cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

🌹❤️ልዩ-ትረካዎች🌹

ተከፈተ ይላል ልዩ የሆነው የ ትረካ ቻናላችን ተጀመረ አቦ ታሪክ ወዳጆች ገባ ገባ በሉ #የፍቅር_ታሪኮች #የፍቅር_ግጥሞች #ልዩ_የሆኑ_ትረካዎች ብቻ የሚያስደስተው በ #voice ነው - #ፍቅር_ግጥም_ትረካ #የ_ፍቅር_ደብዳቤዎች ችግር ካለ ብቻ Comment 𝘼𝙣𝙙 cross @rastakiing @bozenewa_1 @Poprapman

Show more
Advertising posts
405
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#ሰይጣን_ጠፍጥፎ_የሰራውን #እግዜር_እፍፍፍ_ብሎ_ነፍስ_አይሰጠውም? ~ ~ ሮዛ ምልልሷ ስቦኛል፡፡ ሰላምታዋም... በአጠገቤ ስታልፍ ኑሮዋን ኑሮዋን የሚሸተኝ ከሱሪዋ የሚወጣ ፀሀይ የመታው ሳሙና፡፡ ሰላምታዋም <ሲራክ... እንዴት ነህ ባክህ?> ብላ አይኗ ላይ የተሳለ ጥያቄ ያልሆነ ወጣትኛ ቋንቋ... ግዮን ሄጄ ካገኘሁዋት በሁዋላ... የማውቀውንም ሳወራት የምታውቀውንም ስታወራ ውስጥ ለውስጥ በሹክሹክታ ነገር ሀፍረት የሌለው መፋዘዝ እንደተጋራን... <ቻው> የመሰለ ቆማጣ ቋንቋ ያራራቀን... የበድሉ ሱቅ ብቻ የመገናኛ አደባባያችን ነበር፡፡ ድሮም ልብስ እየቀያየረች ሰንደል ስትገዛ አስተውላት ነበር፡፡ አሁን ግን የሴትነት አጠማመድ ጥበቧን ብቻ ሳይሆን የገዛችውን ሰንደል አስተውላለሁ፡፡ ስትለኩሰው እንደደመና እየተጎተተ ይከተላትና ግዙፍ ጥቁር እሷነቷን ይዳብሳል... ወደ መፍዘዝ ባንናለሁ... የተለየ ማዕዘን ውስጥ በስህተት እንደተፈጠርኩ ሁሉ ነገሮች ይገርሙኛል... ገላዎች ይገርሙኛል... አይኖች... ቅንድቦች (በአንድ የስምምነት አቅጣጫ መጋደማቸው) አፍ (የተአምር ወንዝ <በዚህ ፍሰስ> እንደተባለ በአፍ በኩል ጢሱን እየጣለ ሲወርድ)... ጉንጮቿን ስቃይ በዳበሰ እጄ ስነካቸው በጣቶቼ ላይ የሚቀር ጥቁር ነጠብጣብ ያለ የሚመስለኝ፡፡ ቀርቤ የቅንድቦቿን ልሙጥ ማብረቅረቆች ውበት ታውቂያቸዋለሽ ወይ ብዬ ብጠይቅ መልሱን ታውቃለች? አይኗ ወደ ውጭ ነዋ! መስታወት ራሱ አይን የሚያየውን ወዝ ይስታል፡፡ አሞራ እንኳን ሁሌ እንዳቀረቀረ የራሱን ግንባር ሳያይ ይሞታል፡፡ ፍርድ ነው! የሌሎች ውበት እኔ አይን ውስጥ ይቀነባበራል... የእኔም ውበት ሌሎች አይን ውስጥ፡፡ ~ ~ እንደፈለገ ኖሮ በውጤቱ እንደሚፀፀት ሰው ቀሽም የለም፡፡ ውጤት የድርጊት ድምር ነው... ድርጊት ጣፍጦ እንዴት ውጤቱ ይመራል? እንደኮሶ አረቄ ያንዘረዝራል? ነው ወይስ ከእሩብ እውነት ጋር የታሰረ ነፍስ አለን? ሙሉ ድርጊት ቋምጦ ውጤቱን የሚክድ፡፡ ~ ~ ስንዱን... ዝምተኛዋን እናቴን... በሴራ ፈገግታዋ የምግባባትን... ጠይሟን... የማትጎላ... የማትጠፋዋን ስንዱዬን አስባታለሁ አንዳንዴ፡፡ አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ሁለታችን ብቻ ነን ግን ብዙ አናወራም፡፡ እንደኔ ቆዳ ወዝ የሌለው ልሙጥ ስስ የሚያብረቀርቅ የእግሯን አይበሉባ ባሻት ደስ ይለኛል... አውራ ጣቷን ብስመው... እድሜ ያከረራቸው አጥንቶቿን ብዳብስ... ብቆነጥጥ... አይቻት ፈገግ ብል እመኛለሁ፡፡ ያን ለማድረግ ግን ለምን ያሳፍረኛል? ይሄንን ምኞቴን ሳታውቅ ብትሞት ራሱ አልፀፀትም፡፡ ምናልባት ይሉኝታዬ ከፍቅሬ ይገዝፍ ይሆናል፡፡ እሷም ዝም የምትለኝ ያወረሰቺኝ ዘላለም የሚያክል ይሉኝታ ገብቷት ይሆናል ምናልባት፡፡ አልጋዬ ላይ በፈዘዝኩበት መጥታ ያንጨፈረርኩትን ጉሬን እምጵዋ የሌለው አየራዊ አሳሳም ልትስመኝ ትፈልግ ይሆናል፡፡ እኔም እሷም ፍቅራችንን እንገማመታለን... ማንም <ልክ> አይሆንም! <ልክ> ያለው ፍቅር ስላለመኖሩ መገለጫ ነው? ~ ~ እኛ እኮ ጭራፊ ህይወት ብቻ አይደለንም ከሞትም መንደር ድርሻ አለን፡፡ ሞት እኮ ብቻውን አይገድልም! አቅም የለውም! እኛ እና ተፈጥሮ ሰውን እየሸራረፍን እየሸራረፍን ቢያንስ የሩብ ግማሹን ሞት ምድር ላይ ጠፍጥፈን እናበጀዋለን፡፡ ከዚያ ነው ምስኪን መልአከ ሞት የሚመጣው... ሞት የመጣል ስልጣን የለውም የወደቀ ሰብሳቢ ነው፡፡ ትልልቆቹ ሞቶች እኛና ተፈጥሮ ነን... እውነታችንን ተነጋግረን እንዳናወጣው ህሊናችን ተኮራርፏል፡፡ ~ ዝርዝር ነገሮች ነን! ከዋጋችን አንጨምርም አንቀንስም የዋናው ሽርካቾች... ብቻችንን የማንሞላ... የአንድ የሰማይና የምድር ሀሜቶች ውጤት... ዋናው ኑሮ ቀላል ይመስላል (የሽወዳ መልኩ እውነት ቅብ አይደል?) ግን ተደምረን ስንመዘን ከዋናው በላይ የምንከብድ... ሆነ ብሎ ያሴረብን አንዳች አካል እያገጠጠ የሚያየን ዝርዝር ቅጭልጭሎች ነን፡፡ እኔና ሮዛ ልንሞላ የምንጥር ጎዶሎዎች አይደለን? ከከንፈር ወደ ምናምን የምንጓዝ ሞኞች አይደለን? የያዝነው ሁሉ የእኛ የሚመስለን አይደለን? የተጨረሰ ጉዞ የምንጀምር ስልችቶች አይደለን? ግን በእጣ ፋንታ ጨርቅ ውስጥ ደስታን ለማንጠባጠብ ለሁለት እንጨምቃለን፡፡ በፍቅር መሀል የመሰላቸት ንፋስ ቢገባ ምኑ ይገርማል? አይደለም ትላንት የማውቃትን ውበት (እሷን) ከመፈጠር እኩል ጥንት የማውቀው እኔነቴ አልሰለቸኝም? ታዲያ የሚሆነው እየታወቀ ሲሆን መደነቅ የሞኝ ነው፡፡ (ከጥቁርና ነጭ ማስታወሻ ላይ የተወሰደ)
Show all...
#ብችል_ይህቺን_አለምን_ሶስቴ_እገላታለሁ! #ጠዋት_ከሰአትና_ማታ! ~ ፍቅርተ ዘመኗን ሁሉ አይቻታለሁ፡፡ ሴት የመሆን ሂደቷን... ዘምዘም ልጅ ወጣላት ሲባል ሰምቻለሁ፡፡ ሰፈሩ በሙሉ <አቤት ፀባይና መልክ> ብሎ ያደንቃታል... እናቴም ጭምር፡፡ የፍቅርተን እንከን አልባነት በየ ሁሉም አንደበት ስሰማ ነበር፡፡ ወሬ መሀል ስሟ አይጠፋም፡፡
Show all...
ዘመን አና ኑሮ ድሮ ድሮ ያኔ በእነሱ ዘመን ባለነበረ ጊዚ ኑሯቸው ሰቀቀን በ አንድ ብር በለትው በተረፍቸውም ሚሹትን ጠጥተው ይኖሩ ነበረ በደስታ ተዝናንተው አሁን በኛ ገዜ በ አንድ ብር ቀርቶ በአንድ መቶ ብር ምን ይገዛል ከቶ ወደላይ ብቻ ነው የሚቀንስ የለም ደሞዝ እንደገባ ብትን ይላል እልም ያለው ብቻ ይኑር ይመስላል ብሂሉ በደርዘን ይገዛል ሰዎች ኡኡ እያሉ ከማነው ችግሩ እስኪ ተናገሩ በመጋዘናቸው ዘግተው እያጓሩ ጊዜው አለፍ ሲል ብረ እየጨመሩ ተስገብብግበው በልተው ደሀን አማረሩ በኑሮ ውድነት እጅጉን ተማሮ መዝረፍ ይጀምራል ይይዛል ጉሮሮ በሱ አይፈረድም ለምን ይፈረዳል ኑሩ በጣም ከብዶት ሩቅ ይሰደዳል ያልፍልኛል ብሎ ያለ የሌለውን ጨምሮ  ከፋፍሎ ቢወድም ባይወድም ካገሩ ኮብልሎ መንገድ ላይ ይቀራል በውሀ ጥም ተቃጥሎ ለዚ ሁሉ ምክንያት የኑሮ ወድነት ችግር እየሆነ እያቃተን መብላት በሌላ ነገሮች በስብሰን ተነክረን በዘር በሀንማኖት እየተለያየን ሰውነት ተረስቶ ሰው መሆን ተትቶ መተሳሰብ ጠፍቶ መከፍፈል በዝቶ ዘር እየቆጠረን  መረጋገጥ መርጠን እንዴት ይቀንሳል እንዲ አየሆንን ፍቅር ይሻለናል  ሰላም ይበጀናል ምን አልባት ያን ጊዜ ይቀንስ ይሆናል ዮሀንስ ወንደሰን ✍
Show all...
ሳታውቅ እግሩን ረግጣው "I'm solly" ስትለው "ሶሊያና ነው ስምሽ? በቃ ስልክሽን ስጪኝ ልደውልልሽ" አላለም😃 : #ባክህ_አትሻፍድ ኮልታፋ ስለሆነች ነው እንጂ "I'm sorry" ለማለት ፈልጋ ነው🫡                        🔻Stay with us🫶
Show all...
ከድሮ ፍቅረኛዬ ጋር በኔትወርክ ምክኒያት እኮ ነው የተጣላነው... #እሷ፦ "እንዴት አደርክ ውዴ " #እኔ፦ " እንዴት አደርሽልኝ የኔ ማር (sending failed) #እሷ፦ "ለምንድነው የማታወራኝ ውዴ " #እኔ፦ "አረ ኔትዎርኩ እምቢ ብሎኝ ነው (sending failed) " #እሷ "በቃ ለእኔ ያለክ ፍቅር የውሸት ነው ?" #እኔ፦ "አረ ሜሪ ቴክስቱ በኔትዎርኩ ምክኒያት አልላክም ብሎኝ ነው (አሁንም እምቢ አለ አልተላከም ) #እሷ "በቃ ስትፈልግ ገደል ግባ አንተ ባታወራኝ ስንቱ የሚያወራኝ መሠለህ ከእንግዲህ ላገኝክ አልፈልግም " #እኔ፦ "አቦ የራስሽ ጉዳይ ምን ትጨቃጨቂያለሽ የፈለግሽበት ሂጂ (sent successful /ቴክስቱ ተልኳል)😂🤣😄 Join us➜ @lyu_treka
Show all...