Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Open in Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Show more3 586
Subscribers
+224 hours
-17 days
+4230 days
Posts Archive
የኮንስትራክሽን_ብቃት_ማረጋገጫ_ምዝገባ_መመሪያ_1.pdf50.77 MB
ሊዝ ጨረታ ማስታወቅያ:-በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቅያ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክ/ከተማ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ፣ በየካ፣በንፋስ ስልክ ላፍቶ፤በኮልፌ ቀራንዮ ፣በአቃቂ ቃሊቲ፤በአዲስ ከተማ ፣ልደታ እና በጉለሌ ክ/ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ለማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሠረት በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች 1.ለአንድ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 2,300.00 (ሁለት ሺህ ሶስት መቶ ብር) በቴሌ ብር በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከሐምሌ 01/2016 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ድረስ በ(2merkato.com link :- https://addisland.2merkato.com afrotender.com link:-https://addisland.afrotender.com) መግዛት ይችላሉ፡፡ 2.ማንኛዉም በዚህ የመሬት ሊዝ ጨረታ ለመሳተፍ የፈለገ ተጫራች በተራ ቁጥር 1 ላይ በተገለጸዉ ዌብ ሳይት የጨረታ ሰነድ ለመግዛት በመጀመሪያ በስሙ የቴሌ ብር አካዉንት በመክፈት ከአካዉንቱ ተቀናሽ በማድረግ ሰነዱን መግዛት ይጠበቅበታል፡፡ 3. ተጫራቾች ቦታዎቹ የሚገኙበት ቦታ በመሄድ አጠቃላይ የቦታዎችንሁኔታ በማየት ዋጋ ማቅረብ አለባችሁ፡፡ 4. አንድ ተጫራች በአንድ የጨረታ ዙር ከአንድ ቦታ በላይ መጫረት አይችልም፡፡ በመሆኑም ከአንድ በላይ ቦታ ተጫርቶ ከተገኝ ተጫራቹ ከጨረታ ውጪ ይሆናል፡፡ 5. ተጫራቾች ሞልተዉ የሚያቀርቡት የጨረታ መልስ ማቅረቢያ ሰነድ በተጫራቾች መመሪያ ላይ በቀረበው መስፈርት መሠረት መሆን ይኖርበታል፡፡ 6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበት ቦታ ስፋት በመነሻ ዋጋ ተባዝቶ ከሚገኘዉን ጠቅላላ ዋጋ 50% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የክፍያ ማዘዣ /ሲፒኦ/ ለየቦታ ኮዱ በጋዜጣው ላይ የተቀመጠውን መጠን ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ይህ ሳይሆን ቢቀር ወይንም ከ 50% ቢያንስ ተጫራቹ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከውድድር ይሰረዛል፡፡እንዲሁም አንድ ተጫራች ሌላው በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም፡፡ከአዲስ አበባ ውጪ ከሚገኙ ባንኮች ሲፒኦ ስታሰሩ አዲስ አበባ ከሚገኙ ባንኮች በኔትወረክ የተያያዘ መሆን አለበት ይህ ሳይሆን ቀርቶ ችግር ቢፈጠር ቢሮው አይጠየቅም፡፡ 7. ተጫራቾች የጨረታ መልስ ማቅረቢያ ሰነድ ስትመልሱ፣ 7.1 ኦርጅናል ሲፒኦ (CPO) 7.2 የመስሪያ ቤቱ ማህተም ያረፈበት የጨረታ መልስ ማቅረቢያ ሰነድ 7.3 የተጫራቹ መታወቂያ ኮፒ 7.4 ሰነድ ለመግዛት በቴሌ ብር የተከፈለበት ስሊፕ (ደረሰኝ) 7.5 ኦርጅናል የአቅም ማሳያ ማስረጃ 7.6 ተጫራቹ የሚጫረተው በተወካይ ከሆነ የተወካይ መታወቂያ እና የውክልና ማስረጃ ኮፒ 7.7 የውጭ አገር ዜግነት ያለው በትውልድ ኢትዮጵያዊ የሆነ ማንኛውም ተጫራች ከሚኖርበት አገር በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ /ቆንስላ ጽ/ቤት/ የተሰጠውንና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ በውልና ማስረጃ የፀደቀ መታወቂያ የዋናውን ኮፒ ከመልስ ማቅረቢያው ጋር ማያያዝ አለበት፡፡ 7.8 የንግድ ማህበራት ለሆኑት በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ፅ/ቤት የፀደቀ የማህበሩን መመስረቻ ፅሁፍ እና መተዳደሪያ ደንብ ፎቶ ኮፒ ሌሎች ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች ከሆኑ ህጋዊነታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ እና የታደሰ ምስክር ወረቀት ፎቶ ኮፒ 7.9 ጨረታው የሚሳተፉት ባልና ሚስት በአንድ ሰነድ ከሆነ ህጋዊ የጋብቻ ማስረጃ ኮፒ እና በአንድ ወገን ስም የተሰራ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡ 7.10 በአንድ የጨረታ ሰነድ ከአንድ ሰው በላይ ሆነው ለመወዳደር ከፈለጉ ከሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ፅ/ቤት የተረጋገጠ የተደራጁበትን ህጋዊ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 7.11 በአጠቃላይ ከላይ የተገለጹትን ማስረጃዎች በፖስታ በማሸግ የጨረታ ቁጥር እና የቦታ መለያ ኮድ በፖስታው ላይ በመጻፍ ሐምሌ 12/2016ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ስዓት ድረስ ብቻ ለም ሆቴል አካባቢ ኤም ኤ (MA) ህንፃ ላይ በሚገኘው በከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለዚህ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ 8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በ7 ተከታታይ የስራ ቀናት በቦሌ ክ/ከተማ አስተደዳር አዳራሽ የሚከፈት ሆኖ ዝርዝሩ በውስጥ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡ተጫራቾች ቦታውን በአካል ለመመልክት ከፈለጉ በ05/11/16ዓ.ም፣08/11/16 ዓ.ም እና በ10/11/16 ዓ.ም ጠዋት በ3፡00 እና ከሰዓት በ8 ሰዓት ለጨረታ የተዘጋጁ ቦታዎች በሚገኙበት ክ/ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ድረስ በመቅረብ ለዚህ ስራ በሚመደቡ አስጎብኝዎች አማካኝነት ቦታዎቹን መመልከት ይቻላል፡፡ 9. ጨረታውን ያላሸነፉ (ተሸናፊ) ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙትን ሲፒኦ የጨረታው አሸናፊዎች በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ከተገለፀበት ከ15 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ አጫራቹ መ/ቤት ለባንክ በመላክ ወዳሰሩበት የባንክ ሂሳብ ተመላሽ ይደረጋል፡፡ በካሽ ያሰሩ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናውን ለመረከብ በቅድሚያ የሲፒኦውን ጉርድ ኮፒ ማቅረብና ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቀርበው መውሰድ አለባቸው፡፡ ከላይ በተገለጸዉ የጊዜ ገደብ ውስጥ ቀርበው ካልወሰዱ ለሚፈጠረው ችግር አጫራቹ መ/ቤት ተጠያቂ አይሆንም፡፡ 10. መስሪያ ቤቱ (ቢሮው) የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 11. ለተጨማሪ መረጃ የመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ፡- በስልክ ቁጥር +251111570595 መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡ https://www.aalb.gov.et/ ምንጭ~የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የጨረታ ማስታወቂያየጨረታ ቁጥር SSNT-1468 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ብቁ የሆኑ ደረጃ 1 ጠቅላላ ሥራ ተቋራጮችን እና የመንገድ ስራ ተቋራጮችን (GC/RC-1) በጨረታ አወዳድሮ የአርባ ምንጭ ኤርፖርት የአየር ማረፊያ እና ተርሚናል ጥገና ፕሮጀክት (Arba Minch Airport Airfield Maintenance Project) በዲዛይን እና ግንባታ የውል ዓይነት (Design and Build Project Delivery Method) ለማሰራት ይፈልጋል:: ስለሆነም ለስራው ብቁ የሆኑ ተጫራቾች ፣ የዘመኑን የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የታደሰ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከተፈቀደለት አካል በምድብ GC/RC- 1፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ ከመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ (PPPAA) የአቅራቢነት የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ፣በመንግስት ጨረታዎች ለመሳተፍ ፈቃድ ያላቸው እና ከግብር እዳ ነጻ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ አፈፃፀማቸው ከሰባ በመቶ በታች የሆነ (<70%) ከሁለት (2) በላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ፕሮጄክቶች ያላቸው ተቋራጮች በዚህ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ ብቁ አይደሉም። ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት የስራ ቀናት በአቅራቢያቸው ከሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የማይመለስ 100.00 ብር (አንድ መቶ ብር) በሂሳብ ቁጥር 1000006958277(E-99) ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጨረታ ቁጥር SSNT T468 በሚል ገቢ በማድረግና የከፈሉበትን የገቢ ደረሰኝ ቅጅ (Deposit Slip Copy) ከታች በተጠቀሰው የኢሜይል አድራሻ በመላክ የጨረታ ሰነዱን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ክፍል በኢሜይል ማግኘት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000.00 / አምስት መቶ ሺህ ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) ወይም ለ150 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ የሌለው የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ከማንኛውም ኢንሹራንስ የሚቀርብ ዋስትና ተቀባይነት አይኖረውም። አሸናፊው ከተለየ በኋላ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ወዲያውኑ ተመላሽ ይሆናል፡፡ ተጫራቾች በጨረታው ደንብ መሠረት የመጫረቻ ሠነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ክፍል እስከ ዓርብ, ነሐሴ 03 2016 ዓ.ም ከ ቀኑ 08:00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቦሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና መሥሪያ ቤት የጨረታ መክፈቻ አዳራሽ ውስጥ በተመሳሳይ ቀን ከ ቀኑ በ 09:00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
ተጨማሪ ማብራሪያ:-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ክፍል ስልክ ቁጥር 011-517-8025 ኢ-ሜይል: KidistTa@ethiopianairlines.com አየር መንገዱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የጨረታ ማስታወቂያየጨረታ ቁጥር፡ -SSNT-T464 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በሶማሌ ክልል በጂግጅጋ ከተማ ለሚያስገነባው የጂግጅጋ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የምህንድስና ዲዛይን፣ የግንባታ ቁጥጥር፣ የኮንትራት አስተዳደር እና የግንባታ ማማከር አገልግሎት ለሚሰጡ ደረጃ 1 የመንገድ እና አጠቃላይ አማካሪ ድርጅቶችን (Category 1 Road/General Consultants for the Detailed Engineering Design, Construction Supervision, and Contract Administration of Jigjiga Airfield Project located in the Somali Regional State at Jigjiga City) በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ብቁ የሆኑ አማካሪዎችን ስራውን ለማከናወን ጨረታውን እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡ ተጫራቾች በአገር ውስጥ ፍቃድ ከሚሰጥ ህጋዊ አካል ተመዝግበው የማማከር አገልግሎት እንዲሰጡ የተፈቀደላቸው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የተሰጣቸው እና በዘርፉ ለመስራት ለ2016 ዓ.ም ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ ተጫራቾች የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ የሚያሳይ ህጋዊ የስራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የመንግስትተመዝጋቢ ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአቅራቢዎችና አገልግሎት ሰጪዎች ዝርዝር ላይ የተመዘገቡ መሆን ይገባቸዋል፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆነ፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ ፈቃድ ያላቸው እና ከግብር እዳ ነጻ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፣ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት የስራ ቀናት በአቅራቢያቸው ከሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የማይመለስ አንድ መቶ ብር (100.00 ብር) በሂሳብ ቁጥር 1000006958277(E -99) ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጨረታ ቁጥር SSNI-464 በሚል ገቢ በማድረግና የከፈሉበትን የገቢ ደረሰኝ ኮፒ (Deposit Slip Copy) ስካን በማድረግ ከታች በተጠቀሰው የኢሜይል አድራሻ በመላክ የጨረታ ሰነዱን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግዢ ክፍል በኢሜይል ማግኘት ይችላሉ፡፡ በጨረታው የሚካፈል ማንኛውም ተጫራች ለሚጫረትበት አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር (150,000.00ብር) የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስም ማስያዝ አለባቸው:: ከማንኛውም ኢንሹራንስ እና ቅድመ ሁኔታ ያለው የባንክ ዋስትና ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ጨረታው ከተዘጋበት ቀን ጀምሮ ለ150 ቀናት የሚቆይ ይሆናል። አየር መንገዱ ጨረታው የሚቆይበትን ጊዜ እንዲራዘምለት ተጫራቾችን የመጠየቅ መብት አለው። በአሁኑ ወቅት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር በሁለት (2) ወይም ከዚያ በላይ ፕሮጀክቶች ላይ የተሰማሩ የእያንዳንዱ ፕሮጀክት መጠናቀቂያ በመቶ ከ70% ያነሰ ከሆኑ በዚህ ጨረታ እንዲሳተፉ አይፈቀድላቸውም። ተጫራቾች በጨረታው ደንብ መሠረት የመጫረቻ ሠነዳቸውን (ቴክኒካልና ፋይናንሻል) ዋናውን እና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ክፍል እስከ ረቡዕ, ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ቦሌ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መስሪያ ቤት የሠራተኞች መመገቢያ አዳራሽ ውስጥ በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9:30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
ተጨማሪ ማብራሪያ፡-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትራቴጂክ ሶርሲንግ ነን ቴክኒካል ክፍል ስልክ ቁጥር 011-517-4918 አቶ አሰፋ ኃይሉ ኢ-ሜይል: Assefah@ethiopianairlines.com አየር መንገዱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ዝግ መንገዶች
በኮሪደር ልማት ስራ ምክንያት መንገዱ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት እስኪሆን
ከፊጋ መስመር ወደ ቀኝ ታጥፎ ሳህሊተምህረት አደባባይ።
ከጃክሮስ መስመር መብራቱን ተሻግሮ ወደ ሳህሊተምህረት አደባባይ።
ከማእድን ሚኒስቴር ጫፍ ታጥፎ ወደ ሳህሊተምህረት አደባባይ።
ከዛሬ ሐምሌ 1/2016 ዓ.ም ምሽት 2:30 ጀምሮ እንዲሁም፣
ከጠዋቱ 12 ሰዓት መሉ ቀንና ምሽትን ጨምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ለማንኛውም አይነት ተሽከርካሪ ዝግ መሆኑንና
በተጨማሪም
ከአያት ወደ መገናኛ እና ከመገናኛ ወደ አያት ቀጥታ ማለፍ እንጂ አደባባዩን መዞርም ሆነ ማቋረጥ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን።
በዚሁ አጋጣሚ የከተማዋ ነዋሪዎች በልማት ስራው ምክንያት እየተፈጠሩ ላሉ ጊዜያዊ እንግልቶች ላሳያችሁት ትእግስትና ትብብር ከልብ እናመሠግናለን።
ምንጭ~ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን
2016 4TH CONSTRUCTION WORKS (ONLY DIRECT COST).pdf19.60 MB
Surveyor - June 30 to July 10/2024Contract Senga tera in front of A.A.U School of Commerce on Biftu Adugna Building 5th floor , Addis Ababa, Ethiopia Location project Job Requirement Qualification ; Work Experience & required skill: College Diploma or TVETII with COC and 4 Years direct work experience Language: ability of Afan Oromo is advantageous Work Place: Project How to Apply Application dead line: – 7 working days from the date of announcement on this News Paper At Least half of the required work experience should be from construction organization Females are encouraged to apply Interested and qualified applicants are invited to submit their non-returnable application, CV and copies of testimonials to OBM Construction share company Head office located at around Senga tera in front of A.A.U School of Commerce on Biftu Adugna Building 5th floor. 0115621294
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
