en
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Closed channel
1 146
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1830 days
Posts Archive
photo content

photo content
+1

በንግስተ - ነገስታት : ዘውዲቱ : ዘመነ - መንግስት : አልጋ ወራሽ : የነበሩት : ልዑል ተፈሪ : መኮንን : ( ኋላ ቀዳማዊ : ኃይለሥላሴ ) በሚያዝያ : ፲፱ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ.ም. በስማቸው : የሰየሙትን : ትምህርት : ቤት : መርቀው : ከፈቱ ። ( በዚህ : ዓመት : ሚያዝያ : ፲፱ , ፳፻፲፯ ዓ.ም. ፻ ዓመቱን : ይይዛል ። ) በዚያን : ወቅት : ከሚሰጡ : ትምህርቶች : በከፊል … - ግዕዝና : አማርኛ - ፈረንሳይኛ - እንግሊዝኛ - ሥዕልና ሙዚቃ - ጅምናስቲክ …..ነበሩ ( ትዝታዬ ፤ መርስዔ ኀዘን : ወልደ ቂርቆስ ። ) ፲፱፻፲፯ ፤ ሳምንታዊው : ብርሃንና : ሰላም : ጋዜጣ : ተመሰረተ ፤ አዲሱን : ሥነ - ሥዕል : የአውሮፓ : መንገድ : ወይም : የአውሮፓ : ዘዴን : የተከተለ : በማለት : ጻፈ :: ተፈሪ : መኮንን : ትምህርት : ቤት : የሥዕል : ትምህርት : መስጠት : ጀመረ ። ( እሰየ : ገብረ መድህን : የሥነ - ጥበብ : ታሪክ : ተመራማሪ :: ) ይህ : ከሆነ : ከ፹፪ ዓመት : በኋላ : በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. አሁንም : ከቴክኒክና : ሙያ : ኮሌጆች : በብቸኝነት : ሥነ - ጥበብን : እያስተማረ : ይገኛል :: እነሆ : ዘንድሮ : ታህሳስ : ፬ , ፳፻፲፯ ዓ.ም. በቀን መደበኛ : ለ ፲፮ ኛ ፣ በማታው : መርሀግብር : ለ፲፬ ኛ : ጊዜ : ተማሪዎችን : ያስመርቃል :: እርስዎም : በዚህ : ታሪካዊ : ዓውደ - ርዕይ : ላይ : እንዲገኙ : ተጋብዘዋል :

............ 🙏🙏🙏🙏.... ክቡራን አሰልጣኞች ዛሬ ታኅሣሥ 2 ቀን 2017 ዓ ም ሊደረገው የነበረው የመምህራን ማኅበር ስብሰባ በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት  ሳይደረግ በመቅረቱ ይቅርታ እየጠየቅን በቀጣይ ስብሰባው የሚደረግበትን ቀን ከኮሎጁ አስተዳደር አካላት እና ዲን ቢሮ ጋር በመነጋገር የምናሳውቅ መሆን በታላቅ አክብሮት ከይቅርታ  ጋር እናሳውቃለን። 🙏🙏🙏

photo content

photo content
+2

እንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ከቻይናው ይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ጋር አብረዉ ለመስራት ተፈራረሙ ። ታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም የእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ (ዘረ-መል) በመነሳት የቴ/ሙ ትብብርና  አጋርነት (TVET partnership) እና ዘመናዊነት (TVET modernization ) ለማጠንከር በዛሬዉ እለት  ከቻይናው ይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል የትብብር ስምምነት (Memorandum of understanding) ተፈራርመዋል። በፊርማ ስነስርአቱ የይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ዉ ዢሊ እና ልኡኮቻቸዉ ከኮሌጃችን አመራሮች ጋር የተወያዪ ሲሆን ይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ከእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ጋር ጠንካራ የተቋም ግንኙነት መፍጠር ፣  የግብአት እገዛ እንዲሁም  የእዉቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር ተግባራት ላይ አብረዉ ለመስራት ተስማምተዋል ። በተያያዘም ልኡካኑ የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅን  የቢዝነስ ፣ ኤስቴቲክስ ፣ ጋርመንት ፣ ሌዘር ፣ የብረት ስራ እና አዉቶ ት/ክፍሎችን ጎብኝተዋል።  ይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ለኮሌጃችን  ሰልጣኞች፣  አሰልጣኞች እና ሰራተኞች በዲጅታል ማርኬቲንግ ፣ live streaming ( video designing), መስኮች በቅርቡ ስልጠና እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን የግብአት እገዛ እንደሚያደርግም ቃል ገብቷል። በእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ በዋና ዲንነት በቅርቡ የተሾሙት የኮሌጃችን ዋና ዲን  አቶ አብዱልበር መሀመድ ናስር እና የኮሌጃችን አመራሮች በፊርማ ስነስርዓቱ እንደገለጹት የተቋም ግንኙነትን በማጠናከር ተቋማችን ማሳደግ እና የእዉቀት ሽግግር  ማድረግ ከቴክኒክና ሙያ እሳቤዎች አንጻር ዋና ተግባር መሆኑን ገልጸው የይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ከኮሌጃችን ጋር አብሮ ለመስራት በመፈራረሙ ምስጋናቸዉን ያቀረቡ ሲሆን የይያንግ ቮኬሽናል እና ቴክኒካል ኮሌጅ ተወካዮችም በስምምነቱ መደሰታቸዉን ፣ በኮሌጁ ያዩት ነገር የበለጠ ተባብሮ ለመስራት የሚያስችላቸዉ እንደሆነ ገልጸዋል። የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

👉👉👉የስብሰባ ጥሪ👈👈👈 ============================== ሰላም ጤና ይስጥልኝ የእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በሙሉ። ============================== 👉 ሐሙስ ማለትም ታህሳስ 03/2017 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2:30 ሰሀት በቴክኖሎጂ ስብሰባ አዳራሽ አስቸኳይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኙ። ✍️ጉዳዩ:- ሀ) የተመደቡ አዲስ አመራሮችን ትውውቅ። ለ) በ 5ወር የተግባር ምዕራፍ በኮሌጁ የተሰሩና በቀጣይ ለመሰራት የታቀዱ አበይት እና ተጨማሪ ስራዎች ገለፃ። ሐ) ከሰራተኞች የሚነሱ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶች እና የሀላፊዎች የስራ አቅጣጫ። .🙏🙏🙏🙏መልካም ጊዜ🙏🙏🙏🙏.

photo content

Delegates from Guangzhou Polytechnic College, led by President Wuhan, visited our college and agreed to collaborate on two ma
+9
Delegates from Guangzhou Polytechnic College, led by President Wuhan, visited our college and agreed to collaborate on two major components: 1. Supporting the college to capacitate the staff members in the area of digitalization, getting sufficient gadgets for its implementation, and trainees got adequate equipment to make them digitally capable citizens. 2. Our second collaboration point was on the implementation of the dual diploma program given in both colleges in a 2-to-1-year modality (2 years enrolled in Entoto and the final year in Chaina Guangzhou).

photo content
+6

ብልሹ አሰራርን ለመከላካል የአሰራር ስርዓት ጥናት ማጥናት አስፈላጊ መሆኑ ተጠቆመ። ህዳር 20/2017 ዓ.ም እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስአበባ ****** የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከኮሌጁ የሪሰርችና ፐብሊኬሽን ቡድን ጋር በመተበባር የሬጅስትራር ጽ/ቤት አሰራር ለመፈተሽና ድጋፍ ለማድረግ የተያዘውን ዕቅድ የኮሌጁ አመራሮች፣ የት/ት ዘርፍ ተጠሪዎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና አስተባባሪዎች በተገኙበት የጋራ አድርጓል። በዕለቱም የአዲስአበባ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከመከላከል ዘርፍ ዳይሬክቶሬት  አቶ ደምስ ረጋሳ እና አቶ ዮሐንስ አበበ የተገኙ ሲሆን ኮሌጁ በራሱ አቅም አሰራሮችን በጥናት በመፈተሽ ችግሮችን ለይቶ ለማስተካከል እየሄደበት ያለው ነገር የማኔጅመንቱን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እና የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ጥናቱ እስኪጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን ገልፀዋል። የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን የሆኑት አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የኮሌጁ የሥነምግባር ዳይሬክቶሬት ኮሌጁን በከፍተኛ ሁኔታ እየደገፈ እና እያገዘ መሆኑንን ጠቅሰው ይህ ጥናት ሲጠናቀቅም የስልጠና ጥራት ውጤታማነት ለማሻሻል የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል። በተጨማሪም  ኮሚሽኑ በየጊዜዉ  የሚያደርገውን ድጋፍ በእርሳቸው እና በኮሌጁ ስም አመስግነዋል።

photo content
+4

ህዳር 2017ዓ.ም ትምህርታዊ ጉብኝት በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካምብሪጅ አካዳሚ ኢትዮጵያ ተማሪዎች የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ለሁለተኛ ጊዜ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት የተለያዩ የስልጠና ዘ
+9
ህዳር 2017ዓ.ም ትምህርታዊ ጉብኝት በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካምብሪጅ አካዳሚ ኢትዮጵያ ተማሪዎች የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ለሁለተኛ ጊዜ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት የተለያዩ የስልጠና ዘርፍ ሾፖችን ከመመልከታቸውም በላይ በሥነ- ጥበብ ትምህርት ክፍል ውስጥ የሥዕል ስራ ልምምድ አድርገዋል ፤ በተጨማሪም በኮሌጁ ምድረ ግቢ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናውነዋል ። ጉብኝቱን የመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጉብኝት ያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰው አጀማመሩም በትምህርት ቤቱ ጥያቄ መሠረት እንደሆነ ገልጸው ክንውኑ ለሁለቱም ተቋማት ስራቸውን ለማስተዋወቅ ከመርዳቱም ባሻገር ለተማሪዎቹ ደግሞ በሙያው ዘርፍ ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ  ወደፊት ስለሚኖራቸው የሙያ ምርጫ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ጨምረው  አብራርተዋል ። በዘንድሮው ዓመት ጉብኝት ያደረጉት የ6ኛ እና የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ይህ የትብብር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መረጃውን አጋርተዋል ።                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

የቀደሞ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት የአሁን የእንጦጦ ፖ/ሊ ቴ /ኮሌጅ  ከ1941 _1956 ዓ.ም ትዝታውች በፎቶ . . . . ኮሙኒኬሽን ቡድን