en
Feedback
Ethio University Teams

Ethio University Teams

Open in Telegram

Remedial 2015 ቻናል በ ዩኒቨርሲቲ ሲኒየር ተማሪዎች የተቋቋመ ሲሆን ለመጀመሪያ አመት የዩኒቨርሲቲ /እጩ/ ተማሪዎች ለ ግቢ ህይወታቸውን አስፈላጊውን ሁሉ ያቀርባል። እንድሁም 2016 ለምትገቡ remedial & freshman ተማሪዎች የሚጠቅም ነው። 2015 ከተማሩ ተማሪዎች ለ2016 ለሚገቡ remedial አስፈላጊውን መረጃ ሰለ ትምህርት አሰጣጥ ስለ ግቢ life ያስተምራል ::

Show more
1 209
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2930 days
Posts Archive
#AASTU በ2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በአካል ቀርባችሁ ሪፖርት የምታደርጉበት ቀን 👉 ህዳር 23፣ 2016
#AASTU በ2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በአካል ቀርባችሁ ሪፖርት የምታደርጉበት ቀን 👉 ህዳር 23፣ 2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በአካል በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን አቅርቧል፡፡ የዩንቨርስቲውን አብይ መርሀ ግብር ከላይ  በተመለከተው ሰንጠረዥ ይመልከቱ ‼️ ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#ArsiUniversity አርሲ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ምዝገባ ታ
#ArsiUniversity አርሲ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ምዝገባ ታህሳስ 04 እና 05/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ስድስት 3×4 ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ። የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች በቦቆጂ ካምፓስ ፤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በአሰላ ከተማ ዋናው ግቢ ሪፖርት እንድታደርጉ ተብላል፡፡ ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#WerabeUniversity ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ትምህርት ዘመን አዲስ የተመደባችሁ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 24 እና 25/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋ
+1
#WerabeUniversity ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ትምህርት ዘመን አዲስ የተመደባችሁ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 24 እና 25/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ በ2015 ዓ.ም በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ በተመሳሳይ ህዳር 24 እና 25/ 2016 ዓ.ም መሆኑም ተገልጿል። የአንደኛ ዓመት 1ኛ ሴሚስተር መማር ማስተማር ሒደት ህዳር 26/2016 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል፡፡ በተለየያ ምክንያት የአንደኛ ዓመት 1ኛ ሴሚስተር ሳትጨርሱ ዊዝድሮ ያደረጋችሁ እንዲሁም በውጤት ምክንያት የመልሶ ቅበላ ሞልታቹ ትምህርት ያቋረጣቹ ተማሪዎች ህዳር 27/2016 ዓ.ም ሪፖርት ማድረግ ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ እንዲሁም የለሊት አልባሳት (አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ) እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይጠበቅባችኋል። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#DillaUniversity በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በዲላ ዩ
#DillaUniversity በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 28 እና 29/ 2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። በተጠቀሱት ቀናት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ ያኣ ግቢ ሬጂስትራር ጽ/ቤት በመገኘት ምዝገባ አድርጉ ተብሏል። ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት 3×4 ፎቶግራፍ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል

#MekelleUniversity በ2016 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ለተመደባቹህ አዲስ ተማሪዎች ከህዳር 28-30/2016ዓ.ም ባለው ጊዜ ሪፖርት እንድታደርጉ ዩንቨርሲቲው አሳውቋል። 💥የምዝገባ ቦታ ፨
#MekelleUniversity በ2016 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ለተመደባቹህ አዲስ ተማሪዎች ከህዳር 28-30/2016ዓ.ም ባለው ጊዜ ሪፖርት እንድታደርጉ ዩንቨርሲቲው አሳውቋል። 💥የምዝገባ ቦታ ፨ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በዓዲ ሐቂ ግቢ ፨ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ 👉ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ስትመጡ መያዝ የሚጠበቅባችሁን ነገራት ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ‼️ ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#haramayaUniversity ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በመደበኛ
#haramayaUniversity ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በመደበኛ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትለው የማለፊያ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ጥሪ አድርጎል። የተጠቀሱት ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከህዳር  ታህሳስ 5-7/2016 ዓ.ም መሆኑን  ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

የሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ። የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል። ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የRemedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 255 ያመጡ ☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 234 ያመጡ ☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 218 ያመጡ ☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 200 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 224 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 192 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ ☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል። መረጃውን ትምህርት ሚኒስቴርን ዋቢ በማድረግ ያሰራጨው ኤፍ ቢ ሲ ነው። ለ12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇 https://t.me/+aNlMj5bWezE4ZThk ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

#የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለምትከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገልጻለን። Website:  https://result.ethernet.edu.et/ Telegram bot: @moestudentbot

እስካሁን ውጤት ያላያችሁ በዚ በፍጥነት ይሰራል ሞክሩት 👇👇 Eaes.gov.educ.et https://t.me/+K1OweXot5etiMWFk https://t.me/+K1OweXot5etiMWFk https://t.me/+K1OweXot5etiMWFk

ውጤት ለማየት የምትፈልጉ 👇👇👇👇 join as አፍጥኑት https://t.me/+K1OweXot5etiMWFk

ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ? የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ነገ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።
ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ? የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ነገ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ። በዌብ ሳይት 👉 https://eaes.edu.et/ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት 👉 6284 በቴሌግራም 👉 https://t.me/eaesbot [Tikvah ethiopia] ከዚህ ውጪ ስለማይኖር በሀሰት ወሬ እንዳትረበሹ እንገልፃለን !

#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ
#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ ነው ያገኙት። ከ845 ሺህ ፤ 422,500 ሺህ ተማሪ ከ26 በታች ነው ያገኘው። እንደው ዝም ብሎ አንድ ተማሪ ፈተናውን በግምት ቢሞላ እንኳን ሊያገኘው የሚችለው ውጤት ነው። ለዚህ ነው ከታች ጀምሮ በደንብ አጥርተን መስራት አለብን የምንለው። " ስለ 2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ቁጥሮች ምን ይላሉ ? - በ2015 የተፈተኑ ተማሪዎች ብዛት 845,099 ፤ 50 በመቶና በላይ ያመጡ 27,267 ተማሪዎች (3.2%) ብቻ ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ፦ • ከተፈጥሮ ሳይንስ ያለፉ 19,017 ተማሪዎች • ከማህበራዊ ሳይንስ ያለፉ 8,250 ተማሪዎች - በማታ የተፈተኑ 16,541 ያለፉ 12 ተማሪዎች ብቻ - በግል የተፈተኑ 169,502 ያለፉ 498 ተማሪዎች ብቻ - በመደበኛ የተፈተኑ 659,056 ያለፉ 26,757 ተማሪዎች ብቻ - የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ት/ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች #አንድም_ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም / ምንም ተማሪ አላሳለፉም። - በሀገሪቱ ካሉትና የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑት ትምህርት ቤቶች 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም እንኳን ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም። - 27 ሺህ 267 ተማሪዎች በቀጥታ ፍሬሽ ማን ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 160 ሺህ ገደማ ተማሪ በሬሜዲያል ይገባሉ።

🟥GRADE 12 RESULT ✅በአጠቃላይ በ2015 ከተፈተኑ ተማሪዎች ውስጥ 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡት። ከአምናው የተሻለ የፈተና ህግ የማክበር ነገር ዘንድሮ ተስተውሎል 🟥በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለፈተና ከተቀመጡ በድምሩ 845,677 ተማሪዎች 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 31, 224 ተማሪዎች ብቻ ናቸው፡፡ በዚህም 160 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን በሬሜዲያል ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚቀበሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡ ✅አምና 13600 ተማሪዎች  ፈተና አቋርጠው  የውጡ ሲሆን ዘንድሮ  ምንም  ተማሪ  አላቋርጠም በአማካኝ 28.65 ከ መቶ  በአንድ ተማሪ ✅በተፈጥሮ  ሳይንስ 29.8 % በማህበራዊ  ሳይንስ  27% ✅በግል ፈተና የወሰዱ  160ሺህ በላይ ተፈታኞች  14ሺህ በኢትዮጵያ  ከፍተኛው  649 በተፈጥሮ  ሳይንስ   ሴት ከክሩዝ ትምህርት  ቤት ✅ከማህበራዊ  ሳይንስ  533    ከደብረ ማርቆስ አዳሪ ትምህርት  ቤት ✅ከ600 በላይ ያመጡ  205   ተማሪዎች ከተፈጥሮ  ሳይንስ  ✅ከማህበራዊ  ሳይንስ  15 ተማሪዎች  ከ500በላይ ከ600 ✅ከ50% በላይ ተማሪዎች  ከ 26% በታች አምጥቷል  በጣም  አስድጋጭ ነው። ✅በዘንድሮ አመትም Remedial እንደሚደገም አስከትለው ተናግረዋል ። ✅ዘንድሮ 1328 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም ✅ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 16,451 የማታ ተማሪዎች መካከል፤ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡት 12ቱ ብቻ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ✅5ት ትምህርት ቤቶች ብቻ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ አሳልፈዋል👌 ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦ 1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት 2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት 3. ባህርዳር ስቴም ትምህርት ት 4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን) 5. ልጅ ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ) 6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (አዳማ) 7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ 8. የኔታ አካዳሚ 9. ወላይታሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት 10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት 🛑❇️🛑 ውጤት በምን ይታያል ? ❇️❗️❇️❗️" ነገ ጥዋት 12 ሰዓት ላይ በዌብሳይት እና በSMS ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይቻላሉ። "    ❇️    ፕሮፌሰር  ብርሀኑ ነጋ     ❇️      https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#ሙሉ_መግለጫ የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የሰጠው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጥዋት 12 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ። ቲ
+5
#ሙሉ_መግለጫ የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የሰጠው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጥዋት 12 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተከታትሎ መረጃዎችን ያደርሳል። More - @tikvahethiopia

5:30 ሳይሆን መግለጫው 6:00 ነው ። እየጠበቅን እንገኛለን 👏👏🙏🙏 የ 12ኛ ክፍል ውጤትን አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ 6:00 ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል። Share Share አድርጉ 5:30 ሳይሆን መግለጫው 6:00 ነው ። እየጠበቅን እንገኛለን 👏👏🙏🙏 የ 12ኛ ክፍል ውጤትን አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ 6:00 ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል። ✅✅Share Share አድርጉ✅✅ የፈተናው ውጤት መች አንደሚገለፅና ሌሎች ተያያዥ መግለጫዎችን አየጠበቅን እንገኛለን፤ መግለጫዉ እንደተገለፀ እዚዉ ቻናል ላይ በፍጥነት ምናሳዉቃችሁ ይሆናል። ተማሪዎች በትእግስት ጠብቁ! የፈተናው ውጤት መች አንደሚገለፅና ሌሎች ተያያዥ መግለጫዎችን አየጠበቅን እንገኛለን፤ መግለጫዉ እንደተገለፀ እዚዉ ቻናል ላይ በፍጥነት ምናሳዉቃችሁ ይሆናል። ተማሪዎች በትእግስት ጠብቁ!

የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል። .............................................................................. መስከረም 27/2016 ዓ/ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ይሆናል። ተማሪዎችም ትክክለኛውን መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ገፆች ላይ እንድትከታተሉ እናሳውቃለን።

Remedial Exam Schedule❗️
Remedial Exam Schedule❗️

#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ፤ ከመስረም 7 እስ
+1
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ፤ ከመስረም 7 እስከ 11 ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል። መስከረም 14 የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል። በተመሳሳይ በዛው ዕለት የሬድዮ እና የቴሌቪዥን ትምህርት ስርጭት ይጀምራል። የ1ኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ከጥር 27 እስከ የካቲት 1 እንደሚሰጥ የሚያሳየው የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር ከየካቲት 4 እስከ 8 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው የተማሪዎች ፈተና የሚታረምበት ውጤት የሚጠናቀርበትና የሚገለፅበት ወቅት እንደሆነ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር እንደሚያሳየው የካቲት 18 የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከግንቦት 12 እስከ ግንቦት 23 የአጠቃላይ የትምህርት ማጠቃለያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና ይሰጣል። ከግንቦት 26 እስከ 30 የ6ኛ ክፍል አንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 3 እስከ 7 የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ የማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ጊዜ እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል። የሁለተኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ወቅትም ከሰኔ 17 እስከ 21 ሲሆን ከሰኔ 24 - 28 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው ፈተና የማረም፣ ውጤር የሚጠናቀርበት ፣ እና የሚገለፅበት እንደሚሆን ካሌንደሩ ያሳያል። ሰኔ 30 ወላጆች እና የትምህርት ማህበረሰቡ በተገኙበት የአመቱ ትምህርት ማጠናቀቂያ ይሆናል። * * * ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ እንደሚደረግ ማሳስቢያ ሰጥቷል።    

photo content

#Update #MOE የሬሜዲያል ተማሪዎች ፈተና ከመስከረም 07 እስከ 10/2016 ዓ.ም ይሰጣል። የሬሜዲያል/ማካካሻ ትምህርታቸውን አጠናቀው ከሰኔ 26 እስከ 30/2015 ዓ.ም የተሰጠውን የማዕከል ፈተና ላልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናው እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም ፈተናው በ30 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም 07 እስከ 10/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሏል። ከማዕከል የሚሰጠው ፈተና በወረቀት እንደሚሰጥም ተገልጿል። https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13