en
Feedback
Ethio University Teams

Ethio University Teams

Open in Telegram

Remedial 2015 ቻናል በ ዩኒቨርሲቲ ሲኒየር ተማሪዎች የተቋቋመ ሲሆን ለመጀመሪያ አመት የዩኒቨርሲቲ /እጩ/ ተማሪዎች ለ ግቢ ህይወታቸውን አስፈላጊውን ሁሉ ያቀርባል። እንድሁም 2016 ለምትገቡ remedial & freshman ተማሪዎች የሚጠቅም ነው። 2015 ከተማሩ ተማሪዎች ለ2016 ለሚገቡ remedial አስፈላጊውን መረጃ ሰለ ትምህርት አሰጣጥ ስለ ግቢ life ያስተምራል ::

Show more
1 209
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2930 days
Posts Archive
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዓመት እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡ በዚህም የነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2016 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ጥ
+1
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዓመት እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡ በዚህም የነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2016 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ጥር 2 እና 3/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ለአንደኛ ዓመት እና ለሪሚዲያል ተማሪዎች ጥሪ እሰከሚደረግ በትዕግስት እንዲጠብቁ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡ ከላይ የተያያዘው የተቋሙ ጥሪ ትክክለኛ መሆኑን ቲክቫህ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አረጋግጧል፡፡ ጥሪው ታህሳስ 25 እና 26/2016 ዓ.ም ምሽት በብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሚተላለፍ መሆኑንም ሰምተናል፡፡

#BDU ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሲጀመር ተማሪዎች ኃላፊነት ለመውሰድም ይዘጋጁ ብሏል። በአማራ ክልል የሚገኙ 10 የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት 2 ሳምንታት መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል። የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድ ፖስት፣ የፀጥታ አደረጃጀቶች፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ፀጥታ አካላት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ ቆይቶ የውይይቶቹ የመጨረሻው ክፍል ሐሙስ ከተደረገ በኃላ ነው ውሳኔው የተላለፈው። የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ምን አሉ ? - ከመስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተን የነበረ ቢሆንም፣ በክልሉ የፀጥታ ሁኔታ ሳቢያ ተሰናክሏል። - በእኛ በኩል የዝግጅት ክፍተት የለብንም። - በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቁጥጥር ሥር የሆነ የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆነም የፀጥታ ሁኔታ አለ። ከእኛ ውጪ በሆነው ጉዳይ ላይ ምንም ማድረግ አንችልም። ምንም ማድረግ ባልቻልንበት ሁኔታ የሰው ልጅ ጠርቼ አንድ መጥፎ ነገር ቢከሰት ምንድነው የምለው ? የሚለውን ተማሪዎችም፣ ወላጅንም ታሳቢ አድርገን ተማምነን ይቆይ የሚል አቋም ስለነበረን በዚህ ምክንያት ነው እስካሁን ቀስ እያልን የመጣነው። - የመማር ማስተማሩ እንዲጀመር በነበረው ውይይት ሒደት አቅደን የነበረው ተመራቂ ተማሪዎችን ወደ የትምህርት ግቢያቸው ማስገባት ነበር። - እስካሁን ባለን ልምድ ግጭቶች እዚህም እዚያም ሊቀሰቀሱ ይችላሉ። ቀጣይነታቸው ግን ብዙም አይደለም። አንድ ቀን ወይ ሁለት ቀን መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል ከዚያ ግን ያበቃል። - ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ተጠርተው ሲመጡ ታሳቢ ማድረግ ያለባቸው ጉዳዮች አሉ ፤ ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሊያጋጥሙ የሚችሉ ዕክሎችን ከግምት በማስገባት ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው። - ተማሪውም፣ ወላጅም፣ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብም እንደ አገር የሚመለከታቸውም አንድ ላይ ሆነን መደበኛ ትምህርት መጀመር አለብን ብለን ወስነናል። - የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተቋማቸው ከልደት (ገና) በዓል በኋላ ባሉት ቀናት ለተማሪዎቹ ጥሪ ያደርጋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ መሆኑን ያሳውቃል። https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች  በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር ብሏል ሚኒስቴሩ። በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተገልጿል። " የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም  በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። በዚህም መሰረት  ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል። በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል። https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

የመፍትሄ ያለህ . . . " መፍትሄ የሚባል ነገር ሳይሰጠን የትምህርት ዓመቱ 5ኛው ወር ሊገባ ነው " - ተማሪዎች በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች á‹­áˆ›áˆŠ የነበሩ ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ወደ ሚማሩበት ዩኒቨርሲቲዎች አልተጠሩም። ተማሪዎቹ መቼ እንደሚጠሩ አያውቁም ፤ መፍትሄም አልተሰጣቸውም። ስለተማሪዎቹ ጉዳይ መፍትሄው ይሄ ነው ሳይባል የትምህርት ዘመኑ 5ኛ ወር ሊገባ ተቃርቧል። ተማሪዎቹ ቤት ከዋሉ ወራት አልፈዋል። ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ላይ የሚገኙ ሲሆን የነሱ እኩዮች የትምህርት ዓመቱን አጋማሽ ለማጠናቀቅ ቀርበዋል። ተማሪዎቹ እስካሁን ወደ ሚዲያ ወጥቶ መፍትሄ የሚናገር አካል ባለማግኘታቸው " በዚህ ዓመት ላንማር እንችላለን " የሚል ስጋት አድሮባቸዋል። እነዚህ ተማሪዎች  ፤ በቅድሚያ በኮሮና ቫይረስ ተፅዕኖ፣ በኃላም በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ይፈጠሩ በነበሩ የፀጥታ ችግሮችና አሁን ደግሞ በአማራ ክልል ባለው ወቅታዊ የሰላም መደፍረስ ምክንያት ትምህርታቸውን ባግባቡ መማር አልቻሉም። ተማሪዎቹ በእነሱ ጉዳይ ተገቢ መረጃ የሚሰጥ አካል እንደሌለ ይናገራሉ። በራሳቸው መንገድ እየደወሉ ይመለከታቸዋል የሚባሉ አካላት ሲጠይቁ " ምንም አናውቅም " ይሏቸዋል። አንዳንዶች ስልክ አያነሱም፣ አጭር የፅሁፍ መልዕክትም አይመልሱም ፤ ተስፋ የሚሰጥ ነገርም አይናገሩም ሲሉ ይወቅሳሉ። ተማሪዎቹ የዚህ ጊዜ " ባች " ከአንደኛ ዓመት ጀምሮ ብዙ ተግዳሮቶችን እየተጋፈጠ የመጣ " ባች " ነው ብለዋል። * በኮሮና ምክንያት ብዙ ጊዜ ግቢ ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል። * በተለያዩ አለመረጋጋቶች የትምህርት ክፍለጊዜዎች እየተጓተቱ፣ እየተቆራረጡ፣ አንድ ወሰነ ትምህርት በ45 ቀናት እየተማሩ ነው የመጡት። * ብዙ የትምህርት ክፍሎች አልተሸፈኑም፣ እነዚህ ደግሞ የመውጫ ፈተና አካል ናቸው ተማሯቸውም አልተማሯቸውም " ተምረዋቸዋል "ተብሎ ነው የሚታሰበው። * የተማሯቸው የትምህርት ክፍሎች እንኳ በበቂ አልተማሯቸውም። * የመውጫ ፈተና ላይ እንዴት ልንሆን ነው የሚልም ሃሳብ አለባቸው። አሁን ወደ ዩኒቨርሲቲ ቢገቡ ያልተሸፈነው ትምህርት እንዴት መሸፈን እንዳለባቸው ሲያስቡ ተማሪዎቹ ካሁኑ ጭንቅ ውስጥ እንደገቡ አስረድተዋል። ተማሪዎቹ ያለትምህርት ረጅም ጊዜ ቤት መቀመጣቸው ለከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና እንደዳረጋቸውም ገልጸዋል። ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ፤ ትምህርት ሚኒስቴር ድረስ ተማሪዎች ተወክለው á‰˘áŒ á‹­á‰áˆ ፤ ብዙ አጥጋቢ ምላሽ እንዳላገኙ አመልክተዋል። በተለይም የጤና ተማሪዎች ፤ ትምህርታቸው ተጨማሪ ኮርሶች ያሉት የትምህርት መስክ በመሆኑ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ትምህርቱ ካልተሰጠ አስቸጋሪ እንደሆነ አስገንዝበዋል። ምናልባት ጊዜ ካለፈ በኋላ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ በይድረስ ይድረስ ትምህርቱ የሚሰጥ ከሆነ ተማሪው በቂ እውቀት ይዞ አይወጣም ብለዋል። በመጨረሻም ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቷቸው መፍትሄ የሚለውን ነገር በይፋ እንዲያሳውቃቸው ጥሪ አቅርበዋል። ሁኔታው ተስፋ እንዳስቆረጣቸውም አስገንዝበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎችን ቃል የወሰደው ከዶቼ ቨለ ሬድዮ እንዲሁም በውስጥ ከመጡ መልዕክቶች ሲሆን ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ በእነዚህ ተማሪዎች ጉዳይ መሰል መልዕክት ማጋራታችን ይታወሳል። የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ብዙ ጥረት ብናደርግም ይህ ነው ተብሎ ለተማሪና ወላጅ የሚነገር ምላሽ አላገኘንም:: https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

ውድ ተማሪዎች እንዴት ናቹ? በቅድሚያ በጨዋነትና በተረጋጋ መንፈስ እስከዚች ቀን ስለታገሳቹ በጣም እናመሰግናለን። ከተማረ ሰው የሚጠበቀውን አድርጋችዋል። እኛ በ10 ዩኒቨርሲቲ የምንገኝ ተማሪዎችን በመወከል የጋራ የሆነውን አሳሳቢ ጉዳይ ከእናንተ አደራ ተቀብለን ባለፉት ሁለት ቀናት ወደ ትምህርት ሚኒስትር መሄዳችን ይታወቃል። የመጀመርያው ቀን፡  እኛ ላይ እየተፈጠረ ያለውን ጫና ሁሉ የሚያስረዳና የመፍትሄ ሀሳብ የያዘ ደብዳቤ ለትምህርት ሚኒስተር ገቢ ለማድረግ ነበር። ታድያ ይህን ደብዳቤ ገቢ አድርገን ተመለስን፤በሁለተኛው ቀን ደብዳቤው ወደ ሚመለከተው አካል እንደተመራና ጉዳያችንን በዝርዝር ለማስረዳት በድጋሜ ተመለስን። እንደተባለው ደብዳቤው ተመራልን። ነገር ግን ቅሬታውን በዝርዝር ብናስረዳም ከሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ማውራት ስለነበረባቸው ይህ ነው የሚል መልስ በወቅቱ አላገኘንም።ለሶስት ተከታታይ ቀናት በጅግጅጋ ላይ አጠቃላይ በትምሆርት ጉዳይ ስብሰባ ስለሚኖር የእናንተም መልእክት(ደብዳቤ) እዛ ላይ እንደ አንድ አጀንዳ ይቀርባል ተብለን ነው የተመለስነው። ስብሰባው ቃለቀ በሁለተኛው ቀን ማለትም ትላንት (21/03/2016 ዓ ም) በቀጠሮአችን መሠረት  ሁሉም በጉጉት ሲጠብቅ የነበረውን የስብሰባውን ውጤት ለመስማት ወደ ትምህርት ሚኒስትር አቀናን። እናም ጥያቄአችንን መጠየቅ ጀመርን ጉዳዩን የያዙት ዶክተር ሶሎሞን(የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ሾል አስፈጻሚ) የሰጡን ምላሽ እንደሚከተው ነው፡ በስብሰባው ላይ የእናንተም ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ ቀርቧል እናም ብዙ ውይይት ተደርጎበታል።የተደረሰበት ነገር ደግሞ ለተማሪዎች ጥበቃ ተደርጎላቸው ወደ ትምህርት ገበታቸው መመለሾ አለባቸው የሚል ነበር ታድያ ይህ እንዴት ይሆናል? በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች አሁን ላይ አንጻራዊ ሰላምና የአቅርቦት ችግር የሌለባቸው ተማሪዎቻቸውን ጠርተው ማስተማር ይችላሉ ተማሪዎቹ ጊቢ ገብተው ያለምንም ስጋት እንዲማሩ አስተማማኝ ጥበቃ ይደረግላቸኋል፤ አስቸጋሪው ነገር ለተማሪዎች አቅርቦት የሚመላለስበት መንገድ በየጊዜው ተለዋዋች ነገር በመሆኑ ትኒሽ ሊፈትን እንደሚችል ነው የተነሳው ዋናው ጉዳይ ተማሪዎች እንዴት ወደ ጊቢ ይገባሉ መንገዱስ የሚል ነገር ነበር እሱን ከጸትታ ሀይል ጋር በመሆን የሚሰራበት ይሆናል ነው የተባለው።  በብዞቻችን ላይ ጥያቄ ሲፈጥር የነበረው ነገር ለምን በትምህርት ሚኒስትር በኩል ለም  አያሳውቁንም??? የሚል ነበር እኛም እሱን የጠየቅን ሲሆን የተሰጠን ምላሽ እርሱ የዩኒቨርስቲዎች ዝግጅት ነው የሚወስነው ዩኒቨርስቲው እንችላለን በሁሉ ዝግጁ ነን ካሉ መጥራት ይችላሉ። አሁን እንዲ ተወስኗል የሚል መልዕክት ቢወጣ የሰላሙ ሁኔታ ሙሉበሙሉ አስተማማኝ ስላልሆነ እና ምን ሊፈጠር እንደሚችል ስለማይታወቅ ይህን ማለት አስፈላጊ አይደለም ስለዚህ ጊቢዎች በተዘጋጁበት ልክ ተማሪዎቻቸውን በቅርብ ቀናት መጥራት ይጀምራሉ እንደ ዝግጅታቸው ሁሉንም ተማሪ ሊጠሩ ይችላሉ ካልሆ በየደረጃው ያደርጉታል።ይህ ነው የተሰጠን መልስ ማታ በተሰጠው ነገር ላይ ብዞቻቹ ጥያቄ ስታነሱ ስለነበረ ነው ይህን ዝርዝር ጉዳይ ያዘጋጀነው።ካንዳንድ ሌላ አላማ ያላቸው ወዳልተገባ ድርጊት ተማሪን ከሚገፋፉ ልጆች ውጪ ስጋታቹም ጥያቄአቹም ትክክለኛ ነው። ቅርብ ቀን መቼ ነው ለሚለው እኛም ለዶ/ር ሶሎሞን አንስተናል እርሱን የሚወስነው ዩኒቨርስቲው ነው ብሎናል ስለዚህ እኛ ከዚህ በኋላ ዩኒቨርስቲዎቻችንን ነው መጠየቅ ያለብን። ይህም የሚሆነው እኛም ከዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ህብረትና የተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር የጊቢዎችን እንቅስቃሴ የምናሳውቅ ይሆናል። በተጨማሪም ይህ ተባለ ማለት እኛ ጩኸታችንን አቆምን ማለት አይደለም አቅጣቻንን እያየን እንቀጥላለን በቅርቡም መልካም ነገር እንደሚመጣ በመመኘት የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን ሁሉም ወደ ትምህርት ገበታው እስኪመለስ እንቅልፍ አንተኛም። በያላቹበት መልካም ቀን!!                    እናመሰግናለን❤❤ በውስጥ መሾመር የተላከልን ነው። For remedial and freshman student 👇👇Share share share👇👇 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#ArbaMinchUniversity የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች መግቢያ ጥሪ 💥ማስታወቂያ በ2015 የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት በማምጣት በ2016 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች እና በ2015 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች መግቢያ 👉እሁድ ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም፣ የአቀባበልና የጋራ መግለጫ የሚሰጠው ሰኞ ታኅሣሥ 1 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ምዝገባ ማክሰኞ ታኅሣሥ 2 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመረው ረቡዕ ታኅሣሥ 3 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡ 💥ስለሆነም ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡- 📌የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣  📌ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣  📌የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣  📌የፓስፖርት መጠን (Passport Size) የሆኑ ሁለት ጉርድ ፎቶግራፎች እና  📌አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይጠበቅባቹሃል። 💥ሁሉም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ዓባያ ካምፓስ፣ 💥የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የስም ዝርዝራችሁ ከፍደል ተራ “A” እስከ “S” የሚጀምሩ በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው በጫሞ ካምፓስ እና የስም ዝርዝራችሁ ከፍደል ተራ “T” እስከ “Z” የሚጀምሩ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው በሳውላ ካምፓስ በአካል  ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን፡፡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

" መፍትሄ ሳይሰጠን የዓመቱ አራተኛ ወር ሊገባ ነው " - ተማሪዎች በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እስካሁን ለተማሪዎቻቸው ጥሪ አላደረጉም። ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ያልጠሩት በክልሉ ባለው ተለዋዋጭ የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። በክልሉ በሚገኙት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ጊዜው ሳይሄድ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጥሪ ቢያቀርቡም እስካሁን መፍትሄ የሚሰጥ ቀርቶ ጉዳዩን አንስቶ በግልፅ ማብራሪያ የሚሰጥ አካል እንዳጡ ተናግረዋል። በአማራ ክልል በሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች የሚማሩት ተማሪዎች " ያለ ትምህርት ቁጭ ብለን ወራት አልፈዋል ፤ ፍትህ እንሻለን " ብለዋል። መፍትሄ ሳይሰጣቸው የአመቱ አራተኛ ወር መዳረሱን ገልጸዋል። " ስለእኛ ጉዳይ ጀርባ ተሰጥቷል " ያሉት ተማሪዎቹ " ከትምህርት ገበታችን ከራቅን 5ኛ ወራችን ላይ እንገኛለን " እስካሁን ከሚመለከትው አካል የተሰጠ ቁርጥ ውሳኔ የለም ይህ ደግሞ ተማሪዉን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ የስነ ልቦና ጫናና ጭንቀት እንዲገባ እያደረገውን ነው " ሲሉ አስረድተዋል። " ህልም አለን ተስፋችንን አታጨልሙብን ትምህርታችንን እንደ እኩዮቻችን የምንከታተልበት መንገድ ፈልጉልን " ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት ተማሪዎቹ " በእነሱ የትምህርት ጉዳይ ምክንያት ወላጅም እየተጨነቀ መሆኑን አስረድተዋል። ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ አንዳንድ ወላጆች በበኩላቸው ምንም እንኳን የአማራ ክልል ሁኔታ እና ህዝቡ በፀጥታ ችግር እያሳለፈ ያለውን አሰቸጋሪ ሁኔታ ቢረዱም ልጆቻቸው ያለ ትምህርት መቀመጣቸው ከምንም በላይ ቀጣይ መፍትሄ አለመታወቁ እንደሚያስጨንቃቸው ገልጸዋል። ቢያንስ በጉዳዩ ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ወጥቶ መስጠት አለበት ፤ መፍትሄ ካለውም ማሳወቅ ይገባዋል ፤ ልጆቻችን የሀገር ተረካቢዎች  በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የነበረው ዕጣ ፋንታ እንዲደርሳቸው አንፈልግም ብለዋል። ሌሎች ወላጆች በበኩላቸው ከምንም በፊት " ሰላም እና ደህንነት ይቀድማል ሰላም በሌለበት ሰው በየቀኑ በሚሞትበት ፣ ዛሬም ነገም የግጭት ስጋት ባለበት ሁኔታ ትምህርት ማማር አይደለም ፤ ለደቂቃ ቁጭ ብሎ ማሰብ አይቻልም ፤ ስለሆነም የሰላሙ ሁኔታ እስካልተረጋገጠና ለልጆች ደህንነት ሙሉ ዋስትና እስከሌለ ጥሪ ቢደረግ እንኳን አንልካቸውም " ብለዋል። ከምንም በፊት የሚቀድመው ለተከታታይ አመታት በጦርነትና ግጭት ውስጥ እያለፈ የሚገኘው የአማራ ህዝብ ሰላሙን አግኝቶች እፎይ እንዲል ጥሪ ማድረግና ድምፅ ማሰማት ነው ብለዋል። ምን አይነት መፍትሄ አለው ? ለሚለው ጥያቄችንም ጦርነት እና ግጭት በዘለቄታዊ መንገድ በንግግር ተፈቶ በቅድሚያ ህዝቡ ሰላም እንዲያደገኝ እንዲደረግ ፤ ሰላም ከተረጋገጠ በኃላ ተማሪዎችን መጥራት ፤ እስከዚያው ግን አመቱ እንዳይገፋ በሌሎች ተቋማት ገብተው እንዲማሩ ቢደረግ ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎችን እና የወላጆችን ቅሬታ አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማነጋገር ሰፊ ጥረት የሚያደርግ ይሆናል። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#UPDATE 📢 የካንፓስ የመጀመርያ አመት ቆይታ ......በትንሹ ❓ 📚 ፍሬሽማን መሆን እንደእናንተ ስብዕና ይወሰናል ። የተለያየ ሰው የተለያየ experience ነው ያለው ። ግን ብዙዎች ጋር የሚኖረውን የፍሬሾች የጋራ ኑሮ ቆንፅለን ለማየት እንጥራለን ...! 💡 ናፍቆት .....! 📚 አንዳንድ ከቤታቸው ሱቅ ለመላክ ካልሆነ ወጥተው የማያቁ ልጆች ድንገት ከቤተሰብ ሲርቁ ምናምን አይችሉም ይነፋረቃሉ ...ከሰው ጋር የማይግባቡ ዝጋታም ልጆች ስላሉ እነሱም ... ለብቸኝነት ሲጋለጡ ሊከብዳቸው ይችላል ። አንድ ነገር እወቁ ከምትወዷቸው ሰዎች መለየት ይሄ የመጀመርያቹ ሊሆን ይችላል ግን ብርቅ አይደለም ...አቅፎ የሚያስተዛዝን ፤ ህመምን የሚጋራ ደስታን የሚካፈል ጓደኛ ቤተሰብ ወዳጅ መለየት በጣም ከባድ ነገር ነው ። ግን ቻሉት በህይወታችሁ ነፍ ግዜ ከምትወዷቸው የህይወት አጋጣሚ ይለያቹሃል ። ካንፓስም የምታገኟቸው ልጆች ከአመታት ውብ የጓደኝነት ቆይታ በኃላ ትለያያላችሁ ። ናፍቆት ያለ ነው ግን መቻል ነው ። በካንፓስ ጥሩ ጓደኛ ያዙ ...እስክትለምዱት ነው ። ከዛ ይለቃቹሃል ። 💡 ምግብ ....! 📚 እንደ እናትህ ውይ ልጄ ተነስ ቁርስ ብላ ና ትተኛለህ  አቡኪያዬ ...ምናምን የለም በጠዋት ተነስተህ ሰልፍ ካልወጣህ ሲሞረሙር ይውላል ካፌ ሊያልቅም ይችላል ....ሻይ በዳቦ ለመብላት ይሄ ያክል ሰልፍ ልትልም ትችላለህ ግን በመክሰስ ሰዓት 12 ስለሆነ ራት የሚገረሰው ችከላ ካደርክ ይሞረሙራል...ዳቦ ልሹ ስንት ጣዕሙ ..ከረሃብ ይሻላል ። ሩዝ ፤ ፍርፍር ...ስላለ አትቸጋገር ....ግን ጥሩ ነገር መብላት የለመደ ሰው....ወይኔ ግቢው ጥሩ ባልቴት  የሌለው ይመስል ..ጥቅል ጎመን ብለው ቀጭን ሾርባ ጎመን ጣል ጣል ያለበት ሊያቀርቡ ይችላሉ ...ታዲያ አሪፍ ነገር የለመደ አይችልም 500 ብር አከባቢ ይገጨውና ውጪ ይበላል .... ምግቡ እንደ ካንፓሱ ነው  በተለይ በቅርቡ የተከፈቱ አርሲ ፤ ቦንጋ ምናምን ምንም አይልም ባህርዳርም አሪፍ ነው ። ሃሮማያማ በሳምንት አራቴ ነው ስጋ የምትግጡት ...ብቻ ብዙ ልጆች የጣፈጠ ነገር ለምደው እነደ ነገሩ የሚሰራው ምግብ አይጥማቸውም ። 💡 ጓደኛ መረጣ ...! "ጓደኛ መረጣ ላይ መጠንቀቅ አለባችሁ ። በጣም መጥፎ ሰዎችም ጥሩ ልጆችም ይኖራሉ ። ከሱሰኛ ፤ ጨባሽ ፤ ዘረኛ ..ራቁ..በቢሊዮን ማይል ራቁ ...ከእናንተ ጋር የሚሄድ ሰው ፈልጋችሁ ከዶርም ውስጥ አንድ የልብ ጓደኛ በቂ ነው ። ታዲያ ምንም መጥፍ ባህሪይ ቢኖርባቸው ከዶርም ልጅ አትጣሉ ...ትቸገራላችሁ ተንከባክባችሁ ....ተከባብራችሁ በፍቅር አርጉት ...ጓደኛ ምርጫችሁን ተጠንቀቁ ዝም ብሎ ሲያነብ የሚውል የሚተሽንም ሰው አትጠጉ በቃ አራዳ ሆናችሁ ማንበብ ሲኖርበት የሚያነብ ፈታ ግድ ሲል የሚፍታታ ነገሮች የሚገቡ ምርጥዬ ሰው ፈልጉ ። 💡 ሹሾ.... 📚 በዙ ሰዎች ካንፓስ በጓደኛ ምክንያት ያልሆነ ነገር ውስጥ ይገባሉ ይሄ መሆን የለበትም ...ምንም ቢሆን ሹሾ አለም እንዳትገቡ ...ያለባችሁ ችግር ይበቃል ... አንዳንዴ ግዜ ሊተርፋችሁ የምትሰሩት ታጡም ይሆናል ...ሹሾ ከምትገቡ አንዷን/ዱን ጠብሳቹሁ ተጃጃሉ እሱ ይሻላል ... ጭራሽ ሹሰ ውስጥ ራሳችሁን እንዳታገኙ በርቱ ....! 💡 መወዛገብ ......! 📚 ከጠበቃችሁ በጣም የተለየ ነገር ሊገጥማችሁ ይችላል ....ያኔ ውዝግብግብ የተለመደ ነው ።ተሳስታችሁ የሰው ዶርም ከች ትሉም ይሆናል ።ብዙ ግዜ ልጆች እስኪለምዱ ድረስ እንዳይጠፋባቸው አንዴ ባዮት መንገድ ብቻ ነው የሚጓዙት ....ሌላ አጭር መንገድ ቢኖርም አይሄዱም በረጅመ ይሄዳሉ የፍሬሽ ነገር የተለመደ ነው ። በቃ በየስርቻው ሲዋሰቡ ፤ ትምህርት ብሎ መጥቶ አባቱን በሬ አሽጦ ፤ እናቱን ፆም አሳድሮ እሱ ጫት ቤት ፤ ቅምቀማ ስታዮት (2 or 3 ተማሪ እንዳይመስሏቹሁ ወደ ግማሽ የሚጠጋው ተማሪ  .)...በቃ ላይብረሪው ውስጥ 3 ሰው ብቻ ስታዮ ....ትደነግጣላችሁ ወይኔ ካንፓስ ልትሉም ትችላላችሁ ...!ለምግብ ሰልፍ ስታዮ ..ዋይፋይ ሰዎች ለሊት ሙሉ ሲጠቀሙ ስታዮ....በቃ ትወዛገባላችሁ ...ትምህርት ቤት ያላችሁ መሆኑ ትዝ የሚላችሁ ...የፈተና ሰሞን ነው ላይብረሪ 3 የነበረው ሰው መቀመጫ አጥቶ አንድ ወንበር  ለሁለት ተቀምጦ ስታዮ ...ዶርም አዳር ሲቸከል ስታዮ ይገባቹሃል ። 💡 የአስተማመር አይነት ....!. 📚 እንደ Highschol 40 ደቂቃ ሳይሆን 3 ሰዓት ሙሉ አንድ ሳብጀክት ትዳረቃላችሁ .....እሱም ደህና መመህር ካጋጠማችሁ ነው የሚገባችሁ ።  በቃሉ እየተጀነነ ሲያወራ የሚውል.... ኖት የሚቸከችክ  ...ደብተር ሁላ የሚያርም አለ ። የለመዳችሁት አይነት ...የመማር ማስተማር ሂደት ሲቀየር አትደናገጡ እንደ አየሩ መሆን ነው ። እስከትለምዱት ነው ። 💡 ወሲብ.......! 📚 ወሲብ ከባድ ነገር ነው ። እንኳን እንዲሁ ተለቃችሁ ወትሮም ....የporno ቪዲዮ ይታየዋል ለጉድ በቃ ። ሱሰኞች ካጋጠማችሁማ ዶርም ላይ ...በቃ ላይብረሪ ሁላ ወሲብ ይፈፀማል ......በጣም አስጠሊ ነገር ነው ።  ይሄ አይወራ እዛው እዮት ..... 💡 ሙድ መያዝ .....❗️ 📚 ፍሬሾች ገና ከመግባታችሁ ...የሲኒየሪዎች ነቆራ አይጣል በቃ ምንም ስለማታውቁ ...የማይሆ ነገር ሊነግራቹሁ ይችላል የመመዝገቢ ቦታ ጠይቃችሁ ሽንት ቤት ሊሊሉካችሁ ይችላሉ ። ግን አይደብራችሁ እናንተም በተራቹሁ አየር ስለምትይዙ ....ፈታ በሉበት እስክትለምዱ አየር አታብዙ አትኳትኑ ልጎብኝ እያላችሁ አታካሉ ወሬ ሰብስቡ መጀመርያ ። የመጀመርያ ምግብ ካፌ ማሰታወሻ ፎቶ አንሱት ። 📚 ሁሉንም አውርተን አንጨርሰውም ....በቃ የቀረ ካለ ግቢ ታዮታላችሁ ፥ ብዙ አትጨናነቁ እኛም አለን አዳዲስ ነገር እንነግራቹሃለን ። https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ት
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርት ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ነባር የሪሚዲያል ተማሪዎች የምዝገባ  áŒŠá‹œ ታህሳስ 08 እና 09/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ፦ • የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ • የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመንግሥት ከተመደቡለት ተማሪዎች በተጨማሪ በተወሰኑ የትምህርት መስኮች #የግል_አመልካቾችን ለመቀበል ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል፡፡ አመልካቾች ከዚህ በ
#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በመንግሥት ከተመደቡለት ተማሪዎች በተጨማሪ በተወሰኑ የትምህርት መስኮች #የግል_አመልካቾችን ለመቀበል ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል፡፡ አመልካቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፦ 1.  በ2015 አና 2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ የሚያሟሉ፣ 2.  አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና (UAT) በመውሰድ የሚቀመጥን መቁረጫ ነጥብ የሚያሟሉ፣ 3.  በ2015 ዓ.ም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተምራችሁ ለምታመለክቱ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ፣ 4.  ዩኒቨርሲቲዉ በ12ኛ ብሔራዊ ፈተና ውጤት መሠረት ድልደላ ሲያካሒድ አመልካቾች በመረጡት የትምህርት ፕሮግራም አማራጮች ውስጥ ለመደልደል ውጤታቸው ካላበቃቸው ዩኒቨርሲቲው ወደፊት በሚያደርገው ድልደላ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ተወዳድረው ለመደልደል ፈቃደኛ የሆኑ፣ 5.  ለጤና የትምህርት ዘርፎች ዩኒቨርሲቲው የሚጠይቀውን ተጨማሪ ምዘና ማለፍ የሚችሉ፡፡ የማመልከቻ ቀናት፦ ከህዳር 20 እስከ 26/2016 ዓ.ም የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ፦ ህዳር 28 እና 29/2016 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የትምህርት መስኮችን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፦ http://www.aau.edu.et/blog/admission-of-self-sponsored-students-in-the-regular-undergraduate-program-for-the-2023_24-academic-year/ ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#Updated ✳️COC/ የ ቅድመ ምዘና ፈተና  በ ቀለሜ(@Keleme_2013) Channel የተዘጋጀ።😊 ይህ የ ፈተና አይነት Fresh ተማሪዎች የ freshmanን courseኦችን first semester (Second ላይም አንዳንድ fieldoch ላይ ይሰጣል )ተምረው ከጨረሱ በኋላ ተፈላጊነት ወይም ውድድር በሚበዛባቸው   የትምህርት  መስኮች ማጥናት የሚፈልጉ ተማሪዎች ተወዳድረው ለመግባት የሚፈተኑት  ፈተና ነው። ሁሉም የ Natural ተማሪዎች First Semester የሚወስዱት freshman course ተመሳሳይ ነው Social ሎችም እንዲሁ.... ተማሪዎች first semester ተምረው ከጨረሱ በኋላ ግን  በዚህ ይከፈላሉ  (  የ Debremarkos university ን አሰራር መሰረት በማድረግ)። 🔰Natural 1 Medicine 2 pharmacy 3 other natural science 4 technology ❗️ግልጥ እንዲሆንላችሁ ምስሉን ተመልከቱ። 🔰Social 1Law 2 Other social science ነገር ግን law፣Medicine እና Pharmacy ለ መግባት የሚፈልጉ ተማሪዎች በመጀመሪያ Coc መውሰድ ይጠበቅባቸዋል ። 📚የ Debremarkos university ን አሰራር መሰረት በማድረግ Form አሞላል። Medicine እና Pharmacy ለ መግባት የሚፈልጉ ተማሪዎች እንደየ ምርጫቸው በቅደም ተከተል ይሞላሉ። ይሄም ማለት አንድ ተማሪ በ አንደኝነት Medicine ን ከፈለገ👉🏾 1 Medicine በሁለተኝነት pharmacyን ከፈለገ👉🏾 2 pharmacy......  ነገር ግን አንዱን ብቻ መሙላት መብታችሁ ነው። dmu ላይ ለ pharmacy እና ለ Medicine የምትወስዱት Coc exam ተመሳሳይ ነው። 🔰የመወዳደሪያ መስፈርቶች ➖UEE Result 20% ➖ First Semester GPA 50% ➖ COC 30% በዚህ መሠረት ያመጣችሁት ውጤት ከ 100 ይሰራል።በውጤታችሁም መሠረት  ከተፈተኑት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያመጡ አንደኛ የሞሉት ይጠበቅላቸዋል። ተማሪዎች 1ኛ የሞሉት Field ከሞላ ....ሁለተኛ የሞሉት field Maximum numberሊ reach ካላደረገ ወደ ሁለተኛው ይገባሉ ማለት ነው። ከዚህ ጋር ግን ልብ ማለት ያለብን Universityአችሁ ካለው የ ተሟላ Material ፣Budget አቅም አንጻር የሚፈልገው የተማሪ ብዛት Limit አለው So ምንም እንኳን ከ 100 አሪፍ ውጤት ቢኖራችሁ ተማሪዎች ከበለጧችሁ የማግኝት chanceአችሁ ይጠባል።Plus Affirmative action🥺 ለ ሴቶች እና ለ ታዳጊ ክልሎች 5 point ስለሚጨመርላቸው ወንዶች ላይ ውድድሩ ይከብዳል ። Even 5 point ተጨምሮላቸው እንኳን እናንተ በውጤት ምትበልጧቸው ሴቶች ይገባሉ ።በ moe አሰራር መሠረት ሴቶች በብዛት ጤና ላይ እንዲገቡ ይፈለጋል ....So ሴት ሁናችሁ ትንሽ ከሞከራችሁ Medicine እና pharmacy ለናንተ ነው።😋 ❗️የሁላችሁም ጥያቄ የሚሆነው ከወደቅንስ ምንድን ነው ሚንሆነው? Natural  ከወደቃችሁ ወይ other natural science ወይም Technology እንደናንተ ፍቃድ ትመዘገባላችሁ። social  ወደ Other social science ከዚያ የ Second semester Freshman course ትወስዳላችሁ ።ከ Second በኅላ ያለውን እናንተ ትደርሱበት አላችሁ ልተወው ...... 🔰ከዚጋ ልብ ማለት ያለባችሁ ነገር ምትፈተኑት ኮርስ ከ university university ይለያያል። 🎯 ለምሳሌ 📌 debremarkos ለ medicine ና pharmacy ➖biology ➖chemistry ለ Technology ...software ,computer science ለመምረጥ Coc የለውም ምትዳኙት በ Cumulative GPA ነው። 📌ወልቂጤ university ለ medicine ና pharmacy ➖  Engilish, ➖ Biology, ➖ Chemistry & ➖ Maths 📌 BONGA ለ Engineering and technology ➖English ➖Maths ➖Phyisics 📌Borena ለ ሁሉም ➖maths ➖economics ➖civics ➖english ➖logic 40 ጥያቄዎች 📌Debre birhan ለ medicine ➖maths ➖biology ➖psychology ➖english ➖chemistry 60 ጥያቄዎች 🔰 የጥያቄዎች ባህሪ ጥያቄዎቹ እንደ Biology and Chemistry ከ 9-12 ከተማራችኋቸው ውስጥ በብዛት ይመጣሉ። ጥያቄወቹ ቀላል ቢሆኑም የማስታወስ ችሎታን ይጠይቃሉ። English paragraph ጥያቄወች አይቀሩም ።ሌላው General ና የ Case  ጥያቄወች Like እከሌ እንደዚ እንደዚ ሆነ ችግሩ ምንድን ነው ምን አይት መፍትሄ ትሰጠው አለህ አይነት እና Current issues ላይ ለ Medicine Like Covid 19,Ebola virus....... ለ  law አሁን ስላለው ግጭት ....... Sample coc examኦች ላይ በደንብ እዪኣቸው... 🔰ብዛት አሁንም ከ university university ይለያያል እንደ Common ግን የሁሎች Subjecኦች ድብልቅ ሁኖ 30,60(common ),100 ጥያቄ ሊሆን ይችላል። 🔰Time for study Coc ከመውሰዳችሁ በፊት ምታነቡበት ትንሽ ጊዜ ይሰጣችኋል ግን አስቀድማችሁ ካላያችሁ cover ለማድርግ ጊዜ ያጥራል .....ይሄም ከ university university ይለያያል። 🔰አመዘጋገብ Universityው ማስታወቂያ ያወጣል በዚያ መሠረት መግባት በምትፈልጉት field   Department ነው ምትመዘገቡት:: https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

እስካሁን የምዝገባ ጥሪ ያወጡ -ዩኒቨርስቲዎች ‼️ የዩኒቨርስቲ ጥሪዎችን በቅድመ ተከተል አስቀምጠናል።    💠ዛሬ November 18/2016 ነው🙏 ⭐️Kebri-dahri University             🟢November 13 & 14 ⭐️Bulehora University             🟢 November 15 & 16 ⭐️Wollegga University             🟢  November 17 & 18 ⭐️Raya University             🟢November 17 & 18 ⭐️Kotebe University            đŸŸ˘  November 20 & 21 ⭐️Wolkite University            đŸŸ˘ November 20 & 21 ⭐️Gambela University            đŸŸ˘ November 21 & 22 ⭐️Aastu( A.A) University             đŸŸ˘ November 23 ⭐️Dirredawa University              đŸŸ˘ November 23, 24 & 25 ⭐️Worabe University             🟢 November 24 & 25 ⭐️Odabultum University              🟢November 24 & 25 ⭐️Astu(Adam University              🟢 November 24-25 ⭐️Borana University              🟢 November 27-28 ⭐️Bonga University             🟢  November 27 & 28 ⭐️Aksum University            🟢November 27 & 28 ⭐️Dilla University            đŸŸ˘November 28 & 29 ⭐️Mekelle University             🟢 November 28, 29 & 30 ⭐️Arsi University            đŸŸ˘   December 4 & 5 ⭐️Wachamo University            đŸŸ˘December 5 & 6 ⭐️Haramaya University            🟢December 5, 6 &7 For G12,remedial &freshman 👇👇👇👇👇 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

photo content

📢 ዩኒቨርሲቲ እና ተግዳሮቶቹ። 🤗 ዩኒቨርሲቲ ላወቀበት ተማሪ እጅግ በጣም ብዙ መልካም የሆኑ ገፀ በረከቶች አሉት፡፡ እነዚህን መልካም ገፀ በረከቶች ስትገቡ ታጣጥሙታላችሁ🤓። እኛ ግን  የምንፈልገው እናንተ  ተግዳሮቱቹን አውቃችሁ ፡ ራሳችሁን እንድትታደጉ ነው። 😥ተማሪዎች ግቢ ላይ መጥፎ የተባሉ ነገሮች ይገጥማቸዋል። እስኪ የተወሰኑትን እንመልከት 1ኛ) 🥺 ብዙን ግዜ ዩኒቨርስቲዎች ከከተማ ዉጭ በተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ራቅ ብለው ነው የሚገነቡት። ከከተማ ውጭ ስለሆኑ  fresh air የተትረፈረፈበት ፡ ራስን ለማዝናናት ና ለመመሰጥ እንድሁም ለማንበብ ምቹ የሆኑ ጫካዎች ና የተፈጥሮ መስህቦች አሉ።ስለዚህ ተማሪዎች ለመዝናናት ፡ ለማንበብ እንድሁም walk ለማድረግ ወደ ጫካዎች ና ሰው ወደማይበዛበት ቦታዎች ሊሄዱ ይችላሉ። በዚህ ምክንያት ፡ 📌 ሴቶች የመደፈር አደጋ ያጋጥማቸዋል። 📌 ወንዶች ደግሞ የ መሰረቅ አደጋ ያጋጥማቸዋል ምክንያቱም ሌቦች( የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወይም የአካባቢው ሰው ሊሆን ይችላል) ከ ግቢ ተማሪዎች ስልክ ፡ ብር ና ላፕቶፕ በማስፈራራት መውሰድ ለምደዋል። ስለዚህ ፡ ከላይ የጠቀስናቸው ቦታዎች ላይ ስትሔዱ ተሰባስባችሁ መሔድ ወይም ደግሞ አለመሔድ🙅‍♂🤷‍♀። 2ኛ) ይኸ ደግሞ በሴቶች ላይ የሚስተዋል ሲሆን በፈቃደኝነት ስህተት በመስራት የማይመለስ ፀፀት ዉስጥ የምትገቡበት ነው። ገና ወደ ግቢ ስትገቡ ፡ ለግቢው አዲስ ናችሁ ፡ ለአካባቢው ና ለማህበረሱ አድስ ናችሁ ፡ ለዩኒቨርሲቲ ትምህርት ና ግቢ ውስጥ ስለሚሰሩ ነገሮች አድስ ናቸው። ስለዚህ ነባር(senior) ተማሪዎች ይኸን ደካማ ጎናችሁን( አዲስነታችሁን) ተጠቅመው የህይወት መስመራችሁን ያስቷችሗል☹️። ምን መሰላችሁ ሴቶችዬ 🤔 ገና ዩኒቨርስቲ ስትገቡ ነባር ወንዶች ተማሪዎች አፋቸውን ከፍተዉ😂 እጃቸውን ዘርግተው ይቀበሏችሗል።  ምክንያቱም የመጀመሪያ አመት ሴት ተማሪዎች  ተማሪዎች ወደ  ግቢ ስትገቡ ነባር(senior)  ወንድ ተማሪዎች ሴት ይፈልጋሉ። ስለዚህ ምን ያደርጋሉ መሰላችሁ 😎 መጀመሪያ ልክ ግቢ ስትገቢ ያይሻል። ሻንጣሽ ትልቅ ስለሆነ ይመጣና ላግዚሽ ይላል....ከዛን ይሸከምና  እስከ ተመደብሽበት ዶርም #Dorm(setoch_gibi) ድረስ ያወራሻል...ከዛን ግቢውን እንዳላምድሽ  ሾ.ቁ ስጪኝ ይልሻል። አንቺም ለሁሉም ነገር አድስ ስለሆንሽ ሾ,ቁ ትሰጭዋለሽ.....ነገሩ አለቀ🥺። 😴ከዛ ምዝገባ ላይ ተሯሩጦ ያስመዘገብሻል....እሱም በዚሁ.... ይቀጥላል። 🤗ከዛ ግቢውን ያስጎበሽኛል ፡ ከተማውን ያሳይሻል ፡ ላውንች( Lounge) ይጋብዝሻል። 😴.....ከዛ ቡሃላ ምን ይፈጠራል መሰለሽ.......አንድ ቀን #Over እንዉጣ ይልሻል ፡ ከዛም🥃🍷🥂🍻 ትጠጣላችሁ። ከዛም በመጠጥ ሀይል  አብረሺዉ ታድሪያለሽ። ካደርሽ ቡሃላ ምክንያት በመፍጠር ካንቺ ይርቃል ሌላ ይጠብሳል። በቃ ይሄው ነዉ🤢🤨☹️። ☹️ ማርገዝ የምባል ነገር አለ ፍቅር ያሳየሽ መስሎ አታሎ...... ህይወትሽን ያጨልማል። ከ ገጠር የሚመጡ ሴቶች በጣም ደስ ይላሉ ለምን ብትሉኝ አላማቸው አንድ ብቻ ነዉ። ፍቅረኛ አያቁ በትዳር ያምናሉ። የከተማ ልጆች ደግሞ ስታስጠሉ😂😂 ሁሉንም አይደለም። 🥺 ስለዚህ ሴቶችዬ  ጠንካራ ፡ ፅኑ ፡ አላማችሁን የምታስቀድሙ መሆን አለባችሁ💃💃። 3ኛ) Over🕺💃🕺💃🕺 የዩኒቨርሲቲ ተማሪ over ካልወጣ oxygen እንዳጠረው የሚታሰብበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። እንደ ሰደድ እሳት የ ግቢ ተማሪዎችን ህይወት እያበላሸ ያለው over ነው። over ከጥቅሙ ጉዳቶች ያመዝናሉ ምክንያቱም ፡ 📌#over በወንዶች ተማሪዎች ላይ ያለው ተፅዕኖ። የግቢ ተማሪዎች over ወጥተው ይጠጣሉ ። ከዛም ሞቅ ይላቸዋል ፡ ከዛም በ ደረቅ ሌሊት ከ አካባቢው ወጣቶች ጋ ይጣላሉ ፡ ከዛም በጩቤ ይወጋሉ አልያም በጠርሙስ ይመታሉ ። ከዛም በሌሊት 6 ወይም 7 ሰአት ወደ ሆስፒታል😏። ከ አካል ጉዳት እስከ ህይወት መጥፋት የሚያስከትል ችግር በ #over ምክንያት። እንደታደል ሁኖ ካልተጣላችሁ ፡ በ ደረቅ ሌሊት 8 ሰአት ምናምን ወደ ግቢ ዘበኛ ለምናችሁ ትገባላችሁ። ከመጥን በላይ ቀላቅላችሁ ስለምትጠጡ በየ ሽንት ቤቱ ሻታ🤮🤮🤮። 👷‍♂ ወንዶችየ ተጠንቀቁ ነፃነት አገኘን ብላችሁ ነፃነታችሁን እንዳታጡ🤨። 📌 #over በሴቶች ተማሪዎች ላይ ያለው ተፅዕኖ ። በተለይ የ ከተማ ሴቶች shameless ናቸው☹️። ሲጠጡ ራሱ😴😴። ሴቶች #over ይወጣሉ ፡በ ወንዶች ጋባዥነት  ይጠጣሉ🥂🍻🍷 ፡፡ ከዛ ይሰክራሉ ። ከዛ ደግሞ አልጋ ይዘው ለማደር ብር ላይኖርቸው ይችላል። ስለዚህ ጎዳና ላይ ማደር ስለማትፈልጊ ፡ ከአንዱ ጋር ታድሪያሽ🙁። ከዛ ያልተፈለገ ዕርግዝና ሊከሰት ይችላል። ከዛ በሗላ የሚመጣውን ጣጣ አስቡት😱😱።   ሴት ልጅ ሰክራ በየ አስፓልቱ ስትወድቅ ምን ይባላል 🙈🙈 ይሄን የሚያደርጉት.... አወቅን ባይ የከተማ ልጆች ናቸው። 👷‍♀ሴቶችዬ ተጠንቀቁ። ነፃነት አገኘን ብላችሁ ነፃነታችሁን እንዳታጡ።   😈 ክፍል ሁለት ይቀጥላል😈 🗣🗣🗣 ማሳሰቢያ 👆👆 ከላይ የዘረዘርናቸው የግቢ ተግዳሮችን ለመፃፍ እና ለ እናንተ ለማጋራት ያሰብንበት ዋና ምክንያት ግቢ እንደዚህ አይነት ነገር ስለሚኖር ካሁን አውቃችሁት ፡ እንድትጠነቀቁ ነው እንጅ ሾለ ግቢ መጥፎ ነገር መናገር ፈልገን ወይም እንድትሳቀቁ ፈልገን አይደለም። 🕺 ራሳችሁን በአግባቡ መምራት ከቻላችሁ ግን ግቢ ላይ ምርጥዬ ህይወት ይኖራችሗል። 📌 Join at and share 👇👇 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#ዋቸሞ_ዩኒቨርስቲ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት አምጥተው ለ2016 የትምህርት ዘመን ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ
#ዋቸሞ_ዩኒቨርስቲ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት አምጥተው ለ2016 የትምህርት ዘመን ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ምዝገባ ታህሳስ 05 እና 06/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ የ8ኛ ክፍል ስርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አንድ 3x4 ፎቶግራፍ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ። የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን፦ ➢ በዋና ግቢ ሲትከታተሉ የቆዩ በዋና ግቢ ሪፖርት እንዲያደርጉ ➢ በዱራሜ ካምፓስ ሲከታተሉ የቆዩ በዱራሜ ካምፓስ ሪፖርት እንዲያድረጉ ተብሏል።

አንድ ወንድማችን ነው ያጋረን ድምፅ ሁኑን ብሎኝ ነው:: https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.m
አንድ ወንድማችን ነው ያጋረን ድምፅ ሁኑን ብሎኝ ነው:: https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13 https://t.me/compusteam13

#BoranaUniversity በ2015 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፣ በ2014 ዓ.ም ትምህርት ጀምራችሁ በአንደኛ
+1
#BoranaUniversity በ2015 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፣ በ2014 ዓ.ም ትምህርት ጀምራችሁ በአንደኛ ሴሚስተር በውጤት እና በተለያዩ ምክንያቶች Withdrawal በመሙላት ላቋረጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ወደ ቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 27 እና 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡  አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ስምንት 3x4 ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡ ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት እና ለ2015 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ጥሪ አላደረገም‼️ #ቲክቫህ_ዩኒቨርሲቲ በጉዳዩ ዙሪያ የሀዋሳ ዩኒቨርሲ
+1
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት እና ለ2015 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ጥሪ አላደረገም‼️ #ቲክቫህ_ዩኒቨርሲቲ በጉዳዩ ዙሪያ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራርን ጠይቆ ተከታዩን ዘገባ አጋርቷል። አሁን ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱ ገዢው ፓርቲ ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝና ስልጠናው እስከ ህዳር 30/2016 ዓ.ም እንደሚቆይ ኃላፊው ገልፀዋል። በመሆኑም በታህሳስ የመጀመሪያ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ጥሪ ሊደረግ እንደሚችል ነው ኃላፊው የገለፁት። Note: ከላይ በምስሉ የሚታየው መልዕክት ለነባር መደበኛ ፕሮግራም የመጀመርያ ዲግሪ ተማሪዎች የተላለፈ መሆኑን ኃላፊው አብራርተዋል። በነሐሴ 2015 ዓ.ም ወደ ተቋሙ ገብተው የነበሩ የ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዓመት ተማሪዎች፥ ወደ 2ኛ፣ 3ኛ እና 4ኛ ዓመት መዘዋወራቸውን ተከትሎ የተላለፈ የምዘገባ ጊዜ መልዕክት መሆኑን ገልፀዋል። [ዘገባው የቲክቫህ ዩንቨርሲቲ ነው] ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇

#BongaUniversity በ2016 ዓ.ም ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሪሚድያል ፕሮግራም በቦንጋ
#BongaUniversity በ2016 ዓ.ም ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሪሚድያል ፕሮግራም በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ህዳር 27 እና 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ፦ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ የ8ኛ ክፍል ሚኒሰትሪ ካርድ፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ውጤት ሰርተፊኬት ዋናው ኮፒው፣ ➢ ስድስት ፓስፖርት መጠን ያለው ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።

#OdaBultumUniversity በ2016 ዓ.ም በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች፣ በ2015 ዓ.ም በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመ
#OdaBultumUniversity በ2016 ዓ.ም በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች፣ በ2015 ዓ.ም በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትላችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2014 ዓ.ም የአንደኛ ሰሚስቴር ትምህርት ጀምራችሁ በተለያዩ ምክንያቶች Withdrawal የሞላችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 24 እና 25/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ትምህርት የሚጀምረው ህዳር 26/2016 ዓ.ም መሆኑም ተገልጿል። የምዝገባ ቦታ፦ ጭሮ ከተማ በሚገኘዉ አዲሱ ካምፓስ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ የ8ኛ ክፍል ውጤት ሰርተፊኬት ዋናው ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ውጤት ሰርተፊኬት ዋናው ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናው ኮፒው፣ ➢ ስምንት ፓስፕርት መጠን ያለው ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች 🔻  ቻናል👇