en
Feedback
6 017
Subscribers
-124 hours
-257 days
-19830 days
Posts Archive
ኮሎኔሉ ተመቷል ! በመተከል ባምባሲ ወረዳ ኮሎኔል መላኩ የተባለ ወታደራዊ አዛዥ ከቄለም ወለጋ አካባቢ ጠፍተው ይሄዱ በነበሩ ወታደሮች መለጠጡ ታውቋል። የኮሎኔሉ የመትረፍ እድሉ የተመናመነ እንደሆነ የታወቀ ቢሆንም ለህክምና ወደ አዲስ አበባ በሄሊኮፕተር መወሰዱ ተነግሯል። ወታደራዊ አዛዥ ኮሎኔሉ የተመታው ግን መተከል ባምባሲ ወረዳ መንደር 43 መሆኑን የታወቀ ሲሆን ከምድር የተቀላቀሉ ጠባቂዎቹም እንዳሉ ምንጮቻችን ያደረሱን የተረጋገጠ መረጃ ያስፈልጋል። @BoleMereja

"በቀይ ባህር በኩል ወደብ የማግኘት ፍላጎታችን የቅንጦት ሳይሆን የብሄራዊ ደህንነት ጉዳይ ነው" ታዬ አስቀስላሴ @BoleMereja
"በቀይ ባህር በኩል ወደብ የማግኘት ፍላጎታችን የቅንጦት ሳይሆን የብሄራዊ ደህንነት ጉዳይ ነው" ታዬ አስቀስላሴ @BoleMereja

ሰበር መረጃ ‼️ በኢትዮጵያ ከሦስት ልጆች በላይ መውለድ በሕግ ሊከለከል ነው። ይህ ለምን አስፈለገ ? ይህን የሚያሳይ እና የሚያስረዳ መረጃ በዝርዝር ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/3ErHq8GLGTw?si=IDuDx4nGOkN2gYby

"ጀኔራል አበባውንና ጀኔራል በላይ ስዩምን እጠራጠራቸዋለሁ" ጠ/ሚ ዓቢይ አህመድ @BoleMereja
+1
"ጀኔራል አበባውንና ጀኔራል በላይ ስዩምን እጠራጠራቸዋለሁ" ጠ/ሚ ዓቢይ አህመድ @BoleMereja

“በዲላ ከተማ ሰፊ የሆነ የህዝብ አመኔታን ያተረፈው ፓስተር ጆ ፡ቴዲ አፍሮ በ2016 ዓ.ም በመኪና አደጋ ይሞታል ብሎ የተነበየ ቢሆንም ፤በዛሬው ዕለት ከዲላ ወደ አዲስ አበባ በገዛ መኪናው በመጓዝ ላይ ሳለ በደረሰበት የመኪና አደጋ ህይወቱ ማለፉ ታውቋል፥“ ምንጭ፥ Roha Media

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የአቶ አረጋ ከበደ ጠባቂዎች እና አጃቢዎች ከፋኖ ሀይሎች ጋር ተቀላቅለዋል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የአቶ አረጋ ከበደ ጠባቂዎች እና አጃቢዎች ከፋኖ ሀይሎች ጋር ተቀላቅለዋል።

አራት ኪሎ ቤተመንግስት መስመር ወደ ሸራተን መታጠፊያ አካባቢ የደረሰ ከባድ የመኪና ግጭት።
+2
አራት ኪሎ ቤተመንግስት መስመር ወደ ሸራተን መታጠፊያ አካባቢ የደረሰ ከባድ የመኪና ግጭት።

ሰበር ዜና ‼️ አሽንፈነዋል ! የፋኖ ጦር መሪ እና አስተባባሪ አርበኛ ዘመነ ካሴ በአሁኑ ሰዓት  መግለጫ እየሰጠ ነው። ሙሉ መግለጫውን ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/e-TuR4X1MOs?si=ADVLNRNJJbW4IzMN

ስለ ወደብ ጉዳይ....! መንግስት በወደብ ኪራይ ጉዳይ ከሶማሊላንድ "መንግስት" ጋር የተፈራረመው ሰነድ በጥንቃቄ መታየት አለበት። አንደኛ፡ ወደቡ የሌላ ሀገር እስከ ሆነ ድረስ መከራየት ይቻል እንደሆነ እንጂ "የወደብ ባለቤት ሆንን" የሚያስብል አይደለም። ገንዘብ (ወይ ሌላ) እስከከፈልክ ድረስ ከጅቡቲም መከራየት ይቻላል። ሁለተኛ፡ በዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ እውቅና ካልተሰጣት ሶማሊላንድ ጋር መፈራረም ዉሉ በአለምአቀፍ ሕግ እንዴት ይታያል? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። ሦስተኛ፡ በዓለምአቀፍ ሕግ የሶማሊያ አካል ከሆነችው ሶማሊላንድ ጋር ውል መፈራረም እውቅና የመስጠት አንድምታ አለው። ይህም ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ እውቅና የሰጠች የመጀመርያ ሀገር ያደርጋታል። ከሶማልያ ጋር የሚኖረን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በእጅጉ ሊያበላሽ ይችላል። ከጅቡቲ ጋርም ሊያኮራርፈን ይችላል። Via Abreha @BoleMereja

መረጃ ! ዛሬ መስከረም 26 በአዊ ዞን ባንጃ ወረዳ በተደረገ ዉጊያ ከ100 በላይ የሚሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ህይወታቸው አልፏል። 20 የሚሆኑ ቆስለው እንጅባራ ሆስፒታል ገብተዋል። የፋኖ ሰከላ ብርጌድ መሪ ጌራ ወርቅ እንደተናገሩት ጦርነቱ በአዊ ዞን ባንጃ ወረዳ ሱርታ እና ኳችኳች ቀበሌዎች ውጊያ የተደረገ መሆኑንም ተቁመዋል። በፋኖ ሀይሎች በኩልም ከ70 የማያንሱ ተዋጊዎች ተገድለዋል። ቁጥራቸው ለግዜው ያልተገለፀ ተዋጊዎች ቆስለዋል። @BoleMereja

ሰላም @BoleMereja እነዚህ የምትመለከቷቸው የመኪና ዉስጥ ሌቦች (ሿሿዎች) በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፍንጅ ዛሬ ሰሚት ሰባ ሁለት የተያዙ። ሹፌሩና ሁለት ተባባሪዎቹ አመልጠዉናል። ጥንቃቄ ይደረ
+3
ሰላም @BoleMereja እነዚህ የምትመለከቷቸው የመኪና ዉስጥ ሌቦች (ሿሿዎች) በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፍንጅ ዛሬ ሰሚት ሰባ ሁለት የተያዙ። ሹፌሩና ሁለት ተባባሪዎቹ አመልጠዉናል። ጥንቃቄ ይደረግ።

ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለክርስቲያን ምኑ ነው? (በዲ/ን ሕሊና በለጠ) ቤተ ክርስቲያን በባሕርይዋ የአንድ ማኅበረሰብን ባሕል ንቃም ኾነ ተቃውማ አታውቅም። በተቻላት መጠን ማኅበረሰቡ ከነ ባሕሉ ድኅነትን ያገኝ ዘንድ ሃይማኖቷንና ሥርዓቷን አስተምራ ታስተናግደዋለች እንጂ። ከእርሷ አምልኮ በተቃራኒው የሚያመልክ የአንድን ተገዳዳሪ የእምነት ተቋም አምልኮም በማይገባ መልኩ ተችታና አኮስሳ አታውቅም፤ እውነተኛውን መንገድ ግን በተገቢው መልኩ በጥብዓት ታስተምራለች። የዚያ የእምነት ተቋም አምልኮና እምነት ስሕተት ከኾነ ሰዎች ኹሉ ይድኑ ዘንድ እውነትን ትሰብካለች፤ ወደ እውነት ትመራለች፣ ታደርሳለች። ኢሬቻ ምንድን ነው? ባሕል ነውን? መልካም፣ ባሕልስ ከኾነ ቤተ ክርስቲያን የባሕሉን አክባሪ ባሕሉን ሳይዘነጋ ይቀበላት ዘንድ አይገዳትም። እርሷም ከነ ባሕሉ ዐቅፋና ደግፋ ትቀበለዋለች። ግን ኢሬቻ ባሕል ነው? አይመስለኝም። ሰሞንኛ ተናጋሪዎችን እንዘንጋቸውና እስኪ እንዴት እንደተከበረ እንመርምር። የመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች ውኃ ውስጥ ሣር እየነከሩ ወይም ዛፍን ቅቤ እየቀቡ ፈጣሪን ሲያመሰግኑ የሚያሳዩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን ስናይ ነበር። ስለዚህ ይህ በዓል:- #1ኛ ፈጣሪ የሚመሰገንበት ነው (ይህም ተደጋግሞ በአክባሪዎቹ እየተነገረ ነው)። በፈጣሪ መኖር ማመን ደግሞ: ለሃይማኖት ህልውና የመጀመሪያው መስፈርት መኾኑን ልብ ይሏል። ስለዚህ ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለሃይማኖትነት ትልቁን መሥፈርት አሟልቷል ማለት እንችላለን። #2ኛ የታወቀ የምስጋና (አምልኮ?) ሥርዓት (ለምሳሌ:- ሣር ውኃ ውስጥ መንከር፣ ቅቤ መቀባት ...) አለው። ይህም እስልምናም ኾነ ክርስትና የታወቀ የአምልኮ ሥርዓት እንዳላቸው ማለት ነው። #3ኛ እስልምና መስጊድ፣ ክርስትናም ቤተ ክርስቲያን እንዳላቸው ኹሉ: ኢሬቻም /ዋቄፈናም/ ይህ ሥርዓት የሚፈጸምበት ቦታ (Sacred Place, ለምሳሌ:- ውኃና ዛፍ ያለበት ሥፍራ) አሉት። #4ኛ ሃይማኖታዊ የአምልኮ ሥርዓት በካህናት እንደሚመራ: ክብረ በዓሉን የሚመሩ የሥርዓት መሪዎች (አባ ገዳዎች?) አሉት። ስለዚህ ወይ አምልኮ ነው፣ ወይም ደግሞ ከቆይታ ብዛት ወደ ባሕልነት የተቀየረ አምልኮ ነው። #ዐቢይነጥብ - ከላይ ከጠቀስናቸው ከዐራቱ ለጊዜው አንዱን ብቻ እንምረጥ - -ፈጣሪ የሚመሰገንበት መኾኑ ይህ ብቻ "ባሕል ነው" ለሚሉት ቆም ብለው እንዲያስቡ የሚያስገድድ ምክንያት ነው። ፈጣሪን ማመስገን የሚቻለው በእምነት ነው። በመጀመሪያ ይህን ፈጣሪ ማመንና በጥቂቱም ቢኾን በእምነት ማወቅ ይገባል። ቢያንስ ፈጣሪ መኾኑን በእምነት መረዳት ያሻል። ከዚያም እርሱ በሚፈልገው ሥርዓት እርሱን ማመስገን/ማምለክ ይከተላል። እርሱን ማምለኪያ ውሱን ሥርዓት የለም ቢባል እንኳን: የማመስገኛ ሥርዓቱ "ሥርዓት የለሽ በመኾን" ይገለጻል፤ (non-religiousness is my religion) እንዲል አንድ የፍልስፍና መምህር /ፈላስፋ ላለማለት ነው/)። ሙስሊሙ ፈጣሪን የሚያመሰግንበት ሥርዓትና ቦታ አለው፤ ሳምንታዊ(ጁምዓ) እና ዓመታዊ (ኢድ አል ፈጥር፣ ኢድ አልአድሃ) የበዓላት ዕለታትም አሉት። ክርስቲያኑም እንዲሁ ከሳምንታዊ ሰንበትን፣ ከዓመታዊ ልደትና ትንሣኤን የመሰሉ (ዕለታዊና ወርኃዊውን ጨምሮ) ብዙ በዓላት አሉት። ሙስሊሙም ክርስቲያኑም በየበዓላቱና በየታወቀ ሥርዓቱ ፈጣሪን ያመሰግናሉ፣ ያመልካሉ። ነገር ግን ክርስቲያኑ ኢሬቻ የሚል ፈጣሪን የማመስገኛ በዓል በዚቁ (liturgical Calendar) ውስጥ የለም። ሙስሊሙም እንደዚያ። ሌላው ነጥብ: ኹሉም እምነት ፈጣሪን የተመለከተ መሠረተ-ትምህርቱ (Doctrine/Creed) ከሞላ ጎደል ይለያያል። ሙስሊሙም (ካልተሳሳትኩ) "ላ ኢላህ ኢለላህ መሐመዱር ረሱለላህ" የሚል ሸሀዳ (Creed) አለው። ይህንን አዘውትሮ ያደርሳል። ፕሮቴስታንቱ "ክርስቶስ አማላጄ" (ሎቱ ስብሃት) ይላል። እኛ ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ "ኹሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በሚኾን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን" ከሚለው ጀምሮ የክርስቶስንና የመንፈስ ቅዱስን አንድ የባሕርይ አምላክነትና ከአብ ጋር መተካከል፣ የቤተ ክርስቲያንን ኲላዊነት፣ አንድነት፣ ቅድስናና ሐዋርያዊነት፣ የጥምቀትን የኃጢአት ማስተሥሪያነት፣ የትንሣኤ ሙታንን ተስፋነት የምንመሠክርበት የዘወትር ጸሎተ ሃይማኖት (Creed) አለን። እነዚህ እምነቶች ይለያያሉ ብቻም ሳይሆን ይቃረናሉ። እንዴት በአንድነት ምስጋናቸውን ለአምላክ ያደርሳሉ? እኔ አምላክ የምለውን ክርስቶስን አንዱ ከአጠገቤ "አማላጄ" እያለው እንዴት አንድነት ይኖረኛል? አንዱስ "ነቢይ" እያለው እንዴት አብረን እናመሰግናለን? የኔን አምላክ አማላጅም ፣ ነቢይም ማለት እርሱን ማሳነስ ለእኔም ንቀት ነው። ሙስሊሙም አላህን አምላክ ይላል። ኢሳን ነቢይ ይላል። እኔ ከጎኑ ቆሜ ኢየሱስ ክርስቶስን "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ስል እንዴት ይዋጥለታል? አብረን ቡና የምንጠጣ፣ አብረን ኳስ የምንጫወት፣ በንግድ የምንተባበር ሙስሊሞችና ፕሮቴስታንቶች ይኖራሉ። በጣም የምንዋደድ ጓደኛሞችና የሥራ ባልደረቦች ልንሆን እንችላለን። ግን ለአምልኮ ሙስሊሙም መስጊድ፣ ፕሮቴስታንቱም "ቸርች" እኛም ቤተ ክርስቲያን እንሔዳለን እንጂ ፈጣሪን ለማመስገን መስጊድ ወይም ቤተ ክርስቲያን በአንድነት አንሔድም። አንድ የምንኾንበትንና የማንኾንበትን እንለይ እንጂ! በኢትዮጵያዊነት አንድ ነን፤ በባሕል እንተባበራለን፤ በልማት አንድ መኾን እንችላለን፤ እንኳን በሀገር በቤተ ዘመድም በሃይማኖት መለያየት ይገጥመናል፤ ዝምድናን ጨምሮ ግን ብዙ አንድ የሚያደርጉን ጉዳዮች አሉን። ኾኖም በሃይማኖት አንድ ካልኾንን ከእናቴም ጋር ለጸሎትና ለምስጋና አልቆምም። እንኳን ከሙስሊምና ከፕሮቴስታንት ጋር ይቅርና በብሉይ ኪዳን በሃይማኖት አንድ ከነበርነው ከይሁዲውም ጋር ፈጣሪን ለማመስገን በአንድነት አንቆምም። የይሁዲው መሠረተ ሃይማኖት ( ሸማ፣ Creed) በእኛው ብሉይ ኪዳን ላይ ዘዳ.6÷4-9 ያለው ንባብ ነው። ይሁዲዎች ይህንን በእጃቸው ያሥሩታል (Teffilin)። በበራቸውም ይጽፉታል (Mezzuzah)። ንባቡ እኛም የምናምንበትና የምናነበው ነው። ነገር ግን ምንም ያኽል ብንወዳቸው ክርስቶስን ከማያምኑት ከይሁዲ እምነት (Judaism) ተከታዮች ጋር የሃይማኖት ኅብረት የለንም። ወንጌላችንም ያዘናልና "ቢቻለንስ በእኛ በኩል ከሰው ኹሉ ጋር በሰላም መኖርና ሰላምን መከታተል" የክርስትና መርሐችን ነው። (ሮሜ 12÷18፣ ዕብ. 12÷14)። ኾኖም ፈጣሪን የምናመሰግንበት የሃይማኖት ኅብረት የሚኖረን ግን ከተጠመቁት ጋር ብቻ ነው።

በአማራ ክልል ዳግም ጦርነት ማገርሸቱን ተከትሎ: በሰሜን ሸዋ ዞን : ሸዋ ሮቢትና በምዕራብ ጎጃም ዞን ደግሞ ቡሬ ከተሞች በፋኖ ቁጥጥር ስር መሆናቸውን መረጃዎች ደርሰውኛል:: በደንበጫም ውጊያ እየተካሄደ ነው:: ከውይይት ይልቅ ጥይትን የመረጠው የአብይ መንግሥት ኢትዮጵያን ዋጋ እያስከፈለ ነው:: በሰራዊቱ ለምን ያክል ጊዜ ተማምኖ እንደሚቀጥል ባይታወቅም: ደመሰስኩት ያለው ፋኖ እንደገና የተጠናከረ ውጊያ መክፈቱ: 2016 ከባድ የጦርነት ዓመት እንደሚሆን አመላካች ነው::

ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ በሸራተን አዲስ ለአዲስ አመት የምታቀርበውን የሙዚቃ ኮንሰርት የኃይማኖት አባቶችን ትዕዛዝ በማክበር እንደሰረዘች ገለፀች። እኔ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ ጳጉሜ 6 በሸራተን አዲስ ለ
+2
ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ በሸራተን አዲስ ለአዲስ አመት የምታቀርበውን የሙዚቃ ኮንሰርት የኃይማኖት አባቶችን ትዕዛዝ በማክበር እንደሰረዘች ገለፀች። እኔ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ ጳጉሜ 6 በሸራተን አዲስ ለአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ስራዬን ለማቅረብ ተፈራርሜ የተዘጋጀሁ ቢሆንም ይህን ስራ በመሰረዜ የሚያስከፍለኝ ዋጋ ቢኖርም ከሁሉም በላይ በቃሏ የምመራላት ቤትክርስትያን ሀይማኖት አባቶቼን ትዕዛዝ በመቀበል የማቀርበውን የሙዚቃ ስራ ሰርዤአለሁ ! ለውድ አድናቂዎቼ እንዲሁም የፕሮግራሙ አዘጋጆች ይቅርታ እየጠየኩ በሌላ ዝግጅት እንደማስደስታችሁ እና እንደምንገናኝ ስገልፅላችሁ በታላቅ አክብሮት እና ምስጋና ነው! @BoleMereja

photo content
+9

ከዚህ በታች በአማራ ክልል እየተደረገ ባለው ዉጊያ የተደመሰሱ የዐቢይ አህመድ መከላከያ ወታደሮችን ፎቶ መመልከት ትችላላችሁ።

ለበዓለ ሲመት ሽመልስና አወል አርባ ፈገግ ሲሉ አዲሱ የአማር ክልል ፕሬዘዳንት የተሸበሩ ይመስላል ሰላም ለሀገራችን 🙏
ለበዓለ ሲመት ሽመልስና አወል አርባ ፈገግ ሲሉ አዲሱ የአማር ክልል ፕሬዘዳንት የተሸበሩ ይመስላል ሰላም ለሀገራችን 🙏

ናሁም ዮሐንስ ታሰረ‼️ የዮሐንስ ቧያሌው ልጅ ናሆም ዮሐንስ አባቱን ለመጠየቅ በሄደበት በፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ታስሯል።  ናሁም ዮሐንስ ከታሰረ ዛሬ ሶስተኛ ቀኑ መሆኑን ከመረጃ ምንጮቻችን ማረጋገጥ ችለናል። ------------------ ለማንኛውም ፈጣን ወቅታዊ መረጃ ትክክለኛው የዩቲዩብ ቻናላችን ይሄ ነው👇 Subscribe በማለት ተቀላቀሉ። https://youtube.com/c/BoleMereja