ዓምደ ሥላሴ ሰንበት ትምህርት ቤት | Amde Silase Sunday School
Open in Telegram
ይኽ የካራሎ ደ/ታቦር ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የዓምደ ሥላሴ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የዓምደ ሥላሴ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያደርሳል። https://linktr.ee/amdesilase
Show more1 366
Subscribers
+424 hours
+147 days
+2030 days
Posts Archive
#ደብረ_ሊባኖስደብረ ሊባኖስ ገዳም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ደብረ ሊባኖስ ወረዳ የሚገኝ ገዳም የጥንት ሰሙ #ደብረ_አስቦ ነበር። ገዳሙ የተቋቋመው በአራተኛው ክፍለ ዘመን #በአቡነ_ሊባኖስ አማካኝነት ነው። አቡነ ሊባኖስ በቦታው በጸሎት ተወስነው ሲኖሩ ከእርሳቸው በኋላ #ሌላ_ታላቅ_ሐዋርያ እንደሚመጣና ቦታውም በርሱ እንደሚከብር ነገር ግን ለመታሰቢያ ቦታው በስማቸው እንደሚጠራ ከእግዚአብሔር ተነገራቸው። በዚህ ምክንያት ለ700 ዓመታት ያህል ጠፍ ሆኖ ኖሯል። ሌሎች የታሪክ ምንጮች እንደሚሉት አባ ሊባኖስ ከሔዱ በኋላ አባ ዘመደ ሊቃኖስ የተባሉ አባት ወደ ቦታው እንደ መጡ፤ ከርሳቸውም በኋላ አባ ነገደ እስራኤል በኋላም አባ ዘድንግል በየዘመናቸው አያሌ የትሩፋት ሥራዎችን ሠርተውበታል። አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ ደብረ አስቦ ሲመጡ ሐረስ የተባለ ጠንቋይ ቦታውን ወስዶት እንደነበር ይነገራል። ወደ ዋሻው ሲገቡ "እንተ ሶበ ጸዋዕክዎ ለእግዚአብሔር እድኅን እምፀርየ፤ ወይባልሐኒ እምጸላዕትየ ምንስዋን" የሚለውን የዳዊት መዝሙር ይጸልዩ ነበር። ሐረስም ይህንን ሰምቶ አካባቢውን ጥሎ ጠፋ። ጻድቁም ቦታውን ባርከው በአት አድርገውታል። አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚህ ገዳም በተጋድሎ መኖራቸው በየአካባቢው እየተሰማ ብዙ መነኮሳት ተሰባሰቡ። እርሳቸውም እመቤታችንን ይወዱ ስለነበር በዋሻዋ እኩሌታ በሰሌን ጋርደው ታቦተ ማርያምን አኑረው በእኩሌታዋ ደግሞ እርሳቸው ከዐሥራ አምስት ደቀ መዝሙሮቻቸው ጋር ይኖሩ ነበር። በዐፄ ሰይፈ አረእድ ዘመነ መንግሥት /1336-1364/ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተቀበሩበት ዋሻ በመናዱ ለዕጨጌ ሕዝቅያስ አቡነ ተክለሃይማኖት በራእይ በገለጡላቸው መሠረት ዐፅማቸው ግንቦት 12 ቀን ፈልሶ ቤተ መቅደሱ ወደ ተሠራበት አካባቢ መጥቷል። ደብረ ሊባኖስ እየተባለ ስሙ ገኖ መጠራት የጀመረው ከ15ኛው ምእት በተለይም ከዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ /1426 -1460 ዓ.ም/ ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል። የገዳሙ ዋና ሕንጻ ከኢትዮጵያ ነገሥታት ብዙዎቹ ያማረ በመሰላቸው ጊዜያቸው በፈቀደላቸው ጥበብ ሕንጻውን አሠርተዋል። ለምሳሌ የመጀመሪያውን ሕንጻ ያሳነፁት በ1280 የነገሡት አጼ ይኩኖ አምላክ ሲሆኑ፤ ሁለተኛው ደግሞ በ1405 ዓ.ም የነገሡት አጼ ይስሐቅ ነበሩ። እንዲሁም በ1804 ዓ.ም በወሰን ሰገድ ፤ በ1876 ዓ.ም አጼ ዮሐንስ፤ በ1900 ዓ.ም በዳግማዊ ምኒልክ እንደገና ታንጿል። የሥፍራው ገደላማ አቀማመጥ እና የአፈሩ የመሸሽ ባሕሪ ለሕንጻው የማይስማማ በመሆኑ ግንባታው ለብዙ ጊዜ ሊያገለግል አልቻለም። በመጨረሻም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከጥልቅ የግንባታ ጥናት በኋላ ተሠርቶ ኅዳር 9, 1955 ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ተመረቀ። #በተስፋህ_ያመነውን፤ #በቃል_ኪዳንህ_የተማጸነውን፤ ሥጋህን የቆረስክበትን ደምህን ያፈሰስክበትንም #ቦታ_እጅ_የነሳውን ሁሉ #ከሞተ_ነፍስ_አድንልሀለሁ፤ ከዚህ ቦታ #በተስፋ_ጸንተው_በኪዳንህ_ተማጽነው የሚኖሩ ልጆችህን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛልሀለሁ ብሎ ጌታችን ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። #share https://t.me/amdasilase07 #ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts #አቡነ_ተክለሃይማኖት #ደብረ_ሊባኖስ
የጠፋ በግ አዳምን የፈለገው፣ ባገኘውም ጊዜ የተሸከመው፣ እውነተኛ ቸር ጠባቂያችን ክርስቶስ ከአንቺ የተወለደ እመቤቴ ማርያም ሆይ..
ደስ ይበልሽ🤲
ወንድሞቻችን ሆይ ክፉ ሰዎች በዚህ ዓለም በተድላ በደስታ ሲኖሩ ዓይተን "በተድላ በደስታ የሚያኖራቸው ምግባራቸውን ቢወደድላቸው አይደለምን?" ብሎ ማለት እንዳይገባ፣ በጎ ሰዎች በዚህ ዓለም በመከራ ሲኖሩ ዓይተን "በመከራ የሚያኖራቸው ሃይማኖታቸውን ምግባራቸውን ባይወድላቸው አይደለምን?" ብለን ልቡናችን ተስፋ እንዳይቆርጥ መሆን ይገባናል፡፡ በጎውም ሆነ ክፉው የምግባር ዋጋ ከዚህ ዓለም አይደለምና፡፡
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
https://linktr.ee/amdesilase
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
✨✨ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ✨✨
❇️ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት✨ የጉዞ ቀን፦ ቅዳሜ ነሃሴ 23 ✨ የጉዞ መመለሻ ቀን፡ እሑድ ነሃሴ 24 ከንግስ በኋላ ✨ የጉዞ መነሻ ቦታ፦ ካራ አርሴማ ጠበሉ መግቢያ ጋር ✨ የጉዞ መነሻ ሰዓት፦ ጠዋት 1:00 ሰዓት ✨ የጉዞ ዋጋ፦ 1400 ብር መስተንግዶን ጨምሮ መሄድ የምትፈልጉ ይደውሉልን፦ 0962178094 0985462594 0941377308 ✳️ ማሳሰቢያ፦ ማንኛውም ተጓዥ ሲመጣ ክርስቲያናዊ አለባበስ መልበስ ግዴታ ነው። ✨ አርፍዶ ለሚመጣ ተጓዥ መኪና ቢያመልጥዎ ሀላፊነቱን ሰ/ት/ቤቱ አይወስድም። 💥 አዘጋጅ፦ ዓምደ ሥላሴ ሰንበት ት/ቤት https://t.me/amdasilase07 #share #share #share 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ፤ ወልድኪ ይጼውዓኪ፤
ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር።
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤ እና የዕርገት በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ።
https://www.youtube.com/channel/UC1siRxpw-mdM-rXnn1kmoVw?sub_confirmation=1
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
"እስመ ውእቱ ቀደመ አእምሮ ወዜነዎሙ ለአርዳኢሁ በደብረ ታቦር በእንተ መንግሥቱ ዳግመ ምጽአቱ በዐቢይ ስብሐት። እርሱ አስቀድሞ አውቆ ለሐዋርያት በደብረ ታቦር ስለመንግሥቱ ፍጻሜና ዳግመኛ ስለመምጣቱ ነገራቸው። " ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይእንኳን ለጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ክብረ መንግሥቱን ለገለጠበት በዓለ ደብረ ታቦር በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ። 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
✨✨ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ✨✨
❇️ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት✨ የጉዞ ቀን፦ ቅዳሜ ነሃሴ 23 ✨ የጉዞ መመለሻ ቀን፡ እሑድ ነሃሴ 24 ከንግስ በኋላ ✨ የጉዞ መነሻ ቦታ፦ ካራ አርሴማ ጠበሉ መግቢያ ጋር ✨ የጉዞ መነሻ ሰዓት፦ ጠዋት 1:00 ሰዓት ✨ የጉዞ ዋጋ፦ 1400 ብር መስተንግዶን ጨምሮ መሄድ የምትፈልጉ ይደውሉልን፦ 0962178094 0985462594 0941377308 ✳️ ማሳሰቢያ፦ ማንኛውም ተጓዥ ሲመጣ ክርስቲያናዊ አለባበስ መልበስ ግዴታ ነው። ✨ አርፍዶ ለሚመጣ ተጓዥ መኪና ቢያመልጥዎ ሀላፊነቱን ሰ/ት/ቤቱ አይወስድም። 💥 አዘጋጅ፦ ዓምደ ሥላሴ ሰንበት ት/ቤት https://t.me/amdasilase07 #share #share #share 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
#ቡሄ ማለት ምን ማለት ነው ? #ችቦ ለምን እና መቼ ይበራል? #ሙልሙል ለምን ይታደላል? በቡሄ ወቅት #ጅራፍ ለምን ይጮሃል ?
#ቡሄቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡ ወቅቱ የክረምት ፤ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚወጣበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ “ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም “ቡኮ/ሊጥ” ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት “#ሙልሙል” የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡ ✨✨✨
#ጅራፍበደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡ የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ፤ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፤ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡ የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን #በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኅበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡ ✨✨✨
#ችቦችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ አመጣጥ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡ የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ፣ ምሳሌ፣ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ከዚህ ጋርም ተያይዘዞ ችቦ #በ13 ምሽት ይበራል ፣ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡ ✨✨✨
#ሙልሙልበችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ ቡሄ ” እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም፤ ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡ ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ….” ይላሉ፡፡ በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምሥጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡ አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል ከዚም ጋር ተያይዞ ሰንበት ት/ት ቤታችን ለበረካታ ዓመታት ሲወረድ የመጣውን የዝማሬ ሥርዓት ለአጥብያው ምእምን በየቤቱ በመሄድ የቡሄን ዝማሬ ከነሥርዓቱ በመዘመር አገልግሎት ይሰጣል ፤የደብር ታቦርን ሥርዓቱን የጠበቀ ዝማሬ በዚሁ ዓመት በዩቲዩብ ቻናላችን ላይ ተለቋል። ቤተክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት ናት፤ የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ you tube: https://youtu.be/8vWLtyVNG70?si=HRNEdwdvftWWI7kF
#የአብነት_አዳራሽ_ምርቃት“የእግዚአብሔርም ቤት ስለ ተመሠረተ ሕዝቡ ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በታላቅ ድምፅ እልል አሉ።” ዕዝራ 3፥11 የአብነት አዳራሹን ምርቃት ምክንያት በማድረግ ልዩ ጉባኤ ተዘጋጅቷል፤ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት መምህር መልዓከ ታቦር ኃ/ኢየሱስ ትምህርተ ወንጌል ያስተምራሉ፣ ቅኔ፣ ወረብ፣ መዝሙር በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ እናንተን እንጠብቃለን። #ዝክረ_ቅዱስ_ያሬድ #ወጉባኤ_እስጢፋኖስ #ሱባኤ_ጉባኤ #ዓምደ_ሥላሴ #ደብረ_ታቦር #ካራሎ_ቅድስት_ሥላሴ
እንኳን ለጽንሰተ ማርያም በሰላም አደረሳችው🙏" ድንግል ሆይ ከምልጃሽ በቀር ሊጠብቀኝ የሚችል እንደሌለ አወኩኝ ያለ ማህጸንሽም ፍሬ ሊራራልኝ የሚችል እንደሌለ ይህንንም አውቄ ወደ አንቺ ተጠጋሁ በልጅሽም አመንኩ እርሱንም አመለኩ ቸርነቱንም ተስፋ አደረኩ " ❤️ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የነፍስ ምግብ እንጅ
አንዳንድ ሰዎች እንደሚያስቡት ጾም የሥጋ ሥቃይ ሰማዕትነት ወይም መስቀል አይደለም ሥጋ ከነፍስ ጋር የሚተባበርበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ከፍ ከፍ የሚልበት እንጂ። ስንጾም የመጾማችን ዕቅድ ሥጋችንን ለማንገላታት አይደለም ጠባዩን ለመግራት እንጂ። ይህ በመሆኑም አንድ የሚጾም ሰው መንፈሳዊ እንጂ ሥጋዊ ሰው አይሆንም ማለት ነው ።
ጾም መናኝ ነፍስ ስለሆነ በምናኔ ውስጥ ያለ ባልንጀራ ሥጋውን ይዞ ይጓዛል እንጂ ብቻውን አይጓዝም። ጾም ማለት የተራበ ሥጋ ማለት አይደለም የመነነ ሥጋ እንጂ። ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የሥጋ ልዕልና እና ንጽህና እንጂ ለመብላት የሚናፍቅ የሚራብ ሰውነት ያለበት ሁኔታ ማለትም አይደለም፤ መብላት ዋጋውን የሚያጣበትና ሰውነት ለመብላት ካለው ፍላጎት ራሱን የሚያላቅቅበት ሁኔታ እንጂ።
ጾም ነፍስ ከፍ ብላ ሥጋን ከእርስዋ ጋር ከፍ የምታደርግበት ጊዜ ነው። ይህ ጊዜ ሥጋ ጓዙንና ሸክሙን የሚያራግፍበት ጊዜ ስለሆነ እግዚአብሔር ያለ ምንም እገዳ ለመንፈሳዊ ዘላለማዊነት ደስታ የሚሠራበት ጊዜ ይሆናል። ጾም ማለት ነፍስና ሥጋ በኀብረት መንፈሳዊ ተግባር ለማከናውን የሚጠቀሙበት ጊዜ ነው። በጾም ወቅት ነፍስና ሥጋ የነፍስን ሥራ ለመሥራት ይተባበራሉ። ይህም ማለት ለጸሎት ለተመስጦ ለክብርና ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን ሕይወትን ለመጋራት ይተባበራሉ ማለት ነው።
❤️ ብጹዕነታቸው አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
https://t.me/amdasilase07
+9
#ዘዳዊት_በገና_ዘዓምደ_ሥላሴ
#ልዩ_የበገና_መርሃግብር
#መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ
#መልዓከ_ሰላም_ዘውዱ_ንጉሤ
#ነሃሴ_3_2018
#ዓምደ_ሥላሴ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት
#ካራሎ_ደብረ_ታቦር_ቅድስት_ሥላሴ
#ታላቅ_የበገና_ምሽት 🌙✨
"ዘዳዊት በገና ዘዓምደ ሥላሴ" 🙏
🗓️ እሑድ ነሃሴ 3
❤️ ታላቁን አባታችን መጋቤ ስብሐት ዓለሙ አጋ በገናን ከ65 ዓመት በላይ የደረደሩት ከሰፊ የሕይወት ልምዳቸው ጥቂቱን ያጋራሉ 📜🗣️።
⏰ ከ9:00 ሰዓት ጀምሮ መቅረት ያስቆጫል 🚶♂️።
በገና ትምህርት ለመመዝገብ፡👇👇
https://forms.gle/c8SG8jrtE4B3rcgV8
ለበለጠ መረጃ፡
📞 0929010479
📞 0948685897
📍 በዓምደ ሥላሴ ሰንበት ት/ቤት አብነት አዳራሽ 🏛️🎶
https://t.me/amdasilase07
"በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ፣ ከነቢያት ማኅበር ሁሉ ጋራ ወደኔ ነይ፡፡ ካንደበታቸው የወጣውን የምስጋናሽን ኃይለ ቃል ልብ ታስደርጊልኝ ዘንድ፡፡ ድንግል ሆይ፣ የቃልን ካንቺ ሰው መሆን ሥጋ መልበሱንም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ከአስተማሩ፣ በልጅሽም ዕርፈ መስቀል የአሕዛብን ምድር ካረሱ የቃሉንም ድልብ በምድር ሁሉ ከዘሩ ሐዋርያት ጋራ ወደኔ ነዪ፤ ድንግል ሆይ፣ በሥጋቸው የልጅሽን መከራ ከተሸከሙ የሰማዕትነታቸውን ደም ከተቀቡ ሰማዕታት፣ እርሳቸው ሁለት ልሳን ያለው ሰይፍ የሚታጠቁ ድል የሚነሱ የንጉሥ ሠራዊት ናቸው፡፡ ከርሳቸው ማኅበር ጋራ ደግሞ በረድኤት ወደኔ ነዪ፤ ድንግል ሆይ በማመንዘር እድፍ ልብሳቸውን ካላሳደፉ፣ ለመንፈስም ማደሪያ ከሆኑ ንጹሓን ደናግል ማኅበር ጋራ ወደኔ ነዪ"
❤️ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ!
፯ተኛ ዙር ሱባኤ ጉባኤ ዘዓምደ ሥላሴ ልዩ የመክፈቻ መርሃ ግብር፡🗓 አርብ ነሃሴ 1 ⏱ ምሽት ከ12:30 ጀምሮ ✝ መምህር፡ መልዓከ ታቦር ኃ/ኢየሱስ ፋንታሁን በአካል ለመማር ውስን ቦታዎች ይኖሩናል፡ ለመመዝገብ👇👇👇👇 https://forms.gle/MLQDJYaCrxW1AZCw7 👆👆👆👆👆👆👆👆 የርቀት ለመመዝገብ፡ 👇👇👇👇👇👇👇 https://forms.gle/b6uoedCp6yp9BMp16 👆👆👆👆👆👆👆👆 📍 በካራሎ ደብረ ታቦር ቅድስት ሥላሴ ሰንበቴ አዳራሽ ይኼ ልዩ ዕድል እንዳያመልጣችው። https://t.me/amdasilase07
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነዉ የወንድማችን ሃብታሙ ሹሚ #ሮቡ አባቱ ስላረፉ የቀብር ስነስርአታቸዉ ዛሬ 28/11/2018 ዓ/ም ከቀኑ 08:00 ሰዓት በደብራችን በካራሎ ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ስለሚከናወን በስርዓተ ቀበሩ ላይ መገኘት የምንችል አባላት እንድንገኝ ይሁን።
የማጽናኛ መርሃ ግብር ምሽት ከ12:30 ጀምሮ በመኖሪያ ቤታቸው ስለተዘጋጀ በሠዓቱ ተገኝተን ቤተሰቡን እናጽናና።
የአባታችንን ነፍስ በአፀደ ገነት ያኑርልን እመ አምላክ የልባቸዉን ሀዘን ታቅልልን። ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ያድልልን
ዓምደ ሥላሴ ሰ/ት/ቤት
የርቀት ትምህርት (ሱባኤ ጉባኤ) ምዝገባ ጀምረናል፡ለመመዝገብ፡ 👇👇👇👇👇👇👇 https://forms.gle/b6uoedCp6yp9BMp16
አንድ ተማሪ በፈተና አዳራሽ ገብቶ ሁለት ጥያቄዎችን እንዲሠራ ተሰጠው። ጥያቄዎቹ እነዚህ ናቸው።
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ !!
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ !!
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
" ሰው ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑርህ ።
+++ ዝም ብለህ ሥራህን ሥራ+++
ሥራህን ሥራ፦ ጌታ ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰቶታል፤ ያንን መሥራት የእሱ ፈንታ ነው። ቢቻለው እሱን ማገድ የዲያብሎስ ሥራ ነው። በርግጥ ሥራውን እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይጥራል። ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል፤ በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል። የሃሜት ጎርፍ ያስወርድብሃል። ደራሲያን እንዲጠይቁህ፣ እጅግ ስመጥር ሰዎችም በክፉ እንዲናገርብህ ይጠቀምባቸዋል።
ጲላጦስ፣ ሔሮድስ፣ ሐናንያ፣ ቀያፋ ሁሉም በአንተ ላይ ያድማሉ። ይሁዳም በአጠገብህ ቆሞ በሰላሳ ብር ሊሸጥህ ይከጅላል። ይሄ ሁሉ የደረሰብህ ሰይጣን በዚህ ከሥራህ ሊስብህና እግዚአብሔርን ከመታዘዝ ሊያሰናክልህ መሆኑን ልትገነዝብ አትችልምን?
ሥራህን ሥራ፦ ዓላማህ እንደ ኮከብ የጸና ይሁን ተወው ዓለም እንደፈለገው ይነታረክ ይጨቃጨቅ፡፡ አንበሳው ሲያጓራ ፍንክች አትበል። የሰይጣን ውሻዎችን ለመውገር አትቁም፡፡ ጥንቸሎቹን በማባረር ጊዜህን አታጥፋ።
ሥራህን ሥራ፦ ዋሾች ይዋሹ፣ ጠበኞች ይጣሉ፣ ማኅበሮችም ይወስኑ፣ ደራሲዎችም ይድረሱ፣ ሰይጣንም የፈለገውን ያድርግ። አንተ ግን ምንም ነገር እግዚአብሔር የሰጠህን ሥራ ከመፈፀም እንዳያግድህ ተጠንቀቅ።
ሥራህን ሥራ፦ ገንዘብ እንድታተርፍ አልተላክህም፣ እንድትበለጽግም አልታዘዝክም፣ ለክብርህ ተከላከል ብሎ አልተነገረህም፤ ሰይጣን አገልጋዮቹ የሚነዙትን የሐሰት ወሬ እንድታስተባብል አልተጠየቅህም። እነኚህን ሁሉ ነገሮች ብታደርግ ሌላ ሥራ ልትሠራ አትችልም፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ለራስህ እንጂ ለጌታ አልሠራህም።
ሥራህን ሥራ፦ ዓላማህ እንደ ዐለት የፀና ይሁን፣ ጥቃት ይደርስብህ፣ ትበደል፣ ትሰደብ፣ ትታማ፤ ትቆስልና ትናቅ ይሆናል። አንተ ግን በጸና ውሳኔ በማያወላውል ቅናት እስከ መጨረሻ ጸንተህ “የሰጠኽኝን ሥራ ፈፀምኩ ሃይማኖትንም ጠበቅሁ” ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማና የተፈጠርክበትን ግብ ተከተል።
" ዝም ብለህ ሥራህን ሥራ !!!
https://t.me/amdasilase07
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
"እሳትና ውኃን ማዋሐድ እንደማይቻል በሌሎች ኃጢአት መፍረድም በራስ ኃጢአት ከመጸጸት ጋር አብሮ አይሔድም"
✨️️️️️️ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው
"የማያማትብ እጅ ቀኙም ግራውም አንድ ነው"
አባ ፓስዮስ ዘደብረ አቶስ
"እግዚአብሔር ለኃጢአተኛ ሰው ያለው ፍቅር
ጻድቅ ሰው ለእግዚአብሔር ካለው ፍቅር ይበልጣል"
✨️️️️️️ አባ አርሳኒ
✨️️️️️️✨️️️️️️❇️
"ሕፃን ልጅ እናቱ ስታጥበው ያለቅሳል:: ሕፃን እምነት (ትንሽ እምነት) ያላቸው ሰዎችም ነፍሳቸውን የሚያጥብ መከራ ሲመጣባቸው እግዚአብሔርን ያማርራሉ"
✨️️️️️️አባ ስምዖን
"ዕለትን የሠጠህ እርሱ ለእለት የሚበቃህንም ይሠጥሃል"
✨️️️️️️ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
"እጅግ ምርጡ ጸሎት "ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ የፈቀድከውን አድርግልኝ" ማለት ነው"
✨️️️️️️ባሕታዊ ቴዎፋን
✨️️️️️️✨️️️️️️❇️
"ሲያመነዝር ያየኸውን ሰው አንተ ንጹሕ ብትሆንም አትናቀው:: ምክንያቱም አታመንዝር ያለው ጌታ አትፍረድም ብሏል"
✨️️️️️️አባ ቴዎዶር
"አንድ ሰው ኃጢአት ሲሠራ ብታይ እንኳን አትፍረድበት:: አንዳንዴ ዓይንህም ሊሳሳት ይችላል"
✨️️️️️️ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው
"ለኃጢአተኛው ክንፍህን ዘርጋለት:: ኃጢአቱን ልትሸከምለት ባትችል እንኳን ሸፍንለት"
✨️️️️️️ ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ
✨️️️️️️✨️️️️️️❇️
"ይቅር ካላልክ ገነትም ይቅርብህ"
✨️️️️️️አባ ኤፍሬም አረጋዊ
"በሃይማኖታችሁ የሚስቅ እና ሚሳለቅ ቢኖር ጸልዩለት። በፍርድ ቀን የሚያስቅ ነገር አይኖርም።"
✨️️️️️️ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡"
❤️ ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በካራሎ ደብረ ታቦር ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ከወንድማችን ብሩክ (ወልደ አማኑኤል) ጋር የጋብቻ ሥነ ሥርዓትሽን የፈጸምሽው የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ ማኅሌት ዳምጠው (ፍቅርተ ሥላሴ) እንኳን ደስ ያለሽ እንኳን ደስ ያላችሁ ።
የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ አንድነታችሁን ይባርክ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ መልዓኩ ቅዱስ ገብርኤል ይባርካችው፤ ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ እያለች ዓምደ ሥላሴ ሰ/ት/ቤት መልካም የትዳር ሕይወት ትመኝላችኃለች።
" ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል " መጽሐፈ ዲድስቅልያhttps://t.me/amdasilase07
