en
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Open in Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Show more
3 586
Subscribers
+224 hours
-17 days
+4230 days
Posts Archive
Share ለውይይት_የሚቀርብ_Final_Draft_Construction_Industry_Proclamation_1.doc

Share አዲሱ_የተጨማሪ_እሴት_ታክስ_VAT_ረቂቅ_አዋጅ_Michael_Assefa_2015.docx

Share Foreign_Contractors_Performance_Rating_Report_for_the_month_of_December.pdf

Share Local_Contractors_Performance_Rating_Report_for_the_month_of_December.pdf

Share Addis Lissan Ginbot 27-2016.pdf

የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል። • በአንድ ካሬ ሜትር አሸናፊ የሆነው ከፍተኛ ዋጋ 470 ሺህ ብር ሲሆን ዝቅተኛ 20 ሺህ 100 ብር ነው። የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የ2ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ ተሰራጭቷል። በጨረታው ዝቅተኛ ዋጋ የተመዘገበው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ሲሆን ይህም በካሬ ሜትር 20 ሺህ 100 ብር ነው። ከፍተኛው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካሬ ሜትር 470 ሺህ ብር እንደሆነ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። በካሬ ሜትር 470 ሺህ ብር ያቀረበው " ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ት/ቤት " መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአሸናፊዎች ዝርዝር ላይ ተመልክቷል። በአጠቃላይ 4 ሺህ 201 ተጫራቾች የጨረታ ሰንድ በኦንላን መግዛታቸው ተነግሯል። ከነዚህ ውስጥ 2 ሺ 972 ሰነዶች ተሟልተው ተመላሽ እንደተደረጉ ተገልጿል። 1ኛ የወጡ አሸናፊ ተጫራቾች በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ለም ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ኤም.ኤ ህንጻ  ላይ የአዲስ አበባ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በመቅረብ የሊዝ ውል እንዲፈጽሙ ጥሪ ቀርቧል። 1ኛ የወጡ ተጫራቾች ውል የማይፈጽሙ ከሆነ ዕድሉ 2ኛ ለወጡት ተጫራቾች ተላልፎ ይሰጣል።

ከግንባታ ስራ ጋር ቀጥተኛ
ተያያዥነት ያላቸው ከ100,000 ሺ' በላይ አባሎች ያሉበት የቴሌግራም የግንባታ ግብዓት ንግድ ግሩፕ ላይ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ!
በትብብር በተዘጋጀው የቴሌግራም "ዩ ኒ ቲ ፕላትፎርም ላይ ይቀላቀሉ! ይጠቀሙበት፣ ውስን ቦታ ነው ያለን
ለበለጠ መረጃ ስልክ: 📞+251-908280208 | +251- 707999001 | +251-89999001 ቴሌግራም: በ t.me/unitysupplydbot ላይ መልዕክት ቢልኩልን እናስተናግዳለን ዩ ኒ ቲ ኮን.ካታሎግ ሰርቪስ ድህረ-ገፃችን: t.me/UnitySupplierdb1 ☜|]ያጋሩ! በቀላሉ በእጅ ስልክዎ መረጃ ይከታተሉ                                               
መልካም ጊዜ ይሁንልዎ!🙏  
ሁሌም- ወደፊት.. . በአንድነት-ወደስኬት .. .                          

Share የብድር ውል ፎርም.docx

Share የህንፃ መመሪያ ቁጥር 90_2014.pdf

✈️ 23 ትናንሽ አውሮፕላን ማረፍያዎች ሊገነቡ ነው፡፡ ከፍተኛ የአውሮፕላን ማረፍያ በሌለባቸው ነገር ግን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች አሉባቸው በሚባልባቸው አካባቢዎች ትናንሽ አየር ማረፍያዎች እንደሚገነቡ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አስታውቋል፡፡ 👉 የትራንስፖርትና ሎጂስትክስ ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ የኢትዮጵያ መንግስት ለአዳዲስ የአውሮፕላን ማረፍያዎች ግንባታ የሚሆን በጀት አለመያዙን ተናግረው አሁን የሚገነቡ ትናንሽ አየር ማረፍያዎች በተለያዩ ወጪዎች የሚሸፈኑ ይሆናል ብለዋል፡፡ 👉 በተለያዩ የክልል አካባቢዎች የሚገነቡት 23 ትናንሽ አውሮፕላን ማረፍያዎች ተለይተው መታወቃቸውን የተናገሩት ሚኒስትሩ የአዋጭነት ጥናት የመሬት ጥናት እና ሌሎችም ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ 👉 እነዚህ ግንባታዎች በራሳቸው ወጪ ለማከናወን የክልል መንግስታት ፍላጎት ማሳየታቸው የተነገረ ሲሆን ባለሃብቶችም ጭምር ፍላጎት እንዳላቸው ነው የተነገረው፡፡ (ኢትዮ ኤፍ ኤም)

💥ብዙ የኮንስትራክሽን ባለሞያዎች መሰንጠቅ በMix design ትክክል አለመሆን ብቻ የሚመጣ ይመስላቸዋል ነገር ግን ለመሰንጠቅ (cracking ) ምክንያት የሚሆኑ መንስኤዎችን ከዚህ በታች እንዲህ ዳስሰናል :- [1] - አነስተኛ ጥራት ያላቸውን ቁሶች የምንጠቀም ከሆነ . አነስተኛ ጥራት ያላቸውን ቁሶች የምንጠቀም ከሆነ መሰንጠቅ (cracking ) ይፈጠራል ስለዚህ የምንጠቀማቸውን ለኮንክሪት ግብዓት የሚሆኑ ቁሶችን (ሲሚንቶ፣ አሸዋ፣ ኮረኮንች) ጥራት መፈተሽ አለብን ኮንክሪቱ የብረት መዋቅር (reinforcement ) ያለው ከሆነ የብረቱን ጥራት መገምገም አለብን። . [2] - መኮማተር (Shrinkage ) . ኮንክሪቱን በምንደባልቅበት እና ውሃ በምናጠጣበት ግዜ (Curing ) ተገቢውን ጥንቃቄ ካልወሰድን መኮማተር (shrinkage) መሰንጠቅን(cracking)   ያስከትላል ። መኮማተር (shrinkage) ለትልቅ የኮንክሪት ጥንካሬ በጣም አስፈላጊ ነው አስፈላጊውን የውሃ-ሲሚንቶ መመዛዘን (water cement ratio) ካልተጠቀምን በመኮማተር አማካኝነት መሰንጠቅ ሊፈጠር ይችላል ። . [3] - ጥራት ያለው Aggregate የማንጠቀም ከሆነ . Aggregate የኮንክሪትን አጠቃላይ ጥንካሬ ይወስንልናል ጥራቱ ጥሩ ያልሆነ Aggregate የምንጠቀም ከሆነ ከሲሚንቶ ጋር ተፈላጊውን ጥምረት (bond) ስለማይፈጥር ግንባታችን ሊሰነጠቅ ይችላል። . [4] - መዋቅራችን ከአቅም በላይ የሆነ ክብደት ሲያስተናግድ . ግንባታው / መዋቅሩ ተገቢውን ጥንካሬ ሳያገኝ በፊት ለትልቅ ክብደት የሚጋለጥ ከሆነ መሰንጠቅ ይከሰታል። በተጨማሪም መቀሰቻዎችን እና ቅስቱን (formwork ) ያለጊዜው የሚነሳ ከሆነም ግንባታችንን ለስንጣቆ ያጋልጠዋል። . [5] - በትክክል ውሃ እንዲጠጣ የማይደረግ ከሆነ (improper curing ) . ይህ በአገራችን ከሚስተዋሉ ለመሰንጠቅ ከሚዳርጉ ምክንያቶች ቀዳሚው ነው - ውሃ በትክክል አለማጠጣት። ኮንክሪት እንደተገነባ በተገቢው ጊዜ እና መጠን ውሃ መጠጣት አለበት ። «ወንድና ሲሚንቶ ካልጠጣ ይሰነጠቃል» አይደል ሚሉት ሰካራም ወንዶች : . [6] - የውጥረት ስርጭት (stress distribution ) አለመመጣጠን . በጣም ትልቅ የሆነ የብረት መዋቅርን Mix ratioው ትንሽ በሆነ ኮንክሪት የሙሌት ስራ ስንሰራ በብረቱ እና በኮንክሪቱ መካከል ያለ የውጥረት ስርጭት (stress distribution ) non linear ይሆናል ይህ ደግሞ መሰንጠቅን ያስከትላል። . [7] - በሳይት ላይ የሙሌት (casting ) ስራ ሲሰራ ተገቢ ጥንቃቄ ካልተደረገ እና ለስራው ተገቢ የሆነ ባለሞያ (የቀን ሰራተኛን ጨምሮ) ካልተመደበ መሰንጠቅ (cracking) በሚሰራው ኮንክሪት ላይ መፈጠሩ አይቀርም።