9 999
Subscribers
No data24 hours
-457 days
-20030 days
Posts Archive
9 999
" ሩጫው"
ሩጫው አይደል ወይ ሰላምን ፍለጋ
እርካታን ፍለጋ
ሁሉም በየፊናው ሚለው ደፋቀና
ሚለው ጎንበስ ቀና
ገንዘብ ቁስን እንጂ እረፍት መች ይገዛል
በየደረሰበት ሰው ሃሳብ ይገዛል
ጭንቀት ይሸምታል
እረፍት መገኛው ኢየሱስ
ሰላም ማደሪያው ኢየሱስ
ደስታ ሀገሩ ኢየሱስ
እረፍት መኖሪያው ኢየሱስ
ሀብት ጥሪት ይዞ የተትረፈረፈ
ከእድሜ ልክ ያለፈ
ሰላም ከሌለበት ሰላምን ፍለጋ ስንቱ ነው የዋለ
የተንከራተተ
ዛሬን እረፍት አጥቶ ለነገ ያልማል
ነገም ነገን ሲቀርጽ ሳያልቅ ዘመን ያልቃል
እረፍት መገኛው ኢየሱስ
ሰላም ማደሪያው ኢየሱስ
ደስታ ሀገሩ ኢየሱስ
እርካታው መኖሪያው ኢየሱስ
ኢየሱስ ኢየሱስ
ኢየሱስ ኢየሱስ
ኢየሱስ ኢየሱስ
በላው ጠጣው ትርፌ ምንድነው?
አጌጥኩ ለበስኩ ትርፌ ምንድነው?
ተማርኩ አወኩ ትርፌ ምንድነው?
ምድር ሞላልኝ ትርፌ ምንድነው?
ኸረ እኔ በእንጀራ ብቻ ኸረ አልኖርም
ኸረ እኔ በምድሩ ብቻ ኸረ አልኖርም
ክፍተቴ ሌላ ነው ጉድለቴ
የማልሞላው በማንነቴ
እሮጬ እሮጬ ትርፌ የኔ ድካም ነው
የነፍስ እርካታዬ ጌታ ባንተኮ ነው
እንኳን ያንተ ሆንኩኝ አወኩህ እንኳን
እንዳልችል ሆኛለሁ ለሌላ እንዳልሆን
የማምነው እውነት በፍቅር ይዞኛል
ሌላ ሌላ እንዳላይ ውስጤን ሞልተኸዋል
አሰብኩት እራሴን ካንተ ውጪ
አሰብኩት ወጥቼም ከቤትህ
ባዶ ነኝ ቅብዝብዝ የሌለኝ እረፍት
እኔ አልችልም ሰው አልሆንም በሌለህበት
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"ካህን"
ካህን በገዛ ደምህ አዳንከኝ
ካህን በገዛ ቁስልህ አተረፍከኝ
ከፍለክ አቆደስከኝ ህወትህን
ቆርሰ አካፈልከኝ ነብስህን
ከዚህ የጨመረ ምን ፍቅር ይኖራል
ከዚህ ደርዝ ያለፈ ምን መውደድ ይገኛል
መስዋት ከመሆን ከመሞት የባሰ
ለነግስ ነፍስ ከማጣት ከማለፍ ያለፈ
ብልህ የመውደድ ጥልቅ የፍቅር ዳርቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ፍቅር ብቻ በክርስቶስ ብቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ፍቅር ብቻ
ጨለማዩ በርቶ በአንተ ፍቅር ብቻ/2/
በቃል ብቻ በአንደበትህ መቼ ወደድከኝ
በግብር እንጂ በእውነት ትርጉም ያፈቀርከኝ
ፍቅርን አሳየኸኝ ራስህን ለቀህ
ሆነህ ከነብስ ውጭ በፈቃድ ተገለህ
ቅን ደጉ ታመነ የዋህ ስቃይህ ገባው
ፍቅር ተገደልህ ህይወቴ እንዲገባ
ብልህ የመውደድ ጥግ የፍቅር ዳርቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ፍቅር ብቻ በክርስቶስ ብቻ
ህይወቴ ተርፎልኝ በአንተ ፍቅር ብቻ
ጨለማዩ በርቶ በአንተ ፍቅር ብቻ
ብልህ የመውደድ ጥግ የፍቅር ዳርቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ፍቅር ብቻ/2/
ልታድነኝ ልታተርፈኝ ወደህ የሄድክበት
የሞትህ ነው ያልተገባ በደም ያለፍክበት
ከሞት የስቃይ በእንጨት ተንጠልጥለህ
ፃዲቅ ያለሐጢያትህ ከአባይ መሐል ሆነህ
ቅን ደጉ ታመነ የዋህ ስቃይህ ገባው
ፍቅር ተገደልህ ህይወቴ እንዲገባ
ብልህ የመውደድ ጥግ የፍቅር ዳርቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ስቃይ ብቻ በህመምክ ብቻ
ብልህ የመውደድ ጥግ የፍቅር ዳርቻ
ህይወቴ ተገኝቶ በአንተ ፍቅር ብቻ
ምልክ አገልፅህም ዘመኔም ያንስሀል
ለፈሰሰው ደምህ ምኔስ ይክስሀል
እንዲያው ዝም ብዩ ቤዛዩ እልሀለው
በቀረልኝ እድሜዩ ሳመልክህ እኖራለው አዜምልሀለው
ቤዛዩ እልሀለሁ/2/
ብዙ በአንተ ያገኘሁ
አዳኜ እልሀለሁ/2/
ግምት በአንተ ያገኘሁ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
ሁሉን በስርህ
ፊደል ተግጣጥሞ የቱ ቃል ገለጠህ
ቃላት ተሰካክተው ምን ቢባል ተረከህ
ያንተን ልክ አዋቂ አንተ እግዚዓብሔር ብቻ
እራስህ ንገረኝ ምን እንድልህ ብቻ
የተባልከው ሁሉ ካንተ በታች ሆኗል
ለፍጥረት ሚበዛው ላንተ አቅም አንሶታል
ያንተን ልክ አዋቂ አንተ እግዚዓብሔር ብቻ
እራስህ ንገረኝ ምን እንድልህ ብቻ
መጀመርያም መጨረሻም የሌለህ
አልፋ ኦሜጋ ፊተኛም ሗለኛም የሌለህ
እግዚዓብሔር አንተ ነህ ፪
የኔ ትልቅ አንተ ነህ
የኔ ጀግና አንተ ነህ
ሁሉን በስርህ አስተዳዳሪ
በላይ ለሁሉ ሁሉን ፈጣሪ
የግዙፍ ግዙፍ የትልቅ ትልቅ
ቃል በማይደፍረው የከፍታ ጥግ
አንተ እግዚዓብሔር አንተ ብቻ ነህ
ትልቅ መሳዩን ትንሽ ያደረግህ
ጀግና መሳዩን ያንበረከክህ
ጠቢብ መሳዩን ሞኝ ያደረግህ
ያለው መሳዩን ባዶ ያደረግህ
የለም ያሉህ የሉም
ዛሬም የሚሉህ ነገ አይኖሩም ፪x
ይገርመኛል ትጋታቸው የከንቱነት ጥበባቸው
ካንተ ውጪ ህይወት ማሰባቸው
አንተው ባበጀኸው አእምሮ
ባንተ ጥበብ ተቀምሮ
እስትንፋስ ለግሰህ በእፍታህ
ባምሳልህ ሰርተኸው ስታበቃ
የለህም የሚልህ ማን ነው
እኮ የለህም የሚልህ ማን ነው
ለመኖርህ የሱም መኖር ምስክር ነው ፫
ለመኖርህ የኔም መኖር ምስክር ነው
ሉዓላዊነት ከጥንት ከዓለማት በፊት የነበረ
አለህ የለህም ቢባል ከመኖር ያልተገደበ
እግዚዓብሔር አለህ በማደርያህ
እግዚዓብሔር አለህ በዙፋንህ
አለህ በማደርያህ
አለህ በዙፋንህ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
" በሩን ክፈቱ "
ከስም ሁሉ በላይ ኃያል ስም አለው
በዚህ ስም አምነን ድነናል ይኸው
ምስክሮቹ ነን ሕይወት ደርሶናል
ሰማይ ሲጎበኘን ለዓለም በርተናል
ተጠቅልለናል በክርስቶስ በኃያሉ ስም
ከነበርንበት ዓለም የለንም
የሚበልጥ አይተን የሚደንቅ ክብር
ሰውን ኑ እንላለን አልፈን ከምድር
አምላክ ስጋ ሆነ ለኛ ማለደ
ከአብ አስታረቀን ስርየት ወረደ
ሕያው ልጆቹ ነን ዳግም ወልዶናል
ዘላለም ሲያገኘን ከሞት ጠፍተናል
ተጠቅልለናል በክርስቶስ በኃያሉ ስም
ከነበርንበት ዓለም የለንም
የሚበልጥ አይተን የሚደንቅ ፍቅር
ሰው እንጋብዛለን ወደዚህ ክብር
እናንት መኳንንቶች
በሩን ክፈቱ
የክብር ንጉሥ ይግባ
በሩን ክፈቱ
ይሄ ንጉሥ ማነው?
እሱ እግዚአብሔር ነው
የክብር ሁሉ ጌታ?
እሱ እግዚአብሔር ነው
የክብር ሁሉ ጌታ
የክብር ሁሉ ገዢ
እግዚአብሔር ነው
እግዚአብሔር ነው ብርቱና ኃያል
የሰማይ የምድሩ የልዑላን ጌታ
እግዚአብሔር ነው
እግዚአብሔር ነው ብርቱና ኃያል
ሆሆ ኃያሉ እግዚአብሔር
እሱ እኛን ጎበኘ
እንድንዘምርለት ዙሪያው ሰበሰበን
ሆሆ እግዚአብሔር ረዳን
እግዚአብሔር አሰበን
በየደረስንበት ኃያል መዝሙር ሆነን
ምስጋና የተገባው እሱ ነው
ውዳሴ የተገባው እሱ ነው
ለኛ ታየን መድኃኔዓለም
እንደሱ የለም ዘለዓለም
ለኛ ተገለጠ መድኃኔዓለም
እንደሱ የለም ዘለዓለም
ዝማሬ የተገባው እሱ ነው
ስግደትም የተገባው እሱ ነው
ለኛ ታየን መድኃኔዓለም
እንደሱ የለም ዘለዓለም
ለኛ ተገለጠ መድኃኔዓለም
እንደሱ የለም ዘለዓለም
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
#FamilyRequest
የዘማሪት ሀና ተክሌ "ሀብተ ሰማይ" የተሰኘውን ድንቅ የመዝሙር አልበም💽 ከነ ሙሉ ግጥም(lyrics) ነገ (ቅዳሜ) እናደርሳቹሃለን።
ይህን መልዕክት ለወዳጆም share በማድረግ በዝማሬው እንዲባረኩ ይጋብዙ🎁።
💐ተባረኩ💐
🪅መልካም ቀን🪅
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣👇 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
✴️ውድ የቻላናችን ቤተሰቦች በዚህ ድንቅ አልበም ውስጥ የሚገኙ መዝሙሮች እነዚ ናቸው። እንደምትባረኩባቸው እርግጠኛ ነኝ
የግጥም ስህተት ካለ በዚህ ንገሩን
እንዲሁም ሀሳብ አስተያየት ካላቹ
👇
@yonasss2
💛የወደዳቹትን መዝሙር ለምትወዷቸው ሰዎች #share አድርጉላቸው።
ተባረኩልኝ
እወዳቹሃለው💛
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣👇 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"ሊጎበኘኝ ይሆናል"
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
ዝም በሉ የኮቴው ድምጽ ይሰማል ይሰማል
ሊጎበኘኝ ነው መሰለኝ ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
ዝም በሉ የኮቴ ድምጽ ይሰማል
ሊጎበኘኝ ነው መሰለኝ እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
የእውነት መታማቴን ሰምቶ
በውሸትም መከሰሴን ሰምቶ
እምባዬን ሊያብስ መቶልኝ ይሆናል
እሱ እንደሆን ለተገፋ ያዝናል
ነፍሴ አንተን አንተን ትላለች
ክብርህንም ተጠምጣለች
ውድይዬ እባክህ ና
ተገለጠልኝ እንደገና
እንደገና(*3)
ዝም በሉ የኮቴ ድምጽ ይሰማል
ሊጎበኘኝ ነው መሰለኝ እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
የወጀቡ ውሃ በታንኳዬ ሞልቶ
ድረስልኝ ስለው መማፀኔን ሰምቶ
መቶልኝ ይሆናል እየሱስ የናዝሬቱ
የምጎበኝበት ደርሶልኝ ሰዓቱ
ነፍሴ አንተን አንተን ትላለች
ክብርህንም ተጠምጣለች
ውድይዬ እባክህና
ተገለጠልኝ እንደገና
እንደገና(*3)
ዝም በሉ የኮቴ ድምጽ ይሰማል
ሊጎበኘኝ ነው መሰለኝ እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ ሁሉ
ከህዝቡ ይለየኛል አይበል ይላል ቃሉ
ዛሬም ታመንኩ እኔም በአንተ ጌታ
ድሉ ያንተ የማታ የማታ
ነፍሴ አንተን አንተን ትላለች
ክብርህንም ተጠምጣለች
ውድይዬ እባክህና
ተገለጠልኝ እንደገና
እንደገና(*3)
ዝም በሉ የኮቴ ድምጽ ይሰማል
ሊጎበኘኝ ነው መሰለኝ እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
ውድዬ ይሆናል
እየሱስ ይሆናል
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ
ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"እናምነዋለን"
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
እናምንሃለን እናምንሃለን
ካንተ ዘንድ ከጌታ የተስፋ ቃል አለን
ካንተ ዘንድ ከእየሱስ የተስፋ ቃል አለን
ደረቁ ምድር ውሃ ያፈልቃል
ያዘነው ህዝብህ ሳቅን ይስቃል
ልቡ ተሰብሮ ለቆሳሰለ
ገና ወደ ፊት ታምራት አለ
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
እናምነዋለን እናምነዋለን
ከኢየሱስ ከጌታ የተስፋ ቃል አለን
ከኢየሱስ ከራሱ የተስፋ ቃል አለን
ከወገን ርቆ በግዞት ያለ
አጉል ህልመኛ ነው የተባለ
የእግዚአብሔር ጊዜ ለእርሱ ቢመጣለት
ወደ ወንበሩ ያስቸኩሉታል
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
እናምንሃለን እናምንሃለን
ካንተ ዘንድ ከጌታ የተስፋ ቃል አለን
ካንተ ዘንድ ከእየሱስ የተስፋ ቃል አለን
ለእግዚአብሔር ህዝብ ጠፍቶ ምላሹ
ብዙ ያስለቀሰ ልቆ ትንሹ
ከላይ ከሰማይ በእርሱ ይመጣል
አዋጅ በአዋጅ ይገለበጣል
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
እናምንሃለን እናምንሃለን
ካንተ ዘንድ ከጌታ የተስፋ ቃል አለን
ካንተ ዘንድ ከእየሱስ የተስፋ ቃል አለን
ዝናብ ቢጠፋ ነፋስ ባይታይ
ደመናም ባይኖር ባይጠቁር ሰማይ
ይህ በእግዚአብሔር አይን ቀላል ነውና
ዝናብ ያዘንባል ያለደመና
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ
ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"አዲስ ኪዳን"
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
ከሰለሞን መቅደስ የከበረ
አለም ሳትፈጠር የነበረ
አዲስ ቤተመቅደስ ተሰራ
ቀራንዮ ተራራ
አዲስ ኪዳናችን አበራ
ቀራንዮ ተራራ
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
ሰውን በጸጋ ለማዳን
ከላይ ከእግዚአብሔር ተሰጠን
ህግ በሲና ተሰጠ
ተራራው ጨሰ ተናወጠ
ፀጋ ግን ወረደ ጎልጎታ
ዲያቢሎስ ተመታ
ፀጋ ግን ወረደ ጎልጎታ
የሰው ልጅ ተፈታ
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
ሰውን ከኃጥያት ለማዳን
ከላይ ከአርያም ተሰጠን
ሙሴ ህግን አስተማረ
እስራኤልን በዚያ አኖረ
ፀጋ እና እውነት ግን በኢየሱስ
በሰላም ንጉስ
ፀጋ እና እውነት ግን በጌታ
በማይረታ
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
ሰውን ከሲዖል ለማዳን
ከላይ ከአባታችን ተሰጠን
ሰው ሲኖር በኃጢአት ጨለማ
የሞትን ድምጽ እየሰማ
እግዚአብሔር ግን አዝኖልን
እየሱስ ሞተልን
እግዚአብሔር ግን አዝኖልን
እዳ ከፈለልን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
ሰውን በጸጋ ለማዳን
ከላይ ከእግዚአብሔር ተሰጠን
አሮጌው ኪዳን አብቅቶ
በአዲስ ኪዳን ተተክቶ
ዛሬ በፀጋ እንኖራለን
እግዚአብሔር ይመስገን
በኢየሱስ ያመነ ይድናል
ጸጋው ለሁሉ ይበቃል
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን አዲስ ኪዳን
ሰውን በጸጋ ለማዳን
ከላይ ከእግዚአብሔር ተሰጠን
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ
ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"የሰላም ንጉስ"
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
ምድረ በዳ ላቅበዘበዘው
የህይወት ትግል ምጥ ለያዘው
ትደርሳለህ ታሳርፋለህ
አንተ እኮ ጌታ የልብ ነህ
አንተ እኮ እየሱስ የልብ ነህ
እየሱስ እየሱስ የሰላም ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የሰላም ንጉስ
ተስፋው እንደጉም ለበነነ
ገመድ ለአንገቱ ለወሰነ
ከተፍ ብለህ ጣልቃ ገብተሀል
ሞትን በህይወት ለውጠሃል
መርዶን በደስታ ለውጠሃል
እየሱስ እየሱስ አፅናኙ ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የሰላም ንጉስ
የደዌን አልጋ ለተላመደ
ከበሽታ ጋር ለተዛመደ
አንተ ሀኪም ነህ መድኃኒት አለህ
ያለ ጠባሳ ትፈውሳለህ
ያለ ቀጠሮ ትፈውሳለህ
የደዌን አልጋ ለተላመደ
ከበሽታ ጋር ለተዛመደ
እየሱስ ሀኪም ነህ መድኃኒት አለህ
ያለ ቀጠሮ ትፈውሳለህ
ያለ ጠባሳ ትፈውሳለህ
እየሱስ እየሱስ የፈውስ ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የጤና ንጉስ
እኔም እንደ ሰው ቀን ወቶልኛል
ከሲኦል ጫፍ አድነኸኛል
ማዳንህን እናገራለሁ
በጉባዔም ዘምራለሁ
በወገኖች መሃል አዜማለው
እየሱስ እየሱስ የቤቴ ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የቅኔ ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የዜማ ንጉስ
ደረቁ ዛፍ አቆጠቆጠ
ታሪካችንም ተለወጠ
ተዘልለን ተቀምጠናል
ምንም አንሆን አንተን ይዘናል
ምንም አንሆንም ያንተ ሆነናል
ምንም አንሆንም ጌታን ይዘናል
እየሱስ እየሱስ የመንጋ ንጉስ
እየሱስ እየሱስ ዘላለም ንጉስ
እየሱስ እየሱስ የፅድቅ ንጉስ
ዘላለም ንጉስ
የህዝቡ ንጉስ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ
ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"አልረሳም"
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
አልረሳም አልረሳም አልረሳም
የትላንቱን የቀድሞውን የጠዋቱን
ጌታ የባረከኝን ከትቢያ ያነሳኝን
እንዴት እረሳለሁ አስታውሰዋለሁ
እንዴት እረሳለሁ ጌታን አከብራለሁ
ዙሪያው ገደል ሆኖ መውጫ አጥቼ
ከምስጋና ህይወት ተለይቼ
ግን እግዚአብሔርም መጣ......
እንደገና አቆመኝ በአዲስ ጉልበት
አልረሳም አልረሳም አልረሳም
የትላንቱን የቀድሞውን የጠዋቱን
ጌታ የባረከኝን ከትቢያ ያነሳኝን
እንዴት እረሳለሁ አስታውሰዋለሁ
እንዴት እረሳለሁ ጌታን አከብራለሁ
ነፍሴ እጅግ ተርባ ተጠምታብኝ
ቀኑ እንደ እልፍ ቀን ሲሆንብኝ
የሰማይን መስኮት ከፈተና
ጓዳዬን ሞላልኝ በምስጋና
አልረሳም አልረሳም አልረሳም
የትላንቱን የቀድሞውን የጠዋቱን
ጌታ የባረከኝን ከትቢያ ያነሳኝን
እንዴት እረሳለሁ አስታውሰዋለሁ
እንዴት እረሳለሁ ጌታን አከብራለሁ
የመከራው ሌሊት ምነው በዛ
እግዚአብሔር ዝም አለኝ እንደዋዛ
ብዬ ነበር ጌታ አይጥልም
ሰምቶ ይመልሳል ዝም አይልም
አልረሳም አልረሳም አልረሳም
የትላንቱን የቀድሞውን የጠዋቱን
ጌታ የባረከኝን ከትቢያ ያነሳኝን
እንዴት እረሳለሁ አስታውሰዋለሁ
እንዴት እረሳለሁ ጌታን አከብራለሁ
እሰይ ሜዳ ሆነ ያ ተራራ
ሌሊቱ አልፎ ጨለማዬ በራ
የረዳኝ ጌታ እባርከዋለሁ
በጉባኤ መሃል አዜምለታለሁ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ
ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼
@mezemur_lyrics
@mezemur_lyrics
❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
''ምስጋና ይኽው''
ፓ/ር አገኘው ይደግ
እስቲ ልነሳና ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
እስቲ ብዜማዬ ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
ባለውለታዬን ጌታዬን ×(4)
ሞልቶ የተረፈ ብዙ አለኝ ምስጋና
ካስጨናቂዎቼ አድኖኛልና ሀሌሉያ
ማለዳ ነቅቼ በገናዬን ላንሳ
ባይስተካከልም ለውለታው ካሳ ካሳ
ምስጋና ይኽው
አምልኮ ይኽው
አንተ ላደረከው
መዝሙርም ይኽው
ሽብሸባ ይኽው
ዙፋንህን ይክበበው ×(2)
ማድሪያህን ይሙላው
እስቲ ልነሳና ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
እስቲ ብዜማዬ ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
ባለውለታዬን ጌታዬን ×(4)
አልችልው ያልኩትን ቅጥር ያዘለለኝ
እኔ ካንተ ጋር ነኝ አይዞ አትፍራ አለኝ አለኝ
ምስጋናን ልሰዋ ክንዱን ተደግፌ
እሾሁን ጭቃውን ጨለማውን አልፌ አልፌ
ምስጋና ይኽው
አምልኮ ይኽው
አንተ ላደረከው
መዝሙርም ይኽው
ሽብሸባ ይኽው
ዙፋንህን ይክበበው ×(2)
ማድሪያህን ይሙላው
እስቲ ልነሳና ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
እስቲ ብዜማዬ ላመስግነው ጌታዬን
ጌታዬን ባለውለታዬን
ባለውለታዬን ጌታዬን ×(4)
ምህረት ቸርነቱ ፍቅሩ የበዛላችሁ
አቅፎ ተሸክሞ ዛሬን ያሳችሁ
ድምጻችሁን አንሱ እንዘምር ምስጋና
እንደርሱ የሚረዳ አልተገኘምና ሀሌሉያ
ምስጋና ይኽው
አምልኮ ይኽው
አንተ ላደረከው
ሽብሸባ ይኽው
ስግደትም ይኽው
ዙፋንህን ይክበበው ×(2)
ማድሪያህን ይሙላው
ምስጋና ይኽው
አምልኮ ይኽው
አንተ ላደረከው
ጭብጨባ ይኽው
እልልታ ይኽው
ዙፋንህን ይክበበው ×(2)
ማድሪያህን ይሙላው
ዙፋንህን ይክበበው ×(2) |
ማድሪያህን ይሙላው | ×(4)
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"አንተ ግን"
ፓ/ር አገኘው ይደግ
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ፍቅር እንደበረዶ ቀዝቀዞ ወንድም ወንድሙን ሲንቀው
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አዳራሿ ፈርሶ ትህትና ቤት መዝጊያዋን ሲያወልቀው
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ፍቅር ከወደ ላይ ወድቆ
ባህታን ጫማ ቢረገጥ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ግዛትህ አያበቃ
ወሰንህ አይለካ
ሁሉን አሳልፈህ
ዘላለም ትኖራለህ /*2
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ባለጸጋ ነኝ ብሎ ቤቱን ከሰማይ ጥግ ቢሰራ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ደረጃ መሰላሉ በዝቶ ቢወጣ ላይኛው ተራራ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
በገመድ ተጎትቶ ሲወርድ አዳራሹ ስትፈርስ መመኪያው
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አንተ ግን ከብረህ ትኖራለህ የሰው ልጅ ሚዛኑ መለኪያው
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ግዛትህ አያበቃ
ወሰንህ አይለካ
ሁሉን አሳልፈህ
ዘላለም ትኖራለህ /*2
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
የአለም አንደኛ ተነስቶ በክብር ስፍራ ላይ ቢቀመጥ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ቃሉም የንጉስ ቃል ሆኖ በሸንጎ ስብሰባ ቢደመጥ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ሰው ከነበረበት ጨለማ በወንጌል ብርሃን ሲነጠቅ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
በደለኛ መሆኑ ቀርቶ ተፀፅቶ ካንተ ሲታረቅ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ግዛትህ አያበቃ
ወሰንህ አይለካ
ሁሉን አሳልፈህ
ዘላለም ትኖራለህ /*2
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ሁሉም ይሄዳል ይመጣል ነገስታቱ ቢፈጃጁ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
የማለዳዎቹ ተረስተ አፍላዎቹ ይወደሳሉ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
አሀዱ የለህ ማክተሚያ ዓመታትህም አያልቁም
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ዘላለም ጸንተህ ትኖራለህ ነገስታት ቢያውቁህ ባያውቁህ
አንተ ግን ያው አንተ ነህ
ግዛትህ አያበቃ
ወሰንህ አይለካ
ሁሉን አሳልፈህ
ዘላለም ትኖራለህ /*2
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ (አትለወጥም)
አንተ ግን አንተ ግን ያው አንተ ነህ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
