en
Feedback
⚖️ ኢትዮ ህግ አገልግሎት📚📖𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎 𝐋𝐄𝐆𝐀𝐋 𝐒𝐄𝐑𝐕𝐈𝐂𝐄

⚖️ ኢትዮ ህግ አገልግሎት📚📖𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎 𝐋𝐄𝐆𝐀𝐋 𝐒𝐄𝐑𝐕𝐈𝐂𝐄

Open in Telegram

ይህ የቴሌግራም ቻናል በዋነኛነት አዋጆችን፣ ደንቦችን፣ መመሪያዎችን፣ የሰበር ውሳኔዎችን እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዬችን በፍጥነት ለማግኘት ያስችላል። @Lawyer_tebeka @Ethiofeteh tiktok.com/@ethio.ju tiktok.com/@bina858r

Show more
624
Subscribers
-124 hours
+57 days
-130 days
Posts Archive
#በፍትሐብሔር #ክርክር መዝገብ ላይ #የእስር #ትእዛዝ #የሚታዘዝባቸው_ሁኔታዎች በኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ (ፍ/ስ/ሥ/ሕ) መሠረት ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ጉዳዮች ላይ የእስር ትእዛዝ ሊሰጥ የሚችልባቸው ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው። 1፣ የማገጃ (Injunction) ትእዛዝ ባለማክበር:    በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 156 እንደተደነገገው፣ ተከሳሹ በፍርድ ቤት የተሰጠውን የማገጃ ትእዛዝ ያላከበረ፣ በትእዛዙ የተሰጡትን ውሳኔዎች ያልጠበቀ እና እግዱን የጣሰ ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የእስር ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል። 2፣ ንብረት እንዳይበላሽ ለመጠበቅ የተሰጠ ትእዛዝ ባለመፈጸም:     በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 161(2) መሠረት፣ ፍርድ ቤቱ ከፍርድ በፊት ክርክር የተነሳበትን ንብረት እንዳይበላሽ ለመጠበቅ የሰጠውን ማንኛውም ዓይነት ትእዛዝ የማይፈጽም አካል ላይ የእስር ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል። 3፣ የፍርድ ቤትን የመጥሪያ ትእዛዝ ባለመፈጸም (ለምስክር/ማስረጃ ለማቅረብ):     በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 267 እና 268 ላይ እንደተገለጸው፣ አንድ ምስክር ወይም ተከራካሪ ወገን በችሎት ቀርቦ እንዲመሰክር ወይም በእጁ ወይም በስልጣኑ ስር ያለን ማንኛውም ማስረጃ እንዲያቀርብ የፍርድ ቤት መጥሪያ ደርሶት፣ ያለ በቂ ምክንያት ትእዛዙን ያልፈጸመ ወይም የማይፈጽምበትን ምክንያት ቀርቦ ያላስረዳ ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የእስር ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል። 4፣ የፍርድ አፈጻጸም ተከሳሽ ቀርቦ መልስ ባለመስጠት:    በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 386(4) እንደተመለከተው፣ የአፈጻጸም ማመልከቻው የቀረበው የተወሰነ ገንዘብ ለማስከፈል ወይም ፍርድ እንዲፈጸም ሆኖ፣ የአፈጻጸም ተከሳሽ በመጥሪያው መሰረት ያልቀረበ ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ ታስሮ እንዲቀርብና ፍርዱን የማይፈጽምበትን ምክንያት ለመጠየቅ ይችላል። 5፣የፍርድ አፈጻጸም እንዳይፈጸም መሰናክል በመፍጠር ወይም ንብረት በማሸሽ/በመደበቅ:     በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 387 መሠረት፣ የፍርድ ባለዕዳው ፍርዱ እንዳይፈጸም መሰናክል የፈጠረ ወይም የፍርዱን አፈጻጸም ለማዘግየት ንብረቱን ከፍርድ ቤቱ ስልጣን ክልል ውጪ ለማሸሽ፣ ለመደበቅ፣ ወይም ራሱ ለመሰወር ያቀደ መሆኑን የሚያረጋግጥ በቃል መሐላ የተደገፈ አቤቱታ ከቀረበ፣ ፍርድ ቤቱ ባለዕዳው በቀጥታ እንዲታሰር ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል። 6፣ ያለበቂ ምክንያት ፍርድ ለመፈጸም ፈቃደኛ ባለመሆን:     በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 389(1) ላይ እንደተመለከተው፣ የፍርድ ባለዕዳው ያለ በቂ ምክንያት ፍርዱን የማይፈጽም መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም መፈጸም እየቻለ ለመፈጸም ፈቃደኛ ያልሆነ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ፍርድ ቤቱ የፍርድ ባለዕዳውን እስከ ስድስት (6) ወር ሊደርስ የሚችል እስራት ሊፈርድበት ይችላል። 7፣ ችሎት መድፈር/ማስተጓጎል     በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 481 ላይ እንደተገለጸው፣ ማንም ሰው የችሎት ሥራ ዳኛው በሚሰራበት ጊዜ ዳኛው ስራውን እንዳይሰራ ያወከው ከሆነ፣ በችሎት የተከለከሉ ተግባራትን የፈጸመ፣ ወይም ሐሰተኛ የምስክርነት ቃል የሰጠ መሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ፣ በአጠቃላይ ችሎት ደፍሮ ከተገኘ፣ የችሎት መናቅን ያስከተለበት ሰው  በእስራት ወይም የገንዘብ መቀጮ ሊጣልበት ይችላል። (የእስራቱ ጊዜ  በፍ/ስ/ሥ/ሕ/ቁ 481 ላይ ከተደነገገው ጊዜ ጋር ማናበብ ያስፈልጋል)። ማሳሰቢያ: የህግ አንቀጾችና ድንጋጌዎች ትርጉም በልዩ ሁኔታ በፍርድ ቤት ሊወሰን ስለሚችል፣ ለሕግ አገልግሎት የተሰጡትን ቁጥሮችና ይዘቶች ከሕጉ ዋናው ጽሑፍ ጋር ማመሳከር እና ከሕግ ባለሙያ/ጠበቃ ጋር መማከር አስፈላጊ ነው።

የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ስኬል ☝️☝️
+2
የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ስኬል ☝️☝️

ውክልና መሻር / መተው በሀገራችን ፍትሐ ብሔር ህግ የውክልና ስልጣን ውክልናን ሰለ መሻር በሰፈረው ድንጋጌ ሿሚው የጊዜ እና የሁኔታ ገደብ ሳይደረግበት በራሱ ግንዛቤ አስፈላጊ መስሎ በታየው ወይም ባሰበው ጊዜ ሁሉ ለእንደራሴው የሰጠውን የውክልና ስልጣን ማንሳት እና በመካከላቸው የነበረውን ግንኙነት ማቋረጥ ይችላል፡፡ይህን ለማድረግ በፍ/ህጉ ስለ ውሎች በጠቅላላው በሚል ርዕስ ስር ከተደነገገው በተለየ መልኩ ሷሚው ውክልናውን የሚሽር ስለመሆኑ የቅድሚያ ማስጠንቀቀያ(default notice)ለእንደራሴው እንዲሰጥ አይገደድም፡፡ የወኪሉ የውክልና ስልጣኑን ስለመተው ወካዩ የውክልና ግንኙነቱን ማቋረጥ በፈለገ በየትኛውም ጊዜ ሁሉ ስልጣኑን የመሻር መብት እንዳለው ሁሉ እንደራሴውም ስልጣኑን ላለመጠቀም ወይም ለመተው በፈለገ ጊዜ ሁሉ ስልጣኑን ሊተው እና ሊያቆም ይችላል፡፡ይሁንና ከወካዩ ስልጣን በተለየ መልኩ ስራውን ለማቆም በወሰነ ጊዜ አስቀድሞ ወካዩን የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡ህጉ ይህንን ግዴታ ያደረገበት ምክንያት እንደራሴው ስራውን በሚያቆም ጊዜ ንብረቱ ወይም ስራው ከጠባቂ ማጣት የተነሳ ለብልሽት፣ለብክነት ወይም ለጥፋት እንዳይዳረግ በማሰብ ነው፡፡ የተወካዩ መሞት ወይም ስራ ያለመቻል የውክልና ግንኙነት ከሚቋረጥባቸው ምክንያቶች አንዱ እና ሌላኛው የተወካዩ መሞት፣በስፍራው ያለመኖር ፣የመስራት ችሎታ ማጣት ወይም በስራው መክሰር ነው፡፡የፍ/ህጉ አንቀጽ 2230(1)ወካይ እና እንደራሴው በውላቸው እነኚህ ምክንያቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ አስቀድመው በማሰብ በውላቸው ላይ ተቃራኒ የሚሆን ውል አካትተው ካለተስማሙ በቀር በመካከላቸው ያለው ግንኙነት ወድያውኑ ቀሪ ይሆናል፡፡ የወካዩ ህይወት ማለፍ የወካዩ መሞት በውክልና ግንኙነቱ እጣ ፈንታ ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ ከእንደራሴው መሞት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ወካዩ የሞተው ወይም ችሎታውን ያጣው እንደራሴው ስራውን ማከናወን ከጀመረ በኋላ ከሆነ ዕና ክስተቱን ተከትሎ ወድያውኑ ስራውን የሚያቆም ከሆነ በስራው ላይ ጉዳት ሊደርስ የሚችልበት ሁኔታ ካለ ህጋዊ ወራሾች ስራውን ተቀብለው ማስተዳደር ወይም አግባብነት ያለውን አካሄድ እስኪመርጡ እና እስኪያመቻቹ ድረስ እንደራሴው ሿሚው በሰጠው የውክልና ስልጣን ላይ ይቆያል፡፡ በአጠቃላይ በተቋማችን የተሰጠን የውክልና ስልጣን ለመተው ወይም ለመሻር የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው ፡፡ የውክልና ሥልጣን መሻሪያ(በፍ.ህግ ቁጥር 2226/1/ መሠረት) • በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የውክልና ስልጣን መሻሪያ ሰነድ፤ • የውክልና ሻሪው ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ፤ • የሻሪ/ዎች መታወቂያ፤ • ቀደም ሲል የተረጋገጠና የተመዘገበ የውክልና ሥልጣን ሰነድ፤ • ውክልና ለመሻር የቀረበው የንግድ ማህበር ሲሆን ፈራሚው የሚሻረውን ውክልና የሰጠው ሥራ አስኪያጅ ካልሆነ አዲሱ ሥራ አስኪያጅ የተሾመበት ቃለጉባዔ፤ የውክልና ሥልጣን ስለመተው (በፍ/ህግ ቁጥር 2229/1/ መሠረት) • በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የውክልና ስልጣንን መተው ሰነድ፣ • ውክልናውን የሚተወው ሰው ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ፣ • ውክልናውን የሚተወው ሰው/ዎች መታወቂያ፣ • ቀደም ሲል የተረጋገጠና የተመዘገበ የውክልና ሥልጣን ሰነድ፣ አስፈላጊ ነው፡፡ #ምንጭ : የህግና ተያያዥ ማህበራዊ ድረገጾች የተሰናዳ

የፌዴራል_ፍርድ_ቤቶች_የኤሌክትሮኒክ_ዘዴ_አቤቱታ_አቀራረብ_ረቀቂቅ_መመሪያ.pdf5.31 KB

መመሪያ ቁጥር 25/2017 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኤሌክትሮኒክ አቤቱታ አቀራረብ እና ሙግት መመሪያ ቁጥር 25/2017 ጸድቋል                ⚖*⚖ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኤሌክትሮኒክ አቤቱታ አቀራረብ እና ሙግት መመሪያ በማውጣት ከቀጣይ መስከረም 23 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ ስራ ላይ ማዋል ይጀምራል ተብሏል። ⚖⚖⚖👇👇👇⚖⚖⚖

በሀሰት የመመስከር ወንጀል በኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 453 ከንኡስ አንቀፅ 1-4 ስለ ሀሰተኛ ምስክርነት፣ አስተያየት ወይም ትርጉም በሚለው ስር፦ 1. የዳኝነት ወይም የዳኝነት ነክነት ያለው ሥርዓት በሚካሄድበት ጊዜ ምስክር ሆኖ የቀረበ ማንም ሰው ማንኛውንም ተከራካሪ ወገን ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት አስቦ ሀሰተኛ ምስክርነት ወይም የልዩ አዋቂነት አስተያየት የሰጠ እንደሆነ ወይም እውነቱን የደበቀ እንደሆነ ያቀደው ከግቡ ባይደርስም እንኳ በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ግዜ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል። 2. ምስክሩ እውነቱን ለመናገር ምሎ ወይም ማረጋጋጫ ሰጥቶ እንደሆነ  በተለይም የተፈለገው ውጤት በከፊል ወይም በሙሉ ተገኝቶ እንደሆነ ቅጣቱ ከአስር ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል። በተጨማሪም በወንጀል ጉዳይ ተከሳሽ በመስካሪው ድርጊት ምክንያት የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላልፎበት እንደሆነ ወይም ከአስር ዓመት በላይ ፅኑ እስራት ተፈርዶበት እንደሆነ የተመሰከረበት ሰው በስህተት በተወሰነበት ቅጣት ልክ ሀሰተኛ መስካሪው ሊወሰንበት ይችላል። 3. በዳኝነት ወይም በዳኝነት ነክነት ስልጣን ባለው አካል በሚወሰን ጭብጥ አግባብነት ባለው ፍሬ ነገር ሀሰተኛ ትርጉም የሚሰጥ ማንኛውም ተርጓሚ ወይም አስተርጓሚ እንደ አግባቡ ከላይ በተመለከቱት ቅጣቶች ሊቀጣ እንደሚችል ያስቀምጣል። 4. ሀሰተኛ ምስክርነት ወይም ልዩ አስተያየት በሀሰት መተርገም ወይም ማስተርጎም ተደርሶበት ፍርድ ቤት ወይም የዳኝነት ነክ ስልጣን ያለው አካል በሚሰጠው ፍርድ ላይ ተፅእኖ ሊያደርግ የማይችል እንደሆነ ቅጣቱ ከሁለት አመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ነው። https://t.me/legal_service4322 https://t.me/Ethiofeteh2243 👉@Lawyer_tebeka 👉 @Nursiraj

በዕርቅ ማለቅ የሚችሉ የወንጀል አይነቶች በወንጀል ጉዳዮች እርቅ የሚከናወነው በልዩ ሁኔታ ነው፡፡ምክንያቱም በመርህ ደረጃ ወንጀል የህዝብን እና የመንግስትን ጥቅም የሚጎዳ ተግባር ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡ ክስም የሚቀርበው መንግስት በወከለው ዐቃቤ ህግ ሲሆን ሙሉ ወጪውም የሚሸፈነው በመንግስት ይሆናል፡፡ ስለሆነም በወንጀል ህጎች ስር በእርቅ ማለቅ የሚችሉ ገዳዮች በግልፅ ተደንግገው ይገኛሉ፡፡ በወንጀል ህጉ በግል አቤቱታ እንደሚያስቀጡ ከተደነገጉ አንቀፆች ጥቂቶቹን ለአብነት ለመጥቀስ ያክል ፡- 1. ታስቦ የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ 556(1)፣ 2. በቸልተኝነት የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ-559(3))፣ 3. የእጅ እልፊት (አንቀጽ-560(1)) ፣ 4. የዛቻ ወንጀል (አንቀጽ-580) ፣ 5. አመንዝራነት (አንቀጽ-652) ፣ 6. የሥድብ እና ማዋረድ (አንቀጽ-615) ፣ 7. የስም ማጥፋት ወንጀል (አንቀጽ-618) ፣ 8. በቤተዘመድ ንብረት ላይ የተፈጸመ ንብረት ነክ ወንጀል (አንቀጽ-664) 9. ጋብቻን በተንኮል ወይም በማታለል መፈፀም(አንቀጽ-646)፣ 10. ቀለብ የመስጠት ግዴታን ያለመወጣት(አንቀጽ-558)፣ 11. በሌላ ሰው ሀብት ያለአግባብ መጠቀም(አንቀጽ-678)፣ 12. አግኝቶ መደበቅ(አንቀጽ-679)፣ 13. በሰው ንብረት ላይ ሁከት ማድረግ(አንቀጽ-686)፣ 14. በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ(አንቀጽ-689)…ወዘተ ይገኙበታል፡፡ በወንጀል ጉዳዮች እርቅ የሚፈፀምበትን ሂደት ለመምራት ያስችል ዘንድ በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የወጣው መመሪያ ቁጥር 22/2010 ዝርዝር ጉዳዮችን አካቶ ይገኛል፡፡ https://t.me/legal_service4322 https://t.me/Ethiofeteh2243 👉@Lawyer_tebeka 👉 @Nursiraj

በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በክረምት በከፊል የሚሰጡ የዳኝነት አገልግሎቶች የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀጽ 38 ንኡስ አንቀጽ 3 መሰረት ከመደበኛ የፍርድ ቤት የስራ ጊዜ ውጭ አስቸኳይ ጉዳዮች እንደሚስተናገዱ ይገልጻል፡፡ በዚህም መሰረት መሰረታዊ የመብት ጥሰት የሚያስከትሉ በባህሪያቸው ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱ የስራ ጊዜ እስኪጀመር አፋጣኝነታቸው ታይቶ ዉሳኔ ካልተሰጠባቸው የመብት መጣስን ሊያስከትል የሚችሉ እና ሊካስ የማይችል ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ጉዳዮችን አይቶ መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑባቸው ጊዜ ማለትም ከነሃሴ 01 ቀን እስከ መስከረም 30 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ በተረኛ ችሎት በወንጀል እና በፍታብሄር ጉዳዮች መደበኛ የፍርድ ቤት የስራ ጊዜን የማይጠብቁ ጉዳዮች አስቸኳይ ጉዳዮች ሲቀርቡ የሚታዩ ይሆናል በዚሁ መሰረት፡- በፍታብሄር ከሚቀርቡ ጉዳዮች ፡- ➢ አስቸኳይ የእግድ አቤቱታዎች ➢ የልጅ ቀለብ ➢ አካል ነጻ ለማውጣት ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ➢ እንቅስቃሴን ገዳቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ➢ ሰራተኞች በአሰሪዎቻቸው  ላይ የሚያቀርቡት  የደመወዝ ክፍያ የሚመለከቱ አፈጻጸም ጉዳዮች ➢ ከግልግል ዳኝነት ትዕዛዞች ጋር ተያይዞ አስቸኳይ የማህተም አገልግሎት ጥያቄዎች (ለእግድ, መጥሪያ ለማድረስ..) ➢ አንገብጋቢ እና ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ መጠበቅ የማይችሉ በተረኛ ችሎቱ ዳኛ የሚወሰኑ ሌሎች የፍታብሄር ጉዳዮች በወንጀል ከሚቀርቡ ጉዳዮች፡- ➢ ዋስትና ➢ አመክሮ ➢ አርቲዲ (እስረኛ ያለባቸው የሚቀርቡ የወንጀል መዛግብት ) ➢ በተሰብሮ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ➢ ጊዜ ቀጠሮ(አራዳ ምድብ ችሎት) ➢ ለመሰየም የሚቀርብ አቤቱታ ➢ እስረኛ ያለባቸው መዝገቦች ➢ አንገብጋቢ እና ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ መጠበቅ የማይችሉ በተረኛ ችሎቱ ዳኛ የሚወሰኑ ሌሎች የወንጀል ጉዳዮች  ባጠቃላይ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆንባቸው ጊዜያት መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ የማይጠብቁ ጊዜ የማይሰጡ እና አጣዳፊ የሆኑ የወንጀል እና የፍታብሄር ጉዳዮች በተረኛ ችሎት የሚስተናገዱ መሆኑን በማረጋገጥ ሁሉም የፍርድ ቤቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ተገልጋዩ የራሱን አስተዋጽኦ እንዲወጣ እናሳውቃለን፡፡ ምንጭ ፦ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፌስ ቡክ ድረ - ገፅ

" ፍርድ ቤቶቹ ከዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በከፊል ዝግ ይሆናሉ " - ጠቅላይ ፍርድ ቤት ➡️ " ባለጉዳዮች እንዲቀርቡና ውሣኔያቸውን እንዲሰሙ በስልክ ወይም አጭር የጽሁፍ መልእክት እስ
+2
" ፍርድ ቤቶቹ  ከዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በከፊል ዝግ ይሆናሉ " - ጠቅላይ ፍርድ ቤት ➡️ " ባለጉዳዮች እንዲቀርቡና ውሣኔያቸውን እንዲሰሙ በስልክ ወይም አጭር የጽሁፍ መልእክት እስከ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ባሉት ቀናት እንዲያውቁ ይደረጋል! " በ2017 ዓ/ም በፌደራል ፍርድ ቤቶች 190,347 መዛግብት ዕልባት መስጠት መቻሉን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል። የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የሚሰጡት የዳኝነት አገልግሎት ክብደትና ዉስብስብነትን ግምት ውስጥ በማስገባት በቂ እረፍት እንደሚያስፈልጋቸው ታምኖበት በየዓመቱ መጨረሻ ለተከታታይ ለሁለት ወራት ማለትም ከነሐሴ 01 እስከ መስከረም 30 በከፊል ዝግ እንደሚሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከዛሬ ከነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ዝግ ይሆናሉ፡፡ ፍርድ ቤቶቹ በከፊል ዝግ ሆነው በሚቆዩበት የሁለት ወራት ጊዜ በባህሪያቸዉ አስቸኳይ የሆኑና ጊዜ የማይሰጡ እንዲሁም ለዉሳኔ የደረሱ መዛግብትን መርምሮ ውሣኔ የመስጠት አገልግሎቶች እንደሚቀጥሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አሳውቋል።

የፍርድ ቤት እግድ የተሰጠበትን ቤት በሽያጭ በማስተላለፍ የሚደረግ የሽያጭ ውል ሕጋዊ ውጤት የሌለውና ሊፈርስ የሚገባ ስለመሆኑ የፍትሐብሄር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 154 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች እን
+8
የፍርድ ቤት እግድ  የተሰጠበትን ቤት በሽያጭ በማስተላለፍ የሚደረግ የሽያጭ ውል ሕጋዊ ውጤት የሌለውና  ሊፈርስ የሚገባ ስለመሆኑ የፍትሐብሄር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 154 እና ተከታዮቹ  ድንጋጌዎች እንዲሁም የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1808/2 መሠረት በማድረግ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት  በቅፅ 25 መዝገብ ቁጥር  177862 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቶበታል። https://t.me/legal_service4322 https://t.me/legal_service4322 https://t.me/Ethiofeteh2243 Contact us ➱ @Lawyer_tebeka

ቅፅ_27_የፌ_ጠ_ፍ_ቤት_ሠበር_ሰሚ_ችሎት_ውሳኔዎች.pdf4.41 MB

ፍ/ቤቶች ባጠቃላይ ሁለት ወራት (መስከረም እና ነሐሴ) ዝግ ሆነው የሚቆዩ ይሆንል !! ነገር ግን ምን ምን ስራዎች ይከናወናሉ ለሚለው☝️
+1
ፍ/ቤቶች ባጠቃላይ ሁለት ወራት (መስከረም እና ነሐሴ) ዝግ ሆነው የሚቆዩ ይሆንል !! ነገር ግን ምን ምን ስራዎች ይከናወናሉ ለሚለው☝️