሩ ማድረግ አትችልም፣ ያወሩትን ክፉ ነገር ተቃራኒ በመኖር ግን ወሬአቸው ውሸት እንደሆነ የማሳየትን መብትህን ግን ሊወስዱብህ አይችሉም፡፡ አብረሃቸው ለማሳለፍና በማንነትህ ላይ ተጽእኖ እንዲያመጡ የፈቀድhላቸው ሰዎች ብቻ በማንነትህ ላይ ያለህን አመለካከት ይወስናሉ፣ ይህንን ደግሞ መቆጣጠር ትችላለህ፡፡

Understanding the Effects of Marijuana on the Youth -------------- Exciting Announcement for Parents/Teachers Sitota Center f
Understanding the Effects of Marijuana on the Youth -------------- Exciting Announcement for Parents/Teachers Sitota Center for Mental Health Care is pleased to bring attention to a pressing concern affecting today's youth – the alarming rise in adolescent marijuana use. Recognizing the significant impact on the health of our young individuals, we are thrilled to announce an upcoming workshop: Date: March 09 [የካቲት 30] Time: 10:00-12:00 Local Time This enlightening session will be led by distinguished and experienced psychiatrists in the field. This invaluable workshop is an excellent opportunity for parents, guardians, and educators to equip themselves with the knowledge and tools necessary to safeguard the well-being of our youth. Venue: at Hall of Sitota Center for mental Health Care, 4th floor. Admission Fee: FREE Secure your spot filling this form https://forms.gle/TVLJScFMPbf9MYG97

© ጸይም ጽጌሬዳ
© ጸይም ጽጌሬዳ

... ሆኜ አውቃለሁ እንዲህ ሆኜ አውቃለሁ … ሳልበላ ሳልጠጣ ሳልታጠብ ሳልተኛ ውዬ አድሬ አውቃለሁ፤ የለበስኩትን ሳልቀይር ጫማዬንም ሳላወልቅ ተኝቼ ፤ እንደዛው ተነስቼ ጠዋት ወጥቼም አውቃለሁ ቀን ከሌሊት አልቅሻለሁ ጨልሞብኝ ራሴን ጠልቼ ለእንቅልፍ ኪኒን ውጬ አሸልቤአለሁ ከአቅም በታች ኖሬ አውቃለሁ ያልተፈለግኩ የምድር ጥራጊ ፤ የእንግዴ ልጅ ውዳቂ የሆንኩ መስሎኝ ያውቃል ፤ ከለሊቱ 8 ሰአት ከቤት ወጥቼ እስኪነጋ ከተማውን ሳካልል ስዞር አድሬ አውቃለሁ ፤ ለሰአታት ዝናብ ላይ ተቀምጬ አውቃለሁ፤ እንቅልፍ አጥቼ አውቃለሁ ቀን እና ሌሊት ተኝቼም አውቃለሁ ረዥሙን ፎቅ ሽቅብ በዓይኔ ለክቻለሁ የገመዱን ጥንካሬ በእጄ ገምቻለሁ የመርዙን ንጥረ ነገር google አድርጌ ፈትሻለሁ ብዙ ብዙ ሆኜ አውቃለሁ ፤ ድጋፍ አጥቼ ሟሙቼ ፤ ቆዳዬ ጠቦኝ ሳስቼ ነፍሴን ማሰንበቻ ምክንያት አጥቼ አውቃለሁ ማውራት፣ መስማት፣ መስራት፣ ማሰብ፣ መፃፍ፣ ማንበብ መኖር በጠቅላላ ደክሞኝ ያውቃል ሰማይ ተከድኖብኝ ምድር ተንሸራታ ከድታኝ ፤ ከነልብስና ጫማዬ ሻወር ገብቼ ውሃ በላዬ ለቅቄ ለሰዓታት ተዘፍዝፌ አውቃለሁ፤ አንዳንድ ቀን ያሳክከኛ፤ አንዳንድ ቀን ይሞቀኛል ልብሴን እጥላለሁ፤ ሌላ ቀን ይበርደኛል እንዘፈዘፋለሁ ታምሜአለሁ አንዳንድ ቀን ወደላይ፤ አንዳንድ ቀን ወደታች ይለኛል ፤ አንዳንድ ቀን ነስር፤ አንዳንድ ቀን እንባ፤ አንዳንድ ቀን ቁርጠት፤ አንዳንድ ቀን ራስ ምታት፤ አንዳንድ ቀን ማቅለሽለሽ፤ ሌላ ጊዜ ማንቀላፋት፤ ከሁሉ የባሰው ማመን ያቃተኝ ነገር ራሴን ካስቀመጥኩበት ሳጣት ራሴን እዚህ ቦታ ሳገኛት ያቺ ሰው ሁሉ "ጎሽ ጎሽ" የሚለኝ ፤የሚወደኝ፤ ድክመት የማይገኝብኝ ፤ ጥንቅቅ ስትር ያልኩ የሚያውቀኝ ሁሉ የሚያጨበጭብልኝ "ጠይም ጽጌረዳ"ኮ ነኝ እንዴት ሆኖ ምን ሲደረግ? ድካሜ የማይታይ፤ 'እንደሷ ሁኑ' የሚባልልኝ ነኝኮ ... ግን ሆኜ አውቃለሁ ከመቼ ጀምሮ እንደዚህ አይነት ሰው ሆንኩ እልና እልህ ያፍነኛል ደግሞ የሆንኩትን መቀበል ያቅተኛል ያቺ መካሪዋ ሰው አጽናኟ ብርቱ የማትደክመዋ እኮ እኔ? አሁን የት ነኝ? ያቺት እዛ ጥግ ስርቻ ስር ተወትፌ ሸረሪት የሚያደራብኝ እንኳን ለሰው ልደርስ ድረሱለኝ ማለት ያቃተኝ ከራሴ መሸሺያ ያጣሁ ሁለንተናዬን ጠልቼ ከራሴ ሮጪ የማላመልጥ ምስኪን የማውቀውን እንደማላውቅ ያለኝ ሁሉ እንደሌለኝ ሆኜ ሁሉን ከዜሮ ጀምሬ አውቃለሁ ድካምና ጉስቁልና ተጭኖኝ የማለቅስበት ፈልጌ አጥቼ ጉልበቴን አቅፌ ቀርቼ አውቃለሁ ብቻ ብዙ ብዙ ብዙ ነገር ሆኜ አውቃለሁ ፤ አልፎ እንደዚህ ላወራው ልፅፈው ከቻልኩ ድምጽ አውጥቼ ይሄንን ካልኩ ፤ እናንተም ከሰማችሁ ዛሬም ከነጋ 'ግድ የለም ተስፋ አለኝ' እላለሁ እንግዲያውስ ተስፋ አለኝ ! ተስፋ አለኝ እላለሁ ተስፋ አለኝ እላለሁ ተስፋ አለኝ እላለሁ ተስፋ አለኝ!

Repost from WeMind Ethiopia
የሀይማኖት እሴት ባለው ማህበረሰብ ውስጥ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ለአእምሮ ጤና ያለው ጥቅም የትየለሌ ነው፡፡ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ በሚቀጥለው ወርሀዊ ውይይት ይዳሰ
የሀይማኖት እሴት ባለው ማህበረሰብ ውስጥ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ለአእምሮ ጤና ያለው ጥቅም የትየለሌ ነው፡፡ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ በሚቀጥለው ወርሀዊ ውይይት ይዳሰሳል፡፡ እንዳያመልጠዎ! #በነፃ 🎙 እንግዶች 1️⃣ ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብ (በአ.አ.ዩ የስነ-አእምሮ ተባባሪ ፕፎፌሰር፤ የህክምና መምህርና ሀኪም) 2️⃣ ወ/ሮ እሌኒ ምስጋናው (የአእምሮ ህክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች ማህበር አባል መስራችና ፕሬዝደንት) 📅 ቀን፡ ቅዳሜ 02/06/16 ዓ.ም ( FEB 10, 2024 GC) 🕒 ሰዓት፡ 1፡00-2፡00 ቦታ፡ ቴሌግራም በመስመር ላይ (Online Telegram Discussion) 🔗 ታካሚ፣ ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ከሆኑ ለመሳተፍ ይህንን ይጫኑ፡ https://t.me/+cE1r4hqW94tmYTc0 Web: https://sitotapsy.com/ Fb: https://fb.me/sitotapsy/ Ytb: https://www.youtube.com/@sitotapsy Tg: https://t.me/sitotapsy/ Contact link: https://linktr.ee/sitota Deeds, Not words! @gashaw_aweke

እንዳያመልጠዎ! ዛሬ ምሽት 1፡00 ላይ!

https://youtu.be/WPaJjNCm_9I ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብ የምዕራቡ የህክምና እውቀት ከሀገር በቀሉ እውቀት፤ ባህል እና እሴት ጋር መዋህድ አለበት ብለው ያምናሉ፡፡ ለዚህም ከሀይማኖት አባቶች እና ከባህል የመድሀኒት አዋቂዎች ጋር የጋራ የምክክር መድረኮችን በመዛጋጀትና በመምራት፤ እንዲሁም ዘመናዊውን የአእምሮ ህክምና ከመንፈሳዊ እና ሀገር በቀል እውቀት ጋር አብሮ አዋህዶ ከማስኬድ አንጻር የተለያዩ የምርምር ወረቀቶችን በማሳተምም ይታወቃሉ፡፡ በእዚህ የምክክር መድረክ ላይ አራት ታሪኮች ቀርበው ተሳታፊዎቹ የየራሳቸውን እይታ አቅርውበታል፡፡ ከአራቱ ታሪኮች የመጀመሪያውን ከእዚህ በፊት አቅርበናል፨ ቀጣዮቹን ሶስት ታሪኮች እና የተደረገባቸውን ውይይቶች እነሆ! ይህ የምክክር መድረክ ከሙስሊም መንፈሳዊ እና የባህል ህክምና አዋቂዎች ጋር የተደረገ የምክክር መድረክ ነው፡፡ ከኦርቶዶክስ የሀይማኖት አባቶች እና የጥምቀት አገልግሎት ሰጪዎች ጋር የተደረገውን የምክክር መድረክ ለማግኘት በእዚህ ይከተሉን Web: https://sitotapsy.com/ Fb: https://fb.me/sitotapsy/ Ytb: / @sitotapsy Tg: https://t.me/sitotapsy/ Contact link: https://linktr.ee/sitota Deeds, Not words!

Trust in God, but tie your donkey”: Holy water priest healers’ views on collaboration with biomedical mental health services in Addis Ababa, Ethiopia Dr Yonas Baheretibeb Dr Dawit wendimagegn Dr Samuel law

baheretibeb_et_al_2024_trust_in_god_but_tie_your_donkey_holy_water.pdf3.25 KB

እናላችሁ ይህንን ብርቱ ጦርነት ለመቀጠል ላፕቶፔ ላይ ልክ እንደተደፋሁ ዶርማችን ብርግድ ተደርጎ ተከፈተ። የሆነ የሰማይ ስባሪ የሚያክል ሰውዬ (ማለቴ ተማሪ) ወደ ላፕቶፔ ተንደረደረ፡፡ ምን ቅጡ ነው ብዬ ብድግ እንዳልኩ በቆምኩበት በጥፊ ደረገመኝ፡፡ በዛው ቅጽበት ከእርሱ አነስ ያሉ ግን እነርሱም የሰማይ ስባሪ የሚባልላቸው 6 ተማሪዎች ተከታትለው ገቡ፡፡ (ሀረመያ ጤና የተማራችሁ ወንዶች White houseን ታስታውስታላችሁ አይደል?) በነጋታው ስሰማ አገር አማን ብለው ከህይወት ፋና እየተመለሱ ያሉ ሁለት ኢንተርኖችን አጣሞ ነው የመጣው አሉ፡፡ appetizer መሆናቸው ነው እንግዲህ፡፡ ዋናው የድብድቡ ዓላማ በዋዜማው ዕለት፤ ከግቢ ውጭ ለመደባደብ ሙከራ ያደረጉ፤ በእኛ ዶርም ጀርባ የሚኖሩ እንደኔው አዲስ የነበሩ ተማሪዎችን ለመቅጣት ኑሯል፡፡ ለካ እነርሱ ይችን ሰምተው ሸሽተው ሌላ ዶርም ተደብቀዋል፡፡ ማደሪያ ዶርማቸው ዝግ ሲሆንበት ለምን ባዶዬን እመለሳለሁ ብሎ ይሆናል ወደኛ ዶርም የገማው፡፡ ... ጓደኞቹ ካለሁበት ብንቀሳቀስ እንደምመታ አስጠንቅቀውኝ ይዘውት ወጡ፡፡ እንደወጡ፤ ከላይብረሪ ከPharma ጋር ተቀጣቅጦ እየተመለ ከነበረ ጓደኛዬ ጋር ተገጣጠሙ፡፡ ልጁ ወደ ጓደኛዬ መሮጥ ጀመረ፡፡ (ቆይ አዲስ ተማሪ ለአዲስ ተማሪ መተሳሰብ አልነበረበትም? ሌሎች አዲስ ተማሪዎች መረጃው ቀድሞ ደርሷቸው ስለነበር በየዶርማቸው በጊዜ መሽገዋል፡፡ ምናለ ለኛም ቢነግሩን። ህዝቤ መስኮቱንና በሩን ቀርቅሮ፤ መስኮቱ የተቀባውን ቀለም ፍቆ ከውጭ የሚደረገውን ይከታተላል) ...ጓደኛዬ በቁመት ከልጁ አነስ ቢልም የተገነባ ሰውነት ያለው (የቴኳንዶ አሰልጣኝም ጭምር) ነበር፡፡ ጓደኛዬ ልጁን በአንድ ጠረባ ከአፈር ደባለቀው፡፡ ያኔ 6ቱ ልጆች መጥተው ጓደኛዬን አነቁት፡፡ ጓደኛዬ ሂሳብ ሰራ -- ከ7 ሰማይ ስባሪ ጋር ብቻውን ተደባድቦ አይወጣውም፡፡ ማምለጥ ነበረበት፡፡ ወደ ዶርም እየሮጠ ሲሄድ የዶርሙ ልጆች ከውስጥ ቀርቅረው መክፈት ፈሩ፡፡ ሌላ ዶርም እንዳይገባ እያንዳንዱ ዶርመ ከውስጥ ተቀርቅሯል፡፡ ጓደኛዬ አማራጭ ሲያጣ ወደኛ ዶርም ሊመጣ ሲል መሀል ላይ ያዙት፡፡ ያኔ እኔ መውጣት ነበረብኝ (ያው እኔ እንኳን ቴኳንዶ ልችል ይቅርና…. 🤣) የኛ ዶርም ልጆች ተው ትመታለህ ብለው አጥብቀው ይዘውኛል፡፡ ስታገላቸው ለቀቁኝ፡፡ ጓደኛዬን ሂጄ ለማስለቀቅ ሞከርኩ፡፡ ተሳካልኝ፡፡ ጓደኛዬን ከጀርባ ይዤ ሂጄ ምንድነው ጉዱ እየተባባልን እያለ ልጁ በሌላ ቦታ ዙሮ ተከትሎን ኑሯል፡፡ ሁለቱ ይያያዙና ይተላለቃሉ ብዬ ስለፈራሁ መሀላቸው ገባሁና ልጁን ለማረጋጋት ሞከርኩ፡፡ ከሩቅ ለሚመለከተን (በዛ ሌሊት ከሩቅ የሚመለከት የለም እንጅ) በሁለት ዝሆኖች መካከል የገባች አይጥ ነበር የምመስለው🤣 እኔ በአፍ እሱ በከስክስ ጫማው ማውራታችንን ቀጠልን፡፡ ቁመቱ ከስክስ ጫማውን ደረቴ ድረስ ለመስቀል አላስቸገረውም፡፡ እኔ እናገራለሁ እሱ ደረቴን በርግጫ ይወግረዋል፡፡ እንደመንገዳገድ ብዬ እቆማለሁ፡፡ ይደግመኛል፡፡ በ6ኛው ምት (ነጭ ቲሸርት ስለነበር የለበስኩት፤ በነጋታው ደረቴ ላይ የታተመውን የጫማ ኮቴ ቆጥሬ ነው ያወኩት) ከኋላዬ የነበረ የተበላሸ የአልጋ ብረት ክምር ላይ ወደቅሁ፡፡ ብረቱ ክፉኛ አግኝቶኛል፡፡ ከፊት ለፊት፤ ከመሀል አገዳው ላይ፤ የግራ እግሬ ቆዳዬ አጥንቴን ብቻውን አስቀርቶ ግሽልጥ ብሎ ወርዷል፡፡ ለጊዜው አላመመኝም ግን ውሀ በእግሬ ላይ እየፈሰሰ የሚመስል ስሜት ተሰማኝና መብራት ፈልጌ ሳየው መሬቱና እግሬ በደም ተጨማልቋል፡፡ እነ ኤርሚ (ኤርሚ ማለት እምቡላንስ እስኪደርስ እንደ አንቡላንስ የምንገለገልበት የክላሳችን (ከልጁ በመቀጠል ከኮሌቹ 2ኛው) ረጅሙ እና ለግላጋ ልጅ ነው፡፡ እኔም አንድ ሁለቴ የአምቡላንስ አገልግሎቱ ደርሶኛል ሄሄሄሄ) ወደ ግቢው ክልኒክ ወሰዱኝ:: ደሜ የቆመ ቢሆንም ህይወት ፋና (ለምስራቅ ኢትዮጵያ ህዝብ አገልግሎት የሚሰጥ ትልቅ የዩንቨርሲቲው ሆስፒታል ነው) ሂደህ መሰፋት አለብህ ተባልኩ፡፡ ተቃወምኩ -- ከ2 ቀን በኋላ አቶ Pharma ይጠብቀኛላ፡፡ “አይ እንግዲህ! ስርዓት ያዝ” ተባልኩና አምቡላንስ ጋር ተደወለ፡፡ የእግር ህመም፤ ፈተና እና አምቡላንስ ከተገጣጠሙ መሰፋቴ አይቀርም” አልኩና በራሴ ቀለድኩ፡፡ ከሌሊቱ 9 ሰዓት አከባቢ እግሬ ተሰፍቶ ተመለስኩ፡፡ ቀስ በቀስ ነበር እግሬ መጠዝጠዝ የጀመረኝ፡፡ ለመሄድ ሁላ አስቸግሮኝ ነበር፡፡ (ልጁ አሁን የአንድ ሀብታም body guard ሆኗል አሉ) መጎዳት ያስከብር የለ? ድሮም የሀረመያ ጤና ግቢ በካፌ አይታማም ቢሆንም ግን እየተገዛልኝ መመገብ ጀመርኩ። በነጋታው ኤርሚ ፍርፍር ገዝቶልኝ በላሁ፡፡ ቀጣይ ቀን ዶ/ር እዮብ (ያኔ ኢንተርን ነበር) ቋንጣ ፍርፍር ይዞ መጣ (ዶ/ር እዮብ ማለት ወደ ግቢ ስገባ ከበር ድረስ ወገቡ እኪቆረጥ ከባድ ሻንጣዬን ዶርም ድረስ ተሸክሞ ወስዶ፤ እነርሱ ዶርም ውስጥ እያኖረ ግቢውን እና ከተማውን ያለማመደኝ ጥሩ ሰው ነው) [ዶ/ር እዮብ፤ ምን አልባት ይሀን ጽሁፍ እያነበብከው ከሆነ … አ.መ.ሰ.ግ.ና.ለ.ሁ🙏] እስኪሻለኝ ድረስ ተኛሁ፡፡ አንድ ቀን ካሸለበኝ እንቅልፍ ስነቃ ሀይላ (ጓደኛዬ ነው) የሆነ የስስት አስተያየት እያየኝ የነበረውን አልረሳውም፡፡ ሙሉ እንክብካቤ ስለነበረኝ ለቤተሰብ ደውሎ ማስጨነቁ ትርጉም አልሰጠኝም፡፡ ለእረፍት ስመለስ ነው የነገርኳቸው፡፡ ከተሻለኝ በኋለ Pharmaን ተፈጥንኩ፡፡ 0.25 ጎሏችሁ አንድ grade ዝቅ ያለባችሁ… I feel you🤣 ③ ልክ appendicitis ሲያመኝ ዘውዲቱ እንደወሰዳችሁኝ… ልክ እግሬ ሲቆስል ህይወት ፋና እንደወሰዳችሁኝ ሁሉ …. የስሜት መዋዠቅ ህመም (bipolar disorder) ቢያመኝ… ስኪዞፍሬኒያ ቢያመኝ… depression ቢያመኝ… የሱስ ህመም ቢያመኝ.. ስጦታ [ @sitota_psy ] እንድትወስዱኝ እፈልጋለሁ፡፡ ልክ appendicitis ሲያመኝ ፈተና እንደተላለፈልኝ፤ በለስላሳ፥ በአጥሚት እና በመሳሰለው እንደጠየቃችሁኝ፤ እንዳቀበጣችሁኝ፤ እንደጸለያችሁልኝ፤ በጀማ ቤቴ ድረስ ተሰብስባችሁ መጥታችሁ በሳቅ እንዳፈረሳችሁኝ… ድህረ ሰቀቀን ሽብረት (PTSD) ቢያመኝም ተመሳሳይ ድጋፍና የታማሚነት ሚና (sick role) እንድትሰጡኝ እፈልጋለሁ፡፡ ከሌሎች አካላዊ ህመሞች እንደውም የታማሚነት ሚና (sick role) የሚገባኝ በአእምሮ ህመም ከታመምኩ ነው፡፡ በእንደዚህ አይነት ህመሞች ላይ የአንተ ድጋፍ ድጋፍ ብቻ አይደለም፡፡ በራሱ ህክምና ነው፡፡ የማልሰበር የነበርኩት እኔ ከዚህ በሏይ መቋቋም ቢያቅተኝ ድጋፍ ሁነኝ፡፡ ከምሸሸው ነገር ግን ከማልወጣው የብቸኝነት ስሜት አሳልፈህ አትስጠኝ፡፡ በራሴ፤ በዓለሙ ሁሉ፤ በሚመጣውም ሁሉ ተስፋ በምቆርጥበት ጊዜ ከተስፋ መቁረጤ ጋር ብቻዬ ትተኸኝ አትሂድ፡፡ ስትመለስ ላታገኘን ትችላለህና፡፡ እውነት ነው! በግላጭ የማሳይህ ህመምና ቁስል የለኝም ነገር ግን ነፍሴ ከስጋዬም በላይ ምነኛ እንደቆሰለች እንዴት ላሳይህ? እውነት ነው ግንባሬን ዳሰህ “ሰውነቱ እንደ ብረት ምጣድ ይፋጃል” ብለህ ላታውቅልኝ ትችለለህ፡፡ ግን እመነኝ የኢኦል እሳት ከሚመስል ህመም ጋር ነው ትግሌ፡፡ እሺ እርዳታህን ይቅር፡፡ ቢያንስ በቁስሌ ላይ እንጨት አትስደድበት፡፡ ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!!! ስለ ስነ-አእምሮ ያንበቡ t.me/Gashaw_Aweke ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ)

እግር፤ ፈተና እና አምቡላንስ
```````````````````
① 11ኛ ክፍል፤ አዲስ አበባ
```````````````
ቲቸር አለሙ ስለ ecology እያስተማሩ ነው፡፡ የማዳምጣቸው ፍዝዝ ብዬ ጭንቅላቴን በአንድ እጄ ደግፌ ነው፡፡ ጧት ቀኝ እግሬ አላስኬድህ ብሎኝ በግድ እየጎተትኩት ነው ትምህርት ቤት የደረስኩት፡፡ ከምሳ ሰዓት በኋላ መቀጠል እንደማልችል ገባኝ፡፡ ወደ ቤት መመለስ ነበረብኝ፡፡ የምበላው ሁሉ አልረጋልህ ብሎኛል፡፡ የምግብ ፍላጎቴም ተቆልፏል፡፡ ሰላሜ (የአጎቴ ባለቤት) እስኪ ከረጋልህ ብላ በሶ ሰጠችኝ፡፡ ወዲያው ተመለሰ፡፡ (ይህንን አጠገቤ ሆና ስትከታተል የነበረችው የ3 ዓመቷ የአጎቴ ልጅ ወደ እናቷ እየሮጠች ሂዳ “ሸ..ላ..ም…! በሾውን ደፋልሽ…” 🤣🤣 ) በጣም ደከምኩ፡፡ ሀኪም ቤት መሄድ ፈለኩኝ ግን አቅም አጣሁ፡፡ እናቴና አጎቴ ከስራ ተመለሱና በቅርባችን ወዳለጤና ጣቢያ ወሰዱኝ፡፡ እናቴ በጣም ደንግጣ ነበር፡፡ ካርድ ልታወጣ ሂዳ ወደኔ ስትመለስ “ምነው” እላታለሁ “የአባትህ ስም ጠፋኝ” ብላ እርፍ፡፡ አለመሳቅ አልቻልኩም፡፡ ተመልሳ ሄዳ ካርዱን ይዛ መጣች:: እድሜ 23 ይላል (17 ነበርኩኮ… ምስኪን እናቴ!.. 🤣🤣🤣) በአስቸኳይ ድንገተኛ ክፍል ተላኩኝ፡፡ ምን ምን ይሰማሀል ተባልኩ፡፡ ተናገርኩ፡፡ ሀኪሟ ሁለት ጣቶቿን እንደማሾል አድርጋ፥ በቀኝ በኩል፥ ከአንብርቴ ትንሽ ዝቅ ብላ፥ ወጋ አደረገችን፡፡ ህመሙን ፊቴ ላይ አነበበችው፡፡ በግራ በኩል ደገመችኝ፡፡ ህህህ’እ ብዬ እንደመነሳት አደረገኝ፡፡ ቀኝ እግርህን ዘርጋ አለችኝ፤ ዘረጋሁኝ፡፡ በቀኝ በኩል ከእንብርቴ ትንሽ ዝቅ ብሎ ህመም ተሰማኝ፡፡ ቀኝ እግሬን እንደማሽከርከር አደረገችው፡፡ አሁንም እዛው ቦታ አመመኝ፡፡ ሀኪሟ ከጓደኛዋ ጋር “ራሷ ናት” ተባባሉ፡፡ በሙሉ ራስ መተማመን ነው የምታወራው፡፡ ቀናሁባት፡፡ የሪፈር ወረቀት መጻፍ ጀመረች--ወደ ዘውዲቱ ሆስፒታል፡፡ የታመመኩት ህመም በተለምዶ ትርፍ አንጀት በህክምናኛ ቋንቋ appendicitis ነበር፡፡ አንቡላንስ ከመቼው ተደውሎ ተጠርቶ እንደደረሰ እንጃ! አንቡላንስ ሆዬ ሳይረኑንን እያንቦገቦገ አጠገቡ ያሉት መኪናዎች ላይ በጩኸት ሲደነፋባቸው ሸሸት እያሉ ያሳልፉታል፡፡ ያኔ የሆነ ኩራት ቢጤ ተሰማችኝ ብላችሁስ? የእናቴ መደናበር፤ የሀኪሞቹ መዋከብ፤ የአንቡላንሱ በፍጥነት ተጠርቶ መምጣት፤ የመኪኖቹ ቦታ መልቀቅ…. የሆነ ደስታ ነገር ይፈጥራል፡፡ የሆነ “ይህን ያህል ዋጋ አለኝ ማለት ነው?” የሚያስብል ደስታ፡፡ ለትንሽ ሰዓት ጠቅላይ ሚንስተር የሆንኩ ያህል ሳይሰማኝ ይቀራል?… ለጠቅላይ ሚንሰተርስ እንዲህ አይደል የሚደረግለት? [የአፍሪካ ህብረት አከባቢ የሚገኘው የሕይወት አምባ ጤና ጣቢያ ያላችሁ የጤና ባለሙያዎች፤ የአምቡላንስ ሰራተኞች… ሁላችሁንም አ.መ.ሰ.ግ.ና.ለ.ሁ!] ዘውዲቱ ሆስፒታል፤ አልትራ ሳውንድ ተነስቼ ቀዶ ህክመና ማድረግ እንዳለብኝ ተወሰነ፡፡ ያኔ እናቴን አለማየት ነው፡፡ ኦፕሬሽን ሲባል እኔም ያስፈራኛል፡፡ ያኔ ለምን እንደሆነ እንጃ ብዙም ፍርሀት አልተሰማኝም፡፡ እናቴ ግን መረጋጋት አቃታት፡፡ informed concentቱን መፈረም ስለቸገራት አጎቴ ፈረመ፡፡ የቀዶ ህክምናው ጠረጴዛ ላይ እንደተንጋለልኩ አንዲት መርፌ ጉድ ሰራችኝ-- ጲውውው-- አለም ደህና ሰንብች...! ከዛ በኃላ ምን እንደተፈጠረ አላውቅም፡፡ ስነቃ እንብርቴ አከባቢ የሆነ ነገር ትንሽ ያዝ እንዳደረገኝ ይሰማኛል፡፡ በቃ እንደዚህ ብቻ ነው የሚሰማኝ፡፡ አጎቴ አልጋዬ አጠገብ ሆኖ ከንፈሩን ያንቀሳቅሳል፡፡ ውዳሴ ማርያም እየደገመ እንደሆነ መገመት አልከበደኝም፡፡ ሰላሜ ለህዳር ሚካኤል ስለት ገብታለች። እናቴ አልቅሳ እንደነበር ፊቷ ያስታውቃል፡፡ መንቃቴን ሲያዩ ሁለቱም ፊታች በራ፡፡ ወዲያው ቁስሉን ማየት ሰላጓጓኝ ፒጃማዬን ገለጥኩት፡፡ ገረመኝ፡፡ ፕላስተሩ የሸፈነው ክፍል ከማርያም ጣት አይልጥም፡፡ ይችን ብቻ ቀደው ነው ከውስጥ የሆነ ነገር ቆርጠው ያወጡት? በሌላ ቀን ይሄ ነው የሰራህ ብለው አንድ ልጅ እግር ሀኪም አሳዩኝ፡፡ ቀናሁበት፡፡ (የማልረሳው ነገር….ሃሃሃሃ…. ከሰመመን ስነቃ በጣም አስለፍልፎኝ ነበር፡፡ ቀን የተማርኳትን ecology ዝርግፍ አደረኳት፡፡ የማውራውና የምጮኸው ሁሉ ይታወቀኛልኮ… ግን መቆጣጠር አቃተኝ… ሄሄሄ፡፡ አጎቴ ሰው እየረበሽክ ነው ዝም በል እያለ ከንፈሬን ይተመትማል፡፡ ወይ አጎቴ! እሱ መች ጠፋኝ፤ አቅቶኝ እንጅ፡፡ አስባችሁታል… ሌላ ሚስጥር ቢኖረኝ ኖሮ? የእናቴን ሽርደዳ አልችለውም ነበር፡፡) ጠያቂው ጎረፈ፡፡ ሚሪንዳ፤ ጁስ፤ አጥሚቱ… ጎረፈ፡፡ እንክብካቤው ጎረፈ፡፡ ምን ይደረግልህ ተባልኩ፡፡ አቀበጡኝ፡፡ በሆነው ባልሆነ በቀን አስር ጊዜ የምንጣላው እህቴ እንኳ እንዴት እንዳቀበጠችኝ፡፡ ከሁለት ቀን በኃላ final ፈተና ነበረኝ፡፡ ቅድሚያ ለጤንነትህ፤ ለብቻህ ትፈተናለህ ተባኩ፡፡ ለካ መታመም እንዲህ ያስከብራል፡፡ ሌላው በህይወቴ መቼን የማልረሳት ነርስ ነበረች፡፡ እጅግ ቅን እና ስራዋን በአግባቡ የምትሰራ ትልቅ ሴት፡፡ “እሺ ጎረምሳው… “ እያለች የሆኑ ቀልዶች እየፈጣጠረች እያሳቀች መድሀኒት ሰጥታኝ ትሄዳለች፡፡ በመጣች ቁጥር ለመሳቅ ተዘጋጅተን ነው የምንጠብቃት፡፡ ቀናሁባት፡፡ የሰውን ስቃይ መቀነስ ከመቻል በላይ ምን የሚያስቀና ነገር አለ? [እናንተ ትጉህ ሰዎች ምን አልባት ይሀን ጽሁፍ እያነበባችሁ ከሆነ … አ.መ.ሰ.ግ.ና.ለ.ሁ🙏] ከህይወት አምባ ጤና ጣቢያ ጀምሮ እስከ ዘውዲቱ ባጋጠሙኝ ሰራተኞች ቀናሁባቸው። ጤና የመማር ፍላጎቴ የተቀጣጠለው ከዛ በኋላ ይመስለኛል፡፡ አስታውሳለሁ የምለብሰው ሁላ health የሚል ጽፍ ያለበት ሹራብ ነበር፡፡ ከ3 ቀን በኋላ ቤቴ ገባሁ፡፡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ተሰብስበው መጥተው አንዳንዴ እርስ በእርስ እየተተራረቡ አንዳንዴ ቀልድ እያወሩ በሳቅ አነፈሩኝ፡፡ “ኧረ አታስቁት! ቅስሉን እንዳይተረተር” ይባባሉና ህጉን ትንሽ ቆይተው ያፈርሱታል፡፡ ይተራረባሉ፤ ቁስሌን ጨብጬ እስቃለሁ፡፡ ለማገገም ከአንድ ወይ ሁለት ሳምነት በላይ የወሰደብኝ አይመስለኝም፡፡ ② Freshman፤ ሀረር
``````````
ማታ 2 ሰዓት ቢሆንም የተኛሁት፤ 6 ሰዓት ላይ ተነስቼ ሰውነቴን እያነቃቃሁ ነው፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ የሞትና ሽረት ጉዳይ የሆነ ብርቱ ፈተና አለብኝ-- Pharma:: እስኪ ፍረዱኝ ለFreshman ተማሪ pharmacology መሰጠት ነበረበት? አስቡት የየሲስተሙን እያንዳንዷን drug pharmacodynamics, pharmacokinetics, indication, contraindication, how to dose, እና side effect ያዙ ስንባል፡፡ ሌላው ይቅርና የመድሀኒቱቹን ስም ማንበብ ራሱ መከራ ሆኖብን ነበር ሄሄሄሄ… እኛስ ምናች ሞኝ ነው “በM የሚጀምረው…. በS የሚጀምረው…” እያልን ተወጣነው፡፡ ክፋቱ በተመሳሳይ ፊደል የሚጀምሩ መድኒቶች መብዛታቸው፡፡ የአንዱ ሲስተም መድሀኒት ከሌላው እየተደባለቀብ ሁላ ተቸግረን ነበር፡፡ ለሱም መፍትሄ አበጀንለት… slide number… “እዚህ ገጽ ላይ ያለው.. እዛ ገጽ ላይ ያለው…” ሄሄሄ፡፡ (ደስ የሚለው አሁን ካሪኩለሙ ተቀይሯል)

ቤተሰብ መሆን የምችለው እንዴት ነው? የዚህ ቤተሰብ አባል ለመሆኑ በቡድኑ አድሚኖች ፈቃድ ማግኘትን ይፈልጋል፡፡ ለግላዊነተዎ (privacy) ሲባል ቤተሰቡን መቀላቀል የሚችሉት በቡድኑ አድሚን በኩል ፈቃድ ሲያገኙ ነው፡፡ ቡድኑን ለመቀላቀል ፈቃድ ከጠየቁ በኋላ፣ ፈቃድ የሚያገኙት በሚከተሉት መንገድ ነው፡፡ 1.  የስጦታ ሴንተር ፎር ሜንታል ኸልዝ ኬር አገልግሎት ተጠቃሚ ወይም ቤተሰብ ከሆኑ ከሚከተሉት በአንደገኛው መንገድ አባል መሆን ይችላሉ፡፡ - ካርድ ላይ የተመዘገበውን ስልክ ቁጥር ወይም ማንኛውን የአገልግሎታችን ተጠቃሚ መሆነዎን የሚያሳይ ማስረጃ (የምስክር ወረቀት፣ የመድሀኒት ማዘዣ፣ የቀጠሮ ካርድ…) በ t.me/sitotamentalhealthcare ወይም +251995011035 ከላኩልን በተቻለው ፍጥነት ፈቃድ እንሰጥዎታለን፡፡ - በማዕከሉ አገልግሎት ለመቀበል ሲሰጡ በምናዘጋጀው ፎርም ላይ የቴሌግራም አካውንትዎን ወይም ስልክዎን ማስቀመጥ 2. ከስጦታ ውጭ የህክምና አገልግሎት እያገኙ ከሆነ - የአእምሮ ህክምና የአገልግሎት ተጠቃሚ መሆነዎን የሚያሳይ ከማንኛው ሀኪም ቤት የተሰጠ ማስረጃ (የምስክር ወረቀት፣ የመድሀኒት ማዘዣ፣ የቀጠሮ ካርድ…) በ t.me/sitotamentalhealthcare ወይም +251995011035 ከላኩልን በተቻለው ፍጥነት ፈቃድ እንሰጥዎታለን፡፡ 3. በክብር አባላት በኩል ፈቃድ የሚሰጣቸው አባላት የስጦታ ቤተሰብ የክብር አባል ከዚህ ቤተሰብ ይጠቀማሉ ወይም ለቤተሰቡ አስተዋጽ ያደርጋሉ የሚሏቸውን ግለሰቦች በዚህ ሊንክ https://t.me/+cE1r4hqW94tmYTc0 መጋበዝ ይችላሉ፡፡ የተጋባዦቹን ስልክ ቁጥር ወይም telegram user name ዝርዝር በክብር አባላቱ በኩል በማሳለፍ መቀላቀል ይቻላል፡፡ ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ…. ስንተጋገዝ ለውጥ እናመጣለን! ስጦታ-ቃል ሳይሆን ተግባር! ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ) @gashaw_aweke

የቤተሰቡ አባላትን በተመለከተ የስጦታ የመደጋገፊያ ቡድን ቤተሰብ መሆን የሚችሉት የሚከተሉት ናቸው 1. የክብር አባላት የክብር አባላት የምንላቸው፡ - ከዚህ በፊት የአእምሮ ህክምና አገልግሎት ያገኙ እና በማግኘት ላይ ያሉ ግለሰቦች - ተሞክሯቸውን ማካፈል የሚፈልጉ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች… - ለአእምሮ ጤና ጥብቅና የሚቆሙ ግለቦች፣ ድርጅቶች፣ የሚዲያ አካላት… 2. የስጦታ ሴንተር ፎር ሜንታል ኸልዝ ኬር አገልግሎት ተጠቃሚዎች ወይም ቤተሰቦች - የስጦታ ህክምና አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆኑ ይህ ቤተሰብ የተመሰረተው ለእርስዎ ነው፡፡ እኛ ጋር ሲመጢ ብቻ ሳይሆን በቤተዎ ሆነው ጤናዎን እንዲንከባከቡ ለመርዳት ዝግጁ ነን፡፡ 3. የስጦታ ሴንተር ፎር ሜንታል ኸልዝ ኬር ሰራተኞች - የስጦታ ሰራተኞች እርስዎን ለማገዝ ከቤተሰቡ ውስጥ ናቸው፡፡ 4. በሌላ የህክምና ቦታ የአእምሮ ህክምና አገልግሎት የሚያገኙ ተገልጋዮች ወይም ቤተሰቦች - በሌላ የህክምና ቦታ ህክምና የምትከታተሉ ግሰሰቦች ወይም ቤተሰቦች የዚህ ቤተሰብ አባል መሆን ይችላሉ፡፡ 5. በክብር አባላት በኩል ፈቃድ የሚሰጣቸው አባላት - ለቤተሰቡ ድጋፍ አስተዋጽኦ ማድረግ የሚፈልጉ በክብር አባላት በኩል የሚመጡ ግለሰቦችን ወይም ድርጅቶችን ቤተሰብ አድርገን እንቀበላለን፡፡ ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ…. ስንተጋገዝ ለውጥ እናመጣለን! ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ) @gashaw_aweke

ስለ ስጦታ የመደጋገፊያ ቡድን ሰምተዋል? ይህ ቡድን የአእምሮ ህክምና አገልግሎት ተቀባዮች (ታካሚዎች) እና ቤተሰቦቻቸውን ከባለሙያዎች ጋር አስተሳስሮ የያዘ ቡድን ነው የቡድኑ አባላት መሆን የሚችሉት
ስለ ስጦታ የመደጋገፊያ ቡድን ሰምተዋል? ይህ ቡድን የአእምሮ ህክምና አገልግሎት ተቀባዮች (ታካሚዎች) እና ቤተሰቦቻቸውን ከባለሙያዎች ጋር አስተሳስሮ የያዘ ቡድን ነው የቡድኑ አባላት መሆን የሚችሉት ማን እንደሆኑ እና እንዴት አባል መሆን እንደሚቻል በሚከተለው አቀትብላችኋለሁ፡፡ ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ እና የቡድኑ አስተባባሪ) @gashaw_aweke

የሀይማኖት እሴት ባለው ማህበረሰብ ውስጥ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ለአእምሮ ጤና ያለው ጥቅም የትየለሌ ነው፡፡ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ በሚቀጥለው ወርሀዊ ውይይት ይዳሰ
የሀይማኖት እሴት ባለው ማህበረሰብ ውስጥ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ለአእምሮ ጤና ያለው ጥቅም የትየለሌ ነው፡፡ ሀይማኖት (መንፈሳዊነት) ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ በሚቀጥለው ወርሀዊ ውይይት ይዳሰሳል፡፡ እንዳያመልጠዎ! #በነፃ 🎙 እንግዶች 1️⃣ ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብ (በአ.አ.ዩ የስነ-አእምሮ ተባባሪ ፕፎፌሰር፤ የህክምና መምህርና ሀኪም) 2️⃣ ወ/ሮ እሌኒ ምስጋናው (የአእምሮ ህክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች ማህበር አባል መስራችና ፕሬዝደንት) 📅 ቀን፡ ቅዳሜ 02/06/16 ዓ.ም ( FEB 10, 2024 GC) 🕒 ሰዓት፡ 1፡00-2፡00 ቦታ፡ ቴሌግራም በመስመር ላይ (Online Telegram Discussion) 🔗 ታካሚ፣ ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ከሆኑ ለመሳተፍ ይህንን ይጫኑ፡ https://t.me/+cE1r4hqW94tmYTc0 Web: https://sitotapsy.com/ Fb: https://fb.me/sitotapsy/ Ytb: https://www.youtube.com/@sitotapsy Tg: https://t.me/sitotapsy/ Contact link: https://linktr.ee/sitota Deeds, Not words!

ለ CPD ስልጠና ፈላጊዎች  Title- Medication Administration  CPU-15  የስልጠና ክፍያ- 1000 ብር ብቻ  ስልጠናው የሚጀምረው አርብ ጥር 24 ያለን ውስን ቦታ ስለሆነ
ለ CPD ስልጠና ፈላጊዎች  Title- Medication Administration  CPU-15  የስልጠና ክፍያ- 1000 ብር ብቻ  ስልጠናው የሚጀምረው አርብ ጥር 24 ያለን ውስን ቦታ ስለሆነ ቀድማችሁ ተመዝገቡ ስ.ቁ- 0913 597672

ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 25 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል:: የዚህ ወር ርዕስም፡- “እንደ ህብረ
ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 25 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል:: የዚህ ወር ርዕስም፡- “እንደ ህብረተሰብ የስነልቦና ቁስልን መገንዘብ” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳችን የአሃ ሳይኮሎጂካል አገልግሎት መስራች እና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሞገስ ገ/ማሪያም ናቸው፡፡ ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡ https://forms.gle/Y8iPkGRELLR2cFW86 የማስታወሻ መልእክት እና የቦታውን አቅጣጫ ምልክት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ https://t.me/mhaddisababa The monthly Mental Health Addis’ event has come and it will be held on Feb 3, 2024 at Adore Addis Hotel (near Atlas) in the afternoon at 10:00 local time. This time the topic is “Growing as a Trauma-Informed Society.” Our guest speaker is Ato Moges G/Mariam (Founder and Director at Aha Psychological Services). To attend please register by filling this Google form:- https://forms.gle/Y8iPkGRELLR2cFW86 To get a reminder and get direction please join our Telegram Channel: https://t.me/mhaddisababa #mentalhealth #AdoreAddis #mentalhealthawareness #talkmentalhealth #mentalhealthmatters