en
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Open in Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Show more
3 589
Subscribers
-524 hours
+37 days
+3830 days
Posts Archive
በኮንስትራክሽን ውል የስራ ለውጥ/Variation/ቫሬሽን/variation/ ምን አይነት ትርጉም ሊሰጠው ይችላል? በኮንስትራክሽን ውል የስራ ለውጥ(variation) የሚባለው በዋናነት የግንባታ ስራ ጥራትን፣መጠን፣ዲዛይን፣የግንባታ ቁሳቁስ፣የስራ ጊዜ፣የግንባታ ማከናወኛ ቦታ መጠን የመሳሰሉትን የማሻሻል፣የመጨመር ወይም የመቀነስን የሚመለከት የኮንስትራክሽን ውል መሰረታዊ ነጥብ ነው፡፡ ስለዚህ ቫሬሽን የዋናውን የኮንስትራክሽን ውል ይዘት/object of the contract/ በመጠኑ የመለወጥ ባህሪ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡ PPA 2011 ክሎስ 15.1 ይሄንኑ አረዳድ በሚያጠናክር ሁኔታ ለቫሬሽን ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ቫሬሽን ኦርደር/variation order/ የሚባለውስ ምንድን ነው? ማነው ኦርደር ሰጭው? በቃል ኦርደር መስጠት ይቻላል? በምን አይነት መልኩ ነው ትእዛዝ የሚሰጥ? በዚህ ረገድ ህጉ ምን ይላል? ቫሬሽን ኦርደር ከመሀንዲሱ ለተቋራጩ በጽሁፍ የሚሰጥ የስራ ለውጥ ትእዛዝ ነው፡፡ አማካሪ መሀንዲሱ ለግንባታ ስራው መልካም አፈጻጸም ሲባል የስራ ለውጥ ትእዛዝ አስፈላጊ ነው ብሎ ካመነ ትእዛዝ መስጠት ይችላል፡፡ በመጀመሪያ ግን በአማካሪ መሀንዲሱ አማካይነት ለተቋራጩ ስለለውጥ ስራው ባህሪና ምንነት ማሳወቂያ/ኖቲስ/ እንዲደርሰው ይደረጋል፡፡ኖቲስ እንደደረሰው ተቋራጩ የለውጥ ስራውን አስመልክቶ ትሮፖዛል ያቀርባል፡፡ፕሮፖዛሉም የጊዜ ማራዘሚያ/ስኬጁል፣የዋጋ ሁኔታን የሚያካትት ይሆናል፡፡(PPA 15.3) የስራ ለውጥ ትእዛዝ በጽሁፍ ነው መደረግ እንዳለበት PPA 2011 ክሎስ 15.2 ያስቀምጣል፡፡አንዳንዴ ግን አማካሪ መሀንዲሱ በቃል የቫሬሽን ትእዛዝ መስጠት እንደሚችል PPA 2011 ክሎስ 15.2(a) ላይ ፈቃጅ ሆኖ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን በቶሎ የለውጥ ስራ ትእዛዙ ወደ ጽሁፍ መቀየር ይኖርበታል፡፡ እዚህ ጋር አብሮ የሚታየው ነገር የአስተዳደር መስሪያ ቤት ጋር የሚደረጉ ውሎች በጽሁፍ መደረግ ይኖርባቸዋል፡፡ይሄውም ስለውሎች በጠቅላላው በሚመለከተው የውል ህግ አንቀጽ 1724 ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ አንድ ውል የሚሻሻለው ደግሞ ከመጀመሪያው ውል ጋር ተመሳሳይ በሆነ ፎርም ነው፡፡በዚህ ረገድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1722 ላይ "ዋናውን ውል የመለወጥ ጉዳይ ለዚሁ ውል በተደነገገው አጻጻፍ(ፎርም) መሰራት አለበት፡፡" በሚል የተደነገገው የሚያስገነዝበውም ቫሬሽን ዋናውን ውል በከፊል የመለወጥ ሁኔታ ስለሚኖረው ከዋናው የኮንስትራክሽን ውል ጋር በተመሳሳይ የአጻጻፍ ፎርም በጽሁፍ መደረግ ይኖርበታል ማለት ነው፡፡ለዚህ ነው በመርህ ደረጃ ቫሬሽን በጽሁፍ መደረግ አለበት የሚባለው፡፡ የስራ ለውጥ ውል/change agreement/ ምን ማለት ነው? ከህግ አንጻር በዚህ ረገድ ምን ነጥቦች ሊነሱ ይችላሉ? PPA 2011 ክሎስ 15.9 ላይ እንደተቀመጠው በየስራ ለውጥ ውል የሚባለው ከቫሬሽን ኦርደር በኋላ አሰሪው/ተወካይ መሀንዲሱ እና ተቋራጩ በጽሁፍ የሚስማሙበት የማሻሻያ ውል ነው፡፡ ሆኖም በዚህ የፒፒኤ ትርጉም ጸሀፊው አይስማማም፡፡ምክንያቱም አማካሪው ስራ ለመቆጣጠር እንጅ ውል ለመዋዋል በአማካሪነት ውሉ ላይ ብዙ ጊዜ ስልጣን አይኖረውም፡፡በተቋራጭና አሰሪ መካከል የተደረገ የኮንስትራክሽን ውል በአሰሪና ተቋራጭ በሚደረግ ስምምነት/ውል ሊሻሻል ከሚችል በስተቀር አማካሪ መሀንዲሱን ውል እንዲዋዋል እስከመፍቀድ የሚደርስ ትርጓሜ መሰጠቱ ተገቢነት የለውም፡፡ የስራ ለውጥ ውሎች ቀን፣ቁጥርና ቅደምተከተል ይሰጣቸዋል፡፡(ፒፒኤ15.10) ሌላው የስራ ለውጥ ውል ወደኋላ ሄዶ እንደማይሰራና ውሉ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ብቻ አስገዳጅ እንደሚሆን PPA 2011 ክሎስ 15.10 ላይ ተቀምጧል፡፡ በቫሬሽን የተሰሩ ስራዎች የዋጋ አወሳሰን/Valuation of variation/ በምን ሁኔታ ይከናወናል? የተሰራው ተጨማሪ ስራ ከሆነ እና በቢል ኦፍ ኳንቲቲ ላይ ዋጋ ተተክሎለት ካለ በዚያው የዋጋ ሬት የሚሰላ እንደሚሆን PPA 2011 ክሎስ 15.5(a) ላይ ተቀምጧል፡፡ በቫሬሽን የሚሰራው ስራ በቢል ኦፍ ኳንቲቲ ያልተካተተ አዲስ የስራ አይተም ከሆነ በመሀንዲሱና ተቋራጩ በስምምነት በወቅታዊ ዋጋ የሚሰላ እንደሚሆን PPA 2011 ክሎስ 15.5(b) ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ በቫሬሽን የተካተተው የስራ አይተም ዋጋው በቢል ኦፍ ኳንቲቲ ላይ የተካተተ ቢሆን እንኳ የተጋነነ ከሆነ በመሀንዲሱ ሊስተካከል እንደሚችል ደግሞ PPA 2011 ክሎስ 15.5(c) ይገልጻል፡፡ ቫሬሽኑ የተከሰተው በተቋራጩ ጥፋት ከሆነ ደግሞ በአሰሪው ለተቋራጩ ዋጋ አይከፈልበትም በሚል PPA 2011 ክሎስ 15.5(d) በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ ቫሬሽን እስከስንት ፐርሰንት ይፈቀዳል? በፍርድ ቤቶች አካባቢ ያለው የህጉ አረዳድስ ምን ይመስላል? የቫሬሽኑ መጠን ከ25% በላይ በሆነ ጊዜና ከተቋራጩ ጥፋት ባልሆነ ሁኔታ የተከሰተ ከሆነ አማካሪ መሀንዲሱ ስለብልጫው መጠንና ስለዋጋው ከአሰሪው መስሪያ ቤት ጋር በመመካከር ይወስናል በሚል PPA 2011 ክሎስ 15.7 ላይ ተቀምጧል፡፡ የቫሬሽን መጠን ከመጀመሪያው ዋጋ ከ30% በላይ መብለጥ እንደሌለበት በአስገዳጅ ሁኔታ PPA 2011 ክሎስ 15.8 ላይ ተቀምጧል፡፡ በዚህ በጀኔራል ኮንዲሽን ከተቀመጠው ተርሰንት/ከገደቡ በላይ በቫሬሽን ስራ ተሰርቶ ቢገኝስ ምን ይሆናል? እንግዲህ በዚህ ረገድ ጀኔራል ኮንዲሽኑም ሆነ አግባብነት ያለው የግዥ አዋጅና መመሪያ ግልጽ ምላሽ አያስቀምጥም፡፡ ሆኖም ግን ተቋራጩ ስራውን እስከሰራው ድረስ አሰሪው አላግባብ በተቋራጩ ድካምና ገንዘብ በልጽጐ እንዲቀር ፈቃጅ ህግ ሊኖር አይችልም፡፡ፍትሀዊም አይሆንም፡፡ ስለዚህ በዚህ ረገድ በአማካሪ መሀንዲሱ እውቅና እና ትእዛዝ በቫሬሽን ለተሰሩ ስራዎች  ከገደቡ በላይ ያለፈ ቢሆንም እንኳ አሰሪው ለተቋራጩ ሊከፍለው እንደሚገባ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በ5ዳኞች እንደህግ በሚቆጠር ሁኔታ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ ይሄውም አስገዳጅ ውሳኔ በሰ/መ/ቁ 71972 ቅጽ 14 ገጽ 25 ላይ ይገኛል፡፡  ቫሬሽን ከሙስና ጋር ምን ያገናኘዋል? በዚህ ረገድ የኢፌዴሪ የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የኪራይ ሰብሳቢነት መንስኤዎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በሚል በመስከረም 2010ዓ.ም ባዘጋጀው የውይይት ሰነድ ላይ ቫሬሽን ለሙስና አንዱ ምንጭ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይሄውም ለምሳሌ ያህል የማይጣጣሙ ዲዛይኖችና የስራ ዝርዝር መኖር አንዱ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ ሆነ ብሎ የስራ ዝርዝር መዝለል/omission of work item/ ነው፡፡ በአይነቱ አዲስ የሆነ ተጨማሪ ስራ/unrelated and new item of additional work/ ሲያጋጥምስ በየትኛው ህግ የሚታይ ይሆናል? በመርህ ደረጃ አሰሪው መስሪያ ቤት በውል ውስጥ የሌሉትን ስራዎች በአዲስ ዋጋ እንዲሰራቸው ስራ ተቋራጩን ለማዘዝ እንደሚችል በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3284(1) ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡

1) አንድ G+22 የሆነ ህንፃ እንዴት ነው ምንም አይነት Column ሳንጠቀም መገንባት የምንችለው??? መልሱ:- Shear wall በመጠቀም 2) ከ36 ሚ.ሜ በላይ ለሆኑ ፌሮዎች ለምንድነው Lapping የማይፈቀደው?? መልሱ:- ፌሮዎቹ ሳይዛቸው ትልልቅ ስለሆነ Lap ብናደርጋቸው ሎድ ትራንስፈር እንዲኖር ላፕ ሌንግዙ ረጅም መሆን አለበት በተጨማሪም ሁለቱን አንድ ላይ ማሰሪያ ትልቅ ዲያሜትር ያለው ፌሮ/ ሽቦ ያስፈልገናል - አስቸጋሪ ነው:: 3) ሊፍቶች ውስጥ ለምንድነው መስታወት የሚገጠመው?? መልሱ:- በግድግዳ የተከበበ በጣም ጠባብ ቤት ውስጥ ዝም ብለን ብንቆም ምን ይሰማናል?? ሊፍቶች ከጥበታቸው በተጨማሪ እንቅስቃሴ ስለሚያደርጉ ሰዎች ይሰጋሉ ምን አልባት አደጋ ከተከሰተ ፤ መብራት ከጠፋ l ምናምን ብለው - እናም ሰዎች ፀጉራቸውን እያስተካከሉ ፤ l ውበታቸውን እያደነቁ ምናምን ፈታ እንዲሉና ሃሳባቸውን እንዲሰረቅ ነው ሊፍት ውስጥ መስታወት የሚገጠመዉ::

1) አንድ G+22 የሆነ ህንፃ እንዴት ነው ምንም አይነት Column ሳንጠቀም መገንባት የምንችለው??? መልሱ:- Shear wall በመጠቀም 2) ከ36 ሚ.ሜ በላይ ለሆኑ ፌሮዎች ለምንድነው Lapping የማይፈቀደው?? መልሱ:- ፌሮዎቹ ሳይዛቸው ትልልቅ ስለሆነ Lap ብናደርጋቸው ሎድ ትራንስፈር እንዲኖር ላፕ ሌንግዙ ረጅም መሆን አለበት በተጨማሪም ሁለቱን አንድ ላይ ማሰሪያ ትልቅ ዲያሜትር ያለው ፌሮ/ ሽቦ ያስፈልገናል - አስቸጋሪ ነው:: 3) ሊፍቶች ውስጥ ለምንድነው መስታወት የሚገጠመው?? መልሱ:- በግድግዳ የተከበበ በጣም ጠባብ ቤት ውስጥ ዝም ብለን ብንቆም ምን ይሰማናል?? ሊፍቶች ከጥበታቸው በተጨማሪ እንቅስቃሴ ስለሚያደርጉ ሰዎች ይሰጋሉ ምን አልባት አደጋ ከተከሰተ ፤ መብራት ከጠፋ l ምናምን ብለው - እናም ሰዎች ፀጉራቸውን እያስተካከሉ ፤ l ውበታቸውን እያደነቁ ምናምን ፈታ እንዲሉና ሃሳባቸውን እንዲሰረቅ ነው ሊፍት ውስጥ መስታወት የሚገጠመዉ::

ስለ መሰንጠቅ (cracking ) ብዙ የኮንስትራክሽን ባለሞያዎች መሰንጠቅ በMix design ትክክል አለመሆን ብቻ የሚመጣ ይመስላቸዋል ነገር ግን ለመሰንጠቅ (cracking ) ምክንያት የሚሆኑ መንስኤዎችን ከዚህ በታች እንዲህ ዳስሰናል፦   [1] - አነስተኛ ጥራት ያላቸውን ቁሶች የምንጠቀም ከሆነ አነስተኛ ጥራት ያላቸውን ቁሶች የምንጠቀም ከሆነ መሰንጠቅ (cracking ) ይፈጠራል ስለዚህ የምንጠቀማቸውን ለኮንክሪት ግብዓት የሚሆኑ ቁሶችን (ሲሚንቶ፣ አሸዋ፣ ኮረኮንች) ጥራት መፈተሽ አለብን ኮንክሪቱ የብረት መዋቅር (reinforcement ) ያለው ከሆነ የብረቱን ጥራት መገምገም አለብን። [2] - መኮማተር (Shrinkage ) ኮንክሪቱን በምንደባልቅበት እና ውሃ በምናጠጣበት ግዜ (Curing ) ተገቢውን ጥንቃቄ ካልወሰድን መኮማተር (shrinkage) መሰንጠቅን(cracking)   ያስከትላል ። መኮማተር (shrinkage) ለትልቅ የኮንክሪት ጥንካሬ በጣም አስፈላጊ ነው አስፈላጊውን የውሃ-ሲሚንቶ መመዛዘን (water cement ratio) ካልተጠቀምን በመኮማተር አማካኝነት መሰንጠቅ ሊፈጠር ይችላል ። [3] - ጥራት ያለው Aggregate የማንጠቀም ከሆነ Aggregate የኮንክሪትን አጠቃላይ ጥንካሬ ይወስንልናል ጥራቱ ጥሩ ያልሆነ Aggregate የምንጠቀም ከሆነ ከሲሚንቶ ጋር ተፈላጊውን ጥምረት (bond) ስለማይፈጥር ግንባታችን ሊሰነጠቅ ይችላል። [4] - መዋቅራችን ከአቅም በላይ የሆነ ክብደት ሲያስተናግድ ግንባታው / መዋቅሩ ተገቢውን ጥንካሬ ሳያገኝ በፊት ለትልቅ ክብደት የሚጋለጥ ከሆነ መሰንጠቅ ይከሰታል። በተጨማሪም መቀሰቻዎችን እና ቅስቱን (formwork ) ያለጊዜው የሚነሳ ከሆነም ግንባታችንን ለስንጣቆ ያጋልጠዋል። [5] - በትክክል ውሃ እንዲጠጣ የማይደረግ ከሆነ (improper curing ) ይህ በአገራችን ከሚስተዋሉ ለመሰንጠቅ ከሚዳርጉ ምክንያቶች ቀዳሚው ነው - ውሃ በትክክል አለማጠጣት። ኮንክሪት እንደተገነባ በተገቢው ጊዜ እና መጠን ውሃ ሊጠጣት አለበት። [6] - የውጥረት ስርጭት (stress distribution ) አለመመጣጠን በጣም ትልቅ የሆነ የብረት መዋቅርን Mix ratio ትንሽ በሆነ ኮንክሪት የሙሌት ስራ ስንሰራ በብረቱ እና በኮንክሪቱ መካከል ያለ የውጥረት ስርጭት (stress distribution ) non linear ይሆናል ይህ ደግሞ መሰንጠቅን ያስከትላል። [7] - በሳይት ላይ የሙሌት (casting ) ስራ ሲሰራ ተገቢ ጥንቃቄ ካልተደረገ እና ለስራው ተገቢ የሆነ ባለሞያ (የቀን ሰራተኛን ጨምሮ) ካልተመደበ መሰንጠቅ (cracking) በሚሰራው ኮንክሪት ላይ መፈጠሩ አይቀርም።