512
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በ2016 የትምህርት ዘመን አገልግሎት የሚሰጠውን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ፱ኛ ክፍል የቴሌግራም ቻናል በሚከተለው ማስፈንጠሪያ በመቀላቀል የሚተላለፉ መልእክቶችን ይከታተሉ።
https://t.me/ABGSAWAREGrade9
ለ2016 የትምህርት ዘመን የሚያገለግሉ የቴሌግራም ቻናሎች በየክፍል ደረጃው
G-1 https://t.me/+DEgaqD2hLfswY2Q0
G-2 https://t.me/+I33S6j5cE5dmNTFk
G-3 https://t.me/+oH80ZID-TYg5MTVk
G-4 https://t.me/+wBCQMXUqC3YwNmZk
G-5 https://t.me/+eaFpckToCvEwNzU0
G-6 https://t.me/+iSfxnBC9Gt02NDhk
G-7 https://t.me/+fTSYQLyla381YTY0
G-8 https://t.me/+ApqVkaoTqLg5NzU0
ሊንኩን በመከተል ይቀላቀሉ።
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ ጾሙን ጾመ ሥርየት ፤ጾመ መድኃኒት ያድርግልን- አሜን ፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ የእረፍት መታሰቢያ በዓል ተከበረ።
ሐምሌ 22/1982 ዓ.ም በድንገተኛ የመኪና አደጋ ያለፉት የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ዘ ሸዋ እረፍት በአቡነ ጎርጎርዮስ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት አቧሬ ቅርንጫፍ ት/ቤት ተዘክሯል፡፡
በመርሀ ግብሩም ላይ በተማሪዎች እና በመምህራኑ የብፁዕ አባታችን ታሪክ የተወሳ ሲሆን የተለያዩ ዝማሬዎች እና መጣጥፎችም ቀርበዋል፡፡ እንዲሁም በካህናት አባቶች ፀሎተ ወንጌል የተደረሰ ሲሆን ት/ቤቱንም ማዕጥንተ ዕጣን አጥነዋል፡፡
በተጨማሪም ብፁዕ አባታችን ከሚታወቁባቸው ኃይለ ቃል አንዱ "ዝም ብለህ ስራህን ሥራ" የሚለው መልዕክተ ቃል ሙሉ በሙሉ ተነቦ መርሃ ግብሩ በፀሎት ተዘግቷል፡፡
በመርህ ግብሩ ላይም የቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ የክረምት ተማሪዎች ፣መምህራን እና ወላጆች ተገኝተው ተካፍለዋል።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩ ሲሆን ሀምሌ ፳፪/፲፱፹፪ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም ያለፉ ሲሆን በአደጋው ወቅትም አብረዋቸው ዲ/ን ጳውሎስ በቀለ እና ዲ/ን ኤፍሬም ዘውዴ ማለፋቸው ይታወሳል፡፡
የብፁዕ አባታችን በረከት ይደርብን!
