en
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Closed channel
1 145
Subscribers
-124 hours
-47 days
-1930 days
Posts Archive

photo content
+3

ዕለተ ማክሰኞ ጥር 28/2016 ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡ እናቶች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሰጠ። በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ አማካኝነት በእንጦጦ እየተገነባ ያለው የእንጀራ መጋገርያ ፋብሪካ የእናቶችን ተጠቃሚነት ከፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። ከጉለሌ ክፍለ ከተማ አራት ወረዳዎች የተወጣጡ በዚህ ፕሮጀክት ተጠቃሚ የሚሆኑ ከ400 በላይ ለሆኑ እናቶች የሙያ ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሰጠ። ኦረንቴሽኑን የሰጡት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ስልጠናው ሰኞ የካቲት4 እንደሚጀምር አብስረዋል። አክለውም ስልጠናው ደረቅ ምግብ ዝግጅትና ሂሳብ መዝገብ አያያዝ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ገልፀው ስልጠናውን በብቃት ለማያጠናቀቁ ሰልጣኞች ወደ ስራ ከተሰማሩ በኃላ በኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር በ4ቱ የድጋፍ ማዕቀፎች እገዛ እንደሚደረግላቸው በመጠቆም መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል። በተያያዘም በጉለሌ ክ/ከተማ የወረዳ አንድ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ እና ም/ሰራ አሰፈፃሚ አቶ አለልኝ የማነህ ይህንን ስልጠናና የስራ እድል ላመቻቸው የከተማ አስተዳደሩንና ክፍለ ከተማውን አመስግነው ስልጠናውን  ካጠናቀቁ በኃላ ስራ ለማስጀመር የግብአት አቅርቦት እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። በመጨረሻም የጉለሌ ክ/ከተማ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እንዳሻው ምንይችል ስልጠናው በእንጀራ መጋገር ስራ ተሰማርተው እራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን የሚጠቅሙበት መንገድ የሚፈጥር መሆኑን ገልፀው በፕሮጀክቱ እስከ የካቲት10 ስራ የማስጀመር ተግባር እንደሚከናወን ጠቁመዋል። አክለውም ስራውን ከመጀመራቸው በፊት  የማሽን አጠቃቀም ስልጠና እንደሚሰጣቸውም አመላክተዋል።                                         ኮምንኬሽን ክፍል

photo content

photo content
+7

photo content
+9

photo content
+9

ዕለተ ማክሰኞ ጥር 28/2016 ዓ.ም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጉብኝት ተደረገ። የጉብኝት የተደረገበት ዋና ዓላማ በኮሌጁ  የተከናወኑትን ተግባራትን፣የፈጠራ ስራዎች፣የአሰራር ሂደቶች፣ እና የገቢ ማመንጫ  ዘዴዎችን  በጎ ልምድ በመቅሰም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ  ተቋማዊ ሪፎርም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሆን የለመ ነው። በጉብኝቱ የተሳተፉት የኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላትን በመቀበል የእንኳን ደህና መጣንሁ መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን አቶ ሰበኸዲን  በኮሌጅ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ ተቋማዊ ለውጦች  በኮሌጁ አሰልጣኞች መሆኑን ገልፀዋል ። በተጨማሪም የፕሮጀክቱ ባለቤትና ተሳታፊ የሆኑ አሰልጣኞች ሰለ ሰሯቸው ፕሮጀክቶች ገለፃ ያደረጉ ሲሆን በገለፃውም፦ - በኮሌጁ ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጋር አብሮ ለመራመድ    የሚያስፈልጉ ቴክኖሎጂዎች እና ስርዕቶች እየተዘረጉ     መሆኑን - በኮሌጁ ውስጥ ዲጅታላይዜሽንን በሁሉም ዘርፎች    ለመተግበር  ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና    በተጨማሪም በዕቅድ ለመተግበር    በdevelopment ደረጃ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች እንዳሉ - የውስጥ አቅማቸውን በቴክኖሎጂ ከማጠንከር   ባሻገር የተመረጡ ጥቂት አሰልጣኞችን   በAI(Artifical intelligence) ፕሮግራሚንግ   እውቅና እንዲያገኙ ስልጠናዎችን ለማመቻቸት    እየተሞከረ እንደሚገኝ - እንዲሁም በ2030 ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ለመሆን   የያዙትን ራዕይ ለማሳካት ሁሉም የሚጠበቅበትን   ሀላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ ተገልጿል። በጉብኝቱ በኮሌጁ ውስጥ ያሉ የሪሶርስ ማዕከል፣ የኢንኩቤሽን ማዕከል፣ የዓሳ እርባታ ቴክኖሎጂ ማሳያ ማዕከል፣ የከብትና የዶሮ እርባታ፣ smart class room አደረጃጀትና የመንጃ ፈቃድ ማሰልጠኛ የማስጀመር ሂደት ምልከታ የተደረባቸው ሲሆን በጉብኝቱ መገባደጃ  የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለስ ይግዛው በኮሌጁ ውስጥ የተከናወኑ ተግባራት በአሰልጣኞች መልካም ፈቃድ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልፀዋል ። ይህንን መነቃቃትና የስራ ባህል ቀጣይነት እንዲኖረው ተቋማዊ እንዲሆን ማስቻል በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባም አመላክተዋል ። በመጨረሻም  አቶ ተሾመ ፈይሳ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ  ተመራቂ ሰልጣኞች የተሰሩ የስዕል ስራዎችን ለጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በስጦታ አበርክተዋል።                                        ኮምንኬሽን ክፍል

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

ዕለተ ሰኞ ጥር 27/2016 ዓ.ም የኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በደጃዝማች ወንድይራድ  አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጉብኝት አደረጉ። የጉብኝት መርሀ ግብሩ ዋና ዓላማ በት/ቤቱ የተከናወኑ ተግባራትን ተሞክሮ ወደ ኮሌጁ በማምጣት ተቋማዊ ሪፎርም መፍጠር እና ለት/ቤቱ  ቴክኒካል ድጋፍ መስጠት ላይ ያለመ ነው። የደጃዝማች ወንድይራድ ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የግዥ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ከበደ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በግቢ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በግቢው መምህራን እንደሚከወኑ ገልፀው በዚህም የት/ቤቱ ሰራተኞች ፣ የተማሪ ወላጆች ብሎም  የአካባቢውን ማህበረሰብ የሌማት ትሩፍት ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ገልፀዋል። በጉብኝት መርሀ ግብሩም በት/ቤቱ መምህራን የተሰሩ የጓሮ አትክልት፣ የዶሮ እርባታ፣ ከብት እርባታና ንብ ማነብ ስራዎች ምልከታ የተደረገባቸው ሲሆን በጉብኝቱ መገባደጃ  ከጉብኝቱ ተሳታፊዎች ጥሩ ቆይታእና ምልከታ እንደ ነበር ገልፀው ሀብትን በአግባቡ ከመጠቀም አንፃር  እራሳቸውንና ማህበረሰብን ብሎም ት/ቤቱን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን እንደተመለከቱና ይህንን ተሞክሮ ወደ ኮሌጁ በመውሰድ ተጠቃሚነትን መጨመርና ለሌላ ተቋማት አርአያ የሚሆን ተግባር ማከናወን እንደሚጠበቅባቸው  አመላክተዋል። በመጨረሻም ኮሌጅ በተለያዩ ግዚያት በዙሪያው ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ድጋፎችን ሲያደርግ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት የተለያዩ መጻሕፍትን ለትምህርት ቤቱ በስጦታ አበርክቷል።                                                                         ኮምንኬሽን ክፍል

photo content

photo content

photo content

photo content

ዕለተ እሁድ ጥር 26/2016ዓ.ም በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ ለአሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘና መሰጠት ተጀመረ። የሙያ ብቃት ምዘና ስርዓት በሀገራችን ሲዘረጋ መሰረታዊ ዓላማው በዕውቀት የዳበረ፣ በ
+3
ዕለተ እሁድ ጥር 26/2016ዓ.ም በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ ለአሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘና መሰጠት ተጀመረ። የሙያ ብቃት ምዘና ስርዓት በሀገራችን ሲዘረጋ መሰረታዊ ዓላማው በዕውቀት የዳበረ፣ በክህሎት የበለፀገ በአመለካከቱ የተስተካከለ አምራች የሰው ሃይል አቅምን በምዘና በማረጋገጥ ወደ ኢንዱስትሪው እንዲገባ በማድረግ የሀገራችንን ከድህነት የመላቀቅ ራዕይ ማሳካት በመሆኑ በአዲሱ ቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ መሰረት ጥራቱን የጠበቀ የሙያ ብቃት  አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስርዓት ለመዘርጋት በዛሬው ዕለት 70 ለሚሆኑ ከተለያዩ ኮሌጆች ለተውጣጡ  አካውንቲንግ፣ ሴልስ ማኔጅመንት፣ ሴክሬተሪና ሂውማን ሪሶርስ አሰልጣኞች በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምዘና መሰጠት ተጀመረ።                                            ኮምንኬሽን ክፍል

photo content
+1