en
Feedback
" ምክረ ቅዱሳን "

" ምክረ ቅዱሳን "

Open in Telegram

““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” — መዝሙር 9፥1 YouTube ➥ https://youtube.com/@kemaizeni?si=uTXDe4WovSBEF0wz Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19

Show more
586
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+630 days
Posts Archive
የአርሲ ክርስቲያኖች ግድያ ዛሬም ቀጥሏል። ግድያው እንዲሁ እንግደላቸው ተብሎ የተፈፀመ አይደለም። በትርክት የተደገፈ እንዲሁም በአክራሪዎች ርዕዮተዓለም የሚመራ ጭፍጨፋ ነው። ላለፈውም፣ ለዛሬውም፣ ለሚመጣውም የኢትዮጵያ ችግር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ብቸኛ ተጠያቂ የሚያደርጉ ወገኖች ናቸው ይሄንን ግድያ የሚያቀነባብሩት እና የሚያስፈፅሙት። "ክርስቲያኖች ዛሬ የሚገደሉት ትናንት አባቶቻቸው እና አያቶቻቸው ባጠፉት ጥፋት ስለሆነ ነው" እያሉ ግድያው ትክክል ነው ብለው በአደባባይ የሚሰብኩ ሰዎች ያሉበት ሀገር ነው። አክራሪዎች በየሆቴሉ በሚጠሩት ስብሰባ በየሚዲያው በሚያስተጋቡበት ፕሮፓጋንዳ ጠላቶቻችን በአጭሩ ሲገለፁ "ኦሮቶማራ" ይባላሉ ብለው የኮድ ስም የሚሰጡበት እና ግድያውን ቀድመው የሚያመቻቹበት ሀገር ነው። ከምንም በላይ የሚያሳዝነው ግን ይህ ግድያ በቤተክርስቲያን አባቶች ሳይቀር ዋጋ ያልተሰጠው መሆኑ ነው። የሌሎች ሀገራት ቤተክርስቲያናት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳውያን ለሚፈፀመው ግድያ ሀዘናቸውን በሚገልፅቡት ዘመን የእኛዎቹ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ አድርገው ሁሉንም ነገር በዝምታ የሚመለከቱበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። የክርስትኖች ግድያ የሚፈፀመው ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ በተዘረጉ ረዣዥም እጆች ነው። "ይህንን አደጋ ምን ያክሎች ተረድተውታል?" የሚለው ጥያቄ ደግሞ ሌላኛው አሳሳቢ ጉዳይ ነው። Without understanding the extent of the danger, you’ll never be able to deter it. እየተስፋፋ ከመጣው የክርስቲያኖች ግድያ ጀርባ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ አካላት አሉበት። ቢያንስ በፋይናንስ ድጋፍ እና በርዕዮተዓለም ዕሳቤ!

photo content

““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” — መዝሙር 9፥1 Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ http
+3
““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” — መዝሙር 9፥1 Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19

🍃🥀“#እርሱ_ደሙን_አፍስሶልናል ስለዚህ ሌላ ደም መፍሰስ የለበትም!” "በክርስትናችን በሃይማኖታችን መገደላችን የሚቆመው መቼ ነው? ነፃነት እንፈልጋለን:: የሰው ልጆች ደም በከንቱ መፍሰስ መቆም
🍃🥀“#እርሱ_ደሙን_አፍስሶልናል ስለዚህ ሌላ ደም መፍሰስ የለበትም!” "በክርስትናችን በሃይማኖታችን መገደላችን የሚቆመው መቼ ነው? ነፃነት እንፈልጋለን:: የሰው ልጆች ደም በከንቱ መፍሰስ መቆም አለበት:: ይኼ ፖለቲካ አይደለም:: ሰላም መሻት ፣ ዕረፍት መፈለግ ፣ አንሙት ማለት ፖለቲካ ሳይሆን ሰብአዊ መብት ነው:: ሰው መሆን ነው:: ደከመን:: ብዙ ጊዜ ሰማን:: እናንተም በእኛ ፈረዳችሁብን:: እናንተም ወቀሳችሁን:: እውነት አላችሁ:: ግን ለማን ነው የምንነግረው ይኼንን? ማን ነው የሚሰማን ይኼንን? ማን ነው የሚያቆመው ይኼንን? ተለማመድነው እኮ:: ስንቶቻችን ስናልቅ ነው የሚቆመው? ይብቃ:: ሕዝባችን ዕረፍት ይፈልጋል:: ሞት ሰለቸን በቃን:: ደም መፍሰስ ሰለቸን:: ይበቃናል:: ምድሪቷ ዕረፍት ያስፈልጋታል:: ሕዝቡ ዕረፍት ያስፈልገዋል:: ስለ እኛ ደም ፈሰሰ እኮ:: በእርሱ ቁስል ተፈወስን እኮ:: ሌላ ደም አያስፈልግም:: መከራችን እንዲያበቃ ጸልዩ" ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሊቀ ጳጳስ ጥቅምት 27 2018 ዓ.ም. የተናገሩት የብፁዕነትዎ በረከት ይደርብን::

💔"በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት መርቲ ወረዳ በሚገኘው ጋዶ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በኋላ 5 ምእመናን የእርሻ ሥራቸውን
+2
💔"በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት መርቲ ወረዳ በሚገኘው ጋዶ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በኋላ 5 ምእመናን የእርሻ ሥራቸውን አጠናቀው ምሳቸውን እየበሉ ባሉበት ጊዜ በታጠቂዎች በተከፈተባቸው የተኩስ ጥቃት መገደላቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ የደረሰን መረጃ ያሳያል፡፡ በተጨማሪም ከተገደሉት ውጪ ሌሎች 3 ምእመናን ደግሞ ታግተው የተወሰዱ ሲሆን እስከ አሁንም የደረሰቡት እንዲሁም ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡ ይህን የምእመናኑ የግድያ እና የአፈና ተግባር ከሰሞኑ በሀገረ ስብከቱ እንደነበረው ሁሉ ተባብሶ የቀጠለ መሆኑን በመረጃው ተነግሯል፡፡ በተለይም ላለፉት ሁለት ዓመታት የገጠር ቀበሌው እና በውስጡ የሚኖሩ ምእመናን ከስጋት ነጻ ሆነው ኖረው አያውቁም፡፡ የተገደሉት ምእመናን ሥርዓተ ቀብራቸው በአቦምሳ ከተማ በሚገኘው በደብረ ገነት ትንሣኤ ብርሃን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እንደተፈጸመ በመረጃው ተመላክቷል፡፡ Mahibere Kidusan Broadcast Service - ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት

የቤተክርስቲያን አባቶች ሆይ ደግመን ደጋግመን ይሄንን ቃል እንናገራለን። ➘ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅርዋ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት የምትሠራበት ጊዜም አሁን ነው:
የቤተክርስቲያን አባቶች ሆይ ደግመን ደጋግመን ይሄንን ቃል እንናገራለን። ➘ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅርዋ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት የምትሠራበት ጊዜም አሁን ነው:: ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ዓይነት ጊዜ የሚያሳየው ምላሽ ከሌለ ሌላ ቀን ቢጣራ የማይሰማውን ቤተ ክርስቲያን አልባ ክርስቲያን በራሱ ላይ ይፈጥራል:: ““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።”    — መዝሙር 9፥1 Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19

““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” — መዝሙር 9፥1 Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19

““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Ga
““አቤቱ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ።” Face book➥ https://www.facebook.com/share/1A9Keo2sQ4/ Telegram ➥ https://t.me/Gabrielson_19

We request your voice to raise awareness of the suffering of Ethiopian Orthodox Christians who have faced targeted violence f
We request your voice to raise awareness of the suffering of Ethiopian Orthodox Christians who have faced targeted violence for their Faith. Please share and stand for human dignity and religious freedom. World Council of Churches Human Rights Watch Amnesty International United Nations Human Rights BBC News Africa BBC World Service CNN Fox News Washington Post United States Commission on International Religious Freedom Fox News Coptic World Human Rights First #PrayForEthiopia #FaithOverFear #PowerOfPrayer #ChristOurHope #FaithfulTogether #KeepTheFaith #TrustInGod #FaithEndures #FaithInAction #ChurchInPrayer #PrayersForPeace #LightOfChrist #FaithUnitesUs #FaithThatHeals #DivineProtection #GodIsWithUs #SpiritualStrength #FaithfulCommunity #ChristOurRefuge #JusticeForEthiopia #StopPersecution #ProtectTheFaithful #VoiceForTheVoiceless #FaithUnderFire

https://vm.tiktok.com/ZMHcAdm7QmPyw-uZ0Gp/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

*በአንድ ወቅት* በዝሙት ስራዎ በከተማው የምትታወቅ ሴት የምታገኘውን ገንዘብ ትመጸውት ነበር። ቅዱስ አባ ጳውሚን ይኽን ተግባሯን ሰምቶ ሰዎችን ማጠያየቅ ጀመረ ። እንዴት ነች ይኽን መጥፎ ስራዎን ትታለችን ?ለውጥ አላት? ቢላቸው ነገሩን አጋነው ከራሷ አልፋ ሰዎችንም ቀጥራ ቋሚ መታዳደርያዎ እንዳደረገችው ነገሩት ።ይኽች ሴት ወደ እዚኽ ቅዱስ አባት መምጣት እንደምትፈልግና እንዲጸልይላት እንደምትፈልግ ነገር ግን እነዚኽ ሰዎች ተጸይፈዎት እንዳላመጧትም ደረሰበት ። ይኽ አባት ካለችበት ቦታ ሄደ።ከዚኽ በፊት  የእግዚአብሔርን ቃል ሲጸልይ ሰምታው ስለነበር እንዳየችው እግሩ ስር ወድቃ ማልቀስ ጀመረች ። እግዚአብሔር ይቅር እንዲለኝ ጸልይልኝ :ከአሁን ጀምሮ እከተልኸለኹ እያለች አምርራ አለቀሰች ። እሱን ተከትላ ወደ ሴቶች ገዳም ገባች። በምንኩስና መላ ዘመኗን እግዚአብሔርን አገለገለች ። *#ተስፋ የለኝም* :እግዚአብሔር አይምረኝም አትበል(ይ) ምንም ይሁን ማንነትኽ አንተን የሚወድኽ እግዚአብሔር ይቅር ይልኸል ተስፋ አትቁረጥ። # *ዱርየ ነው* :ጸጉሩን ይፈትላል :ሱሪውን ዝቅ ያደርጋል :ሜካፕ ታበዛለች:ሱሪ ትለብሳለች በሚል መደምደምያ ከምንፈርድባቸው በፍቅር እናቅርባቸው እመኑኝ ከእኛ የተሻሉ ታዋቂ ክርስትያኖች ይሆናሉ ። # *የምንሰጠው* ምጽዎት በእኛ ንፉግነት ሰርተኽ አትበላም :እጅ እግር እያለኽ ብለን እየተሳደብን የሰጠነው ሳይሆን በፍቅር የሰጠነው ምጽዎት በሰማይ ዋጋ አለው ። ቆርኔሌዎስ ..“... ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ።” ሐዋ10፥2

https://vm.tiktok.com/ZMHvt2AvY1uTS-AeGgm/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል፦ አንዳንድ ቀን ድኾችን ስትረዱ አያለሁ፡፡ ነገር ግን በጣም አዝንባችኋለሁ፡፡ ምክንያቱም "እከሌ ይኼን ያህል ብር ሰጠ" ለመባል ብቻ ስለምትመጸውቱ፡፡ ታዲያ ከ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል፦ አንዳንድ ቀን ድኾችን ስትረዱ አያለሁ፡፡ ነገር ግን በጣም አዝንባችኋለሁ፡፡ ምክንያቱም "እከሌ ይኼን ያህል ብር ሰጠ" ለመባል ብቻ ስለምትመጸውቱ፡፡ ታዲያ ከዚህ በላይ ምን የሚያሳዝን አለ? ለምንድነው ደካማውና ሟቹ እኔ እንዳመሰግናችሁ የምትፈልጉት? ባለጸጋው እግዚአብሔርን ትታችሁ ከድኻው ከእኔ ምስጋናን የምትሹት ለምንድን ነው? የዘለዓለም ሕይወት የምሰጠው እኔ ነኝን? እንዴት ነው የምታስቡት? እግዚአብሔር ድኻ ነውን? ታዲያ እርሱ እንደማያመሰግናችሁ አድርጋችሁ በመቍጠር እኔ በደለኛው እንዳመሰግናችሁ የምትጠብቁት ለምንድን ነው? (አምስቱ የንስሐ መንገዶች - ገጽ 80) እንደዚህ አይነት አጫጭር አስተማሪ ምክሮች እና ተግሳፆች ለማግኘት ..

ወዳጄ ሆይ! በብዙዎች እንደሚደርሰው አንተም ቤትህ ተቃጥሎብህ ሀብትህንና ንብረትህን አውድሞብሃልን? ኢዮብ ምን እንደ ደረሰበት አስታውስ  እግዚአብሔርንም አመስግን፡፡ ምንም ፤ እንኳን አለማመስገን ይችል የነበረ ቢኾንም ከማመስገን ግን አልተከለከለምና፡፡ አንተም እንደ ኢዮብ ከማመስገን ባትከለከል ሀብትህን ኹሉ በነዳያን እጅ እንዳስቀመጥከው ኾኖልህ ታላቅ የኾነ ክብርን ትቀበላለህ! ዘመንህን ኹሉ በማጣትና በመራብ፣ እንደዚሁም ለመቊጠር እንኳን በሚታክቱ መከራዎችአሳልፈሃልን? 👉 በደዌ፣ በድኽነት፣ በብቸኝነትና ስፍር ቊጥር በሌላቸው መከራዎች የተንገላታውን እንደዚሁም ከዚያ በኋላ ታላቅ የኾነ ክብር  ያገኘውን አልዓዛርን አስበው (ሉቃ.16፡20)፡፡ 👉በረሀብ፣ በጥም፣ በመራቆት የኖሩትን ሐዋርያትን አስታውሳቸው፡፡ 👉 ነቢያትን፣ አበውን እንዲሁም ጻድቃንን ባስብክ ጊዜም አንዳቸውስ እንኳን በተድላ በደስታ ሕይወት ይኖሩ በነበሩ ሰዎች መካከል ሳይኾን በነዳያን፣ በችግረኞችና በተጨነቁ ሰዎች መካከል ታገኛቸዋለህ! ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ❣️ ✍️

እኛ እና ሐጅ" በክርስቶስ ፍቅር ባንገናኝም በኢትዮጵያ ፍቅር ተገናኘን። በሃይማኖት ባንገናኝም በምግባር ተገናኘን። ሐጅነት እንደ እርሳቸው ነው። ኦርቶዶከሳዊነትም እንደዚህ ነው።ሐጅ ግድብ አይደሉም።እኛም ግድቦች አይደለንም። ጠባብ አይደሉም። ጠባቦች አይደለንም። ኢትዮጵያን ይወዳሉ።ኢትዮጵያን እንወዳለን። ይወዱናል።እንወዳቸዋለን።ያከብሩናል።እናከብራቸዋለን። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኞች እውነተኛ መሪ እውነተኛ አባት ካዩ ሁሉን አክባሪ መሆናቸውን በሐጅ ተመልከቱ። እኔ ደግሞ እርሳቸውን ከማክበሬ የተነሳ ተጠምቀው ቢሞቱ እያልኩም ስመኝላቸው ነበር።ምን ይባላል? ከሕግ በላይ የኾነው ጌታ እርሱ ይሁናቸው ። ። ። ።ሌሎች የእስልምና አባቶችም እንደ እርሳቸው ለመወደድ ከእርሳቸው ተማሩ። በኢትዮጵያ የማያፍ፥ በኢትዮጵያ የሚኮሩ፦ ለኢትዮጵያ የሚያስቡ፥ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ሐጅ ሙፍቲ። via አሹ ጆርናል ✍️

☑️ ........ ሐጅን ..እንደ... ጳጳሱ ........❤!!!!!!!!! ኦርቶዶክሳውያን ለፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የሰጡትን ፍቅር ለሐጅ ሙፈቲንም አሳይተዋል። ኦርቶዶክሶች ለሐጅ ያለቸውን አክብሮት ዛሬ በዚህ ልክ አሳዩ።ሐጅ ግን በዚህ ልክ በኦርቶዶክሳውያኑም እንደሚወደዱ ያውቁ ይሆን? እንጃ። አቡነ ሺኖዳ ግብጻዊም ለግብጽ ሙስሊሞች በዕረፍታቸው ቀን እንዲህ ነበሩ ። ። ። ። ። መላ ግብጻውያንን በዕንባ አራጭተው ነበር። ☑️የኦርቶዶክሳውያን ከፍታ የታየበት የሐጅ ሽኝት። ለኔ በሐጅ ሙፍቲን ሞት የታየኝ የሐጅ በሁሉ ተወዳጅነት ብቻ ሳይሆን የኦርቶዶክሳውያኑም ሁሉን ወዳጅነት ነው። ☑️ ኦርቶዶክሳውያን እንዲህ ናቸው።አማኒ መናፍቅ፤ ኀጥእ እና ጻድቅ ሳይሉ መውደድ የሃይማኖታቸውም መገለጫ ነው። ይቅርታ አድርጉልኝ። እኔ የሐጅን የሕይወት ታሪክ የሚገልጥ ከቤታቸው የሚጽፍ ሰው ጠፍቶ ወይም የእርሳቸውን መላ ሕይወታቸውን አውቄው መመስከሬ አይደለም።በዚሁ በምድያው" የኦርቶዶክሳውያኑ ደግነት እና ሁሉንም ወዳጅነት ሲንጸባረቅ አይቼ ደስ አሰኝተውኝ ነው። ሐጅን እንደ ጳጳሱ መውደዳቸው ገርሞኝ ነው ። ☑️የሐጅ ሙፍቲ ከፍታ እና የኦርቶዶክሳውያኑ ከፍታ" ☑️በሐጅ ሙፍቲ ሞት ምክንያት ምድያዎች በኀዘን ሰክረዋል፤ ቲክታኮች እና ቲክቶከሮች እምነት ሳይገድባቸው በዕንባ ታጅበዋል፤ ዩቲዩበሮጅ ሰበር ዜና በሚል ሰቆቃ ታጭቀዋል።ፌስቡኮች ገጻቸውን በሙሉ በሐጅ ሙፍቲን ፎቶ አዘምነዋል። ፖለቲከኞች ተራ በተራ በዕንባ ቀለምነት በጣት ብዕርነት በፌስቡክ ወረቀትነት የኀዘን መግለጫቸውን አንጸባርቀዋል።ቤተ እምነቶች የታላቋ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ እምነትትን ጨምሮ የዕንባ ሙሾ ደርድረዋል። ኹሉም ቤተ ሙስሊም አባ አባ በማለት ኀዘኑን ገልጧል።እየገለጠም ነው። ☑️በዚህ ሁሉ መካከል ግን አንድ ነገር ገረመኝ። ምን እንደኾነ ታቃላችሁ? ምድያው ላይ ከፍተኛዎቹ ኀዘንተኞች ኦርቶዶክሳውያኑ ኹነው መመልከቴ ነው። ☑️ ቤተ ሙስሊሙም አላዘነም ማለቴ አይደለም።ነገር ግን ምድያውን በማጥለቅለቅ ባለ ማተቦቹ የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል። ለኔ ገረመኝ። ይሄ ሕዝብ ምን አይነት ሕዝብ ነው? እኝህ አባት በሃይማኖት አይመስሉት፤ እንዴት በዚህ መጠን ወደዳቸው?አልኩኝ።አንዳንድ ቦታ ላይስ ዕንባ የሚያነቡ ድምጽ አሰምተው የሚያንጎራጉሩ ኦርቶዶክሶችም አሉ። እኝህን የሀገር በረከት የምግባር አባት የሀገር አድባር የነበሩ አባት ከቤተ ሙስሊሙ በላይ ክርስቲያኑ የተረዳቸውም እስኪመስል ድረስ ይወደዳሉ ። ። ☑️ይህ ነገር ከምን መጣ? አልኩኝ። አንድ ነገር ግን ወደ ውስጤ መጣ። የሐጅ ኹሉን ወዳጅነታቸውን እና የኦርቶዶክሶች ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ የሚል ታላቅ ሰው ካገኙ ኹሉን ወዳጅ መሆናቸውን ተመልከትኩ ። ☑️አስረጅ" ዶ/ር ዐቢይ ወደ መሪነት ሲመጡ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ የሚል የድምጽ ደወል እያሰሙ ነበር። ያን ጊዜ ሃይማኖታቸው ምን እንደሆነ ታውቆ ነበር። ጴንጤ እንደሆኑ ኹሉም ኢትዮጵያዊ ያውቅ ነበር። ነገር ግን ከአንደበታቸው በተደጋጋሚ ሲወነጨፍ የነበረውን ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ የሚል ሚሳኤላዊ ቃል በመስማት ሁሉም ኦርቶዶከሳዊ እልል አሉ። ባለ"ማተብ ባለ ቅኔዎች በቅኔያቸው እንደ ነገሥታቱ አወደሷቸው ፡ አሞገሷቸውም ። ባለ ማተብ ዘፋኞች ሃይማኖት ሳይገድባቸው አሸሸ አቢይ መጣልሽ ከመሸ እያሉ አሞካሿቸው። ባለ ማተብ ሰባክያን ነቢዩ ሙሴ አሻጋሪው አሏቸው። ባለ ማተብ የጥበብ ሰዎች አንዱ ሞተር፤ አንዱን ፍሬን፤ አንዱን ነዳጅ እያደረጉ ከአቻዎቻቸው ጋራ በምሳሌ ገለጧቸው። ባለ ማተብ ወጣቶች በክንዳቸው ተነቀሷቸው፤ ባለ ማተብ የሰልፍ ሰዎች በሙሉ በቲሸርታቸው አዘመኗቸው። ምን ያልተደረገ ነገር ነበር? ይሄ ኹሉ ሲደረግ ግን ዶ/ር አቢይ ጴንጤ መኾናቸውን ኹሉም ኦርቶዶክሳዊ ያውቅ ነበር። ☑️ ይሄ ምን ያሳያል ካላችሁ? የኢትዮጶያ ኦርቶዶክስ አማኞች ኢትዮጵያን የሚወድላቸውን ሰው ኹሉ" ሃይማኖት ሳየገድባቸው የሃይማኖት ጽንፍ ሳይዙ ምን ያህል እንደሚወዱት የሚያሳይ ነው። ኹኖም ዶ/ር ዐቢይ ያንን ያህል ጨርቁን ጥሎ ያበደላቸው ኦርቶዶክሳዊ ዛሬ በምን ያህል ይወዳቸዋል? እርሳቸውስ በምን ያህል ይወዱታል?ካላችሁ" መልሱን መልአከ ሞት ይንገራችሁ ። ☑️እርሳቸው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ" ሲሉ ያ"ሲያጨበጭብላቸው የነበረው ባለ ማተብ ኹሉ ዛሬ የት ሄደ? እርሳቸውስ ኦርቶዶክስ ሀገር ናት። ስንኖር ኢትዮጵያዊ ሰንሞት ኢትዮጵያ ያሉትን ድንቅ ቃል የት አደረሱት? ቃል ብቻ አድርገው ለምን አስቀሩት? ይሄ ያሳዝናል።ዶ/ር አቢይ አለመታደላቸው እንጅ እንደ ሐጅ መሆን ነበረባቸው። በሁሉ ተወደው ኑረው ፤ በሁሉ እንደ ተወደዱ መሞት። ይሄ ግን" ዶ/ር ላይ አልሠራም። ከሽፏል ማለት ይቻላል። እንጅማ ሲገቡ በእርሳቸው ልክ ኦርቶዶክሳዊው ያቀነቀነለት ሰው ማን ነበር? በሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ተወደው ነበር።ዳሩ ግን በሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ዘንድ ሳይወደዱ ቀሩ። በሁሉ ሳይወደዱ ይሞቱ ይሆን? እንጃ። ዶ/ር አቢይ እንደ መጡ አካባቢ በሚያሳዩት ንግግር ለኢትዮጵያ ያላቸው ፍቅር ሙፍቲን ይመስሉ ነበር። ሙፍቲ ቀጠሉ።ዶ/ር አቢይ ኦርቶዶክሳውያኑ ላይ ያላቸውን ምልከታ አቋረጡ። ሙፍቲ ዛሬ በኦርቶዶክሶች ገጽ ዘምነው ዋሉ። የሁላችን አባት ተባሉ። ዶ/ርስ? በሞቱ ጊዜ የእነ ማን እና የእነ ማን አባት ይባሉ ይኾን?እንጃ ።ፈጣሪ ይወቀው ። ☑️ሐጅ ሙፍቲ ግን በሥጋው ዓለም መጨረሻቸው አማረ። በሁሉም ልብ ነግሠው ሄዱ። ታድያ የሐጅ ሞት የኦርቶዶክሳውያኑን ከፍታም አሳየን። ሐጅ በሃይማኖት ሳይመሽጉ ለሁሉ በአባትነት እንደ ተገለጡ ኦርቶዶክሶችም በሃይማኖት ሳይጠቡ የሐጅን ደግነት ገለጡ። ይሄ የሁለቱን ከፍታ ያሳያል ኦርቶዶክሳውያኑ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ለሚል ሁሉ ያላቸውን ልዩ አክብሮት እና ልዩ ፍቅር ያሳያል። እኝህን አባት ኦርቶዶክሳውያኑ ያከበሯቸው በሃይማኖታቸው እውነታ አይደለም።በምግባራቸው እውነታ ነው እንጅ።ሃይማኖቱማ የእኛ በእነርሱ እይታ ሀሰት ይባላል።የእነርሱም በእኛ አስተምህሮ ሀሰት ነው።ሀሰትም ይባላል። ሰውየው ግን በሃይማኖት ብንለያይም በምግባር ተጋመዱን።ተዛመዱን። ☑️በኢትዮጵያ ሰንሰለትነት ከኦርቶዶክሳውያኑ ጋራ ተሳሰሩ። በማተብ ባንገናኝም።በኢትዮጵያ ተገናኘን። በማተብ ባንተሳሰርም በሀገር ፍቅር ተሳሰርን፤ በውሃ ጥምቀት ባንገናኝም በዐባይ እና በጣና ተገናኘን፤ በክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም በኩል ባንገናኝም በኢትዮጵያዊ ደም እና አጥንት ተገናኘን። በሃይማኖት ወደብነት ባንገናኝም በምግባር ተርሴስነት ተገናኘን። ፈጣሪን የምናይበት ዐይን የምንረዳበት ልቡና ቢለያይም ኢትዮጵያን የምናይበት ዐይን እና የምነረዳበት ልቡና ግን ተመሳሰለ። ኢትዮጵያን በመውደድ ላይ ሐጅ እንደኛ። እኛም እንደ ሐጅ ነን መሰለኝ ።

የብጹዕ አባታችንን እንባ ስላየሁ ፤በግብዝነትና ለታይታ ወይም ሌላውን ለመንካት እንዳልሆነ ክርስቶስ ምስክሬ ነው። ነገርግን በእወነተኛዋና ቀጥተኛዋ መንገድ እገኝ ዘንድ ባለ ማህተብ የተዋህዶ ልጅ አድ
+1
የብጹዕ አባታችንን እንባ ስላየሁ ፤በግብዝነትና ለታይታ ወይም ሌላውን ለመንካት እንዳልሆነ ክርስቶስ ምስክሬ ነው። ነገርግን በእወነተኛዋና ቀጥተኛዋ መንገድ እገኝ ዘንድ ባለ ማህተብ የተዋህዶ ልጅ አድርጎ እግዚአብሔር ስለመረጠኝ አመሰግነዋለሁ።መጨረሻዬም እንዲያምር እለምነዋለሁ።

ኮቪድ 19 ከአለም ቁጥጥር ውጪ ወቶ በሰዓታት ውስጥ ብቻ በሺህ የሚቆጠሩ ነፍሳትን በሚረፈርፍበት ከሐገርም አልፎ እንደ ዓለም በተጨነቅንበት በዛ ክፉ ጊዜ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፀሎተ
ኮቪድ 19 ከአለም ቁጥጥር ውጪ ወቶ በሰዓታት ውስጥ ብቻ በሺህ የሚቆጠሩ ነፍሳትን በሚረፈርፍበት ከሐገርም አልፎ እንደ ዓለም በተጨነቅንበት በዛ ክፉ ጊዜ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፀሎተ ቡራኬ ካደረጉ በኋላ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ሁለተኛውን የፀሎት ፕሮግራም እንዲያደርጉ ሲጋበዙ '' በዚህ ፀሎት ላይ ሌላ ፀሎት አላደርግም '' ብለው የትህትናቸውን ጥግ ያሳዩ ድንቅ የፍቅር አባት ነበሩ ! የሐገር ካስማ ነፍስዎት በሰላም ትረፍ 💔