en
Feedback
Ethiopian Coffee and Tea Authority

Ethiopian Coffee and Tea Authority

Open in Telegram

Ethiopian Coffee and Tea Authority

Show more
6 550
Subscribers
+324 hours
+307 days
+14230 days
Posts Archive
በዓለም የቡና ገበያ ውስጥ የኢትዮጵያ ወርቃማ ዕድል ''ብዛት ላስጨነቀው ገበያ ጥራትን ማቅረብ!!'' በሳህለማርያም ገ/መድህን ​የዓለም የቡና ገበያ በአሁኑ ወቅት በመንታ መንገድ ላይ የቆመ ይመስላል። በብራዚል በቀረበ ከፍተኛ ምርት፣ በአንፃሩ የጥራት መቀነስ!!!! ይህ ደግሞ ትልቅ የዋጋ ዥዋዥዌ እና የገበያ ጥርጣሬ ሊፈጥር እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም ። ባለፈው ሳምንት የኒው ዮርክ አረቢካ ቡና ዋጋ በ 5.5% እስከ 6.2% ቅናሽ ማሳየቱ በገበያው ላይ መደናገጥን ቢፈጥርም፣ ከዚህ የዋጋ መውረድ በስተጀርባ ያለው እውነተኛ ምስጢር ግን ለአገራችን አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ትልቅ የወደፊት ዕድል ይዞ ሊመጣ ይችላል። ​የዋጋው መቀነስ ምክንያት የብራዚል የቡና ምርት መጠን (Quantity) በመጨመሩ እና ወደ ውጭ የምትልከው መጠን በ 9.9% በማደጉ ምክንያት የተፈጠረ ጊዜያዊ የአቅርቦት መትረፍረፍ ግምት ነው። ነገር ግን ገበያው ትልቁን እውነታ የተረዳው ይመስላል። የምርት ብዛት እንጂ የጥራት ማደግ አይደለም! በብራዚል የጣለው ያልተጠበቀ ዝናብ የምርት ጥራቱን እጅግ ያወረደው ሲሆን፣ የ2026/27 የምርት ዘመን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዝቅተኛ ጥራት ከታየባቸው አንዱ ሊሆን እንደሚችልም ተገማች አድርጎታል። ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ሊከፍት የሚችለው የዕድል በር: ​ዓለም አቀፍ የቡና ገዢዎች በቅርብ ወራት ውስጥ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚያስፈልጋቸውን ከፍተኛ የጥራት ደረጃ (Specialty Grade) የሚያሟላ ቡና በከፍተኛ ሁኔታ መፈለጋቸው አይቀሬ ነው። ይህ ደግሞ ተፈጥሮ የታደለችውን ልዩ ጣዕምና ጠረን ይዛ ለምትገኘው ኢትዮጵያ ታላቅ የምስራች ነው! ​ምርጥ ጥራት ከፍተኛ ዋጋ ያወጣል: የዓለም ገበያ በጥራት በወረደ ቡና በሚጥለቀለቅበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ የተጠበቀና ከፍተኛ ጥራት ያለው ቡና (Specialty Coffee) በልዩ የዋጋ ተመን (Premium Price) የመሸጥ ዕድሉ እጅግ ከፍተኛ ይሆናል። የዓለም አቀፍ ቡና ቆዪዎች እና አስመጪዎች ጥራት ያለው ቡና ፍለጋ ዓይናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ማዞራቸው ስለማይቀር፣ አሁን የተፈጠረውን የጥራት ክፍተት በበላይነት ለመቆጣጠር ያስችለናል። ​እናስ ምን መደረግ አለበት? ​አርሶ አደሮች፦ ከተክሉ እንክብካቤ ጀምሮ እስከ አሰባሰብ (ምርጥ ቀይ ፍሬዎችን ብቻ መልቀም) እና ማድረቅ ሂደት ላይ ለጥራት ልዩ ትኩረት መስጠት። የምርት ብዛት ላይ ብቻ ከማተኮር፣ ደረጃውን የጠበቀ ቡና ማዘጋጀት የበለጠ አትራፊ ሊያደርግ ይችላል። ቡና ማዘጋጃና ማጠቢያ​ ባለቤቶች፤ የቡና ማጠቢያና ማድረቂያ ጣቢያዎችን ንፅህና መጠበቅ፣ የእርጥበት መጠንን በትክክል መቆጣጠር እና የቅምሻ (Cupping) ደረጃውን በጥብቅ መከታተል። ​ላኪዎች (Exporters)፦ በዓለም ገበያ ላይ ያለው የደረጃ መውረድ ያስከተለውን የጥራት ፍላጎት በመረዳት፣ የኢትዮጵያን ቡና ልዩ ጣዕም እና ደረጃ አስተዋውቆ በጥሩ ዋጋ ለመሸጥ የተጠናከረ ድርድር ማድረግ ያስፈልጋል የፀሀፊው መልዕክት ነው። ​ ​በቡና ገበያ ውስጥ "ብዙ ምርት ማለት ሁልጊዜ የተሻለ ቡና ማለት ላይሆን ይችላል!" አሁን ዛሬ እያየነው ባለው ተጨባጭ የዓለም ገበያ ሁኔታ አሸናፊ የሚሆነው ብዙ ቡና የላከ ሳይሆን፣ ገበያው የሚፈልገውን ከፍተኛ ጥራት ማቅረብ የቻለ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ይህንን የጥራት ብልጫ በመጠቀም በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪነታቸውን እና ጥቅማቸውን የሚያረጋግጡበት ወርቃማ ወቅት አሁን ይመስላል።

የዓለም አቀፍ የቡና ንግድ ፍሰትን የሚያሳይ አዲስ የመረጃ ቋት ይፋ ሆነ በሳህለማርያም ገ/ መድህን ​አዲስ የወጣ የመረጃ ቋት እንደሚያሳየው፣ በዓለማችን ከፍተኛ ቡና አምራች ከሆኑ ዐሥር አገራት የሚላከውን ምርት ከሲሶ በላይ (35%) የሚቆጣጠሩት ዐሥር ግዙፍ የንግድ ኩባንያዎች ናቸው። እንዲሁም ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዙት 30 ኩባንያዎች አጠቃላይ የዓለም አቀፉን የቡና ኤክስፖርት 55 በመቶ ይሸፍናሉ። ​ትሬስ (Trase) በተሰኘው ተቋም የተሰበሰበው ይህ መረጃ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚመረተው ቡና 79 በመቶ የሚሆነው ወደ አውሮፓ ህብረት ገበያ የሚያቀርቡ ኩባንያዎች እጅ እንደሚገባ ይጠቁማል። ይህም በቅርቡ የሚወጣው የአውሮፓ ህብረት የደን ጭፈፋን የመከላከያ ሕግ ያላቸዉን ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳያል። ​የሕጉን ተፅዕኖ አስመልክተው የትሬስ ተመራማሪው ማርክ ታይትሊ ሲናገሩ፡- ​“የአውሮፓ ህብረት ከዓለም አቀፉ የቡና ምርት 40 በመቶ ያህሉን ብቻ የሚያስገባ ቢሆንም፣ ምርቱን የሚያቀርቡት ኩባንያዎች ግን የዓለም አቀፉን ገበያ አራት አምስተኛ (4/5ኛ) ድርሻ ይሸፍናሉ። እነዚህ ኩባንያዎች ሕጉን ለማሟላትና የቡናውን ምንጭ በትክክል ለመከታተል የሚያስችሉ አሰራሮችን አንዴ ከዘረጉ በኋላ፣ ተመሳሳይ ደረጃዎችን ከአውሮፓ ውጪ ባሉ ሌሎች ገበያዎች ላይም ተግባራዊ ማድረጋቸው አይቀሬ ነው። ይህም ማለት ሕጉ ከአውሮፓ ህብረት ወሰን በላይ እጅግ የጎላ አዎንታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል ማለት ነው” ብለዋል። ​ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​የገበያ ድርሻ፦ አሜሪካ ከዓለም አቀፉ የቡና ገበያ 18 በመቶ በመሸመት ከአውሮፓ ህብረት ቀጥላ ሁለተኛዋ ትልቅ አስመጪ አገር ናት። ​ከፍተኛ ጥገኝነት፦ እንደ ኡጋንዳ (57%)፣ ሆንዱራስ (58%) እና ሕንድ (58%) ያሉ አገራት ኤክስፖርታቸው በከፍተኛ ሁኔታ በአውሮፓ ህብረት ገበያ ላይ የተመሰረተ ነው። ​የአነስተኛ አርሶ አደሮች ሕይወት፦ መረጃው በድህነት ወለል ውስጥ የሚኖሩ አነስተኛ ቡና አምራች አርሶ አደሮችን ለመደገፍ በንግድ ሰንሰለቱ ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት መስፈን እንዳለበት ያመላክታል። ​ተመራማሪው አክለውም፣ ይህ መረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ቡና ከተመረተበት ቀጠና ጀምሮ በነጋዴዎች በኩል አልፎ ለተጠቃሚዎች እስከሚደርስበት ድረስ ያለውን ጉዞ በጥራት ለመከታተል ያስቻለ በመሆኑ፣ ገዢዎች፣ አበዳሪዎችና መንግሥታት የላቀ ለውጥ ማምጣት በሚችሉባቸው የንግድ ሰንሰለቶች ላይ በትክክል አተኩረው እንዲሰሩ መንገድ ይከፍታል ሲሉ ገልጸዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፤ የ10 አመት የተከለሰ ኮምፕሬሄንሲቭ የቡና ስትራቴጂ ዕቅድም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ። ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣ ከቡና ሻይና ቅመማ ቅመም አብቃይ ክልሎች እና የባለስልጣኑ አመራሮች በታደሙበት መድረክ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና   የ10 አመት የተከለሰ ኮምፕሬሄንሲቭ የቡና ስትራቴጂ ዕቅድ ላይ የግምገማና ውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ መክፈቻ ላይ የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የቡና ሻይ ቅመማ ቅመም ልማት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ታጋይ ኑሩ ንግግር አሰምተዋል። በንግግራቸው ያለባለድርሻ አካላት ተሳትፎ  የታቀደ ከዳር እንደማይደር ስለሚታወቅና የተገኘውም የክንውን ውጤት በመድረኩ በታደሙ አካላት እና በቡና ተዋናዩ ጥረት ስለሆነ በጋራ ለመነጋገር መድረኩ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል። ከተዘጋጀ ፓኬጅ የተቀዱ በአንገብጋቢነት የሚለዩ የቡና ኢኒሼቲቮች እንዳሉ የተናገሩት ኃላፊው ወደአርሷደሩ እንደወረደ ገልጸዋል፤ በጉዳዩ ላይም ስልጠና ይሰጣል ብለዋል። በማስከተልም አቶ ቦንሳ መርጋ የባለስልጣኑ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ዕቅድ አፈጻጸሙን አቅርበዋል። ሲያቀርቡም 1.6 ሚሊዮን ሄክታር በቡና እንደተሸፈነ ገልጸው ከአምናው አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ14 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። የምርት አፈጻጸሙን ሲያቀርቡም 1.5 ሚሊዮን 80 ሺ ቶን እንደሆነ ተናግረው ምርታማነት 9.4 ኩንታል በሄክታር እንደሆነ ገልጸዋል። ከላይ የተጠቀሱት ውጤቶች የተመዘገቡበት ምክንያቶችን ሲናገሩ በአዲስ ቡና ተከላ፣ በማሳ እንክብካቤ፣ በጉንደላ እና በነቅሎ ተከላ ላይ ስራዎች በመሰራታቸው ነው ብለዋል። በቀጣይም ጉንደላና ነቅሎ ተከላ ላይ በይበልጥ መሠራት አለበት ሲሉ አሳስበዋል። በተመሳሳይ መልኩ በሻይውና በቅመማቅመም ሰብሎች ላይ ያለውን አፈጻጸም አቅርበዋል። የኤክስፖርት አፈጻጸሙን ሲያቀርቡም 40 በመቶ የዓለም ዋጋ በቀነሰበት፣ የሆርሙዝ ክስተት በታየበት፣ የነዳጅ ዋጋ በናረበት፣ የብራዚል ቡና በገፍ ወደገበያ በገባበት ሁኔታ የታቀደው 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተሳክቷል ብለዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን ከታቀደው የቡና መጠን ያነሰ ተልኮ መሳካቱም ስኬቱን ለየት ያደርገዋል ብለዋል። በዚህ ሁሉ ተግዳሮቶች ውስጥ ለመጣውም ውጤት ምክንያቶቹን ሲያቀርቡም ከጀረጃ 1 እስከ ደረጃ 3 ያሉ ቡናዎች መጠን እና ዋጋቸው መጨመር መሆኑን ጠቅሰው ይህ ምን ያህል የቡና ጥራት ላይ ውጤታማ ስራ እንደተሰራ ማሳያ ነው ብለዋል። በማስከተልም ስትራቴጂ ዕቅዱ ቀርቦ  በሁለቱም አጀንዳዎች ላይ ሐሳቦች ከታዳሚው ተሰንዝረው የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል። አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው

በ #ፓኪስታን #ኢስላማባድ ለመጀመሪያ ጊዜ የ #ኢትዮጵያ ቡና መሸጫ ካፌ ተከፈተ ​በእስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመንታ ከተሞች እስላማባድ እና ራዋልፒንዲ የመጀመሪያው የሆነው የኢትዮጵያ
+1
#ፓኪስታን #ኢስላማባድ ለመጀመሪያ ጊዜ የ #ኢትዮጵያ ቡና መሸጫ ካፌ ተከፈተ ​በእስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመንታ ከተሞች እስላማባድ እና ራዋልፒንዲ የመጀመሪያው የሆነው የኢትዮጵያ ቡና ካፌ መከፈቱን አስታወቀ። ​በፓኪስታን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ዑመር ሁሴን (ዶ/ር) እሁድ ዕለት ባካሄዱት የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት፣ የኤምባሲው ሠራተኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በተገኙበት በባህላዊ የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት ካፌውን መርቀው ከፍተዋል። ​አምባሳደሩ በምረቃው ወቅት እንደገለፁት፣ ካፌው መከፈቱ በኢትዮጵያ እና በፓኪስታን መካከል እያደገ ከመጣው ሁለትዮሽ ግንኙነት ጎን ለጎን የባህል እና ሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር አዲስ መንገድ ይከፍታል። ​https://www.facebook.com/share/p/1CHvfNAmPG/

ሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በሙዳ–ድኖቆሰ ቀበሌ በአርሶ አደር ጓሮ እየለማ የሚገኘው የቡና ልማት በአሁኑ ወቅት አበረታች ገጽታ እያሳየ ይገኛል። በተለይም በቡና ዛፎቹ ላይ በብዛት የተያዙ የቡና ፍሬዎች የልማቱን የምርት አቅም የሚያሳይ ሲሆን፣ በጓሮ ልማት ውስጥ ከበቆሎና ሌሎች ሰብሎች ጋር ተቀናጅቶ መልማቱም የመሬት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው። የጓሮ ቡና ልማት ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ከመፍጠሩም በላይ የቤተሰብ ኢኮኖሚን በማጠናከር የአካባቢውን የቡና ምርት አቅም ለማሳደግ የሚጫወተው ሚና የጎላ ነው። በዚህም መነሻነት የቡና ችግኝ ማፍላት፣ በተገቢው የአተካከል ዘዴ መትከል፣ የእርሻ እንክብካቤን ማጠናከር እና የተቀናጀ የቡና ልማትን ማስፋፋት ለቀጣይ የምርት ዕድገት ወሳኝ ናቸው። በሙዳ–ድኖቆሰ ቀበሌ የሚታየው ይህ የቡና ልማት ገጽታ በጓሮ ልማት የተሻለ ምርትና የተሻለ ገቢ ለማምጣት የሚቻል መሆኑን የሚያሳይ አበረታች ምሳሌ ነው። መረጃው የሙደ ድኖቆሳ ቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ነው።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። መልካም በዓል!!!
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። መልካም በዓል!!!

ዓለም አቀፍ የቡና ሁኔታን በወፍ በረር!! ​የገበያ ሁኔታ ​የአሜሪካ የግብርና ሚኒስቴር (USDA) በ2026/27 የምርት ዘመን የዓለም ቡና ምርት አዲስ እና ታሪካዊ ደረጃ ላይ ይደርሳል ሲል መግለጹ
ዓለም አቀፍ የቡና ሁኔታን በወፍ በረር!! ​የገበያ ሁኔታ ​የአሜሪካ የግብርና ሚኒስቴር (USDA) በ2026/27 የምርት ዘመን የዓለም ቡና ምርት አዲስ እና ታሪካዊ ደረጃ ላይ ይደርሳል ሲል መግለጹ ተሰምቷል። የዓለም የቡና ምርት በ10.8 ሚሊዮን ጆንያዎች በማደግ በድምሩ 189.7 ሚሊዮን ጆንያ በመድረስ አዲስ የምርት ጣሪያ ይመዘግባል ተብሎ ይጠበቃል። የዓለም አቀፍ የቡና ፍጆታ 179.7 ሚሊዮን ጆንያ ይደርሳል ተብሎ የተገመተ ሲሆን፣ የዓመቱ መጨረሻ የተጠራቀመ ክምችት ደግሞ ወደ 26.3 ሚሊዮን ጆንያ ያድጋል። ለዚህ የምርት እድገት ኢትዮጵያ፣ ብራዚል፣ ቬትናም እና ኡጋንዳ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ በተቃራኒው የኢንዶኔዢያ ምርት ከመጠን በላይ በጣለው ዝናብ ምክንያት በ1 ሚሊዮን ጆንያ ይቀንሳል ተብሏል። በ​ሳህለማርያም ገ/መድህን

☕️ 1 ዩሮ ወደ 11.20 ዩሮ  ፦ አውሮፓ እሴት ባልተጨመረበት ቡና የምታገኘው ግዙፍ ትርፍ ! ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው አጠቃላይ ቡና ውስጥ 34 በመቶ የሚሆነው መድረሻው የአውሮፓ ገበያ መሆኑን «የቡና ምጣኔ ሀብታዊ ተፅዕኖ በአውሮፓ» (Economic Impact of Coffee in Europe) የተሰኘ ጥናት ይፋ አድርጓል። ይህንን የቡና ኢኮኖሚ የዳሰሰ ጥናት ያጠናው በዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) የሚገኘው «አውሮፓ ኢኮኖሚክ ሪሰርች ሊሚትድ» (European Economic Research Limited) የተባለ ተቋም ነው። ሰነዱ የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራትን ጨምሮ እንግሊዝ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድን ያካተተ ሰፊ ቀጠናን የተመለከተ ነው። በጥናቱ መሠረት እ.ኤ.አ. በ2024 የአውሮፓ ሀገራት ከኢትዮጵያ 523.6 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቡና ያስገቡ ሲሆን፣ ይህም ለአውሮፓ አጠቃላይ የቡና ገቢ ንግድ (Import) 3.4 በመቶውን ብቻ የሚሸፍን ቢሆንም፣ ለኢትዮጵያ ግን አጠቃላይ የውጭ ሸቀጥ ሽያጭ 11.8 በመቶውን የሚሸፍን ዋነኛው የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ነው። ጥናቱ እንደሚያሳየው አውሮፓ ራሷ ቡና የማታመርት ብትሆንም እ.ኤ.አ. በ2025 ከቡና ዘርፍ ከግማሽ ትሪሊዮን ዩሮ በላይ የምጣኔ ሀብት ምርታማነት (Economic Output) እና 251.5 ቢሊዮን ዩሮ አጠቃላይ የተጨመረ እሴት (GVA) አግኝታለች። እ.ኤ.አ. በ2025 ብቻ ወደ አውሮፓ 18.7 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጣ 2.9 ሚሊዮን ቶን ቡና የገባ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ከ97 በመቶ በላይ የሚሆነው አምራች ሀገራት የላኩት ያልተቆላና ያልተቀነባበረ አረንጓዴ ቡና መሆኑ ተጠቅሷል። ሰነዱ እንደሚጠቁመው ቡናን የመቁላትና የማቀነባበር ሥራዎች የሚከናወኑት ምርቱ ከሚመነጭባቸው አገሮች ይልቅ ወደ ሸማቹ ማኅበረሰብ በቀረቡ የአውሮፓ ቀጣናዎች ነው። እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አምራች ሀገራት ያልተቆላና እሴት ያልተጨመረበት አረንጓዴ ቡና ብቻ በብዛት የሚልኩ ሲሆን አውሮፓውያን ግን ቡናውን ካስገቡ በኋላ በማከማቸት፣ በመቁላት፣ ካፌይን በመቀነስ፣ ፈጣን (Soluble) ቡና በማምረት እና በተለያዩ የችርቻሮ ሽያጭ፣ የሆቴልና ቱሪዝም (Hospitality) ዘርፎች ላይ በማዋል ከፍተኛውን ጥቅም ለራሳቸው ያተርፋሉ። የጥናቱ የምጣኔ ሀብት ማባዣ (Economic Multiplier) ሙሉ ሐሳብ እንደሚያሳየው፤ እያንዳንዱ አምራች ሀገር 1 ዩሮ የሚያወጣ አረንጓዴ የቡና ምርት ወደ አውሮፓ ገበያ ሲያስገባ፣ ቡናው አውሮፓ ከገባ በኋላ በሚደረግለት ፦ - የማቀነባበር፣ - የማሸግ፣ - የችርቻሮ ሽያጭ እና በካፌዎች አማካኝነት በሚቀርብበት ሰንሰለት ውስጥ አልፎ 11.20 ዩሮ ቀጥተኛ የአውሮፓ ምጣኔ ሀብት ምርታማነትን (Direct European Economic Output) ይፈጥራል። ይህ መረጃ ከሪፖርተር ጋዜጣ መወሰዱን እንገልጻለን። @tikvahethiopia

የ 2018 የቡና አጠቃላይ ሁኔታ ብዙ መዋዠቅ፣ ማገገም እና ትራንስፎርሜሽን የተስተዋለበት ዓመት   2018 ዓ.ም ለዓለም አቀፍ የቡናው ኢንዱስትሪ ወሳኝ አመት ሆኖ እየተገባደደ ይገኛል፡፡ አዲሱ የምርት ዘመን እንደመጀመሩ እስቲ 2018 ዓ.ም  ምንን አስመልክቶን እንዳለፈና ይህ ለቀጣይ ምንን እንደሚያመላክት  እንመልከት፡-   ዓለማቀፍ የአቅርቦት ሁኔታ፡- USDA በመባል የሚታወቀው የአሜሪካ የልማት ድርጅት መረጃ እንደተነበየው 189.7 ሚሊዮን 60 ኪ.ግ ኬሻ ቡና በ2018/19 ለዓለም ገበያ ይቀርባል፤ ከዚህም 105.9 ሚሊዮን አረቢካ፣ 83.8 ሚሊዮን ሮብስታ ይሆናል፡፡ ከቡና ተጠቃሚዎች አንጻር ዓለማቀፍ የቡና ፍጆታ 179.7 ሚሊዮን ኬሻ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡   ዋነኛ አምራች አገራት፡- ብራዚል፡- 71.9 ሚሊዮን ኬሻ ታመርታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአየር ንብረት ሁኔታ ችግር እንዳለ ሆኖ ይህ ምርት ሪከርድ የሰበረ ምርት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ቬትናም፡- 32.5 ሚሊዮን ኬሻ፡፡ ከዚህ መካከል 31.4 ሊዮን ሮብስታ ቡና ይሆናል፡፡ የቬትናም የምትልከው ቡና እየጨመረ የመጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኮሎምቢያ፡- 13.4 ሚሊዮን ኬሻ ታመርታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህ ቢሆንም ቡዌናቬንቱራ የተባለ አካባቢዋ የነሐሴ ወር የመሬት መንቀጥቀጥ መንገዶቿና ሎጂስቲኮቿ ላይ ጉዳት አድርሶባታል፡፡ (ይህም የማምረትና የምርት ማጓጓዟ ላይ እክል ይፈጥራል ተብሎ ይሰጋል፡፡) ኢትዮጵያ፡- 12.1 ሚሊዮን ኬሻ ቡና ታመርታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በውጭ ምንዛሪ ረገድ ደግሞ 3 ቢሊዮን ዶላር ታስገኛለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ (እንደሀገራችን እቅድ ደግሞ 4 ቢሊዮን ዶላር ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡) ኡጋንዳ፡- 7.2 ሚሊዮን ኬሻ፡፡ አገሪቱ በ2030 ዓ.ም 20 ሚሊዮን ኬሻ ቡና ለማምረት አልማለች፡፡ ኢንዶኔዢያ፡- ከመጠን በላይ በዘነበው ዝናብ ምክንያት የዚህች ሀገር የቡና ምርት ወደ 11.4 ሚሊዮን ኬሻ ዝቅ ይላል ተብሎ ተገምቷል፡፡  ሕንድ፡- የአየር ንብረት ጫና እያለባት 6.1 ሚሊዮን ኬሻ ታመርታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሆኖም ቀጣይነት ያለው የሕንድ ቡና ፍላጎት እየተስተዋለ የመጣ ጉዳይ ነው፡፡ ሁንዱራንስ፡- ከ6 ሚሊዮን ኬሻ የተሻገረ ቡና ታመርታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፔሩ፡- የዝናብና የቡና በሽታ ችግሮች ተጋርጠውባት 4.8 ሚሊዮን ኬሻ ታመርታለች ተብሎ ተገምቷል፡፡   ፖሊሲ ኢንዱስትሪውን ቀይሮታል የአውሮፓ ሕብረት ከደን ምንጣሮ ነጻ ምርት ደምብ  እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር ከዲሴምበር 20/2026 ጀምሮ የተሰበሰበ  የቡና ዱካ እና ከደን ነጻ ዳታ የቡና ንግድ ሁኔታውን የሚወስን ይሆናል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ፡- Ø  የኬንያ ቡና ACT 2026 ተጨማሪ የቡና ቻናሎችን (መስመሮችን) ዘርግታለች Ø  ታንዛኒያ የቡና ዋጋ ቤንች ማርክ አስተዋውቃለች Ø  የብራዚል-ዩኤስ የንግድ ፖሊሲ ዓለማቀፍ የቡና ፍሰት ሁኔታ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን ቀጥሏል፡፡   የ2026 የቡና ዋጋዎች የሚያበቁት መቼ ነው? የነሐሴ አጋማሽ ደራጃዎች፡- የዓለም ዓቀፍ የንግድ ድርጅት፡-  ለ0.5 ኪሎ ቡና 285 ሳንቲም የኒዮርክ አረቢካ፡- ለ0.5 ኪሎ ቡና ከ3.15 -3.20 ዶላር   የቡና ታሪክ እልፍ ብሏል ቡና የሸቀጥ ታሪክ ያለው ከመሆን ተሸግሯል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቡና የአየር ንብረት መቋቋም፣ የዱካ ሁኔታ፣ ዳታ፣ የገበያ ተደራሽነት፣ ታማኝ ግንኙነት፣ ሎጂስቲክ፣ የእሴት ስርጭት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ደንቦች፣ የጥራት ጉዳዮች የሚመለከቱት ሆኗል፡፡ ስለሆነም በቀጣይ ምን ያህል ቡና ተመረተ ብቻ የቡና ሁኔታዎችን አይወስንም፤ ይልቅ የዓለም የቡና እሴት ሰንሰለትን ውስጥ ብስለት በተሞላበት መልኩ ግንኙነት መፍጠር፣ ግብይት ማካሄድ እና ማስተዳደር ወሳኞች ሁኔታዎች ይሆናሉ፡፡   ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ ቡና ሁኔታ እንዴት ታዩታላችሁ? ሐሳባችሁን በኮሜንት መስጫ ላይ ያጋሩን፡፡   ምንጭ፡- ዓለማቀፍ የስፔሻሊቲ ቡና ማኅበር ሊንክድኢን ላይ እንደፖሰተው https://lnkd.in/p/eAPtxm4b ጥንቅር፡- በአሸናፊ ጌታሁን

ኮሎምቢያ ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ገጠማት!! እ.ኤ.አ. ነሐሴ 10 ቀን 2026 በኮሎምቢያ ቾኮ (Chocó) ግዛት ሳን ሆሴ ዴል ፓልማር (San José del Palmar) መንደር አቅራቢያ 7.4
ኮሎምቢያ ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ገጠማት!! እ.ኤ.አ. ነሐሴ 10 ቀን 2026 በኮሎምቢያ ቾኮ (Chocó) ግዛት ሳን ሆሴ ዴል ፓልማር (San José del Palmar) መንደር አቅራቢያ 7.4 ሬክተር ስኬል የሚለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ። አደጋው በዚህ ክፍለ ዘመን በሀገሪቱ ከተመዘገቡት የመሬት መንቀጥቀጦች ሁሉ እጅግ ሀይለኛው ሲሆን፣ እስካሁን ከ169 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ እየተነገረ ነው፡፡ አደጋው ዋና ዋና የቡና አምራች ክልሎችን (ሪሳራልዳ፣ ቫሌ ዴል ካውካ፣ ካልዳስ፣ አንቲዮኪያ፣ ቾኮ እና ኪንዲዮ) በከፍተኛ ሁኔታ ጎድቷል። የብሔራዊ የቡና አምራቾች ፌዴሬሽን (FNC) ዋና ስራ አስኪያጅ ዠርማን ባሃሞን (Germán Bahamón) እንዳሉት በአሁኑ ወቅት ብቸኛው እና ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው የሰው ህይወት ማዳን መሆኑን ገልጸው፣ የቡና ምርት መዋቅሮችን የመልሶ መገንባት ስራ ከመንግስት ጋር በመሆን በሂደት እንደሚከናወን አስታውቀዋል። በዋና ዋና መንገድ መሰረተ ልማቶች እና በሀገሪቱ ዋና የወደብ ከተማ ቡኤናቬንቱራ (Buenaventura) ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት የኮሎምቢያ የቡና ኤክስፖርት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቆሟል። የኮሎምቢያ የቡና ላኪዎች ማህበር (Asoexport) ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ጎሜዝ እንደገለጹት፣ የወደብ እና የመንገድ አገልግሎቶች መቼ እንደሚከፈቱ የታወቀ ጊዜ የሌለ ሲሆን፣ የኤሌክትሪክ እና የኮሙኒኬሽን መቋረጥም በቡና ማቀናበሪያ ተቋማት ስራ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል ተብሏል። ምንጫችን ግሎባል ኮፊ ሪፖርት ነው!! አገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር በተለየ በቡናው ዘርፍ ያላት የጋራ ትብብር ቀላል ባለመሆኑ በደረሰው ሰብአዊም ሆነ የንብረት ጉዳት ባለስልጣን መ/ቤቱ በዚህ አጋጣሚ ሀዘኑን ይገልጻል፡፡

የካናዳ ትልቁ የቡና ኢንዱስትሪ ጉባኤ በሚመጣው ህዳር ወር ይካሄዳል የካናዳ የቡና ማህበር (CAC) አመታዊውና ትልቁ የቡና ኢንዱስትሪ ጉባኤ የሆነው "NEXT WAVE" 2026፣ በፈረንሳይኛው አቆጣጠ
የካናዳ ትልቁ የቡና ኢንዱስትሪ ጉባኤ በሚመጣው ህዳር ወር ይካሄዳል የካናዳ የቡና ማህበር (CAC) አመታዊውና ትልቁ የቡና ኢንዱስትሪ ጉባኤ የሆነው "NEXT WAVE" 2026፣ በፈረንሳይኛው አቆጣጠር ህዳር 12 ቀን 2026 (November 12, 2026) እንደሚካሄድ በይፋ አስታወቀ። ላለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት የመግቢያ ትኬቱ ሙሉ በሙሉ ተሸጦ የነበረው ይህ ታላቅ መድረክ፣ ዘንድሮም ከመላው ሰሜን አሜሪካ የተውጣጡ በርካታ የቡና ባለሙያዎችን፣ የዘርፉን መሪዎችና ፈጠራ አቅራቢዎችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። ካናዳ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የቡና ፍጆታ ካላቸው ሀገራት አንዷ ስትሆን፣ ከ71% እስከ 73% የሚሆኑ አዋቂ ዜጎቿ በቀን እስከ ሶስት ሲኒ ቡና ይጠጣሉ። የጉባኤው ዋና ዓላማዎች 1. ጠቃሚ ውይይቶች፦ በዓለም አቀፍ ገበያ፣ በሰራተኞች ዘላቂነት እና በካናዳ የቡና ኢንዱስትሪ ተፅዕኖዎች ላይ የሚያተኩሩ የፓነል ውይይቶች። 2. የገበያ ግንዛቤዎች፦ በካናዳውያን የቡና አጠቃቀምና ወጪ ላይ የተደገፉ ዳታ ተኮር ገለፃዎች። 3. ስትራቴጂካዊ ትስስር፦ በቡና ቆዪዎች፣ ቸርቻሪዎችና አቅራቢዎች መካከል ጠንካራ የንግድ ትስስር የሚፈጠርበት መድረክ። 4. ተነሳሽነትና ፈጠራ፦ የቴክኖሎጂ እድገቶችን፣ ዘመናዊ የምርት ቅንብሮችንና አዳዲስ ፈጠራዎችን ማሳያ። Source: Coffee Geography Magazine

የቡና ምርት እመርታ በአረንጓዴ ዐሻራ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በከፍተኛ ህዝባዊ ተሳትፎ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በኢኮኖሚ ረገድ ዘርፈ ብዙ ውጤቶችን እያስመዘገበ ነው፡፡ በጠቅላይ ሚኒስርት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት 2011 ዓ.ም የተጀመረው ይህ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በመጨመር፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በውጭ ምንዛሬ፣ በምግብ ሉዓላዊነት ራስን በመቻል እና ምርትና ምርታማነትን በመጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያረከተ ይገኛል፡፡ በመርሐ ግብሩ ከሚተከሉት ችግኞች መካከል እንደ ቡና፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ እና ማንጎ የመሳሰሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ቡና ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተከለ ሲሆን በውጤቱም ከፍተኛ እምርታ ተመዝግቦበታል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ የቡና ምርት በመጠን እና በጥራት መጨመሩን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም ከቡና የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን አመልክተዋል፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት ዓመታዊ የቡና ምርት 550 ሺህ ሜትሪክ ቶን ብቻ ነበር፤ ይህ ቁጥር በ2018 ዓ.ም በሦስት እጥፍ አድጎ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ማምረት ተችሏል፡፡ በ2018 ዓ.ም ብቻ ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ከ3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ በ2014 ዓ.ም ተመዝግቦ ከነበረው 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጋር ሲነጻጸር ከእጥፍ በላይ ማደጉን ያሳያል። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስካሁን ከተተከሉት ችግኞች ውስጥ 16 በመቶ የሚሆነውን የቡና ተክል ይሸፍናል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ የተተከሉት የቡና ችግኞች ሙሉ ለሙሉ ምርት መስጠት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ አሁን በዓለም ቡና አምራችነት ካለችበት 5ኛ ደረጃ ወደ 3ኛ ብሎም 2ኛ ከፍ እንድትል ያስችላታል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ቡናን እንደ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ተክል ተወስዶ በመሰራቱ በአጭር ጊዜ የምርት መጠን እና ጥራትን በመጨመር የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ያለመ ትልቅ ብሔራዊ ፕሮግራም ሆኗል። ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን