" ምክረ ቅዱሳን "
Open in Telegram
““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” — መዝሙር 9፥1 YouTube ➥ https://youtube.com/@kemaizeni?si=uTXDe4WovSBEF0wz Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19
Show more586
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+630 days
Posts Archive
586
በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርርቲያን ስም እንገልጻለን!!
የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ዜና እረፍት የሰማነው በታላቅ ሀዘን ነው።ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የሰላም የፍቅር ፣የአንድነት ተምሳሌት አባት ነበሩ።
በአገልግሎት ዘመናቸው ለአገር አንድነትና ለሰላም ቅድሚያ የሚሰጡ፣የርህራሔና የፍቅር ሰው በመሆናቸው
በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የተወደዱና የተከበሩ የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመላው ኢትዮጵያን ዘንድ በመልካም ስብዕናቸውና በርሕራሔያቸው በታሪክ ሲታወሱ ይኖራሉ።
በእኒህ የኢትዮጵያውያን ሁሉ አባት በነበሩት በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ዕረፍት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
አባ ሳዊሮስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ
586
ትዝ ይለኛል የመጀመርያ ቀን እኔም ትምህርት ካልሄድኩ ብዬ ሰሙዬን ሳስቸግራት....ሰሙዬ የምላት ስለምወዳት እንጂ ሙሉ ስሟ ሰሚራ ነው።እሷምኮ እንድማርላት ትፈልጋለች..ግን ደሞ ለኔ ደብተርና ስክሪፕቶ መግዛት አትችልም።እንኳን ልማር ለምበላውም መስጂድ ስር ቀኑን ሙሉ ለምና ነው ምታጎርሰኝ።እንደውም ሲጠፋ እኔን አብልታ እሷ ሳትበላ ያደረችበትን ቀናቶች መቼም አረሳቸውም.....!!ታድያ አንድ ቀን በጠዋት የለበስኩትን ሸራ እየጎተተች....
"ኢሳም..ኢሳም..ተነስ" አለቺኝ(ገና እንደነቃሁ አይኔን ስገልጥ እንደሁሌው ከብዙ ኮቴዎች ጋ ተፋጠጥኩ።ተኝቼ የሰወችን ጫማ ማየት ልማዴ ነበር....ዛሬ ግን ሰሙዬ እድል አልሰጠቺኝም እጄን አፈፍ አድርጋ ሙጫዬን ሳላነሳ ይዛኝ ስትበር እድገት በጥረት ትምህርት ቤት አደረሰቺኝ...ማታ ካልተማርኩ ብዬ ስላለቀስኩባት ከንክኗት መሆኑ ነው...
"እባካችሁ ቀስ እያልኩ ገዛለሁ ልጄ ከልጆች ጋ ይዋል መንገድ ላይ ነው ምኖረው ደሀ ነኝ በአላህ"እያለች የሆነ ጥቁር አጭር ሰውዬ ፊት ቆማ ትለምን ያዘች
ሰሙዬኮ ልመና አትችልበትም ነበር...መስጂድ በር ላይ እራሱ ሌሎቹ ሲለምኑ እሷ ዝም ነው።"አላህ ያቃል"ትላለች ግን ዛሬ ለኔ ለልጇ ብላ በአላህ ብላ ስትለምን ሰማኋት....ታድያ የሷን ልመና ሰምቶ ማን እምቢ ይላታል??ማንም!!ሰሙዬ እኮ ናት....ሰሙዬ የኔ የዋህ....
በነጋታው ያለ ደብተር ትምህርት ሄድኩ....ያቺ ቡጫቂ ከነቴራ እና ቁምጣዬን ትላንቱን በሙታንቲ ውዬ ሰሙዬ በእንዶድ አጥባልኝ ፏ ብያለሁ።ያው ጫማዬም ታቹ ቢያልቅም ላዩ አያስነቃም...ክፍል እንደገባሁ ደሞ
"ሀ ሁ ትችላለህ?"ብሎ ወሬ ከጀመረኝ ከ መውደድ ጋ ተዋወቅን
ደብተር ባይኖረኝም ብዙ ወረቀት እና እስራስ ሰጠኝ..ጓደኛ ሆነኝ..ከዛ ቀን ወዲህ ተግባብተን አብረን መዋል መጠራራት ጀመርን።የሆነ ቀን ከትምህርር እንደወጣን የሆነ ቦታ ይዞኝ ሄደ።የሚያምር ፀጥ ያለ ግቢ ገባን።ብዙ ባለነጭ ልብሶች ያሉበት ቦታ....የሚጣፍጥ ምግብ የሚሰጥበት ቦታ ገባን
መውደድ ምንድነው አልኩት በሰወች መሀል እየተንሾካሾኩ
ቤተክርስትያን አለኝ
አልገባኝም...ግን ደሞ ምንም ቢሆን እንዲህ ፀጥ ያለ እና የሚጣፍጠጥ ምግብ የሚሰጥበት አይቼ ስለማላቅ ሁሌ እየተከተልኩት መግባት ጀመርኩ....በተለይ ደሞ የሆነች ስእል የምንስማት ነገር ደስ ትላለች። የሆነ የሚጣፍጥ ጠረን አላት።መውደድ "የሁላችንም እናት ናት"ስላለኝ እወዳታለሁ። በዛላይ "የጠየቅኳትን ታደርግልኛለች"ሲል ስለሰማሁ ሁሌ ስእሏ ስር እየሄድኩ "ሰሙዬን አደራ"እላታለሁ.....ሰሙዬ ስላችሁ እንደውም የሆነ ቀን ሰሙዬን አመማትና ብዙ ቀን ከትምህርት ቤት ቀርቼ ትንሽ ሻል ሲላት ሄድኩ።የሚያሳዝነው ግን ዳሪክተሩ ጠርቶኝ ዩኒፎርም የለክም፤ደብተር የለክም፤ትቀራለህ..ስለዚህ ወላጅ አምጣ ብሎ አባረረኝ....አሁን በዛሬ ቀን ቀላጅ ኬት ይመጣል???ሰሙዬ ደሞ አሟታል....
የማውቀው ሌላ እናት መውደድ የሚጠራት ማርያም ናት።ባታናግረኝም እንደ ሰሙዬ ባትቆጣኝም እናቴ ናት ።እሷን ይዤ ከሄድኩ እምቢ አይለኝም ብዬ ቤተክስስትያን ሄጄ ብር ማጠራቀሚያ ላይ ሁሌ ተቀምጣ ማያትን ስእል ሄዤ ስበር ሄድኩ....ብፈራም ከሰሙዬ ህመም አይበልጥም ብዬ እኮ ነው....
እቹት እናቴ..አልኩት ገና እንደደረስኪ እየተንተባተብኩ
አንተ መቀለጃ አደረከኝ??እናትህን አምጣ አላልኩህም ??አለ ዳሪክተሩ አይኑን አጉረጥርጦ እየመጣ chacha
"ወላሂ እናቴ ናት"አልኩት.. ወላሂ ያልኩት እንዲያምነኝ ነበር ስእሏን በደረቴ ማቀፌ ደሞ እንዳይቀማኝ ነው....እሱ ግን አላዘነልኝም ከጊቢ እንድወጣ ሲነግረኝ እያለቀስኩ ተመልሼ ማርያም ጋ ሄድኩና....
መውደድ የሁሉም እናት ናት ብሎኝ የለ??....እና ሲያባርሩኝ ለምን ዝም አልሽ???ሰሙዬ አሟታልኮ...እሷስ አታሳዝንሽም?? አልኳት እንደመውደድ ብርክክ ብዬ እያለቀስኩ
"ታሳዝናለች አንተንም ታሳዝናለህ "የሚል ድምፅ ከጀርባዬ ሰማሁ።ማርያም ያናገረቺኝ መስሎኝ ደንግጬ ነበር ግን የሆነች የሚያምር ነጭ ልብስ የለበሰች ሴትዮ ናት...እፍስ አድርጋ ስታቅፈኝ የማርያም ሚጣፍጠውን ጠረን አሸተትኩት.....ደሞ ሴትየዋ እንባዬን እየጠረገችልኝ....
እኔ አለሁልህ የኔ አባት...እኔ ላልቅስ!! ማርያም ሰምታካለች እሺ ...ብላ ይዛኝ ወጣችና መጀመርያ ልብስ ገዛችልኝ። ከዛ ብዙ ደብተርና ስክሪፕቶ ገዛችልኝ። ከዛ ምሳ ጋበዘቺኝ ።ከዛ ከሰሙዬ ጋ እሷ ቤት መኖር እንደምንችልና እሷ እንደምታስተምረኝ ቃል ገባችልኝ...ማርያም ግን ደግ ናት እውነት
የመውደድ ማርያም የኢሳም ማርያም የሁላችንም ማርያም እንባችንንን ታብስልን!!! ምንም ሆነን ብንሄድ አቤት ምትለን እማምዬ ምልጃዋ አይራቀን!!!
586
ከዝሙት እንዴት ልውጣ
በዝሙት ኀጢአት ለወደቅን ሰዎች አንደኛና አይነተኛ መፍትሄው፥ ንስሐ መግባት ነው። ንስሐ የበደለውን እንዳልበደለ ዘማዊውን እንደ ድንግል ታደርጋለች። ልክ በስጋ ደዌ ስንያዝ ወደ ሃኪም ቤት በመሄድ የህክምና አገልግሎትና ክትትል አድርገን እንደምንድን ሁሉ፤ የዝሙት መንፈስ ገዳይነቱ በስጋ ብቻ ሳይሆን በነፍሳችንም ሞትን የሚያስከትል አስከፊ ደዌ ስለሆነ ከዚህ ለመውጣት፦
1ኛ/ እንደመፃጉ ለመዳን ፈቃደኛ የሆነ ልቦና እና ስለፈፀምነው የዝሙት ኀጢአት ከልብ የሆነ ፀፀት ሊኖረን ይገባል። ለእውነተኛ ንስሐ መሰረቱና ዋነኛው መስፈርቱ ህሊናችን የሰራነውን ጥፋት አምኖ ስንፀፀት ነው።
2ኛ/ ለነፍሳችን ሃኪም የሆነ እንደደዌያችን አይነትና መጠን ቀኖና የተባለውን መድኀኒት እየሰጠ በየጊዜው ክትትል አድርጎ ሙሉ ለሙሉ እስከምንፈወስ ተመላልሰን የሚያክመንና የሚመክረን የንስሐ አባት ያስፈልገናል። “የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።” (ማቴ ፲፮᎓፲፱) ስለዚህ ንስሓ መግባትም ሆነ ንስሐ አባት መያዝ የሰው ትዕዛዝ ሳይሆን የፈጣሪ መመሪያ ነው።
3ኛ/ እግዚአብሔር ያዘዘልንን ንስሐ የተባለውን ፍቱን መድሐኒት በንስኀ አባታችን አማካኝነት ወስድን የሚሰጡንን ቀኖና በአግባቡ መፈፀም አለብን፤ ለዘመናት ከሰራነው ኅጢአት ይልቅ ንስኀ ገብተን በተወሰነ የቀኖና ግዜ የሰራናት ፅድቅ ያንን ሁሉ ስፍር ቁጥር የሌለውን ጥፋት አስፍቃ ወደ መንግስተ ሰማያት ለመግባት እንድንበቃ ታደርጋለችና።
4ኛ/ ንስኀ ገብተን ቀኖናችንን ከፈፀምን በኋላ ከዘለዓለም ሞት ወደ ዘለዓለም ህይወት ተሸጋግረናልና ደግመን በኀጢአቱ እንዳንወድቅ እንደ ንስኀ ሳናቋርጥ የምንወስዳቸው አማራጭ የሌላቸው የፈውስ መድሃኒቶች ወይም መንፈሳዊ ትጥቃችን ደግሞ አብዝቶ መፆም ፣ አብዝቶ መፀለይ፣ አብዝቶ መስገድ ናቸው። እያንዳንዱ ሰፊ የሆነ ትምህርት የሚሰጥበት ቢሆንም እንኳን ነገር ባበዛን ቁጥርም ዋናውን ግንዛቤ ሳናስጨብጥ እንዳንቀር በማሰብ በአጭሩ እንደሚከተለው ገልጸናልና በንስኀ አባቶቻችን መሪነትና መካሪነት በፅናትና በእምነት ሆነን ሁሉንም በአንድ ጊዜ ሳይሆን እንደ መንፈሳዊ እውቀታችን መጠን ደረጃ በደረጃ መፈፀም አለብን። ዋናው ነገር የእያንዳንዳችን የዝሙት አይነት ስለሚለያይ በየግላችን የምንፈተንበት የዝሙት ሃሳብ በምን ምክንያት እየመጣ እንደሚዋጋን በተከታታይ ከሚያጋጥሙን ፈተና አንፃር በራሳችን የህሊና ዳኝነት መዝነን መንስኤውን ካገኘነው መፍትሔው ግልፅ ስለሚሆንልን በዚህ አግባብ እንጠቀምባቸዋለን ማለት ነው።
5ኛ/ ፀሎትን በሚመለከት ጠዋትም ማታም የምንፀልየው ከዘወትር ፀሎት መዝሙረ ዳዊት ና ውዳሴ ማርያም ውጪ ጊዜ የምናገኝ ከሆነ ፥ እንደ መንፈሳዊ እወቀት ደረጃችን መጠን በግላችን በቋሚነት የምንፀልየው ፀሎት ሊኖረን ይገባል። ለምሳሌ ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ ወንጌለ ዮሐንስን፣ ድርሳናትን፣ መዝገበ ፀሎት እና ስለ ንስኀ ትምህርት የሚሰጡ መፃህፍትን በተጨመሪ ማንበብና መፀለይ ይቻላል።
6ኛ/ ስግደትን በሚመለከት፦ አብዝቶ በመስገድም እርኩስ መንፈስን መዋጋት ይቻላል። ስንሰግድ በፊታችን መስቀል ወይም ቅዱሳን ስዕላት ወይም ወንጌል አድርገን በትዕምርተ መስቀል እያማተብን ጉልበታችንን እና ግንባራችንን መሬት እያስነካን መሰገድ ይገባል።
586
✨🌹ይእቲ ተዓቢ እምአንስት እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት መድኃኒቶሙ ለነገሥት አክሊል ንጹሕ ለካህናት ብርሃኖሙ ለከዋክብት✨🌹
✨🌹ከሴቶች ይልቅ ከፍ ከፍ ትላለች ፡፡ የሰማዕታት እናታቸው ነች ፡፡ የመላእክት እኅታቸው ነች ፡፡ የነገሥታት መድኃኒታቸው ነች ፡፡ ለካህናት ንጹሕ አክሊላቸው ነች ፡፡ የከዋክብት ብርሃናቸው ነች ፡፡✨🌹
586
🍂 “አዘክሪ ድንግል አንብዐ መሪረ… “ #ድንግል_ሆይ ከአይኖችሽ ፈሶ በተወዳጁ ልጅሽ ፊት ላይ የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ 🙏🏽✨
እመቤታችንም ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ትዕማን ወደምትባል አንዲት ከበርቴ ባለሀብት ቤት ሄዳ ቁራሽ እንጀራንና ለልጇም ጥቂት ወተትን ለመነቻት፡፡
✨
ያቺ ክፉ ሴት ግን ልብን በሀዘን የሚሰብር ክፉ ንግግርን ተነጋረቻት፡፡ ጻድቅ ዮሴፍም ‹‹ #እንግዳን_ካለ_ይሰጡታል_ከሌለ_በሰላም_ይሸኙታል_እንጂ_ለምን_ክፉ_ንግግርን_ትናገሪያታለሽ?›› እያለ ሲነጋገሩ አሽከሯ ኮቲባ የእመቤቷን ቁጣ ሰምታ መጥታ ጌታችንን ከመሬት ላይ ጥላ እንደ ድንጋይ አንከባለለችው፡፡
✨
እመቤታችንም እጅግ ደንግጣ እያለቀሰች ልጇን ፈጥና ልታነሣው ስትል ዮሴፍ ‹‹ #ተይው_አታንሽው_ኀይሉን_ያሳይ›› አላት፡፡
✨
ያንጊዜም ትዕማንን ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻት፡፡ ገረዷ ኮቲባም በለምጽ ተመታች፡፡ በቤታቸውም ውስጥ በሕይወት የቀረ የለምና የሩቅ ቤተሰቦቿም ጦጣ ሆነው ከተራራ ወደ ተራራ ሸሹ፡፡ እመቤታችን ፣ ዮሴፍና ሰሎሜም በትዕማን ቤት 6 ወር ከተቀመጡ በኋላ መልአኩ ተገልጦ ከዚያ እንዲወጡ አዘዛቸውና ወጡ፡፡
✨
🙏🏽አዘክሪ ድንግል አንብዐ መሪረ
ዘውኅዘ አምአእይንትኪ
ወወረደ ዲበ ገጸ ፍቁር ወልድኪ 🙏🏽
🍂 #ድንግል_ሆይ ከአይኖችሽ ፈሶ በተወዳጁ ልጅሽ
ፊት ላይ የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ ..
586
🙏🙏🙏❤️❤️❤️
የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምልጃ እና በረከት አይለየን
ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው
ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ አባታችን በተወለዱ ጊዜ አንደበታቸው ከምስጋና የተገኘ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ቋድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡
አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር ሲቆዩ በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ልጅ እንዲሰጣቸው ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡
ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡
አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡
ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡
አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው መጋቢት አምስት አርፈዋል፡፡
በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙ ት አ ን ሳ
ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-
0918077957 ..
586
+1
በዓል ዘገብረ ተኣምር !!
እቲ ዝነወሓን ብሕታውን ጉዕዞ ታቦት ዘገበረ ተኣምር ተጀሚሩ።
ታቦት ኣቡነ -ገሪማ በብዓመቱ 29 መስከረም ካብ እንዳ ኣቡነ ገሪማ ገዳም ተበጊሱ ናብ ደብረ መንክር ቅዱስ ሚኪኤል ዓድዋ ብድምቀት ተዓጂቡ ብምውራድ 30 መስከረም ብድምቀት ናብ ቦትኡ ገዳም ኣቡነ ገሪማ ይምለስ።
586
✨🌹 #ቅድስት_አርሴማ 🌹✨
የንጉሥ ድርጣድስ የመከራ ጽዋ ሳያስፈራት ምድራዊ ሀብትን እና ሹመትን በመናቅ በሐይማኖቷ ጸንታ በመስከረም 29 ቀን አንገቷን ተሰይፋ የሰማዕትነት አክሊልን የመቀዳጀቷን በዓል እናከብራለን ። 🙏🏽
ከእርሷም ጋር በሐይማኖት በገድል ጸንተው የሚኖሩ ሃያ ሰባቱ ቅዱሳን አብረዋት ሰማዕት ሆነዋል። ✨
🌹 #ሰላም_ለጸዓተ_ነፍስኪ 🌹
ወደ አዘነበለ አንገትሽ በሚያልፍ ሰይፍ ጊዜ
ለነፍስሽ መውጣት ሰላምታ ይገባል።
አርሴማ ሆይ መሥዋዕትን በሚቀበል ጌታሽ ዘንድ
የተረፈ ረድኤትሽ በእኔ ላይ ይወርድ ዘንድ
በአንደበቴ እለምንሻለሁ ።
የተቆጠሩ ሞትሽ ይህን አሳይቶኛልና
✨ የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ
ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን✨
ቃልኪዳኗ ሀገራችን ኢትዮጵያን
ከክፉ ይሰውርልን
🙏🏽🙏🏽🙏🏽
586
ይህ ቃል ያስደነግጠኛል
ምን ያስደነግጣችኋል? ሞት ነውን? ይሄማ ከሞት በኋላ ሕይወት መኖሩን ለማያምኑት አይደለምን?
ረሀብ ነውን? ይህስ ቢሆን “ስለ ጽድቅ የሚራቡ ብጹዓን ናቸው ይጠግባሉና” ማቴ. 5፥6 የሚለውን ቃል ኪዳን ለማያምኑት አይደለምን?
ስደት ያስፈራል እንዳትሉኝ ክርስቶስ እንደተሰደደ ለማያምኑት ነው።
እኔ ግን ሳስበውም ሆነ ሳነበው የሚያስደነግጠኝ “የማይጠቅም ይህንን ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል” ማቴ. 25፥30 የሚለው ነው።
ከቀናት መካከል ይህ የፍርድ ቀን ያስፈራኛል፤ ከቃላት መካከልም ይህ ያስደነግጠኛል። የጌታ ቃል ነው ከማን ዘንድ ሂደው ይህንን ፍርድ ያስሽሩታል? ባሮቹን ሊቆጣጠር በፈለገ ጊዜ በስንፍና ያገኘውን ይህንን ባሪያ ሊራራለት የሚችልበት ምንም በጎ ስራ አላገኘበትምና የሚገባውን ፍርድ ፈረደበት።
ይህ ሰው መክሊቱን መቅበሩ ብቻ ይመስላችኋልን? ለፈጣሪው ያለውንም ንቀት ተመልከቱት። “ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ ፈራሁም ሂጀም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት” ማቴ. 25፥25 ነበር ያለው። የድፍረት ኃጢአት የገዛው ሰው ነው። “ጌታ ሆይ” ብሎ ሲጀምር ሐዋርያትን ወይም ከቅዱሳን አንዱን ይመስላል ነገር ግን ከክፉ ሰዎች እንደ አንዱ ይናገራል። “የሰነፍ ከንፈሮች ግን ራሱን ይውጡታል የአፉ ቃል መጀመሪያ ስንፍና ነው የንግግሩ ፍጻሜም ክፉ እብደት ነው” መክ. 10፥12 ብሎ መጽሐፍ እንደተናገረ የማይጠቅም ንግግርን ተናገረ።
ለስንፍናው እግዚአብሔርን ተጠያቂ ሲያደርገው ተመልከቱ።
የእነዚህ ባሮች ጌታ በመጣ ጊዜ በመጀመሪያ “አውጡና ጣሉት” የሚላቸው ጳጳሳቱን ሊቃነ ጳጳሳቱን ካህናቱን ነው። በማይገባ ከምዕመናን ጋር የተቀላቀለውን በውግዘት ከቤተ ክስቲያን አውጥተው ለሰይጣን እንዲሰጡት ታዝዘዋል። ከቤተ ክርስቲያን ከተለየ ከሰማያዊቷ ቤተ መቅደስም የተለየ ነው። በቤተ ክርስቲያን በኩል ያላገኘውን ክርስቶስ በመንግስተ ሰማያት ሊያገኘው አይችልም። በኋላ ደግሞ መላእክት ናቸው ከገነት ከመንግስተ ሰማያት ውጭ ይተዉታል።
ጌታ ሆይ አፋችን በተናገረው የስንፍና ልክ ትፈርድብናለህን? የልባችንንስ ጠማምነትን ተመልክተህ ከምሕረትህ ውጭ ታደርገናለህን? ይህስ አይሁንብን ጌታዬ! በፊትህ ኃጢአቱን ለሚናዘዝልህ ሰው በአንድ ቀን ለቅሶ የዘለዓለም ደስታን ትመልሳለህ በፊትህ የድፍረት ኃጢአትን ለአንድ ቀን የሚሰሩትን የዘለዓለም ለቅሶን ታመጣባቸዋለህ።
በጻድቃን ዘንድ አንድ ቀን ብዙ ናት በዋዘኞች ዘንድ ግን በከንቱ የምታልፍ ተራ ነገር ናት። ጻድቃን አንተን ስለሚያስቡ ዘወትር ያተርፋሉ፤ ኃጥአን ግን አንተን ስለሚረሱ ዘወትር የዘለዓለም ሕይወታቸውን ይከስራሉ።
ፍሬ አገኝባታለሁ ብለህ መጥተህ ፍሬ ያጣህባትን በለስ ለአንድ ዓመት ብቻ ታግሰሃታልን? ደግመህስ ምናልባት ለከርሞ ብታፈራ ብለህ ዕድል ሰጥተሃት የለምን? ጌታ ሆይ ለኛም ዕድል ስጠን! ምናልባት ለከርሞ ብንጠቅም “ይህን የማይጠቅም ባሪያ ከዚህ አውጡት” ብለህ አትፍረድብን።
የተራቡትን ባየናቸው ጊዜ ዝም ብለናቸው ያለፍነው በኛ ዘንድ ያስቀመጥኧው መክሊት ያለ መሆኑን ረስተን ነው። እኔ እጅ ላይ ያስቀመጥሀትን ቀዝቃዛ ውኃ ከተጠሙት ሰዎች እጅ ሳላደርሳት እንደቀበርኋት አትምጣብኝ።
ምጽዋት የሚጠይቁንን ቸል ያልናቸው በእጃችን ያለው ገንዘብ ያንተ መሆኑን ዘንግተን የራሳችን መስሎን ነው። አንተ የተራቡትን ባጠገብሃቸው ቀን የተረፈውን እንጀራ እንዲሰስቡት አድርገህ ነበር ማቴ. 14፥20 በየጊዜው የተራበ መጥቶ እንዲጠግብበት ነው። እኛ በልተን ያተረፍነውን እንኳን ድሆች እንዳይበሉት እጃችንን ጠርገንበት የምንነሳ ግፈኞች ነን። ድሆች እርቧቸው ያለቀሱት ለቅሶ የኛን ደስታ እንዳይቀማን በጉልበት ያስቆምናቸው ለቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት መጣል የሚችል ጌታ ያላቸው መሆኑን ረስተን ነው።
የበደሉንን ይቅር ያላልነው አንተ በደላችንን የረሳህልን መሆኑን ባናስብ ነው። እኛ ለወንድሞቻችን ከምንተወው ይልቅ አንተ ለኛ የተውህልን ይበዛ ነበር እኛ ግን ልብ አላደረግንም።
በዚህ ሁሉ ዓይንህ እንዳየች አትፍረድብን። በወንጌል ከተጻፉልን ሁሉ እንደዚህ ያሉ የሚያስደነግጡ የፍርድ ቃላት አሉ።
እናንተም የሚያስደነግጣችሁን ቃል ከታች ጻፉልኝ
©️ሊቀሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ
586
+ ጌታዬን በቅዳሴ አየሁት! +
"ራእየ ኒፎን የተሰኘውን ድንቅ መጽሐፍ የተረጎሙልን ቀሲስ ታምራት ውቤ በመጽሐፉ ላይ ቅዱስ ኒፎን ስለ ሥርዓተ ቅዳሴው የተመለከተውን በሚያትትበት ክፍል (ገጽ 206) ላይ በኅዳግ ማስታወሻ አድርገው ያስቀመጡት እጅግ ድንቅ የሆነ እውነተኛ ታሪክ አለ። ቅዳሴው ምን ያህል ክቡር እንደሆነ የሚያሳይ ነውና፥ ላጋራችሁ ወደድኩ። በኅዳግ ማስታወሻው ላይ ቀሲስ ታምራት ውቤ እንደሚከተለው ጽፈዋል፦
---
አንዲት የመንፈስ ቅዱስ ልጄ ምክረ ካህን ተቀብላና አስፈላጊውን የጥንቃቄ ዝግጅት አድርጋ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ቢያንስ አርባ ቀን ሳያልፍ ለምን እንደማትቀበል አጥብቄ ስጠይቃት እጅግ ውስጥን የሚነካና የሚያስደነግት አንድ ገጠመኟን አጫወተችኝ። ከእርሷ ሰማሁት ለቀደሙ የበቁ አበው ተገልጦ በመጽሐፍ ያነበብሁት እንጂ ይህ ድንቅ ምሥጢር የተገለጠለት ሰው አጠገቤ ተቀምጦ በዚህ መልኩ እሰማዋለሁ ብዬ ፈጽሜ አስቤው የማላውቀው ነው የሆነብኝ። ጆሮዎቼ ድንቅ ሥራውን እንዲሰሙ ለፈቀደልን ጌታዬ አምላኬና መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለሙ ክብር ይግባው።
“አንድ ቀን በሰንበተ ክርስቲያን ቅዳሴ ተካፍ የጌታን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ተዘጋጅቼ ቤተክርስቲያን ሄድኩ” በማለት ታሪኩን ታጫውተኝ ጀመር። “ቅዳሴ ስካፈል ቆይቼ ከቅዱስ ምሥጢር የምንካፈልበት ሰዓት ሲደርስ በውስጤ ጸሎት እኣደረስኩ ከሌሎች ከተዘጋጁ ጋር ለመቀበል ተራዬን መጠበቅ ያዝሁ። መጋረጃው ተገልጦ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ካህናቱ ከመቅደስ ሲወጡ ግን የማየው የተለየ ሆነብኝ። ካህናቱ ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ በመግነዝ የተጠቀለለ ሰው ከመቅደስ ተሸክመው ወጡ። ያየሁት ነገር እንግዳ ስለሆነብኝ ምናልባት በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን ስለ ሄድሁ የእንቅልፍ ስሜት ተጫጭኖኝ ስለ መሰለኝ አንቀላፍቼ ወይም ነቅቼ እንዳለሁ ለማረጋገጥ የራሴን ሙከራ አደረግሁ። በፍጹም አላንቀላፋሁም! አሁንም ስፈራ ስቸር እይታዬን የጌታችንን ቅዱስ ጅጋውንና ክቡር ደሙን ወደምንቀበልበት ወደ ቅድስቱ አደረግሁ። አሁንም የምመለከተው ግን ተመሳሳይ ነው። ከፊት ያለው ሰው እየተቀበለ ሲመለስም ይታየኛል። አሁንም የማየው ግን በመግነዝ የተጠቀለለ ሰው ካህናቱ ተሸክመው ቆመው ነው።
የእኔም ተራ ሊደርስ እየተቃረብኩ ነው። ልደርስ ትንሽ ሲቀረኝ በቤተክርስቲያን ምንማረው ቀስ በቀስ ወደ ኅሊናዬ መምጣት ጀመረ። ‘የምንቀበለው ቅዱስ ሥጋው ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው ነው’ እየተባለ በሚገባ ተምሬያለሁ። የምመለከተውም በዕለተ ዓርብ ዮሴፍ ዘአርማትያስና ፈሪሳዊው ኒቆዲሞስ በንጹሕ በፍታ ገንዘው በአዲስ መቃብር ሊያኖሩት ሲወስዱት የነበረውን ሁኔታ ነው። ካህናቱ ተሸክመው ከመቅደስ ሲወጡ የተመለከትሁት ምን እንደሆነ በተረዳሁበት ቅጽበት መንቀሳቀስ አልቻልኩም። ከፍርሃቴ የተነሳ ላብ አሰጠመኝ። ሰልፉን ለቅቄ ባለሁበት ተንበርክኬ ካህናቱ ከቤተመቅደስ ይዘውት በወጡበት ሁኔታ እንኪመለሱ ተመለከትሁ። ከዚያች ቀን በኋላ ደፍሮ ወደ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ መቅረብ አቃተኝ።” ስትል አጫወተችኝ።
እኔም እንዲህ ኃጢአትና ክፋት በመካከላችን፤ እግዚአብሔርን አለመፍራት፥ ድፍረትና ቸልተኝነት በመቅደሱ በሠለጠነበት በዚህ ዘመን ምሕረቱን ከእኛ ያላራቀ እግዚአብሔርን አመሰገንሁ። ልጄንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ይህንን የገለጠላት እንድትርቅ ሳይሆን ክብሩንና አማናዊነቱን እንድትረዳው መሆኑን አሳምኜ ከመቀበል እንዳትርቅም አበረታትቼ ላክኋት። ለእርሷ የተገለጠው ድንቅ ነገር ለሁላችን ትምህርት እንዲሆን ፈቃዷን ጠይቄ እነሆ ተጻፈ። "
እምወደው ፀሃፊ
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom
586
+ የሰጠኸኝ ሴት +
እግዚአብሔር አዳምን "አትብላ ካልሁህ ዛፍ በላህን?" ብሎ ጠየቀው:: አዳምም :- ከእኔ ጋር እንድትሆን የሠጠኸኝ ሴት ከዛፉ ሠጠችኝና በላሁ አለ::
የሰጠኸኝ ሴት! በጣም ይገርማል:: ሚስቴ አላለም::
አዳምና ሔዋን የተገናኙ ቀን አዳም ያለውን አስታውሱ
"ይህች አጥንት ከአጥንቴ
ይህች ሥጋ ከሥጋዬ" ብሎአት ነበር::
ምንም እንክዋን አዳም ወላጆች ባይኖሩትም ሰው እናትና አባቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ብሎም ነበር::
ራቁታቸውን ቢሆኑም አይተፋፈሩም ነበር::
አሁን በራቁቱ ብቻ ሳይሆን በሔዋንም አፈረባት::
እናትና አባቱን ይተዋል እንዳላለ ሔዋንን ራስዋን ተዋት::
ከሚስቱ ጋር መተባበር ቀርቶ ክስ ጀመረ::
አካሌ አጥንቴ ሥጋዬ ማለቱ ቀረና የሠጠኸኝ ሴት አለ::
የጫጉላው ጊዜ አለፈና ከሚስትነትዋ ሴትነትዋ ብቻ ታየው::
በጋብቻ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር የሠጠንን ነገር
ሁሉ ቀድመን የራሳችን እናደርጋለን ነገሮች ሲበላሹ ግን ባለቤትነቱን ወደ እርሱ እንመልሰዋለን::
የሠጠኸኝ ሥራ
የሠጠኸኝ ወላጆች
የሠጠኸኝ ሰፈር
የሠጠኸኝ ሀገር
የሠጠኸኝ መሪ
የሠጠኸኝ ጉዋደኞች
የሠጠኸኝ ደካማ ሥጋ
የሠጠኸኝ ዓይን
ትናንት ሲሠጠን ዘምረን የተቀበልነውን ሥጦታ ዛሬ ለምሬት እንጠቅሰዋለን:: የሠጠኸኝ የሠጠኸኝ .... ሠጠኝና በላሁ ብለን ቀርጥፈን ለበላነው ዕፀ በለስ ፈጣሪን እንከስሰዋለን::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 17 2012
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
586
#መልአኩ_ቅዱስ_ገብርኤል ሆይ! አናንያን፣አዛርያን፣ሚሳኤልን ከሚነድ እሳት እንዳወጣሃቸው እኛንም ልጆችህን ከሚያስፈራን የሚያስጨንቀን ነገር ሁሉ ጠብቀን፣ ከገባንበት እሳት አውጣን አሜን!
በችግራችሁ ጊዜ ከሰው አለቃ ይልቅ የመላእክት አለቃ ከእሳት ከመከራ የሚያወጣው ቅዱስ ገብርኤል ይድረስልን አሜን።
