1 148
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-1930 days
Posts Archive
1 148
ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
እናት ዓለም ሙከራዊ ተውኔት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ለእይታ በቃ።
የተፈሪ መኮንን ት/ቤት የተመሰረበትን እንዲሁም የቲያትር ትምህርት የተጀመረበትን 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቲያትር ት/ክፍል የተዘጋጀ ሙከራዊ ተውኔት በትላንትናው ዕለት ሰኔ 11/2017ዓ.ም በአገራችን ግዙፉ ቲያትር ቤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ለእይታ በቅቷል።
የተውኔቱ ደራሲና አዘጋጅ አሠልጣኝ (መ/ሐ ቀሲስ) ትጉህ መሐሪ ሲሆን ናጌብ ሲባ በረዳት አዘጋጅነት ፣ ቴወድሮስ በላይ በሙዚቃ አዘጋጅነት አና ኬሮግራፊ ፣ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቲያትር ትምህርት ክፍል ሠልጣኞች በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ዋ/ዳይሬክተር አቶ ባረከ ታደሠ በፕሮግራሙ መክፈቻ ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንጋፋና ግዙፍ ተቋም ሲሆን ለኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ እድገት የራሱን አስተዋጽኦ ያደረገ ባለዉለታ ተቋም መሆኑን አንስተዉ በዛሬዉ ዕለት በቀረበው እናት ዓለም ሙከራዊ ተውኔት ስለሃገር እና ስለእናት (እናትም ሃገር ናት ሃገርም እናት ናት) የሚል መልዕክት በሚያስተላልፈው ተውኔት መደሰታቸዉን እንዲሁም በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በኪነጥበቡ ዙሪያ በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸዉ ገልጸዋል።
በተያያዘም የተዉኔቱ ደራሲና አዘጋጅ (መ/ሐ ቀሲስ) ትጉህ መሐሪ በእለቱ የቲያትር ትምህርት የተጀመረበትን 100ኛ ዓመት የሚገልጽ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።
እናት ዓለም ሙከራዊ ተዉኔት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ሲቀርብ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን በተመልካቹ ዘንድም ከፍተኛ አድናቆት አግኝቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
ሰኔ 11/2017ዓ.ም
የ15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንትየመዝጊያ ፕሮግራም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር ጉብኝት ተጠናቀቀ።
"ብሩህ አዕምሮ በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል የተከበረው 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ማጠቃለያ ፕሮግራም በትላንትናው ዕለት ሰኔ 11/2017ዓ.ም የጉብኝቱ ባለተራ የተፈሪ መኮንን ክላስተር በክላስተሩ ስር ያሉ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አሠልጣኞች ፣ ሠልጣኞች እና በጉለሌ እና በአራዳ ክፍለ ከተማ ስር በኮሌጆቹ ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንተር ፕራይዝ አንቀሳቃሾች በተገኙበት ጉብኝት ተካሂዷል።
በጉብኝቱ ስፍራ በኢትዮጵያዊ ባህል እንግዶችን ተቀብሎ ያስተናገደው አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ጎብኝዎች ከጉብኝት መልስ አረፍ ብለው ሃሳብ እንዲለዋወጡ እርስ በርስ እንዲወያዩ አስችሏቸዋል ።
በስፍራው ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጃችን ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ጉብኝቱ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ዕውቀት የተጋራንበትና ያጋርንበት መሆኑን ጠቁመው በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ለነበረው ኢትዮጵያዊ አቀባበል ምስጋናቸውን ችረዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም
እናት ዓለም ሙከራዊ ተውኔት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ለእይታ በቃ።
የተፈሪ መኮንን ት/ቤት የተመሰረበትን እንዲሁም የቲያትር ትምህርት የተጀመረበትን 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቲያትር ት/ክፍል የተዘጋጀ ሙከራዊ ተውኔት በትላንትናው ዕለት ሰኔ 11/2017ዓ.ም በአገራችን ግዙፉ ቲያትር ቤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ለእይታ በቅቷል።
የተውኔቱ ደራሲና አዘጋጅ አሠልጣኝ (መ/ሐ ቀሲስ) ትጉህ መሐሪ ሲሆን ናጌብ ሲባ በረዳት አዘጋጅነት ፣ ቴወድሮስ በላይ በሙዚቃ አዘጋጅነት አና ኬሮግራፊ ፣ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቲያትር ትምህርት ክፍል ሠልጣኞች በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ዋ/ዳይሬክተር አቶ ባረከ ታደሠ በፕሮግራሙ መክፈቻ ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንጋፋና ግዙፍ ተቋም ሲሆን ለኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ እድገት የራሱን አስተዋጽኦ ያደረገ ባለዉለታ ተቋም መሆኑን አንስተዉ በዛሬዉ ዕለት በቀረበው እናት ዓለም ሙከራዊ ተውኔት ስለሃገር እና ስለእናት (እናትም ሃገር ናት ሃገርም እናት ናት) የሚል መልዕክት በሚያስተላልፈው ተውኔት መደሰታቸዉን እንዲሁም በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በኪነጥበቡ ዙሪያ በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸዉ ገልጸዋል።
በተያያዘም የተዉኔቱ ደራሲና አዘጋጅ (መ/ሐ ቀሲስ) ትጉህ መሐሪ በእለቱ የቲያትር ትምህርት የተጀመረበትን 100ኛ ዓመት የሚገልጽ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።
እናት ዓለም ሙከራዊ ተዉኔት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ሲቀርብ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን በተመልካቹ ዘንድም ከፍተኛ አድናቆት አግኝቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+9
ሰኔ 12/2017ዓ.ም
የ15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንትየመዝጊያ ፕሮግራም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር ጉብኝት ተጠናቀቀ።
"ብሩህ አዕምሮ በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል የተከበረው 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ማጠቃለያ ፕሮግራም በትላንትናው ዕለት ሰኔ 11/2017ዓ.ም የጉብኝቱ ባለተራ የተፈሪ መኮንን ክላስተር በክላስተሩ ስር ያሉ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አሠልጣኞች ፣ ሠልጣኞች እና በጉለሌ እና በአራዳ ክፍለ ከተማ ስር በኮሌጆቹ ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንተር ፕራይዝ አንቀሳቃሾች በተገኙበት ጉብኝት ተካሂዷል።
በጉብኝቱ ስፍራ በኢትዮጵያዊ ባህል እንግዶችን ተቀብሎ ያስተናገደው አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ጎብኝዎች ከጉብኝት መልስ አረፍ ብለው ሃሳብ እንዲለዋወጡ እርስ በርስ እንዲወያዩ አስችሏቸዋል ።
በስፍራው ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጃችን ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ጉብኝቱ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ዕውቀት የተጋራንበትና ያጋርንበት መሆኑን ጠቁመው በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ለነበረው ኢትዮጵያዊ አቀባበል ምስጋናቸውን ችረዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+1
ሰኔ /2017 ዓ.ም
ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ስፖርታዊ ውድድሮች የመዝጊያ መርሀ ግብር ተካሄደ።
15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት '' ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል።
በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች የተካሄዱ ሲሆን የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ ከተሳተፈባቸውና ዋንጫና ሜዳሊያ ያስገኘባቸው ውድድሮች
በወንዶች ቮሊቮል ፣ በሴቶች ጠረጴዛ ቴኒስ፣ በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በቅደም ተከተል
በወንዶች ቮሊቮል 1ኛ ወጥቶ ዋንጫ ፣
በሴቶች ጠረጴዛ ቴኒስ 2ኛ እና 3ኛ ፣ በወንዶች እግር ኳስ 3ኛ በመውጣት የዋንጫና ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል ።
በመዝጊያ ስነስርአቱ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ም/ዲኖች ለዚህ ውጤት ትልቅ አስተዋፅኦ ላደረጉ የስፖርት ክበብ አባላትበሙሉ የስፖርት ክበቡ አሰልጣኞችና አስተባባሪዎች እንዲሁም የስፖርት ክበቡ ደጋፊዎች፣ የኮሌጁ አመራሮች ፣ የኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት እና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
ሰኔ 6/2017ዓ.ም
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ዓለምአቀፉን የትምህርት ጥራት (ISO 21001-2018) ሰርትፍኬት ለማግኘት የመጨረሻውን የምዘና ሂደት አከናወነ።
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ዓለምአቀፉን የትምህርት ጥራት (ISO 21001-2018) ሰርትፍኬት ለማግኘት ከግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ስራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። በመሆኑም በዓለምአቀፍ ስታንዳርድ ለመመዘን ኮሌጁ ራሱን የማደራጀት እና የማስተካከያ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቶ ለመጨረሻው የሰርትፍኬት ደረጃ መድረሱ በዛሬዉ ዕለት ተረጋግጧል ።
ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የመጡ ባለሙያዎች ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተለያዩ መንገዶች ባደረጉት ምዘና እና ክትትል ማለትም በቃለ መጠይቅ(interview) ፣ የሰነድ ግምገማ (document review) እና ምልከታ (observation ) ተቋሙ የተቀመጡ ስታንዳርዶችን በማሟላት ብቁ ሆኖ መገኘቱን የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የISO 21001-2018 የጥራት አመራር ሃላፊ አቶ ሚካኤል ጎኣ ገልጸዋል።
ለትምህርት ተቋማት የሚሰጠው ዓለምአቀፍ የትምህርት አስተዳደር ስርአት ሰርትፍኬት ISO 21001-2018ን ለመተግበር ውጫዊ ምዘና የተደረገ ሲሆን በምዘናውም የተቋሙ መሰረተ ልማቶች ፣ የማስተማሪያ ወርክሾፖች ፣ የቢሮ አስተዳደር ስርአት ፣ የደንበኞች እርካታ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበሠሰብ ስለ ዓለምአቀፉ የትምህርት አስተዳደር ስርአት ISO 21001-2018 ያላቸው ግንዛቤ ትልቅ ቦታ የተሰጣቸው እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
በመጨረሻም ለዚህ ትልቅ ስኬት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በትልቅ ተቋማዊ ራዕይ ለተሳተፉ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ የተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ምስጋና አቅርበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ አለም አቀፉን የትምህርት ጥራት (ISO 21001-2018) ሰርትፍኬት ለማግኘት የመጨረሻውን የምዘና ሂደት አለፈ።
ሰኔ 6 ቀን 2017ዓ.ም
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ አለም አቀፉን የትምህርት ጥራት (ISO 21001-2018) ሰርትፍኬት ለማግኘት ከግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ስራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። በመሆኑም በዓለምአቀፍ ስታንዳርድ ለመመዘን ኮሌጁ ራሱን የማደራጀት እና የማስተካከያ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቶ ለመጨረሻዉ የሰርትፍኬት ደረጃ መድረሱ በዛሬዉ እለት ተረጋግጧል ።
ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የመጡ ባለሙያዎች ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተለያዪ መንገዶች ባደረጉት ምዘና እና ክትትል ማለትም በቃለ መጠይቅ(interview) ፣ የሰነድ ግምገማ (document review) እና ምልከታ (observation ) ተቋሙ የተቀመጡ ስታንዳርዶችን በማሟላት ብቁ ሆኖ መገኘቱን የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የISO 21001-2018 የጥራት አመራር ሃላፊ አቶ ሚካኤል ጎኣ ገልጸዋል።
ለትምህርት ተቋማት የሚሰጠዉ አለምአቀፍ የትምህርት አስተዳደር ስርአት ሰርትፍኬት ISO 21001-2018ን ለመተግበር ሁለት ዙር ዉጫዊ ምዘና የተደረገ ሲሆን በምዘናዉም የተቋሙ መሰረተ ልማቶች ፣ የማስተማሪያ ወርክሾፖች ፣ የቢሮ አስተዳደር ስርአት ፣ የደንበኞች እርካታ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበሠሰብ ስለ አለምአቀፉ የትምህርት አስተዳደር ስርአት ISO 21001-2018 ያላቸዉ ግንዛቤ ትልቅ ቦታ የተሰጣቸዉ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
በመጨረሻም ለዚህ ትልቅ ስኬት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በትልቅ ተቋማዊ ራዕይ ለተሳተፉ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰቦች የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ምስጋና አቀርቧል።
የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
