en
Feedback
Leulseged Pulpit

Leulseged Pulpit

Open in Telegram
9 999
Subscribers
No data24 hours
-457 days
-20030 days
Posts Archive
➠ርዕስ:ሽኩር ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

ተናገር ባነበብን ቁጥር ባወቅነው የማንለምደው ቃልህን በገባን ቁጥር ባወቅነው ምንፈልገው ቃልህን ነው ዛሬም እንድትልልን ሳይሆን ልትል ያሰብከው ያግኘን ያለመከልከል ተናግረህ ያለገደብ ሥራብን መንፈስህ ይግዛን ይስፈንብን በሙላት የልብህ አሳብ ያጥምደን የሚያቆመን ያ ነው በጽናት እናድጋለን እንጂ ሰርክ ወደ አንተ ልናድግ አይቻለንም በአንተ ላይ ከፍለን ባወቅንህ ቁጥር ዝግ እንበል እንይ ወደላይ ምን ብናውቅ ጥበብ ቢጠጋን ሲመስለን ያወቅን የበቃን አናውቅም ባወቅንህ ቁጥር ደቀመዝሙር ነን ሁሌ በአንተ ሥር ተማሪዎች ነን ሁሌ ልጆችህ መቼም በማንጨርሰው ትምህርትህ ከፍለን ባወቅነው ጥቂት ትሑት አድረገን ባንተ ፊት ታማኝ አድረገን ለቃልህ አብቃን ለውድ አሳብህ መስታወት በሆነው ቃልህ አንቃን በውድ መንገድህ ተናገር ኢየሱስ ተናገር በኃይል እንሰማሃለን ተናገር መንፈስ ቅዱስ ተናገር በሙላት እንሰማሀለን ተናገር እንሰማሀለን ተናገር እንሰማሀለን ባነበብን ቁጥር ባወቅነው የማንለምደው ቃልህን በገባን ቁጥር ባወቅነው ምንፈልገው ቃልህን ነው share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:ተናገር ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

"ፍለጋ" ሊያገለግልህ የጠራኸው በሕዝብህ ፊት የሾምከው ስንቱ ርቆህ ያገለግላል ለራሱ ክብር አድሮ ይውላል ስንቱ ርቆህ የራሱን ክብር ያገለግላል ለዝናው ስሙ ታግሎ ይኖራል፡፡ ያላንተ ጉዞ ስም ዝናን ብቻ ይዞ የሥጋ ጥረት በሌለህበት ያለአንተ ክብር በእኔነት ፍቅር በጸጋ ካባ ለራስ ወከባ ለከንቱ መንገድ ባንተ ሲነገድ ፍለጋ ክብርን ፍለጋ ዝናን ፍለጋ ብልጫን ፍለጋ ፍለጋ ንዋይን ፍለጋ ትኩረትን ፍለጋ ፍለጋ አምልኮተ ዝና አምልኮተ እኔ በአምልኮ መልክ ሽፋን በፍቅሬ ተይዤ በንጉሥ ዙፋን ላይ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ በውድድር መንፈስ ምስባክ ለታይታ በትወና ህይወት የእኔ ለእኔ ዋይታ ፍለጋ ክብርን ፍለጋ ዝናን ፍለጋ ብልጫን ፍለጋ ፍለጋ ንዋይን ፍለጋ ትኩረትን ፍለጋ ፍለጋ በሌለህበት ሳውልህ ለዝና ስሜ ስፈልግህ ተላላ የልቤን ባያገኘው ካንተ ማን ሊሰውረው ከባዶ ጩኸት ከሌለህበት ዝምታዬ ካገነነህ ባለህበት ክብሬ ያ ነው ያከበረህ እኔነቴን የሰበረ ፍለጋዬ ይሁን ለጉዳይህ ፍለጋዬ ይሁን ለሐሳብህ ፍለጋዬ ፍለጋዬ ይሁን ለክብርህ ስራዬን ትመዝናለህ ከመንበርህ ታየኛለህ ፍለጋዬን አጥራው መንገዴን ላረካ የቆምኩለትን የራስ ጥሜን መከሩ ብዙ ነው ሥራ አለ በቤቱ ወደሞት የሚነዳ አለ በየዕለቱ በራስ ፍቅር ታመን መሽቶብን ይነጋል ኢየሱስን ሳያይ ስንቱን ሞት ይቀድማል እድሜአችን ቢበዛ ሰባ ነው ቢያልፍ እንኳን ሰማንያ ምን አለን ክብር ምን አለን ንዋይ ኢየሱስ ከአንተ ወዲያ ምን አለን ዝና ምን አለን ክብር ኢየሱስ ከአንተ ወዲያ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ: ፍለጋ ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

በታሪክህ ክቡር የሰው ልጅ ክቡር በሰማይ በምድር የአንድ ዘር ቅጂ የአንድ ነፍስ ስፍር አሻራ መልኩ ቢለይ ቀለሙ ወርቁ ሲፈተሽ አንድ ነው ደሙ ከጎሳ ከዘር ከባህል ትውፊት ከሀገርም በላይ ከብሄር በፊት አብ የፈጠረው በሁሉ አንግሶ ወልድ የሞተለት ደሙን አፍስሶ ሰው ነው ክቡር ሰው የተከበረ በአምላክ እግዚአብሔር የተመተረ ምኑን ቢለያይ ድንበር አብዝቶ አንድ አድርጎታል ክርስቶስ ሞቶ ክቡር ክቡር ክቡር ክቡር ክቡር ክቡር ክቡር ክቡር ፍጡር ክቡር ክቡር ክቡር በታሪክ ማይገናኘውን የታሪክ ልዩነት ያለውን የዘር የዳር ድንበር ያበጀውን በምንም በምንም ጭራሽ ማይገጥመውን ኢየሱስ በታሪክህ አንድ አደረግከው በታሪክ አገናኘኸው በመስቀልህ አንድ አደረግከው በመስቀልህ አገናኘኸው ጨዋ የለም ባሪያ የለም ጉራማይሌውን አንድ አደረግህ ማይገናኘውን አገናኘህ ህዝብ ልጅ አንተ አባት ተባልህ ህዝብ ልጅ አንተ አብ አባት ተባልህ ጉራማይሌውን አንድ አደረግህ ማይገናኘውን አገናኘህ ህዝብ ልጅ አንተ አባት ተባልህ ህዝብ ልጅ አንተ አብ አባት ተባልህ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ: በታሪክህ ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

የታደልን በአንተ የተጠራ ወገን በአንተ የተወደደ ከጥፋት ባህር ንዳድ በስምህ የተጋረደ ክብሩ ኢየሱስ የሆንክለት መጠሪያ የዘውድ ስሙ በኪዳንህ የሚራመድ በደምህ የገባህ ከደሙ በክብርህ እሳት የሚነድ በህልውናህ ዓለም በእረፍት ጠል የረሰረሰ ከህዝብህ በቀር የለም የለም ከእኛ በቀር የለም የለም ከህዝብህ በቀር የለም የታደልን ህዝብ በአንተ ታየን ተመረጥን ተወደድን መስዋዕት በሆንክ በተነሳህ ከሞት ከሞት አመለጥን ክብራችን ነህ ሞገሳችን ብንዘምርልህ ብንዘምር የማይደክመን ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ የታመንብህ ጽኑ መጠለያ ክብራችን ነህ ሞገሳችን ብንዘምርልህ ብንተርክህ የማይደክመን ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ የታመንብህ ጽኑ መጠለያ እናመልክሃለን (×፭) በማይጠፋ ሕይወት በማይሞት ገርስሰህ የዘላለምን ሞት በብርሃንህ ብርሃን አሳየኸን አንተው ባለህበት አሰፈርከን ምን እንላለን? ምን አለን? ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር ክበር እንላለን ንገስ ንገስ ንገስ ንገስ እንላለን ተሞኝተን አይደለም ምናመልክህ ኢየሱስ ኢየሱስ የምንልህ በደንብ ገብቶናል አንድ ፍቅርህ ልንርቅ እኛ አንችልም ከእቅፍህ ተሞኝቼ አይደለም የማመልክህ ኢየሱስ ኢየሱስ ሁሌ ምልህ ኧረ እኔስ ገብቶኛል አንድ ፍቅርህ ልርቅ እኔ አልችልም ከእቅፍህ ምን አለን ከአንተ ውጪ እኛ ምን አለን ከአንተ ውጪ ምንጠራው አንተን ነው ምንጠራው ምናሳየው አንተን ነው ምናሳየው ምንጠራው አንተን ነው የምንጠራው ምናሳየው አንተን ነው ምናሳየው share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:የታደልን ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

ረግቻለው ለሰላሜ የሚሆነኝን አውቄያለሁ አግኝቻለሁ ለእፎይታዬ የሚበጀኝን አምኛለሁ ተቀብያለሁ የእግዚአብሔር ልጅ በርቶልኛል በመንፈሱ ረግቻለሁ ላልወሰድ በምድር ተረት ለዘልአለም ታክሜያለሁ ከአላማኞች በተሰወረ ከጠቢባን ዘንድ ባልነበረ የሞኝነት በሚመስል ታምር እኔ አርፌያለሁ በአንተ ማመን ሚስጥር ባንተ ደስ ብሎኛል ፀጋ በዝቶልኛል ረክቻያለሁ አመሰግናለሁ ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረግቻለሁ አመሰግናለሁ ባንተ ደስ ብሎኛል ጸጋህ በዝቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ የማይነጥፍ ነው ሰላሜ የማያልፍ ነው እረፍቴ ማደርያህ ለሆን ወደህ ዘልቀሀልና በህይወቴ የማይደበዝዝ ፍቅር ነው ሽንገላም ወረትም በሌለው ካንተ ያልተቀበልኩት ምን አለኝ ቀረ ምለው አንተ ሞልተኸኛል ህይወት በዝቶልኛል ረክቻለሁ ልጅህ ተብያለሁ ባንተ ደስ ይለኛል ሰላም ረግቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ በሰማያዊ በረከት በራስህ ተባርኪያለሁ እዚህ እንዳልናወጥ ከእቅፍህ ገብቻለሁ አልሸበርም በአለም በሚሰማው ክፉ ወሬ ባልከኝ ረግቻለሁ በያዝከኝ እስከዛሬ አንተን ይዞ ያልረካ ማነው አንተን ይዞ ያልሰከነ ማነው አንተን ይዞ የባከነ ማነው አንተን ይዞ የባዘነ ማነው ባንተ ደስ ብሎኛል ጸጋህ በዝቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:ረግቻለው ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

"እግዚአብሔር ይመስገን" ባርኮቴ ብዙ ነው የተደረገልኝ ስንቱ ነው በረከቴን እቆጥራለሁ የተደረገልኝ ብዙ ነው እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን እግዚአብሔር ይመስገን አምና ላይ ደረስኩኝ ካቻምናን ዘግቼ ዘንድሮን ደግሞ አየሁ አምናን ረስቼ ከማላየው ክፋት በክንዱ ሸሽጎኝ ከማላውቀው ጥፋት በድንቅ አስመልጦኝ እኔ አለሁኝ በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት እኔ አለሁኝ! ዛሬ ሰላም ነው ቤቴ ተጠብቆ በአባቴ እንደቀልድ ደህና ነሽ ወይ ሲሉኝ እግዚብሔር ይመስገን አልኩኝ እግዚብሔር ይመስገን እግዚብሔር ይመስገን መድኃኒዓለም ይክበር አባቴ ይመስገን የምልበት ብዙ አለኝ ብዙ አለኝ ብዙ አለኝ ብዙ አለኝ የሠራው ሰማዩን ያበጀው ምድሩን እግዚአብሔር አይደል ወይ የሚያይ?? አምላኬ አይደለም ወይ ባበጀው ምድር ላይ የሚያኖረው ሕዝቡን እኔን እግዚአብሔር አይደለም ወይ አምላኬ አይደለም ወይ መውጣት መግባቴ በእኔ አይደለም ሰላም ውሎ ማደሬም ቀልድ አይደለም ጤናዬን ሰላሜን እርሱ ይዞት እንጂ ጠላት መች ዘንግቶ የእኔን ደጅ ቀን ይመሻል ይነጋል እያየሁት ክረምት በጋውንም ይኸው ለመድኩት ትናንት ዛሬንም ያየሁት በእርሱ ነው ያልተነካሁት?? ምክኒያቱ በእግዚአብሔር ነው በደግነቱ እኔን ያኖረኛል በቸርነቱ እኔን ያቆመኛል በደግነቱ እኔን ያኖረኛል በቸርነቱ እኔን ያቆመኛል በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት ዓመታቶቹ የእርሱ ናቸው በቸርነቱ የሚያቀዳጀው በሆነውም ባልሆነውም ልቤን አላዝልም እግዚአብሔር ይመስገን ለነገማ አልተክዝም እግዚአብሔር ይመስገን share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:እግዚአብሔር ይመስገን ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

ግታው ሰበቤን ከነገር ጅማሬ ፍጻሜ ይልቃል ቀን ሳለ ጎበዝ ከየት እንደወደቀ ያስባል የጅማሬ ውበት የዳነበቱ ደብዝዞ ሳያልቅ በመንገድ ከንቱ በጸጋ ሽፋን ፋኖ ተማምኖ ስቆ ለውሃ ብዙ አለና የቀረ ባክኖ አልፈልገውም ለብታዬን እግሮቼን አድስ እኔ አልሻም መባከን በልማድ መደንዘዝ ግታው ሰበቤን ያደከመኝን ሰበብ በኩሬን የሚያስንቀኝን ግታው ምክኒያቴን የተጫነኝን ምክኒያት በኩሬን የሚያስጥለኝን፡፡ መሀል ሰፋሪ እዚህም እዚያም ሁሉ አይቅርብኝ አገም ጠቀም የለብታ ወንዝ ከባድ ፈተና ወይ ያልበረደው ወይ እሣት ያልገባው ገና አቋም በሌለው ከከልካይ ማዶ በነፃ ክልል ይነጉዳል ፈቅዶ፡፡ ግታው ሰበቤን ያለዘበኝን አክብጄ እንዳልይዝ ያጠመደኝን ግታው ምክኒያቴን የታገለኝን ለሁለት ጌቶች ያሰለፈኝን ነግቶለት ሕይወት ጉዞ ጀምሮ በአንተው ምሕረት በስም ተምሮ ከመንከራተት ተርፎ ያልተረፈ ዛሬም የሚባክን ልቡ ያላረፈ ገና! ዳግም ባርነት ዳግም እስራት ባልሰከነች ነፍስ ልጓም በሌላት፡፡ ይብቃኝ ምክኒያቴ የተጫነኝ አጥብቄ እንዳልይዝ ያታገለኝ ግታው ምክኒያቴን ያደከምኝን ትጥቄን ያላላ ያለዘበኝን በመንፈስ አንቃኝ አዚሜን ገፍፈህ የታገትኩበትን ገመዴን ፈትተህ ግታው ሰበቤን ያበረታኝን ለሁለት ጌቶች ያሰለፈኝን share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:ግታው ሰበቤን ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

እውነት እና እውነት በሰው ክፋት ማዕበል ምድር ስትናወጥ ፈጣሪ እንኳን በሰራው ፍጡር እስኪጸጸት የአንድ ኖህ ጎዳና አካሄድ ቢቀና የሰው ህይወት አልቀጠለም ወይ እንደገና በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ ማን አብሮ ይዘልቃል ከባይተዋር ጋራ እንደውሃና ዘይት አይደሉም ወይ እውነትና ሃሰት ምን አንዱ ቢበዛ መቼም አያብሩም ዘላለም በርቀት በጊዜም ፈተና ወደቅክ ሚለው የለም በእሳት ንዳድ አልፎ አመድ አያውቀውም በልዩነት መንገድ በሰላም ይተማል አጃቢ ሳያሻው ዘላለም ይኖራል የዝምታው ድምጸት ከመብረቅ ጽኑ ነው አለት ከሚያነቃ ከሚሰነጥቀው እርሱ ተረጋግቶ ሀገር ይረበሻል የለህም የሚለው እንቅልፍ አጥቶ ያድራል ከብዙ ግርግር አባይ ከዋለበት እውነት ከሚመስል አሳች ከበዛበት ዘንድሮም ጉዳዩ ከእውነት ጋር ብቻ እውነትና እውነት ከራሱ ጋር ብቻ በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ ማን አብሮ ይዘምታል ከባይተዋር ጋራ የታመነ ጓዳው ዮሴፍ ትንሹ ዛፍ ባልዋለበት ቢውል በእመቤቲቱ አፍ ከእመቤትስ በላይ ሹምስ ማንን ያምናል በሃጥእ ዘመን ዘንድ ጻድቅ ወህኒ ይወርዳል ምን ቢታፈን ሃቁ በሚያልፍ ባለጊዜ በማያልፍ ተክሷል ደርሶ የእውነት ጊዜ ባደባባይ ቢያፍር እውነትን አንግሶ ክብሩም ባደባባይ ይኸው ተመልሶ ሀብት ነው ጌጥ እውነት ምን ቢያጡም ለጊዜው ከርሞ ሚመነዘር ከፋይ ለከፈለው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ብርሃን ቃሉን ሲሰጥ ጨለማን ሲደክመው የእውነት ቤት ይደምቃል ለ እግዚአብሔር ያደረው ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ እውነት እግዚአብሔር ነው የማይለውጥ ጽኑ በሰልፍ ብዛት የማይደክመው ከበረታው በላይ ብርቱ ባህሪው ሰላም ነው አያምንም በሁከት ራሱን ለማሳመን አይገባም ከጭንቀት ህሊና ወዳጁ ጊዜ መፍቻ ቁልፉ ተረጋግቶ ይኖራል ተከድቶ በስንቱ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:እውነት እና እውነት ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

ብቻ ልቤን አንደበትህ ይታክታል የሆድን ሁሉ ቢናገር ለመጣው ለሄደው ሁሉ የሚያልፍበትን ቢዘረዝር የሰሚም- የሰሚም ጆሮ ይዝላል ለጊዜው ለሰሞንም ቢያዝን ብቻ ልቤን ደግፈው አልፈዋለው ብርቱውን ቀን ብቻ ልቤን ደግፈው አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን እጠራሃለሁ በስምህ ውስጥ ሰላም አለ እጠራሃለሁ በስምህ ውስጥ ብርታት አለ በስምህ ውስጥ እግዚአብሔር በስምህ ውስጥ እረፍት አለ በስምህ ውስጥ ጽናት አለ በስምህ ውስጥ ሰላም አለ በስምህ ውስጥ ከፀሓይ በታች መልስ ባጣሁለት ጉዳይ ቢያይልም ግርታዬ አይኔን ተክያልህ ሰማይ ከያዘኝ ከከበበኝ በላም አንተን አምንሃለሁ ብቻ ልቤን ደግፈው አልፈዋለው ብርቱውን ቀን ብቻ ልቤን ደግፈው አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን ልቤ ተጠብቆ በሚሆነው ነገር እታገስሃለሁ አለህ አንድ ነገር ብቻ ልቤን ጠብቀው አልፈዋለው ብርቱውን ቀን ብቻ ልቤን ደግፈው አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን በስምህ ውስጥ ሰላም አለ በስምህ ውስጥ እረፍት አለ በስምህ ውስጥ ጽናት አለ በስምህ ውስጥ ልብ ብቻውን ሲቀር በሃሳብ ሲወረር በሁነኛ ነፋስ በማዕበል ሲሰወር ደጋፊ ከሌለው ማን ከማን ያስጣል ልብ የወደቀ ቀን ለሞት እጅ ያሰጣል ልቤን የሚታደግ ብርቱ ግንብ አለቴ አጥር ሃይሌ ስምህ ነው የተስፋ ጽናቴ አንተ ነህ እግዚአብሔር ጽኑ መታመኛ አደራ የምለው አንተን ነው የልቤን መገኛ በስምህ ውስጥ ሰላም አለ በስምህ ውስጥ እረፍት አለ በስምህ ውስጥ ጽናት አለ በስምህ ውስጥ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖

➠ርዕስ:ብቻ ልቤን ➠ዘማሪ:ሀና ተክሌ ➠አልበም :ሀብተ ሰማይ ➠@mezmur_lyrics 🔻የዚን ዝማሬ ሙሉ ግጥም🔻

" እረኛ" ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖረ ልቡ ስለመንጋው ያደረ ለአንዲት ምስኪን ነፍስ ግድ እያለው ብዙ አሉኝ ብሎ አንዷን የማይተው ይሄዳል ያለእረፍት ሁሉ ጋ የጠፋችውን ያቺኑ ፍለጋ ሲያገኛት ሌላ እንደሌለው ደስታው መለኪያም የለው የባዘነውን የሚመልስ የጠፋውን የሚፈልግ የተሰበረውን የሚጠግን የሚያጸና የደከመውን ይህ ነው የእኔ እረኛ ይህ ነው የእኔ መዳኛ ይህ ነው የእኔ መጽናኛ ኢየሱስ መልካሙ እረኛ መታመኛዬ መጠገኛዬ መደገፊያዬ መታደጊያዬ ጠያቂ አለኝ ጠያቂ ፈላጊ አለኝ ፈላጊ ጠያቂ አለኝ ጠያቂ መሽቶም ሲነጋ ጠባቂ ይህ ነው የእኔ መጽናኛ ኢየሱስ መልካሙ እረኛ፡፡ ውዴ የሚታደገኝ ራሱን ሰጥቶ የሚያውቀኝ ከልብ በስም ለይቶ ለአፍታም ለቅጽበት አይለየኝ ለሚሰማሩብኝ አይተወኝ የእረኞች አለቃ እረኛዬ የገዛኝ በፍቅር መጋቢዬ ኢየሱስ የነፍሴ አባት ጠባቂዋ ከዱር ከገደሉ ማምለጫዋ የባዘነውን የሚመልስ የጠፋውን የሚፈልግ የተሰበረውን የሚጠግን የሚያጸና የደከመውን ይህ ነው የእኔ እረኛ ይህ ነው የእኔ መዳኛ ይህ ነው የእኔ መጽናኛ ኢየሱስ መልካሙ እረኛ መታመኛዬ መጠገኛዬ መደገፊያዬ መታደጊያዬ ጠያቂ አለኝ ጠያቂ ፈላጊ አለኝ ፈላጊ ጠያቂ አለኝ ጠያቂ መሽቶም ሲነጋ ጠባቂ ይህ ነው የእኔ መጽናኛ ኢየሱስ መልካሙ እረኛ share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ
   🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼      @mezemur_lyrics      @mezemur_lyrics     ❖ ───  ✦ ─── ❖