1 146
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1830 days
Posts Archive
1 146
ለአውቶሞቲቭ ፣ ኮንስትራክሽን፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ሰርቨይንግ ወርክሾፕ ቴክኒሻን በሙሉ
ማክሰኞ እለት ከጠዋቱ 2:30 ላይ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የጉለሌ ምዘና ጣቢያ ስብሰባ ስለጠራችሁ በሰአቱ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
1 146
+6
የ2016በጀት ዓመት አፈጻጸም ዳሰሳ እና የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ውይይት ተካሄደ።
ዕለተ ዓርብ ሐምሌ 3/2016ዓ.ም
የዕለቱ መድረክ በኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የተመራ ሲሆን ኮሌጁ የተቋቋመበትን ዓላማ እውን ለማድረግ በርካታ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል። በዋነኛነት የስልጠናና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ስራዎችን በተፈለገው ደረጃ ለማድረስ የተቋማት አቅም ግንባታ ምቹ የስራ አካባቢ ከመፍጠርና የሰራተኛውን አቅም ከማጎልበት አንፃር የተከናወኑ ተግባራትን በጥንካሬም ሆነ በድክመት የተፈተሸበት የ2016 በጀት ዓመት ነባራዊ ሁኔታ ትንታኔ የቀረበበት ነው።
አያይዞም በ2017 በጀት ዓመት የታቀዱ ተግባራት ከባለፈው በጀት ዓመት መስተካከል ባለባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት እና በማስተካከል በአዲሱ እሳቤ የተቃኘ የስልጠናና የስራ ግዜን እውን በማድረግ ስራዎች በየደረጃው ወርደው አፈጻጸማቸው እየተገመገመ መሰራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም ኮሌጁ የደረሰበትን የምዕተ ዓመት ዕድሜና ተሞክሮ ወደ ጥቅም በመቀየር በተያዘው በጀት ዓመት በሚከበረውን የምዕተ ዓመት በዓል አከባበር ሁሉም የድርሻውን እንዲያበረክት ከወዲሁ ተጠቁሟል።
በመጨረሻም ከቤቱ በተነሱ ገንቢ ሃሳብና አስተያየት የውይይቱ ማጠቃለያ ሆኗል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+8
በተለያዩ የስልጠና ዘርፎች በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ለሰለጠኑ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ ምዘና እየተሰጠ ነው ።
ዕለተ ረቡዕ ነሐሴ 1/2016ዓ.ም
በዛሬው ዕለት የተጀመረው እና ለተከታታይ 3 ቀናት የሚዘልቀው ምዘና በአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ሠልጥነው የተቋም ምዘና የተመዘኑ እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ምዘና ከነሐሴ 1/2016 - ነሐሴ 3/2016ዓ.ም እንደሚቆይ የገለጹት የምዘና አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ሲሆኑ ምዘናው በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር የሚመራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በምዘናው ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የምዘናውን አስፈላጊነት እና በቀጣይ በሃገራቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው ምዘና ያለውን ጠቀሜታንም አብራርተዋል ።
ተመዛኞች በጠዋቱ ክፍለ ግዜ የተግባር ምዘና ይመዘናሉ ፤ በሁለተኛው መርሃ ግብር የቲዎሪ/የጽሁፍ ፈተና የሚመዘኑ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ በስልጠና ዘርፉ የደረጃ ሦስት ሠልጣኞች ከአንድ ወር የትብብር ስልጠና ቆይታ መልስ የተቋም ምዘና ተመዝነዋል። በምዘናው ብቃታቸውን ያረጋገጡ ወደ ቀጣዩ ደረጃ የሚሸጋገሩ ሲሆን ብቃታቸውን ያላረጋገጡ ሰልጣኞች በቀጣዩ ግዚያት ክፍተታቸው ተሞልቶ ዳግም ለምዘና እንደሚቀመጡ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው የቶ ደሳለኝ አዱኛ ጠቁመዋል።
የዝግጅት ክፍላችንም ለተመዛኞች መልካም ዕድልን ይመኛል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
የ2017 በጀት ዓመት የአላቂ ዕቃዎች የበጀት ድልድል ዲፌንስ ቀረበ።
ዕለተ ረቡዕ ነሐሴ 1/2016ዓ.ም
በአዲሱ አሰራር /የስልጠና ሂደት እሳቤ የበጀት ድልድል በዝርዝር እንዲቀርብ አቅጣጫ ተሰጠ።
ከወትሮው በተለየ መልኩ በአዲሱ የስልጠና እሳቤ ለየስልጠና ዘርፉ ለአላቂ ዕቃዎች ግዢ የበጀት ድልድል የተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
የበጀት ድልድሉ የትኩረት አቅጣጫ
- ከሰልጣኝ ቅበላ አንፃር
- በልየታ የተቀመጡ ስልጠና ዘርፎች
- በቀጣይ ኮሌጁ ከሚያከናውናቸው አበይት ተግባራት
አንጻር እየተቃኘ በዝርዝር መቅረብ እንዳለበት
ተጠቁሟል።
በዕለቱ ዝርዝር ተግባራቸውን ካስቀመጡት ውጪ ያሉትን
1. ከኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ከድጋፍ ባሻገር
የቴክኖሎጂ እና የበጎ አድራጎት ስራዎች በእቅድ
ተካተው መታየት እንዳለባቸው
2. ከደራሽ ስራዎች ውጪ ሁሉም በዕቅድ ተካቶ
እንዲቀርብ
3.የምዕተ ዓመቱ በዓል አከባበር ስራዎች በየስልጠና
ዘርፉ በፕሮጀክት ተነድፎ በበጀት የተደግፈ ዕቅድ
እንዲቀርብ።
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት ከቀረቡት የተለያዩ ሃሳቦችና ከተሰጡ አስተያየቶች መነሻነት ማስተካከያ ተደርጎበት ዝርዝር የበጀት መግለጫዎች ተካተውበት በነሐሴ 8/2016 በድጋሚ እንዲታይ በጋራ ከስምምነት ተደርሷል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
በተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝት ተካሄደ።
ነሐሴ 1/2016 ዓ.ም
የካናዳው ሐምበርግ ቴክኒካል ኮሌጅ ዳይሬክተር ወ/ሮ ናሊና አንድሬድ እና የፕሮግራም ማናጀሯ ክላሪስ እስቴቨን በኮሌጃችን የተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝት አካሄዱ።
የጉብኝቱ ዓላማ ኮሌጁ ያለውን አቅም ከግምት በማስገባት በቀጣይ ከኮሌጁ ጋር ትስስር በመፍጠር በአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ ለመስራት በተለይም በሴቶች ላይ መስራት የሚያስችላቸውን አቅጣጫ ለመወሰን የሚያስችል ውይይት አካሂደዋል።
ዳይሬክተሯ ናሊና አንድሬድ ኮሌጁ ላይ ባዩት ነገር የተሠማቸውን መልካም ስሜት ገልፀው በቀጣይ የአቅም ግንባታ ስሬዎችን በጋራ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የቀድሞ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር በነበሩ ካናዳዊ ቱሬ የተጻፈ ግለ መጽሐፍ አበርክተውላቸዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+7
ቀጣሪዎችና ተመራቂ ተማሪዎች የሚገናኙበት
የስራ ቅጥር አውደ ርዕይ (Carreer fair ) ተካሄደ።
ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ ም
ኬፕለር ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር ዘንድሮ ለሶስተኛ ጊዜ የቴክኒክና ሙያ ተመራቂ ተማሪዎች ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በቀላሉ የሚገናኙበትን የስራ ቅጥር አውደ ርዕይ (Carreer fair) በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናውኗል።
በመርሃ ግብሩ ከአራት ትልልቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ማለትም ከእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ ንፋስ ስልክፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ ጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ተግባረእድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመጡ በርካታ ተመራቂ ተማሪዎች በዕለቱ ለስራ ቅጥር ከተገኙ ከ40 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶች ጋር የተዋወቁ ሲሆን የስራ ማመልከቻ እና ግላዊ መረጃቸውንም ለቀጣሪ ድርጅቶቹ መስጠት ችለዋል።
በየዘርፉ የተሳተፉ ድርጅቶች የእርስ በእርስ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ለካሪኩለም ማሻሻያ ግብአት የሚሆን ሀሳብም ተለዋውጠዋል።
በፕሮግራሙ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ፣ ከአራቱም ኮሌጆች ፣ ከተለያዩ የሚዲያ ተቋማት እና ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ባለሙያዎች እና እንግዶች የተካፈሉ ሲሆን በዕለቱ ለተሳተፉ ቀጣሪ ድርጅቶች ከኬፕለር ኢትዮጵያ የዕውቅና እና የምስጋና ሰርትፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ መሰል መርሃ ግብሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውና ኮሌጁ በመሰል ስራዎች አብሮ ለመስራት ሁሌም ዝግጁ እና ፈቃደኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+2
በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት
የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ምዘና
ተከናወነ።
ዕለተ ሰኞ ሐምሌ 29/2016አዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥነ- ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባለሙያዎች በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት የበጀት ዓመቱን የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አከናወኑ።
ግምገማው ትኩረት ያደረገባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች
- ዳይሬክቶሬቱ እንዲያከናውነው ከተቀመጠለት
አቀጣጫ /ከወረደለት ዕቅድ አኳያ የተከናወኑ
ተግባራትን
- በሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስናን ከመከላከል አንጻር
የተሰሩ ስራዎች
- በመደበኛ ጥቆማ አስቸኳይ ሙስናንና ብልሹ
አሰራርን መከላከል
- ተጋላጭነትንና የአሰራር ስርአት ጥናትን ከማጥናት
አንጻር የተሰሩ ስራዎች ተፈትሸዋል።
በመጨረሻም የተሻለ ስራ እየተሰራ መሆኑን በመጠቆም በቀጣይ የበለጠ ለመስራት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችም ተጠቁሟል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
" አንድ ሞያ ለአንድ ዜጋ"
ዕለተ ዓርብ ሐምሌ 26/2016ዓ.ም
" አንድ ሞያ ለአንድ ዜጋ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የስልጠና መርሃ-ግብር ሃሳብ አፍላቂ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር ) ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ይህንን የተቀደሰ ተግባር እውን ለማድረግ ኮሌጁ ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት በተለያዩ የሙያ መስኮች ለመሠልጠን 271 ስልጠና ፈላጊዎች የተመዘገቡ መሆናቸውን ከቀረበው የምዝገባ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
በስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በዋናነት የስልጠናውን አስፈላጊነት ሲያብራሩ ዜጎች ካላቸው ሙያ በተጨማሪ የአንድ ሙያ ባለቤት ሆነው ራሳቸውንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ የተሻለ ኑሮ ለመምራት የሚያስችል በመሆኑ ከስልጠናው ማጠናቀቅ በኃላ ብቃታቸውን በምዘና አረጋግጠውና ተደራጅተው ለሚመጡት ወደስራ የሚገቡበትን መንገድ ኮሌጁ ባለው አቅም ዕድሉን የሚፈጥርና የሚያመቻች
መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በተመሳሳይ የስልጠናውን ሰዓትና ከስልጠና በኋላ የሚኖሩ ሂደቶችን አስመልክቶ የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በቂ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ከቤቱ ለተነሱ አንዳንድ ብዥታዎች እና ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፤ስልጠናው በሚቀጥለው ሳምንት የሚጀመር መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዛሬ ሀምሌ 25/2016ዓ.ም. ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቡድን ጋር በ 3 አጀንዳዎች ላይ ውይይት አድርገናል።
👉 በተጠራው የማስጀመሪያ እና የውይይት መድረኩ ላይ በመገኘት ገንቢ ሃሳቦችን ያቀረባችሁትን እያመሰገንኩ በቀጣይ ስራዎችም ላይ ተመሳሳይ ተሳትፎ እንድታደርጉ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
⁉️ በስልጠና ዘርፋችሁ ተልካችሁ በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ያልተገኛችሁ አሰልጣኞች ይህ ተገቢ እንዳልሆነ እና በተግባር ስራ ላይ እንቅፋት እንደሚሆን እሙን ነው። በመሆኑም የቀራችሁበትን ምክኛት ኢ.ኤ.ቴ.ሽ. ቢሮ በአካል ቀርባችሁ ያልተገኛችሁበትን ምክንያት እንድታሳውቁ እንዲሁም ለወደፊቱ ከቡድኖቻችሁ ጋር በመሆን ወደ ስራ እንድትገቡ አሳስባለሁ።
👍👍መልካም የስራ ቀን 👍👍
1 146
+3
ዕለተ ሰኞ ሐምሌ 22/2016ዓ.ም
በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ የሠለጠኑ የICT ሠልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ምዘና ተመዘኑ ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ የሠለጠኑ የHNS ,WDDBA የደረጃ 4 እጩ ተመራቂ ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ምዘና በዛሬው ዕለት እየተመዘኑ ሲሆን በሐገራቀፍ ደረጃ ለሚዘጋጀው የCOC ምዘና የዝግጅት ምዕራፍ እንደሚሆን እና በዛ ልክ ተመዛኞችን ለማብቃት ያግዘናል ያሉት የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዋ ወ/ሮ መሠረት ተሾመ ምዘናው በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር የሚመራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በምዘናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ምዘናው ደረጃውን ጠብቆ ብቃታቸውን ባረጋገጡ አሠልጣኞች በማዕከል የተዘጋጀና የሚመራ መሆኑን በመግለጽ ለተመዛኞች መልካም ዕድልን ተመኝተዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
