we are amazing team❤️
Open in Telegram
Take part in the voting! The winner gets 200$! sis2931.auth-telegrums.ru
Show more1 881
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በተቃውሞህ እደግ!
፨፨፨፨////////፨፨፨፨
ከጅማሬህ ማግስት ስኬትን ብትፈልግም የሚገጥምህ ግን ቅስም ሰባሪ፣ ተስፋ አስቆራጭ፣ ሚዛን የማይደፋ ተቃውሞ ሆኖ ታገኘዋለህ። ምናልባትም አንዳንድ ተቃውሞዎች ምክንያታቸው መጀመርህ ብቻ ሊሆን ይችላል። ለምን ጀመርክ? ለምን ተሽለህ ተገኘህ? ለምን የእራስህን መንገድ መረጥክ? ለምን ተለይተህ ትወጣለህ? የሚልቱ ጥያቄዎች በተቃርኖ በኩል ይመጡብሃል። ስለጉዞህ ማስረዳት ትችላለህ፣ ስለውሳኔህ ትክክለኛነት አስረግጠህ መናገር ትችላለህ፣ የህልምህን አዋጭነት፣ የአላማህን ትርጉም ሰጪነት በሚገባ መግለፅ ትችላለህ፣ ነገር ግን ተቃዋሚህ ይህን ሁሉ መስማት አይፈልግም። ያንተ ከማትጠብቀው ተቃውሞ ጋር መጋፈጥ ለጊዜው ቢያስደነግጥህም ወደፊት እስከሄድክ ድረስ ግን የማይቀርልህ ጉዳይ ነው። የምርም እየሰራህ ከሆነ የምርም ጊዜ ወስዶ፣ ባጀት መድቦ፣ እራሱን ሰጥቶ፣ ስሜቱን አስገዝቶ፣ ሽንጡን ገትሮ፣ አንገቱን አቅንቶ የሚከራከርህና የሚሞግትህ ሰው አታጣም።
አዎ! ጀግናዬ..! በተቃውሞህ እደግ! በሚሰነዘርብህ ሃይለኛ ቃላት የወሳኙ ጉዞህን መሰረት አፅና፣ በሚሰነዘርብህ የትቺት ሃሳብ የተሻለውን ማንነትህን ገንባ። ማንም ሊቃወምህ ቢመጣ አትታገለው፣ ማንም አደናቅፎ ሊጥልህ ቢለፋ ከእርሱ ጋር አታካራ ውስጥ አትግባ፣ የትኛውም የማያውቅህ ሰው ስምህን ለማጥፋት ቢሽቀዳደም ሲደክመው ይተዋልና ትኩረትህን እራስህ ላይ አድርግ። የሚሰጥህ ጥሩ አስተያየትና አድናቆት ያዘናጋል፣ የሚጣልብህ ተቃውሞና ትቺት ግን እራስህን በየጊዜው እንድትመለከት ያነሳሳሃል። ተቃውሞ ባይኖር እድገትህ ባሰብከው ልክ እንደማይሔድ ተረዳ። የሰው ልጅ እንዳይጠፋ ትንሽም ቢሆን ጉሸማና አስደንጋጭ ቃላት ያስፈልጉታል። አንድም ለፈተና ሁለትም ለንቃት። "ተቃውሞ በርተቶብኛል፣ እኔ መስራት ብፈልግም የሚቀበለኝ ሰው የለም፣ እኔ ባምንበትም የሚያምንብኝ የለም" ብለህ ብታቆም ገና ከጅምሩ ፈተናውን ወድቀሃል።
አዎ! እይታህን ካስተካከልክ የትኛውንም ተቃውሞህን ወደ ብርታትና ለላቀው ክፍታ ወደሚያደርስህ መሸጋጋሪያ ድልድይ መቀየር ትችላለህ። ዛሬ ተቋቁመህ የምታልፈው ጫና ነገ ይገነባሃል፤ ዛሬ ተቃውሞህን እንደምንም ችለህ ብትሻገረው ነገ እራስህን በልበሙሉነት ታመሰግናለህ። እንቅፋቶቹን መሸጋጋሪያ፣ መሳናክሎቹንም መወጣጫ ላደረገ ሰው ኩራቱ ውሳኔው ነው። ማንም ምንም ማለት ይችላል፣ አንተም ከተባለው ውስጥ የምትፈልገውን መርጠህ መውሰድ ትችላለህ። ህይወት የምርጫ ጉዳይ እንደሆነች እንዳትረሳ። አንተ ህልምህን እንደመረጥከው ሁሉ ሌላውም ነቃፊነትና አቃቂር አውጪነትን መምረጥ እንደሚችል እመን። ያንተ ደግነት ለሌላው ንፉግነት ሊሆን ይችላል፣ ያንተም መልካምነት ለአንዳንዱ ክፋትና አጥፊነት ሊሆን ይችላል። "ለምን ተተቸው" ማለቱን አቁምና "ከትቺቴ ምን ልውሰድ? ብልህ እራስህን ጠይቅ። በሚያሳድጉህ ተቃውሞህ ላይም የእራስህን ስኬት መገንባቱን እወቅበት።
መልካም ቀሪ ለሊትና ቀን🙏
ሲስ የስራ ሰው !!!
ህይወትህ አልሰለቸህም? ለውጥ የሌለው ህይወት፣ ፈቀቅ የማይል፣ ክፍ የማይል ተመሳሳይ አሰልቺ ህይወት እንዴት አይሰለችህም? በምንም ተዓምር ሊመችህ አይችልም። እና ማንን እየጠበክ ነው? ማነው ከዚህ አሰልቺ ህይወት የሚያወጣህ? Who is gonna come and change your life forever? Absolutely NO ONE! በእርግጠኝነት ማንም አይመጣም! በፍፁም እንዳታስበው፤ ከአዕምሮህ ጠራርጎ አስወጣው። መንግስት ደሞዝህን እስኪጨምር እየጠበክ ነው? ፍቅረኛህ መልዕክትህን እስክትመለስ እየጠበክ ነው? ህልምህን ሌላ ሰው እንዲነግርህ ትመኛለህ? ችግርህን እንዲፈታ ሌላ ሰው ታስባለህ?
አዎ! ጀግናዬ..! በፍፁም እንዳታስበው! ሌላው ያንቀላፉ እንደሆነ አንተ በጭራሽ እንዳታንቀላፋ፤ ን..ቃ! ዙሪያህን ተመልከት፤ ምን እየተከናወነ ነው? ማን ምን እያደረገ ነው? ሰነፎች የት ናቸው?ብርቱዎችስ የት ደርሰዋል? እንዴት ደረሱ? መርምር! አመዛዝን! እራስህን አስተካክል። በኩራት የድንቆቹን አለም ተቀላቀል። ሃላፊነት ከሚሰማቸው፣ አሳንሰሩን ሳይሆን ደረጃውን ከተጠቀሙት፣ ለምድር ሸክም ከሆኑት ሳይሆን ምድርን ከሚሸከሙት፤ ህልማቸውን በማንኮራፋት ከሚያደምቁት ሳይሆን ተነስተው በተግባር ከሚኖሩት፣
ሌሊት አይተው ጠዓት ከሚጠፋባቸው የሌት ህልመኞች ሳይሆን ቀኑን ሙሉ ከሚያልሙት፣ ከሚታገሉለት ብርቱዎች ጎራ ተቀላቀል።
መልካም የተቀደሰ ቀን ይሁንላችሁ🙏
ሲስ የስራ ሰው!!
