376
Subscribers
-124 hours
+77 days
+3330 days
Posts Archive
እንደምን አመሻችሁ
ከ2016 የትምህርት ዘመን ጀምሮ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ወደ ሙሉ ትግበራ እንደሚገባ ቀድሞ መገለፁ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሠረት የተዘጋጁ የተማሪ መማሪያ መፅሃፍት እና የመምህሩ መምሪያ መፅሃፍት ከቴሌገራም ቻናሉ በማውረድ ለመምህራን እና ለተማሪዎች በማድረስ የመማር ማስተማር ሥራውን እንድታከናውኑበት እናሳውቃለን፡፡
ጤና ይስጥልኝ!
ይህን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የተዘጋጀውን በየክፍል ደረጃው የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች የክፍለ ጊዜ ድልድል በመመልከት ከ2016 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ወደ ትግበራ እንድትገቡበት አሳውቃለሁ፡፡
//መልካም ምሽት//
ጤና ይስጥልኝ!
በዚህ የተማሪዎች ምደባ መሠረት ተማሪዎቻችሁ ወደ ተመደቡበት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሄደው እንዲመዘገቡ እንድታደርጉ አሳውቃለሁ፡፡
//መልካም ምሽት//
ጤና ይስጥልኝ!
ለአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትውውቅ ሥልጠና ለመስጠት እንዲያመች ከላይ የተቀመጠውን ደብዳቤ እና ቅፅ በመመልከት ማድረግ ያለባችሁን እንድታደርጉ አሳውቃለሁ።
//አመሠግናለሁ//
ጤና ይስጥልኝ!
የ2016 የትምህርት ዘመን የትምህርት ካሌንደር እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል። በመሆኑም ሁሉንም የትምህርት ሥራ በትምህርት ካሌንደሩ መሠረት እንድትፈፅሙ አሳሳባለሁ።
ማስታወሻ፦ ለሁሉም የት/ት አመራር
1ኛ. የ2015 አረንጓዴ አሻራ ማኖር መርሃግብርን በተመለከተ ከዚህ ቀደም በተላለፈው አቅጣጫ መሠረት ላከናወናችሁ ት/ቤቶች ምስጋና እያቀረብን የተተከሉ ችግኞች ዓይነትና ብዛት በዚሁ የቴለግራም ቻናል እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።
2ኛ. የ2015 አረንጓዴ አሻራ ማኖር መርሃግብርን በተመለከተ ከዚህ ቀደም በተላለፈው አቅጣጫ መሠረት ያላከናወናችሁ ት/ቤቶች በት/ቤት በሚከበረው የወላጆች ቀን (ካርድ በሚሰጥበት ቀን) ተማሪዎችን፣መምህራንን፣መላጆችን፣የት/ቤቱ አመራርና አስተዳደር ሰሪተኞችን በማሳተፍ አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሃግብር እንድታካሂዱ እያሳሰብን የተተከሉ ችግኞች ዓይነትና ብዛት በዚሁ የቴለግራም ቻናል እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።
እናመሰግናለን!!
