9 999
Subscribers
No data24 hours
-457 days
-20030 days
Posts Archive
9 999
ተናገር
ባነበብን ቁጥር ባወቅነው
የማንለምደው ቃልህን
በገባን ቁጥር ባወቅነው
ምንፈልገው ቃልህን ነው
ዛሬም እንድትልልን ሳይሆን
ልትል ያሰብከው ያግኘን
ያለመከልከል ተናግረህ
ያለገደብ ሥራብን
መንፈስህ ይግዛን
ይስፈንብን በሙላት
የልብህ አሳብ ያጥምደን
የሚያቆመን ያ ነው በጽናት
እናድጋለን እንጂ ሰርክ ወደ አንተ
ልናድግ አይቻለንም በአንተ ላይ
ከፍለን ባወቅንህ ቁጥር
ዝግ እንበል እንይ ወደላይ
ምን ብናውቅ ጥበብ ቢጠጋን
ሲመስለን ያወቅን የበቃን
አናውቅም ባወቅንህ ቁጥር
ደቀመዝሙር ነን ሁሌ በአንተ ሥር
ተማሪዎች ነን ሁሌ ልጆችህ
መቼም በማንጨርሰው ትምህርትህ
ከፍለን ባወቅነው ጥቂት
ትሑት አድረገን ባንተ ፊት
ታማኝ አድረገን ለቃልህ
አብቃን ለውድ አሳብህ
መስታወት በሆነው ቃልህ
አንቃን በውድ መንገድህ
ተናገር ኢየሱስ
ተናገር በኃይል
እንሰማሃለን
ተናገር መንፈስ ቅዱስ
ተናገር በሙላት
እንሰማሀለን
ተናገር እንሰማሀለን
ተናገር እንሰማሀለን
ባነበብን ቁጥር ባወቅነው
የማንለምደው ቃልህን
በገባን ቁጥር ባወቅነው
ምንፈልገው ቃልህን ነው
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"ፍለጋ"
ሊያገለግልህ የጠራኸው
በሕዝብህ ፊት የሾምከው
ስንቱ ርቆህ ያገለግላል
ለራሱ ክብር አድሮ ይውላል
ስንቱ ርቆህ የራሱን ክብር ያገለግላል
ለዝናው ስሙ ታግሎ ይኖራል፡፡
ያላንተ ጉዞ
ስም ዝናን ብቻ ይዞ
የሥጋ ጥረት በሌለህበት
ያለአንተ ክብር
በእኔነት ፍቅር
በጸጋ ካባ ለራስ ወከባ
ለከንቱ መንገድ ባንተ ሲነገድ
ፍለጋ ክብርን
ፍለጋ ዝናን
ፍለጋ ብልጫን
ፍለጋ
ፍለጋ ንዋይን
ፍለጋ ትኩረትን
ፍለጋ ፍለጋ
አምልኮተ ዝና አምልኮተ እኔ
በአምልኮ መልክ ሽፋን በፍቅሬ ተይዤ
በንጉሥ ዙፋን ላይ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ
በውድድር መንፈስ ምስባክ ለታይታ
በትወና ህይወት የእኔ ለእኔ ዋይታ
ፍለጋ ክብርን
ፍለጋ ዝናን
ፍለጋ ብልጫን
ፍለጋ
ፍለጋ ንዋይን
ፍለጋ ትኩረትን
ፍለጋ ፍለጋ
በሌለህበት ሳውልህ
ለዝና ስሜ ስፈልግህ
ተላላ የልቤን ባያገኘው
ካንተ ማን ሊሰውረው
ከባዶ ጩኸት ከሌለህበት
ዝምታዬ ካገነነህ ባለህበት
ክብሬ ያ ነው ያከበረህ
እኔነቴን የሰበረ
ፍለጋዬ ይሁን ለጉዳይህ
ፍለጋዬ ይሁን ለሐሳብህ
ፍለጋዬ ፍለጋዬ ይሁን ለክብርህ
ስራዬን ትመዝናለህ
ከመንበርህ ታየኛለህ
ፍለጋዬን አጥራው መንገዴን
ላረካ የቆምኩለትን የራስ ጥሜን
መከሩ ብዙ ነው ሥራ አለ በቤቱ
ወደሞት የሚነዳ አለ በየዕለቱ
በራስ ፍቅር ታመን መሽቶብን ይነጋል
ኢየሱስን ሳያይ ስንቱን ሞት ይቀድማል
እድሜአችን ቢበዛ ሰባ ነው
ቢያልፍ እንኳን ሰማንያ
ምን አለን ክብር
ምን አለን ንዋይ
ኢየሱስ ከአንተ ወዲያ
ምን አለን ዝና
ምን አለን ክብር ኢየሱስ ከአንተ ወዲያ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
በታሪክህ
ክቡር የሰው ልጅ ክቡር በሰማይ በምድር
የአንድ ዘር ቅጂ የአንድ ነፍስ ስፍር
አሻራ መልኩ ቢለይ ቀለሙ
ወርቁ ሲፈተሽ አንድ ነው ደሙ
ከጎሳ ከዘር ከባህል ትውፊት
ከሀገርም በላይ ከብሄር በፊት
አብ የፈጠረው በሁሉ አንግሶ
ወልድ የሞተለት ደሙን አፍስሶ
ሰው ነው ክቡር ሰው የተከበረ
በአምላክ እግዚአብሔር የተመተረ
ምኑን ቢለያይ ድንበር አብዝቶ
አንድ አድርጎታል ክርስቶስ ሞቶ
ክቡር ክቡር ክቡር
ክቡር ክቡር ክቡር
ክቡር ክቡር ፍጡር
ክቡር ክቡር ክቡር
በታሪክ ማይገናኘውን
የታሪክ ልዩነት ያለውን
የዘር የዳር ድንበር ያበጀውን
በምንም በምንም ጭራሽ ማይገጥመውን
ኢየሱስ በታሪክህ አንድ አደረግከው
በታሪክ አገናኘኸው
በመስቀልህ አንድ አደረግከው
በመስቀልህ አገናኘኸው
ጨዋ የለም
ባሪያ የለም
ጉራማይሌውን አንድ አደረግህ
ማይገናኘውን አገናኘህ
ህዝብ ልጅ አንተ አባት ተባልህ
ህዝብ ልጅ አንተ አብ አባት ተባልህ
ጉራማይሌውን አንድ አደረግህ
ማይገናኘውን አገናኘህ
ህዝብ ልጅ አንተ አባት ተባልህ
ህዝብ ልጅ አንተ አብ አባት ተባልህ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
የታደልን
በአንተ የተጠራ ወገን
በአንተ የተወደደ
ከጥፋት ባህር ንዳድ በስምህ የተጋረደ
ክብሩ ኢየሱስ የሆንክለት መጠሪያ የዘውድ ስሙ
በኪዳንህ የሚራመድ በደምህ የገባህ ከደሙ
በክብርህ እሳት የሚነድ በህልውናህ ዓለም
በእረፍት ጠል የረሰረሰ ከህዝብህ በቀር የለም
የለም ከእኛ በቀር የለም
የለም ከህዝብህ በቀር የለም
የታደልን ህዝብ በአንተ ታየን
ተመረጥን ተወደድን
መስዋዕት በሆንክ በተነሳህ ከሞት ከሞት አመለጥን
ክብራችን ነህ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ብንዘምር የማይደክመን
ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ
የታመንብህ ጽኑ መጠለያ
ክብራችን ነህ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ብንተርክህ የማይደክመን
ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ
የታመንብህ ጽኑ መጠለያ
እናመልክሃለን (×፭)
በማይጠፋ ሕይወት በማይሞት
ገርስሰህ የዘላለምን ሞት
በብርሃንህ ብርሃን አሳየኸን
አንተው ባለህበት አሰፈርከን
ምን እንላለን? ምን አለን?
ክበር ክበር ክበር
ክበር ክበር ክበር
ክበር ክበር ክበር ክበር እንላለን
ንገስ ንገስ ንገስ ንገስ እንላለን
ተሞኝተን አይደለም ምናመልክህ
ኢየሱስ ኢየሱስ የምንልህ
በደንብ ገብቶናል አንድ ፍቅርህ
ልንርቅ እኛ አንችልም ከእቅፍህ
ተሞኝቼ አይደለም የማመልክህ
ኢየሱስ ኢየሱስ ሁሌ ምልህ
ኧረ እኔስ ገብቶኛል አንድ ፍቅርህ
ልርቅ እኔ አልችልም ከእቅፍህ
ምን አለን ከአንተ ውጪ
እኛ ምን አለን ከአንተ ውጪ
ምንጠራው አንተን ነው ምንጠራው
ምናሳየው አንተን ነው ምናሳየው
ምንጠራው አንተን ነው የምንጠራው
ምናሳየው አንተን ነው ምናሳየው
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
ረግቻለው
ለሰላሜ የሚሆነኝን አውቄያለሁ አግኝቻለሁ
ለእፎይታዬ የሚበጀኝን አምኛለሁ ተቀብያለሁ
የእግዚአብሔር ልጅ በርቶልኛል በመንፈሱ ረግቻለሁ
ላልወሰድ በምድር ተረት ለዘልአለም ታክሜያለሁ
ከአላማኞች በተሰወረ
ከጠቢባን ዘንድ ባልነበረ
የሞኝነት በሚመስል ታምር
እኔ አርፌያለሁ በአንተ ማመን ሚስጥር
ባንተ ደስ ብሎኛል ፀጋ በዝቶልኛል
ረክቻያለሁ አመሰግናለሁ
ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረግቻለሁ አመሰግናለሁ
ባንተ ደስ ብሎኛል ጸጋህ በዝቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ
ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ
የማይነጥፍ ነው ሰላሜ የማያልፍ ነው እረፍቴ
ማደርያህ ለሆን ወደህ ዘልቀሀልና በህይወቴ
የማይደበዝዝ ፍቅር ነው ሽንገላም ወረትም በሌለው
ካንተ ያልተቀበልኩት ምን አለኝ ቀረ ምለው
አንተ ሞልተኸኛል ህይወት በዝቶልኛል ረክቻለሁ ልጅህ ተብያለሁ
ባንተ ደስ ይለኛል ሰላም ረግቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ
በሰማያዊ በረከት በራስህ ተባርኪያለሁ
እዚህ እንዳልናወጥ ከእቅፍህ ገብቻለሁ
አልሸበርም በአለም በሚሰማው ክፉ ወሬ
ባልከኝ ረግቻለሁ በያዝከኝ እስከዛሬ
አንተን ይዞ ያልረካ ማነው
አንተን ይዞ ያልሰከነ ማነው
አንተን ይዞ የባከነ ማነው
አንተን ይዞ የባዘነ ማነው
ባንተ ደስ ብሎኛል ጸጋህ በዝቶልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ
ሰላም ረግቶልኛል ፍቅርህ ዘልቆልኛል ረክቻለሁ አመሰግናለሁ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
"እግዚአብሔር ይመስገን"
ባርኮቴ ብዙ ነው
የተደረገልኝ ስንቱ ነው
በረከቴን እቆጥራለሁ
የተደረገልኝ ብዙ ነው
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይመስገን
አምና ላይ ደረስኩኝ
ካቻምናን ዘግቼ
ዘንድሮን ደግሞ አየሁ
አምናን ረስቼ
ከማላየው ክፋት በክንዱ ሸሽጎኝ
ከማላውቀው ጥፋት በድንቅ አስመልጦኝ
እኔ አለሁኝ
በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት
በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት
በእርሱ ምሕረት በእርሱ ደግነት
እኔ አለሁኝ!
ዛሬ ሰላም ነው ቤቴ
ተጠብቆ በአባቴ
እንደቀልድ ደህና ነሽ ወይ ሲሉኝ
እግዚብሔር ይመስገን አልኩኝ
እግዚብሔር ይመስገን
እግዚብሔር ይመስገን
መድኃኒዓለም ይክበር
አባቴ ይመስገን የምልበት
ብዙ አለኝ
ብዙ አለኝ
ብዙ አለኝ
ብዙ አለኝ
የሠራው ሰማዩን ያበጀው ምድሩን
እግዚአብሔር አይደል ወይ የሚያይ??
አምላኬ አይደለም ወይ
ባበጀው ምድር ላይ የሚያኖረው ሕዝቡን
እኔን
እግዚአብሔር አይደለም ወይ
አምላኬ አይደለም ወይ
መውጣት መግባቴ በእኔ አይደለም
ሰላም ውሎ ማደሬም ቀልድ አይደለም
ጤናዬን ሰላሜን እርሱ ይዞት እንጂ
ጠላት መች ዘንግቶ የእኔን ደጅ
ቀን ይመሻል ይነጋል እያየሁት
ክረምት በጋውንም ይኸው ለመድኩት
ትናንት ዛሬንም ያየሁት በእርሱ ነው
ያልተነካሁት?? ምክኒያቱ በእግዚአብሔር ነው
በደግነቱ እኔን ያኖረኛል
በቸርነቱ እኔን ያቆመኛል
በደግነቱ እኔን ያኖረኛል
በቸርነቱ እኔን ያቆመኛል
በእርሱ ምሕረት
በእርሱ ደግነት
በእርሱ ምሕረት
በእርሱ ደግነት
ዓመታቶቹ የእርሱ ናቸው
በቸርነቱ የሚያቀዳጀው
በሆነውም ባልሆነውም
ልቤን አላዝልም
እግዚአብሔር ይመስገን
ለነገማ አልተክዝም
እግዚአብሔር ይመስገን
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
ግታው ሰበቤን
ከነገር ጅማሬ ፍጻሜ ይልቃል
ቀን ሳለ ጎበዝ ከየት እንደወደቀ ያስባል
የጅማሬ ውበት የዳነበቱ
ደብዝዞ ሳያልቅ በመንገድ ከንቱ
በጸጋ ሽፋን ፋኖ ተማምኖ
ስቆ ለውሃ ብዙ አለና የቀረ ባክኖ
አልፈልገውም ለብታዬን እግሮቼን አድስ
እኔ አልሻም መባከን በልማድ መደንዘዝ
ግታው ሰበቤን ያደከመኝን
ሰበብ በኩሬን የሚያስንቀኝን
ግታው ምክኒያቴን የተጫነኝን
ምክኒያት በኩሬን የሚያስጥለኝን፡፡
መሀል ሰፋሪ እዚህም እዚያም
ሁሉ አይቅርብኝ አገም ጠቀም
የለብታ ወንዝ ከባድ ፈተና
ወይ ያልበረደው ወይ እሣት ያልገባው ገና
አቋም በሌለው ከከልካይ ማዶ
በነፃ ክልል ይነጉዳል ፈቅዶ፡፡
ግታው ሰበቤን ያለዘበኝን
አክብጄ እንዳልይዝ ያጠመደኝን
ግታው ምክኒያቴን የታገለኝን
ለሁለት ጌቶች ያሰለፈኝን
ነግቶለት ሕይወት ጉዞ ጀምሮ
በአንተው ምሕረት በስም ተምሮ
ከመንከራተት ተርፎ ያልተረፈ
ዛሬም የሚባክን ልቡ ያላረፈ
ገና!
ዳግም ባርነት ዳግም እስራት
ባልሰከነች ነፍስ ልጓም በሌላት፡፡
ይብቃኝ ምክኒያቴ የተጫነኝ
አጥብቄ እንዳልይዝ ያታገለኝ
ግታው ምክኒያቴን ያደከምኝን
ትጥቄን ያላላ ያለዘበኝን
በመንፈስ አንቃኝ አዚሜን ገፍፈህ
የታገትኩበትን ገመዴን ፈትተህ
ግታው ሰበቤን ያበረታኝን
ለሁለት ጌቶች ያሰለፈኝን
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
እውነት እና እውነት
በሰው ክፋት ማዕበል ምድር ስትናወጥ
ፈጣሪ እንኳን በሰራው ፍጡር እስኪጸጸት
የአንድ ኖህ ጎዳና አካሄድ ቢቀና
የሰው ህይወት አልቀጠለም ወይ እንደገና
በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው
መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው
እውነትን በተቀማ ትውልድ
ማን ይሆን የእውነት ዘመድ
ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ
ማን አብሮ ይዘልቃል ከባይተዋር ጋራ
እንደውሃና ዘይት አይደሉም ወይ እውነትና ሃሰት
ምን አንዱ ቢበዛ መቼም አያብሩም ዘላለም በርቀት
በጊዜም ፈተና ወደቅክ ሚለው የለም
በእሳት ንዳድ አልፎ አመድ አያውቀውም
በልዩነት መንገድ በሰላም ይተማል
አጃቢ ሳያሻው ዘላለም ይኖራል
የዝምታው ድምጸት ከመብረቅ ጽኑ ነው
አለት ከሚያነቃ ከሚሰነጥቀው
እርሱ ተረጋግቶ ሀገር ይረበሻል
የለህም የሚለው እንቅልፍ አጥቶ ያድራል
ከብዙ ግርግር አባይ ከዋለበት
እውነት ከሚመስል አሳች ከበዛበት
ዘንድሮም ጉዳዩ ከእውነት ጋር ብቻ
እውነትና እውነት ከራሱ ጋር ብቻ
በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው
መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው
እውነትን በተቀማ ትውልድ
ማን ይሆን የእውነት ዘመድ
ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ
ማን አብሮ ይዘምታል ከባይተዋር ጋራ
የታመነ ጓዳው ዮሴፍ ትንሹ ዛፍ
ባልዋለበት ቢውል በእመቤቲቱ አፍ
ከእመቤትስ በላይ ሹምስ ማንን ያምናል
በሃጥእ ዘመን ዘንድ ጻድቅ ወህኒ ይወርዳል
ምን ቢታፈን ሃቁ በሚያልፍ ባለጊዜ
በማያልፍ ተክሷል ደርሶ የእውነት ጊዜ
ባደባባይ ቢያፍር እውነትን አንግሶ
ክብሩም ባደባባይ ይኸው ተመልሶ
ሀብት ነው ጌጥ እውነት ምን ቢያጡም ለጊዜው
ከርሞ ሚመነዘር ከፋይ ለከፈለው
እውነትን በተቀማ ትውልድ
ማን ይሆን የእውነት ዘመድ
ብርሃን ቃሉን ሲሰጥ ጨለማን ሲደክመው
የእውነት ቤት ይደምቃል ለ እግዚአብሔር ያደረው
ጽኑ ጽኑ ጽኑ
ጽኑ ጽኑ ጽኑ
እውነት እግዚአብሔር ነው የማይለውጥ ጽኑ
በሰልፍ ብዛት የማይደክመው ከበረታው በላይ ብርቱ
ባህሪው ሰላም ነው አያምንም በሁከት
ራሱን ለማሳመን አይገባም ከጭንቀት
ህሊና ወዳጁ ጊዜ መፍቻ ቁልፉ
ተረጋግቶ ይኖራል ተከድቶ በስንቱ
ጽኑ ጽኑ ጽኑ
ጽኑ ጽኑ ጽኑ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
ብቻ ልቤን
አንደበትህ ይታክታል
የሆድን ሁሉ ቢናገር
ለመጣው ለሄደው ሁሉ
የሚያልፍበትን ቢዘረዝር
የሰሚም- የሰሚም ጆሮ ይዝላል
ለጊዜው ለሰሞንም ቢያዝን
ብቻ ልቤን ደግፈው
አልፈዋለው ብርቱውን ቀን
ብቻ ልቤን ደግፈው
አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን
እጠራሃለሁ
በስምህ ውስጥ ሰላም አለ
እጠራሃለሁ
በስምህ ውስጥ ብርታት አለ
በስምህ ውስጥ
እግዚአብሔር
በስምህ ውስጥ እረፍት አለ
በስምህ ውስጥ ጽናት አለ
በስምህ ውስጥ ሰላም አለ
በስምህ ውስጥ
ከፀሓይ በታች መልስ ባጣሁለት ጉዳይ
ቢያይልም ግርታዬ አይኔን ተክያልህ ሰማይ
ከያዘኝ ከከበበኝ በላም አንተን አምንሃለሁ
ብቻ ልቤን ደግፈው
አልፈዋለው ብርቱውን ቀን
ብቻ ልቤን ደግፈው
አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን
ልቤ ተጠብቆ በሚሆነው ነገር
እታገስሃለሁ አለህ አንድ ነገር
ብቻ ልቤን ጠብቀው
አልፈዋለው ብርቱውን ቀን
ብቻ ልቤን ደግፈው
አልፈዋለሁ ክፍውን ቀን
በስምህ ውስጥ ሰላም አለ
በስምህ ውስጥ እረፍት አለ
በስምህ ውስጥ ጽናት አለ
በስምህ ውስጥ
ልብ ብቻውን ሲቀር በሃሳብ ሲወረር
በሁነኛ ነፋስ በማዕበል ሲሰወር
ደጋፊ ከሌለው ማን ከማን ያስጣል
ልብ የወደቀ ቀን ለሞት እጅ ያሰጣል
ልቤን የሚታደግ ብርቱ ግንብ አለቴ
አጥር ሃይሌ ስምህ ነው የተስፋ ጽናቴ
አንተ ነህ እግዚአብሔር ጽኑ መታመኛ
አደራ የምለው አንተን ነው የልቤን መገኛ
በስምህ ውስጥ ሰላም አለ
በስምህ ውስጥ እረፍት አለ
በስምህ ውስጥ ጽናት አለ
በስምህ ውስጥ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
9 999
" እረኛ"
ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖረ
ልቡ ስለመንጋው ያደረ
ለአንዲት ምስኪን ነፍስ ግድ እያለው
ብዙ አሉኝ ብሎ አንዷን የማይተው
ይሄዳል ያለእረፍት ሁሉ ጋ
የጠፋችውን ያቺኑ ፍለጋ
ሲያገኛት ሌላ እንደሌለው
ደስታው መለኪያም የለው
የባዘነውን የሚመልስ
የጠፋውን የሚፈልግ
የተሰበረውን የሚጠግን
የሚያጸና የደከመውን
ይህ ነው የእኔ እረኛ
ይህ ነው የእኔ መዳኛ
ይህ ነው የእኔ መጽናኛ
ኢየሱስ መልካሙ እረኛ
መታመኛዬ መጠገኛዬ
መደገፊያዬ መታደጊያዬ
ጠያቂ አለኝ ጠያቂ
ፈላጊ አለኝ ፈላጊ
ጠያቂ አለኝ ጠያቂ
መሽቶም ሲነጋ ጠባቂ
ይህ ነው የእኔ መጽናኛ
ኢየሱስ መልካሙ እረኛ፡፡
ውዴ የሚታደገኝ ራሱን ሰጥቶ
የሚያውቀኝ ከልብ በስም ለይቶ
ለአፍታም ለቅጽበት አይለየኝ
ለሚሰማሩብኝ አይተወኝ
የእረኞች አለቃ እረኛዬ
የገዛኝ በፍቅር መጋቢዬ
ኢየሱስ የነፍሴ አባት ጠባቂዋ
ከዱር ከገደሉ ማምለጫዋ
የባዘነውን የሚመልስ
የጠፋውን የሚፈልግ
የተሰበረውን የሚጠግን
የሚያጸና የደከመውን
ይህ ነው የእኔ እረኛ
ይህ ነው የእኔ መዳኛ
ይህ ነው የእኔ መጽናኛ
ኢየሱስ መልካሙ እረኛ
መታመኛዬ መጠገኛዬ
መደገፊያዬ መታደጊያዬ
ጠያቂ አለኝ ጠያቂ
ፈላጊ አለኝ ፈላጊ
ጠያቂ አለኝ ጠያቂ
መሽቶም ሲነጋ ጠባቂ
ይህ ነው የእኔ መጽናኛ
ኢየሱስ መልካሙ እረኛ
share♻️share♻️share♻️
🟡የመዝሙር ግጥሞችን ከፈለጉ ይህን link👇ተጭነው ይቀላቀሉ🎼 𝙟𝙤𝙞𝙣⬇️ 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 🎼 @mezemur_lyrics @mezemur_lyrics ❖ ─── ✦ ─── ❖
