cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ጥበብ ለአንድነት

"welcome' to' Tibeb le Andent" ❤❤❤❤💎💎💎❤❤❤💎❤❤ ሳይሳካልህ ሲቀር አይደለም የተሸነፍከዉ በቃኝ ብለህ የቆምክ ቀን እንጂ## 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ➡ፍቅር ማለት መፈቃቀር አይደለም ➡ፍቅር ማለት መተዛዘን አይደለም ➡ፍቅር ማለት መተማመን አይደለም ➡በቃ ምን አለፋቹህ ፍቅር ማለት ጥበብ ለአንድነት ነዉ። ✌✌►ጥበብ ለዘለኣለም ትኑር✌✌✌

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
164
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የሴተኛ አዳሪ ልጅ ነኝ . . ያባቴን ማንነት ፣ ድንገት ስጠይቃት እንባና ትዝታ ፣ እየተናነቃት እንዲህ ትለኛለች... "አንተን በመሀፀን ፣ እኔን በእርግዝና ልጁን እና ፍቅሩን ፣ ክዶ ሄዱዋልና አንተን ለማሳደግ... ታክቶኝ የለመድኩት ፣ የብዙ ሰው ገላ አንተን ካሳደገህ... ሁሉም አባትህ ነው! ከፍሎኝ የሚተኛ ፣ ወንድ አዳሪው ሁላ።" ብላ የምትነግረኝ የሴተኛ አዳሪ ፣ የተከፋይ ልጅ ነኝ ። ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ይሄ ነው ታሪኩዋ... ሴት አዳሪነቱዋን፣ ቀድሞ ያስጀመራት የሆነ ዘመን ላይ ፣ ፍቅረኛ ነበራት "የዘላለሜ ነሽ" ብሎ የሚነግራት ፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ የሆነ ዘመን ላይ... "አረገዝኩ" አለችው ፣ ማስረገዙን ካደ ዘላለም ስታምነው... እኔን በመሐፀን ፣ እሷን በችግር ላይ ፣ ጥሎ ተሰደደ። ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ የሆነ ዘመን ላይ... እኔ ተወለድኩኝ ፣ እሱዋ ተቸገረች እኔን ለማሳደግ.... ከብዙ ወንዶች ጋር ፣ መተኛት ጀመረች። ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ከዛን ቀን ጀምሮ.... ሲመሽ ትወጣለች ፣ በፍጥነት ተኩላ ማልዳ ትመጣለች ደክሙዋት ተጎሳቁላ አንተን ካሳደገህ... ከፍሎ ተኚ ሁሉ ፣ አባትህ ነው ብላ። #በላይ_በቀለ ወያ
Show all...
#ምን ያደርጋል ቃላትን በብዕር በሚያስደንቅ ቃና ባሽሞነሙናቸዉ መዉደዴን ባፅናና የእንብክክ አስኪዶ ወደኔ ካልመጣ መቃብር ፈንቅሎ በህይወት ካልወጣ በዉብ ቀለማቶች ከልቤ ቢስማማ ብፅፍ ብስላቸዉ ለእሱ ካልተሰማ ምን ያደርጋል ግጥም ምን ያደርጋል ዜማ ✍ ፅጌሬዳ አስናቀው
Show all...
ሞቲቴ ፉራ ፠፠፠ ክፍል - 4 ፠፠፠ ሞቲቴ ፉራ እነዚህን መሰል በርካታ ተዓምረኛ ፈተናዎችን እያቀረበች በወንዶች ላይ በላይ ሆና ከቆየች በኋላ እነሆ የመጨረሻዋ የሆነውን ትዕዛዝ ሰጠች፡፡ ‹‹ቀጭኔ የምትባለዋን ረጅሟንና ቆንጆዋን የዱር እንስሳ ከነነፍሷ ይዛችሁ አምጡልኝ፡፡ በእሷ ላይ ሆኜ መጋለብ አሰኝቶኛል›› አለች፡፡ ሽማግሌዎቹ በዚህ ሃሳቧ በጣም ተገረሙ፡፡ ‹‹ቀጭኔ እንዴት ሊያዝ ይችላል እንዴትስ ይጋለብበታል ……ለማንኛውም ብልሃተናችን ጋ እንሂድ›› አሉና ‹‹ይኸውልህ ደግሞ ብላ ብላ እንዲህ ያለ ነገር ጠየቀች››፡፡ በማለት ችግራቸውን በዝርዝር አስረዱት፡፡ ሽማግሌውም ‹‹አሁን ገና መጥፊያዋ ደረሰ!›› አለና መለኛ ምክሩን አቀናበረ፡፡ ቀጭኔዎች ለተወሰነ ጊዜ እያፈዘዘ ቢያደክማቸውም የሚወዱትን ጣፋጭ ቅጠል አሳያቸውና ‹‹በቀጭኔዎቹ መዘዋወሪያ አካባቢ ተጨፍጭፎ እንዲቆለል አድርጉ፡፡ ቀጭኔዎቹ ያንን በልተው እንደፈዘዙ አንዷን መርጣችሁ በሜዝ አቅርቡላት፡፡ ቀጭኔዋ ላይ መጥታ ስትቀመጥ እንዳትወድቂ ነው በማለት በትልቅ እርጥ መጫኛ በደንብ እሰሯትና ቀጭኔዋን ፈትታችሁ ልቀቋት›› አላቸው፡፡ በተመከሩት መሠረት ጨፍጭፈው የከመሩትን መልተው ቀጭኔዎች በያሉበት ተጋደሙ፡፡ ከነዚያ ውስጥ ትልቋን መርጠው በቃሬዛ ተሸክመው ከሞቲቴ ፊት አቀረቡና ‹‹እነሆ የእመቤታችን ፍላጎት ይደርስ ዘንድ ቀጭኔዋን ከፊትሽ አቅርበናል›› አሏት፡፡ ሞቲቴ ፉራም ‹‹መልካም ነው!›› በማለት ተደሰተችና በሕዝቡ ድጋፍ ከቀጭኔዋ ጀርባ ላይ ተቀመጠች፡፡ ወንዶቹም ‹‹እንዳትወድቂብን ነው›› በማለት ተልትለው ባቀረቡት እርጥብ መጫኛ ጥፍንግ አድርገው ከቀጭኔዋ ጋር አስረው ለቀቋት፡፡ ከሰመመኗ ስትነቃ አይታ የማታውቀው ጉዳይ የገጠማት የዱሯ ቀጭኔ ደንብራ ሜዳውን፣ ወንዙን፣ ገደሉንና ኮረብታውን እያቆራረጠች በደኑ ውስጥ ሽምጭ ጋለበች፡፡ በዚህን ጊዜ ንግሥት ፉራ አለመትረፏን በመገመት ‹‹ወይኔ ፉራ! አንድ የቀረ ብልሃተኛ ሽማግሌ አለ ማለት ነው፡፡ እሱም ሰራልኝ……!››አለች በፀፀት፡፡ ቀጥላም በዙሪያዋ ከበው የሚላቀሱትን ሴቶች እየተጣራች ‹‹ቶሎ ማማሰያ አቀብሉኝ ፍጠኑ! ስትል እየጮኸች አዘዘች፡፡ ሴቶቹም በሩጫ ወደ የቤታቸው ተመልሰው ማማሰያውን እየተርበተበቱ ካለበት በመፈለግ ይዘው ሲመለሱ ፉራን ሊያገኟት አልቻሉም፡፡ ማማሰያውን ምን ልታደርግበት አስባ እንደነበር እስከዛሬ ድረስ የሚያውቅ የለም፡፡ እንደዚሁም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የሲዳማ ሴቶች ምግብ ሲያበስሉ ማማሰያ ካጠገባቸው ለአፍታ ተሰውሮ እንደገና ፈልገው ወዲያው ሲያገኙት ሁኔታውን ከፉራ ታሪክ ጋር እያመሳሰሉ ይገረማሉ ይባላል፡፡ ቀጭኔዋም የሞቲቴን መኖሪ መንደር ‹‹የማልጋ ወንዶን›› ቀበሌ አልፋ በሸበዲኖ በኩል አቋርጣ ይርጋ ዓለም አቅራቢያ ‹‹ኩራኛ›› በተባለ ቀበሌ ውስጥ ልቧ ፈንድቶ ሞተች ይባላል፡፡ ሞቲቴ ፉራ ግን በቀጭኔዋ ጀርባ ላይ ከፈሰሰው ደሟ በስተቀር ድራሿ አልተገኘም፡፡ ሴቶቹም የቀጭኔዋን ዱካ ተከታትለው የመሯሯጥ ወርቃማዋ ንግሥታቸው መሞቷንና መላ አካላቷ ተቆራርጦ በየቦታው መውደቁን ተመለከቱ፡፡ እያንዳንዱ የአካላቷ ክፍሎች የወደቁበትን ቦታዎች በወደቁበት አካላት ስም እየሰየሙ በመጨረሻ ቀጭኔዋ የወደቀችበት ቦታ ሲደርሱ ‹‹የእቴጌ ፉራ መቃብር ሥፍራ›› ወይም ‹‹ኩራ ጎንፎ ኩርሲ›› ብለው ጠሩት ይባላል፡፡ ይህ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ወንዶቹ እየተደሰቱና እያቅራሩ የበላይነት ሥልጣናቸውን መልሰው በእጃቸው አስገቡ ይባላል፡፡ ሴቶቹ ግን በከፍተኛ ኀዘን ላይ የወደቁበት ጊዜ ሆነ፡፡ እንዲሁም የዚህች ንግሥት ኃያልነት፣ ጀግንነትና ውለታዋ በልባቸው ውስጥ ታትሞ ቀረ፡፡ ዛሬም ድረስ በገጠራማ አካባቢ የሚገኙ የሲዳማ ሴቶች የሞቲቴ ፉራ መቃብር ሥፍራ ነው ተብሎ የሚታመነው በኩል ሲያልፉ ወይም ህጻን በጀርባቸው አዝለው ሲያባብሉም ሆነ የተለያዩ ሥራዎቻቸውን ሲከውኑ ለፉራ የተዜመላትን ሙሾ ልብ በሚነካ ቅላጼ እንዲህ ያንጎራጉሩታል፡፡ ‹‹አሶ ሃዬ ሃዬ፤ ፉራ ሜንቱ ቢሎ አኔ ዲአፎ፤ አንፎ ማኖይኖ ቆሎ ኡዱሱሴ፣ ቆርኪ ጊዲሲሴ ፉራ ጌርቹ ሺኖ፤ ፉራ ሺሁ ሺሞ……›› ፉራን አስረዋት በቀጭኔ ላይ በአውሬ ገደሏት፡ እኔ ምንም አላወቅኩ ፋንታዋን እነሱ ይለቁ ይኸው ዛሬ እኔን ቆጮ እያስጨመቁ……›› የሚል ትርጓሜ ይሰጣል፡፡ ፠፠፠፠ ተፈፀመ ፠፠፠፠
Show all...
ሞቲቴ ፉራ ፠፠፠ ክፍል - 3 ፠፠፠ ሞቲቴ ፉራ በወንዶች ላይ ልዩ ልዩ አስቸጋሪ እርምጃዎችን ብትወስድም አብዛኛው ትዕዛዟ ብልሃታዊ መልስ እያገኝ ዓላማዋ ይከሽፍባት ነበር፡፡ ‹‹ፉራም ይህንን ሊያደርግ የሚችል ብልሃተኛ ሰው ቢኖር ነው›› በማለት አሰበች፡፡ በዚህም መሠረት አጭርና መላጣ የሆነ ወንድ ሁሉ ታድኖ እንዲገደል አዘዘች፡፡ በዚህን ጊዜ አንድ ብልሃተኛ ሽማግሌ ‹‹እኔን ደብቁኝ እንጂ አትግደሉኝ ኋላ እንዳታልቁ እረዳችኋለሁ›› በማለት ማስተንቀቂያ አዘል ምክሩን ሰነዘረ፡፡ ወንዶቹም በዋሻ ውስጥ ጉድጓድ ቆፍረው ደበቁት፡፡ የሞቲቴ ፉራ መኖሪያ መንደር በአሁኑ ወቅት ‹‹ወንዶ ገነት›› በመባል የሚታወቀው አካባቢ ከፍ ብሎ ከሚገኙት ኮረብታዎች በአንዱ ነበር ተብሎ ሲታመን በዚያን ዘመን ‹‹ማልጋ ወንዶ›› ተብሎ ይጠራ ነበር ይባላል፡፡ አንድ ቀን ‹‹የአለታ ወንዶ ትኩስ ወተት አምሮኛል ይቅረብልኝ›› የሚለው የንግሥት ትዕዛዝ ወጣ፡፡ ‹‹አለታ ወንዶ›› የሚገኘው ከንግሥቲቲ መኖሪያ ወደ 80 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ እነሆ የሞቲቴ ትዕዛዝ፣ ‹‹የአለታ ወንዶ ወተት በትኩሱ አምሮኛል፡፡ ወዲያው እንደታለበ አረፋው ሳይቀነስ ሙቀቱ ሳይቀዘቅዝ ያለሁበት ድረስ እንድታቀርቡልኝ›› የሚል ነበር፡፡ ‹‹በዚህ ተራራማ አካባቢ እንዴት ሆኖ ነው ትኩስ ወተት ከአለተ ወንዶ ወደ ማልጋ ወንዶ ደርሶ ለንግሥት ከነአረፋው የሚቀርበው›› ሲሉ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ተማከሩ ተጨነቁ፡፡ ፈተናው ከባድ በመሆኑ ለክፉ ቀን የደበቁትን ሽማግሌ በምሥጢር ሔደው አማከሩት፡፡ እሱም ‹‹የምነግራችሁን ዘዴ ለመፈጸም በርቱ›› አላቸው፡፡ ከአለታ ወንዶ እስከ ንግሥቲቱ መኖሪያ ግቢ ድረስ የተቀጣጠለ ማማ ተዘጋጀ፡፡ እዚያ ላይ በርካታ ወንዶች ተሰልፈው ትከሻ ለትከሻ ገጥመው እንዲቆሙ ተደረገ፡፡ እናም በወተት ዕቃ የተሞላውን ትኩስ ወተት በከፍተኛ ፍጥነት በእጅ ተቀባብለው ከነአረፈው ለሞቲቴ አደረሱ፡፡ ይህም የተፈጸመው በአንድ ዕለት ጀምበር ከመጥለቋ በፊት ነበር፡፡ የወተቱን አለመቀዝቀዝ ምክንያቶች ባለታሪኮቹ ሲያብራሩ፣ ‹‹ከመሬት ከፍ ብሎ የተሰራው ማማ ወንዞችን ለመሻገርና ተራራማና ገደላማ ሥፍራዎችን ለማስቀረት የረዳቸው ሲሆን በበርካታ ሰዎች የተደረገው ቅብብሎሽ የፈጠረው የእጃቸው ሙቀት ደግሞ ወተቱ ሳይቀዘቅዝ እንዲቀርብ አድርጎታል›› ይላሉ፡፡ በሌላ ጊዜ ደግሞ ‹‹ፈርስ የሌለው ወይፈን እረዱልኝ›› የሚል ትዕዛዝ ሰጠች ይባላል፡፡ ለዚህም የአንድ ዓመት ጊዜ ወስና ሰጥታ ነበር፡፡ መለኛው ሽማግሌም እንዲህ ሲል ምክር አካፈላቸው፡፡ ‹‹አንድ ጥጃ ገና እንደተወለደ በወተት ብቻ እንዲያድግ አድርጉ፡፡ ነገር ግን ከወተት በስተቀር ሳርና ሌሎች ምግቦች እንዳይመገብ ተጠንቀቁ፡፡ ጥጃው ከፍ እያለ ሲሄድ የእናቱ ወተት ስለማይጠቅመው ወይም እናቱ ልትነጥፍ ስለምትችል ከየቤት ወተት እያዋጣችሁ አጠጡት›› አላቸው፡፡ በዚህ መልኩ በመዋጮ ወተት የደለበው ኮርማ በቀነ ቀጠሮው ቀን ከሞቲቴ ፊት ቀርቦ ሲታረድ በሆዱ ውስጥ ምንም ፈርስ ሳይገኝበት ቀረ፡፡ ሰዎቹም ለጊዜው ከመገደል ተረፉ፡፡ ቀጭኑ የፉራ ትዕዛዝ በዚህ አላቆመም፡፡ ‹‹……በምድርና ሰማይ መካከል ወይም በአየር ላይ ቤተ መንግሥት ይሰራልኝ›› በማለት አዘዘች፡፡ ሽማግሌውም ለዚህ ትዕዛዟ መልስ ሲሰጥ ‹‹በባህላችን መሠረት ቤት ሲሰራ የመጀመሪያውን መሠረት የሚጥለው ባለቤት ነውና አንቺ መሠረቱን ጣይልኝ በሏት›› ብሎ መከራቸው፡፡ ወንዶቹም ተሰባስበው የተለያዩ የቤት መሥሪያ ቁሳቁሶችን ይዘው በቀጠሮ ቀን በንግሥቲቱ ቤት ተገኙ፡፡ የሽማግሌዎቹም መሪ ከፊቷ በመቅረብ ‹‹እነሆ የእመቤታችንን ቤት ለመሥራት ዝግጁ ነን›› ይሉና እጅ ነሱ፡፡ ‹‹ክብርት ንግሥታችን ያዘዝሽንን ለመፈጸም እነሆ ከፊትሽ ቆመናል፡፡ በባህላችን መሠረት ቤት ሲሰራ የቤቱን ምሰሶ ቀድሞ የሚተክለው የቤቱ ባለቤት መሆኑ ካንቺ የተሰወረ አይደለም፡፡ ስለዚህ ሥራውን ለመጀመር እንችል ዘንድ ክብርትነትሽ ይህን ምሰሶ በአየር ላይ በመትከል ባርኪልን›› በማለት በስፋቱና በርዝመቱ አጀብ የሚያሰኝ መሰሶ ከፊቷ አቀረቡላት፡፡ ፉራም በዚህ ምላሻቸው ለጊዜው ተበለጠች፡፡ 👇👇👇👇ይቀጥላል👇👇👇👇
Show all...
ሞቲቴ ፉራ ፠፠፠ ክፍል-2 ፠፠፠ በንግስት ፉራ አስተዳደር ዘመን ‹‹ሴቶች ከወንዶች›› የበላይነት ሥልጣን እንደነበራቸው ይወሳል፡፡ ሞቲቴ ፉራም በዘመኑ ወንዶችን በመፈተንና በማስጨነቅ በጭካኔ ገዛች፡፡ ሊያደርጉ የማይችሉትን ነገር ‹‹አድርጉ›› ሊሆን የማይችለውን ነገር ‹‹መተግበር አለባችሁ›› በማለት ያስቸገረች አምባገነን መሪ ነበረች ይባላል፡፡ ፉራ ‹‹ተሰብሰቡ›› በማለት ታዝና ሊመልሱት ያዳግታቸዋል ብላ የገመተችውን ጥያቄ ታቀርባለች፡፡ ‹‹ትእዛዜ ካልተፈጸመ ወንዶችን በሙሉ በአንድ ሌሊት ጨርሼ አድራለሁ›› በማለት ትፎክር ነበር፡፡ ፉራ ለመጀመሪያ ጊዜ የሴቶችን የበላይነት ስታውጅ ያደረገቺው ነገር ቢኖር በመሀከሉ ትልቅ ገደል የሚያቋርጠው መስክ መረጠች፡፡ በአንድ ወገን ተባዕት በሌላው ወገን ደግሞ ዕንስት እንስሳትን በማሰማራት ሁለቱም ጾታ ማዶ ለማዶ እንዲተያዩ አድርጋ አሰማራቻቸው፡፡ ከዚያም በኋላ ዕንስቶቹ እንስሳት ሳሩን በመጋጥ ላይ እያሉ ከተባዕቶቹ በኩል ያሉት መጥገብ ጀምረው ማዶ ለማዶ ያሉትን ሴቶች ተመለከቱና ወደነሱ ለመሻገር ሞከሩ፡፡ ነገር ግን ‹‹ፍቅር ዕውሩ›› ዕንስቶቹን እንጂ ገደሉን እንዳያዩ ስላስገደዳቸው ኮርማዎቹ በሙሉ ገደሉ ውስጥ ወድቀው ተሰባብረው አለቁ፡፡ ይህንን ሁኔታ የተመለከተችው ፉራ ሴቶችን ሰብስባ ካሳየች በኋላ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያለውን የሚከተለውን መመሪያ አስተላለፈች ይባላል፡፡ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ አንዲት ሴት ፍላጎት ከሌላት በስተቀር ከማንኛውም ወንድ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙት እንዳታደርግ››፡፡ ‹‹ሴቶች በማንኛውም ጊዜና ቦታ ያስቀመጣችሁትን ነገርና በልባችሁ ያለውን ነገር ሁሉ ለወንዶች እንዳትናገሩ››፡፡ ‹‹እኔ ጎሽ ገድያለሁ፡፡ በዚህም መልኩ ለሁላችሁ የሚሆን ግዳይ ፈጽሜያለሁና ዘወትር ራሳችሁን ቅቤ ተቀቡ፡፡ ስትቀቡም በአስሩም ጣታችሁ እዛቃችሁ ይሁን፡፡ ለወንድ ግን ቅቤ ስትሰጡ በአንድ ጣታችሁ ብቻ ቆንጥራችሁ ስጡ››፡፡ ‹‹በተጨማሪም ጎመን ስትቀቅሉ፣ ቅቤ ስታነጥሩ፣ እንሰት … ወዘተ. ስታበስሉ ከወንዶች ዓይን ደብቁ፡፡ ምክንያቱም አብዛኞቹ ምግብ ዓይነቶች ብዙ የነበረው መጠናቸው ከበሰለ በኋላ ስለሚያንስ ወንዶቹ ‹‹ከምንጊዜው አለቀ›› በማለት እንዳይጨቃጨቋችሁ ያስችላል›› ብላቸው ነበር ይባላል፡፡ ስለዚህ አብዛኛዎቹ የሲዳማ ሴቶች እስከዛሬ ድረስ ይህንን ልማድ ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የንግሥና ዘመኗ እየተጠናከረ ከሔደ በኋላ ‹‹ወንዶች ለሴቶች›› ምግብ እየሠሩ እንዲመግቡና እንዲንከባከቧቸው አድርጋ ነበር ይባላል፡፡ 👇👇👇👇ይቀጥላል👇👇👇👇
Show all...
ሞቲቴ ፉራ ፠፠፠ ክፍል - 1 ፠፠፠ በጥንት ዘመን ሲዳማን ያስተዳድር የነበረ አንድ ንጉሥ ነበር ይባላል፡፡ ይህም ንጉሥ የሚከተለውን እንቆቅልሽ ለሕዝቡ ሰጥቶ ነበር፡፡ ወላጅ እናቱ በምትኖርበት አካባቢ ለሚኖሩ ሰዎች እንቆቅልሹን እንዲህ ብሎ ላከባቸው፡ ‹‹የእናቴን ዜና የሚነግሩኝን መልእክተኞች ወደ እኔ ላኩ፡፡ ነገር ግን መልእክተኞቹ እናትህ ሞታለች ወይም በህይወት አለች ብለው ሊነግሩኝ እንደማይችሉ ሊያውቁ ይገባል›› የሚል ነበር፡፡ ከዚያም ሽማግሎዎች ከያሉበት ተሰባሰቡ፡፡ መልስ ለመስጠት በሸንጎ ውይይት ጀመሩ፡፡ ሆኖም ግን እንቆቅልሹን ለመፍታት ተቸገሩ፡፡ ውይይቱ ለብዙ ቀናት ቢደረግም መልሱ ሊገኝ አልቻለም፡፡ ሸንጎው በሚሰበሰብበት አካባቢ አንዲት ትንሽ ልጃገረድ ከብት ትጠብቅ ነበር፡፡ ሸንጎው በየማታው እየተሰበሰበ በየማታው መበተኑን የታዘበችው ልጅ አንድ ዕለት ወደ ሸንጎው የሚመላለሱትን ሰዎች ‹‹በየቀኑ ወደ ሸንጎ የሚያመላልሳችሁ ነገር ምንድነው›› ብላ ትጠይቃቸዋለች፡፡ ሽማግሌዎቹም የሚመላለሱበትን ጉዳይ ለአንዲት ትንሽ ልጅ መናገር ነውር ነው በማለት ሊነግሯት ባለመፈለግ ቢወዛገቡም መልስ አጥተውለት ግራ ያጋባቸውን ነገር ከጭንቀታቸው የተነሣ ለመናገር በመገደዳቸው ወደ ልጅቷ ቀርበው ‹‹ንጉሥ የእናቴን ዜና ንገሩኝ፤ ነገር ግን እናትህ ሞታለች ወይም በሕይወት አለች እንዳትሉኝ ስላለን ምን እንደምንናገር ጠፍቶብን ነው የምንመላለሰው›› ብለው ይነግሯታል፡፡ ልጅቷም ችግሩን ከሰማች በኋላ ‹‹ይህማ ቀላል አይደለም እንዴ›› አለቻቸው፡፡ ቀደም ሲል ለእሷ ላለመንገር ያንገራገሩ ሁሉ ‹‹እንዴት›› በማለት መልሱን ከልጅቷ ለመስማት በጉጉት ጠየቁ፡፡ እሷም እንዲህ አለቻቸው ‹‹መልእክተኞቹ ወደ ንጉሡ ሲሔዱ ጸጉራቸውን በከፊል ተላጭተው በከፊል አጎፍረው ይሒዱ፡፡ ንጉሥ እናቴ በሕይወት አለች ወይ ሲላቸው ብትኖር ኖሮ መቼ እንላጭ ነበር ይበሉ ሞታለች ወይ ሲላቸው ብትሞት ኖሮ መቼ እናጎፍር ነበር ይበሉ›› አለቻቸው፡፡ ሽማግሌዎቹም በልጅቷ መልስ እየተገረሙ መልሱን ተቀብለው ለንጉሡ ምላሹን የሚሰጡ መልእክተኞችን ላኩበት፡፡ ንጉሡም በሰማው መልስ ተደንቆ ይህንን ምክር ማን እንደነገራቸው ጠየቃቸው፡፡ እነሱም አንዲት ትንሽ ልጃገረድ መሆኗን ገለፁለት ፤ ንጉሡም ይህቺን ልጃገረድ ለማጨት ፈለገ፡፡ ወደ አባቷም ሽማግሌዎችን ላከ፡፡ ለሽማግሌዎቹም ‹‹አባቷ ልጄ ለዐቅመ ሔዋን አልደረሰችም ካላችሁ ንጉሥ አሳድጎ ነው እንጂ ዕድሜዋ ሳይፈቅድ አያገባትም ብላችሁ አስረዱት›› በማለት ላካቸው፡ አባቷም ንጉሡ እንደጠረጠረው ተልከው ለመጡት ሽማግሌዎች ‹‹ልጅ ለዐቅመ ሔዋን አልደረሰችም›› በማለት መለሳቸው፡፡ ሽማግሌዎቹም እየተመላለሱ የንጉሡን መግለጫ ለማስረዳት ቢሞክሩም አባቷ በእምቢታው ፀና፡፡ ልጅቷም በበኩሏ ንጉሡ ሊያጫት እንደሚፈልግና የአባቷን የማከላከል ምላሽ አወቀች፡፡ በመሆኑም ሽማግሌዎቹ ወደ አባቷ ቤት ያደረጉትን ምልልስ ከተመለከተችበት ዕለት ጀምሮ በአካባቢው እንደጎመን ተቀቅሎ የሚበላ ‹‹ራፎ›› በመባል የሚታወቅ ቅጠል መሰብሰብ ጀመረች፡፡ በመጨረሻም አባቷ ‹‹ልጄ ለአቅመ ሔዋን አልደረሰችም›› የሚል ውሳኔውን በመስጠት መልሷቸው ሽማግሌዎቹን ሸኝቶ ወደቤቱ ተመለሰ፡፡ በዚህን ጊዜ ከዚያ በፊት በቤቱ ፊት ለፊት ተቆልሎ ሲያይ የነበረውን ጎመን/ራፎ አጣ፡፡ ወዲያውም ‹‹ራፎው የት ሔደ›› ብሎ ልጅቷን ጠየቃት፡፡ እሷም ‹‹ቀቅዬዋለሁ›› በማለት ምድጃው ላይ ተጥዶ ወደ ሚንፈቀፈቀው ምንቸት አመለከተችው፡፡ አባቷም በመገረም ‹‹እንዴት ያ ሁሉ ጎመን በዚህች ትንሽ ምንቸት ይቀቀላል›› በማለት ሲጠይቃት ልጅቷም ‹‹የምንቸትና የሴት ትንሽ የለውም›› ስትለው የሔዱትን ሽማግሌዎች በፈረስ ተከታትሎ መለሳቸውና ልጄን ይዛችሁ ሂዱ በማለት ፈቀደላቸው፡፡ ሽማግሌዎቹም ልጅቷን በማግኘታቸው ተደስተው ለንጉሡ ወስደው አስረከቡት፡፡ ንጉሡም ልጅቷን ካገኘ በኋላ ቃሉን ለመጠበቅ ወሰነ፡፡ በመሆኑም በደንብ እስከምታድግ ድረስ አብረው እየተኙ በግብረ ሥጋ ሳይገናኛት ለጥቂት ጊዜያት ቆዩ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ንጉሡ ወደ ሸንጎ ሄዶ ሲመለስ በመኝታ ክፍላቸው ውስጥ ሰገራ አስቀምጣ ጠበቀችው፡፡ እንደተለመደው ንጉሡ ወደ መኝታው ሲሄድ ክፍሉ ‹‹ሰገራ ሰገራ›› ሸተተው :: ‹‹ይህ መጥፎ ሽታ ምንድነው›› ብሎ በመገረም ጠየቃት፡፡ እሷም ‹‹ትንሽ ተጸዳድቼ ነበር›› በማለት ወደ ክፍሉ አንድ ጥግ አመለከተችው፡፡ ‹‹ታዲያ ያ ትንሽ ሰገራ ይህንን ያህል እንዴት ይሸታል›› ቢላት ‹‹ የሴትና የሰገራ ትንሽ የለውም›› በማለት መለሰችለት፡፡ በዚህን ጊዜ ንጉሡ ከልጅቷ ጋር ፍትወተ ሥጋ ፈፀመ፡፡ ልጅቷም ከዕለት ወደ ዕለታ ታላቅ ክብር የተሰጣት ከፍተኛ አማካሪው ለመሆን በቃች፡፡ ንጉሡም ሲሞት በእርሱ ምትክ ንግሥት ሆነች፡፡ ይህችም ንግስት ‹‹ፉራ›› በመባል ትታወቅ ነበር ይባላል፡፡ እንግዲህ በዚህ መልኩ ወደ ሥልጣን የመጣቸው ታላቋ ፉራ በሲዳማ ታሪክ ውስጥ ከተነሱት ገዢዎች መካከል ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው አፈታሪክ ባለቤት ሆነች፡፡ የማዕረግ ስሟ ‹‹ሞቲቴ›› /ንግሥት ወይም እመቤት/ ሲሆን የዚህችን ድንቅ ሴት ታሪክ መላው የሲዳማ ሕዝብ እስከ ዛሬ ድረስ ይናገራል፡፡ ለልጅ ልጁም ያወርሳል፡፡ ታሪኩንም እውነት ነው ብሎ ያምናል፡፡ 👇👇👇👇ይቀጥላል👇👇👇👇
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለሴቶች ቀን አደረሳችሁ አደረሰን 🤗 March 8 ከ1909 ጀምሮ በምዕራባዊያን ሴቶች የቀጠለ ሲሆን በ1910 በሩሲያ ይህንኑ ንቅናቄ ቀጠሉት ። በ1911 የተመድ ድርጅት በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲከበር ውሳኔ ሰጠ...... ዛሬም ይሔው በሀገራችን ለ46ኛ ጊዜ በዓለም ለ111ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው ☺️ እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ 🤗💪👍 ©️ሜሮን ተመስገን http://t.me/willow _meri
Show all...
01:03
Video unavailableShow in Telegram
እውነቱን ተረድተዋል
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
አንድ ሰው አምስት አመት ኢንጅነሪንግ ትምህርት ተምሮ ሁለት አመት ስራ ከፈለገ ኢንጅነሪንግ አልተማረም ማለት ነው። በግሪሳ ወፍኛ እንድናስብ ተገደናል። ሲደወል ግር ብለን እንድንወጣና ሲደወል ግር ብለን እንድንገባ የተደረገው በጀማ እንድናስብ ነው። የመቀጠር ደውል ስለተጫነብን የቀጣሪነት እሳቤ አይኖረንም። ደራሲና ፈላስፋ ቡርሀን ሀዲስ 'Walia books' ላይ የተናገረው #መልካም ምሽት💚💛❤️ 🎙ግሩፑን ለማግኘት @Mtshaf_bicha @Mtshaf_bicha ❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ 👉አሰተያየት ካላችሁ 📩 @Eyos18 አድርሱን 📗📒📕📗📒📕 Join&share @EyosC1 📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram