en
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Assaye Derbie

Channel Assaye Derbie (@asayede) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 334 subscribers, ranking 2 646 in the Blogs category and 2 341 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 334 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -107 over the last 30 days and by 3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 35.85%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.04% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 139 views. Within the first day, a publication typically gains 1 726 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 31.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Blogs category.

14 334
Subscribers
+324 hours
-197 days
-10730 days
Posts Archive
ስለ ድል ማውራት የምንችለው በአሸባሪው ሃይል አስከሬን ላይ ራያን እና መረብን አልፈን ስንሄድ እንጂ ከራያ ወደ ቆቦ የዘመተውን ወራሪ የደመሰስን ቀን አይደለም።

አቋሙ የማይዋዥቅ፣ አቅም ልኩ የማይወርድ የአምና ንግግሩን፥ዘንድሮ ቀይሮ፥ አርባ የማይቀላምድ የሶማሌ ሳንጃ፥ የኢትዮጵያ ጋሻ፥ ሙስጠፌ መሃመድ❗️ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ አንዳንድ ፖለቲከኞች እንደ እስስት እየተቀያየሩ ከፖለቲካው ጋር እራሳቸውን ያስማማሉ፡፡ የሆነ ግጭት ሲነሳ አሸናፊው እስኪለይ ድረስ ‹‹ዝም አይነቅዝም›› ብለው አንገታቸውን ይደፋሉ፡፡ አሸናፊው ሲታወቅ ደግሞ ‹‹ካለመናገር አመራር መሆን ይቀራል›› በሚል አቋም መድረኩን ተቆጣጥረው ያረበርባሉ፡፡ እንደ ሙሥጠፌ ያሉት ግን በሚለዋወጠው ፖለቲካ ፈንታ ከእውነታው ጋር እራሳቸውን አስማምተው እስከ መጨረሻው ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ የፌደራል ወንበር ላይ ተቀምጠው እንደ ክልል የሚያስቡ አመራሮች ባሉበት ሁኔታ፣ የክልል መሪ ሲባሉ ለአገር ተቆርቋሪ ሆነው ይከሰታሉ፡፡ እውነት ለመናገር ከብልጽግና ባለሥልጣናት የአሸባሪ ቡድኑን ሤረኝነት፣ ክፋት፣ እራስ ወዳድነት፣ አረመኔነት ተረድተው ከልባቸው የሚጠየፉ አመራሮችን ጥቀስ ብባል ከሙሥጠፌ መሐመድ ቀጥዬ ታዬ ዴንዳን እጠራለሁ፡፡ ልዩነቱ ግን ታዬ ህውሓትን የሚታገለው ከክብ ላይ ቀንሶ በሆነ ዲያሜትር ውስጥ በሚያስብ ጭንቅላት ሲሆን ሙስጠፌ ግን አገር ሆኖ ነው፡፡ በመሆኑም ትሕነግ ‹‹ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ›› ብሎ ሲደነፋ ታዬ ‹‹ከእሷ በፊት አንተ ትፈርሳለህ›› ይለዋል፡፡ ‹‹አማራ ኤሊት ላይ ሒሳብ አወራርዳለሁ›› ማለቱን ሲሰማ ግን ‹‹መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ›› በማለት በልቡ ይመርቀዋል፡፡ ሙሥጠፌ ግን ‹‹ምን አገባኝ›› በማለት ፈንታ እውነቱን ይዞ ‹‹ያለፈ ሒሳብ ማወራረድ ካለ እኛንም እንዳትረሳን›› በማለት ይዋረዳል ከተባለው አካል ጋር እራሱን ይቀላቅላል፡፡ በማንነታቸው የተዛተባቸው አመራሮች ‹‹እኛ ባለሥልጣናት እንጂ ኤሊት አይደለንም›› ብለው ዝም ሲሉ ከእውነታ ጋር መወገን የሚመርጠው የሶማሌው ፕሬዝዳንት ግን የአማራ ኤሊት ሆኖ ይከሰታል፡፡ ምክንያቱም ሙስጠፌ ጁንታው በአፉ የአማራ ጠላት መሆኑን ቢያውጅም በተግባር ግን የአገር ጠላት መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ አማራውንም የሚጠላው ‹‹እኔን የማታነግስ አገር ትፈራርስ›› የሚል እቅዱን ለማሳከት እንቅፋት የሚሆንበትን አካል ሲያስብ አማራ ቀዳሚ ሆኖ ስለሚታየው መሆኑን ይገነዘባል፡፡ አሸባሪው አካል በአማራ እና በአፋር ላይ የከፈተው ጦርነት ዓላማው ምን እንደሆነ ስለሚረዳም ‹‹አሸባሪው የከፈተው ጥቃት ለአገር ቀጣይነት እንጂ ለመሬት ባለቤትነት የሚካሄድ ስላልሆነ ይመለከተናል›› እያለ ከተፍ ይላል፡፡ እንዳለውም አማራው ማረሻውን ጥሎ ነፍጡን ያነሳው ለአገር ቀጣይነት እንጂ ለራያና ወልቃይት መሬት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ራያና ወልቃይት ለአሸባሪው ሃይል የሰሊጥ መሬት ሲሆን ለአማራው ግን ማንነት ነው፡፡ አሸባሪው ሑመራን የሚፈልገው ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ሲሆን አማራው ግን ወልቃይትን የሚፈልገው አገሩን ማስቀጠል ስለሚፈልግ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈም የሽብር ቡድኑ ይሄን ሕዝብ የሚወጋው ‹‹አማራን በመደምሰስ ኢትዮጵያን ማፍረስ›› የሚል ሕልም ይዞ ሲሆን፣ አማራው ደግሞ አጸፋውን የሚሰጠው ‹‹ባንተ መቃብር ላይ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር›› እያለ ነው፡፡ በዚህም መሠረት አንዳንዶች በዘመቻው ተሳትፈናል ለማለት ያህል የይስሙላ ጦር ልከው በዝምታቸው ሲበረቱ ብሎም እንደ ፔንዱለም ሲወዛወዙ እንደ ሙስጠፌ ያሉ ሐቀኛ አመራሮች ግን በማይዋዥቅ አቋማቸው ተገልጠው ከውጊያው ይልቅ በፕሮፖጋንዳው ተማምኖ ወደ ጦርነት የገባውን አሸባሪ መፈናፈኛ ያሳጡታል፡፡ ስለዚህ ልክ እንደ ትናንቱ ሁሉ ዛሬም ክብር ለሙስጠፌ መሃመድ ኡመር ብንል ምን ይለናል? #ኮፒ በማድረግ ፌስቡክ ላይ ያጋሩት

የአሸባሪውን የፕሮፓጋንዳ ክፍል "አርቆ አሳቢ ነኝ" የሚለው "ተልባ ዜጋ" ተቆጣጥሮ ያልተጀመረውን ትግል ለማሰናከል እየተርመጠመጠ ነው። ጁንታው መከላከያ ላይ ሲተኩስ በእግር ኳስ ወሬ እራሱን በመጥመድ የሚታወቀው ሃይል ኢትዮጵያ እራሷን ስትከላከል የተኩስ ድምጽ እንዳያስደነግጠው ጆሮውን አፍኖ ሚዛን ሚዛን እየተጫወተ ነው። እውነት እውነት እላችኋለሁ... ይሄን ሆዴ ቡቡ የእግር ኳስ ኤሊት ዝም ማስባል ካልተቻለ ሰላም ማግኘትም ሆነ አሸባሪ ድርጅቱን ማጽዳት የሚቻል አይደለም።

መስቀል አደባባይ ቀርቶ ራያና ሑመራ ላይ ለመሰለፍ ዝግጁ ነኝ! አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ የነገው የመስቀል አደባባይ ሰልፍ ሕይወቱን ሰውቶ ለሚያስከብረን ሠራዊት ያለንን ክብርና ድጋፍ የምንገልጽበት፣ አሸባሪዎችን የምናወግዝበትና ሕዝባዊ አንድነታችንን የምናሳይበት በመሆኑ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ ላለው አገር አፍራሽ ሃይል የሚያስተላልፈው መልዕክት ከባድ ነው፡፡ስለሆነም እኔም በዚህ ሰልፍ ላይ ተገኝቼ የሚከተሉትን ሐሳቦች የማስተላልፍ ይሆናል፡፡ እርስዎስ? ➜መከላከያ ሠራዊታችን ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው ክህዴት ፈጽመው በለኮሱት ጦርነት ውስጥ ለጋ ሕጻናትን እና እናቶችን በማዝመት ከልጆቻቸው ሞት ፖለቲካዊ ትርፍ ለማጋበስ አስበው ካሜራ ይዘው የሚዞሩ አሸባሪዎች ለፍርድ ይቀረቡ! ➜በስኳር ስርቆትና በሙሰኝነት ታስረው የኖሩ የዚያ ትውልድ አባላት ችግር እንጂ አገር አያሸጋግሩም! ➜በውጫዊ ሃይል ጫና የምትፈርስ አገር፣ የሚነግስ አሸባሪና፣ የሚፈስስ ወንዝ አይኖርም! ➜ከአውሮፓ ሕብረትና ከአሜሪካ መንግሥት እንዲላክልን የምንፈልገው የታሸገ እንጂ የተበተነ ዱቄት አይደለም፡፡ 😁 ➜እናቱን የሚደበድብ የሙቀጫ ልጅ በመፍለጫ ተሰነጣጥቆ ማገዶ ከመሆን አይዘልም! ➜በውስጣዊ ጉዳዮቻችን ገብተው መሬት የሚደለድሉና ጥይት የሚያከፋፍሉ መንግሥታት አፍራሽ እጃቸውን ሰብስበው ለጋሽ መዳፋቸውን ይዘርጉ! ➜የኢትዮጵያን ሕዝብ አሥር ዓመት የጠበቀውን የደስታ እለት ለመንጠቅ አስቦ ‹‹የአባይ ግድብ ተሞላ›› የተባለ ቀን በአፋር ሕዝብ ላይ ጦርነት የከፈተው ጁንታ በዚህ ዘመቻ ሙሉ ለሙሉ ጸድቶ ፋይሉ መዘጋት አለበት፡፡ ➜በተደጋጋሚ ያነቀፈውን ድንጋይ መንግሎ የማይጥል መንግሥት ከእንቅፋቱ ጎን ተፈንግሎ መገኘቱ አይቀርም። ➜እኛ ኢትዮጵያውያን ሊያፈራርሱን ሲሞክሩ የምንሰባሰብ ሕዝቦች መሆናችንን ለማወቅ ከሰሞኑን ለአገራቸው እና ለሠራዊታቸው አጋር ሆነው የዘመቱ የክልል የጸጥታ ሃይሎችን ማየት ይበቃል፡፡ ➜ከኢትዮጵያ የሚፈልቀውን የአባይ ውሃ የሚጠጡ አገራት ልዩ ጥቃታቸውን አቁመው ልዩ ጥቅማችንን ማክበር ይኖርባቸዋል፡፡ #Share በማድረግ ለሌሎች ያጋሩ!

የትሕነግ አሸባሪዎች ከጦርነት እሳት ውስጥ የከተቷቸውን የሕፃናት እና የሴቶች አስከሬን በሲኖ ትራክ ጭነው በመፈርጠጥ ላይ ይገኛሉ። የዚህም ሤራቸው ዓላማ ወደ ጦርነት ባስገቧቸው ሕፃናት ተጠያቂ በመሆን ፈንታ "ምንም የማያውቁ ሕፃናት ተገደሉብኝ" በሚል ሙሾ አልቃሽና ከሳሽ ለመሆን ነው። ይሄንን መረጃ ፌስቡክ ላይ በማጋራት የትሕነግን ሴራ ለሁሉም ያሳውቁ!

‹‹ኦሮሞ አዋጊም ሆነ ተዋጊ መሆን አይችልም?›› አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖ የትሕነግ ልጆች ለኦሮሞ ሕዝብ ያላቸው ንቀት እጅግ የወረደ በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አገር መምራት የማይችል ሕፃን አድርገው ‹‹አቡሽ›› እና መሽረፈት›› እያሉ ይሳለቁበታል፡፡ ኢታማዦሩን ‹‹በደርግ ዘመን ወደ ትግራይ ከዘመተ በኋላ አንድ ጥይት ሳይተኩስ የተማረከ ነው›› እያሉ ያናንቁታል፡፡ ኢታማዦር ለመሆን ይቅርና እንደ ወታደር ጦርነት ላይ ለመዝመት ብቁ አይደለም›› በሚል ፕሮፖጋንዳ ሥሙን ያጠፉታል፡፡ እንደ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ያለውን ጀግና የጦር መሪ ምርኮኛ ከመሆን የዘለለ እጣ ፈንታ እንደሌለው ይነግሩኻል፡፡ ማዕረጉን ገፍፈው ንቀታቸውን በሚገልጽ ቅጽል ሥም ይጠሩታል፡፡ ዛሬ ደግሞ በእነ አሉላ ሰሎሞን የሚመራው የሳይበር አሸባሪ ከአፋር፣ ከአማራ፣ ከሲዳማ፣ ከደቡብ፣ ከሶማሌ፣ ከጋምቤላ፣ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ከዘመተው ልዩ ሃይል በተለየ መልኩ ከኦሮሚያ የዘመተውን ልዩ ሃይል በቅጽበት ውጊያ መደምሰሳቸውንና መማረካቸውን እየገለጹ ነው፡፡ ጦረኝነትና ጀብደኝነት በዘር የሚተላለፍ ይመስል እራሳቸውን ብቻ እንደ ጦረኛ የሚቆጥሩት የትሕነግ ትምክህተኞች ጀግናውን የኦሮሞ ሠራዊት ከምርኮኛ ተርታ መድበው ‹‹ተው ይቅርብህ እያልነው የዘመተውን የኦሮሞ ሠራዊት በቅጽበት ውስጥ ሟችና ምርኮኛ ስላደረግነው ቄሮ ሆይ ከዚህ ተምረህ አርፈህ ተቀመጥ›› የሚል መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህ የንቀት ፕሮፖጋንዳቸው መላውን የኦሮሞ ወጣት ለውጊያ የሚያነሳሳ እንጂ ተሸናፊ ስነ ልቦናን የሚያወርስ አይደለም፡፡ የሚነዙት የውሸት ሰበር ዜናም ለእራሳቸው የሚሰጡትን የተጋነነ ግምትና ለኦሮሞ ያላቸውን ንቀት ከመግለጽ የዘለለ ፋይዳ የለውም፡፡ ምክንያቱም በአድዋም ሆነ በማይጨው፣ በካራማራም ሆነ በባድሜ ጦርነት ላይ ኦሮሞ ከመዋጋት በተጨማሪ ማዋጋት የሚችል ጦረኛ ሕዝብ መሆኑን ያሳየ ጀግና ሕዝብ ነው፡፡ በጣሊያን ጊዜ እንኳን ያለውን ታሪክ ብንመለከት ባንዳው ራስ መንገሻ ጉግሣ ጣሊያንን በእልልታ ተቀብሎ አገሩ ላይ ሲዘምት በሰላሌው ጀግና ‹‹አቢቹ›› የሚመራው የጎበዝ አለቃ ግን ጣሊያንን እና ባንዳን ሲያግለበልባቸው ነበር፡፡ በመሆኑም የኦሮሞ ሕዝብ ልክ እንደ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሁሉ ተዋግቶ ከሚያሸንፈውና ለአገሩ መስዋዕት ከሚከፍለው አርበኛ ተርታ የሚሰለፍ እንጂ የውጭ ወራሪ በመጣ ቁጥር የሚበነድድ ወይም ደግሞ ሳይዋጋ የሚማረክ አይደለም፡፡ ሐቁ ይሄ ቢሆንም ታዲያ እራሳቸውን ከግሪክ አማልክቶች ተርታ የሚመድቡት እኒህ የእፉኝት ልጆች በአገር መሪነትም ሆነ በጦር መሪነት ለሚታወቁት የኦሮሞ ልጆች ያላቸው ንቀት በጣም የሚያስገርም ነው፡፡ ከሰሞኑም አፈር ድሜ ሊያስበላቸው ወደ ውጊያ የዘመተውን የኦሮሞ ሠራዊት ከሌሎች ወንድሞቹ ለይተው ‹‹ማርከነዋል›› እና ‹‹ደምስሰነዋል›› ማለታቸው ይሄን ንቀታቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ የሚገርመው ነገር ታዲያ እንደ ግርማ ጉተማና ብርሐነ መስቀል ያሉ የኦሮሞ ኤሊቶች ከኦሮሞ የወጡ የአገርና የጦር መሪዎችን ከሚደግፈው ዜጋ ይልቅ ከሚያንቋሽሸው አካል ጋር አብረው እየሠሩ መሆናቸው ነው፡፡ ትሕነጎች ‹‹ዐቢይ ይውረድ›› ሲሉ ‹‹ዳውን ዳውል›› የሚሉ፣ የኦሮሞ አዋጊዎችን ሲያናንቁ ‹‹አዎ እኛ እኮ ምርኮኞች እንጂ አዋጊዎች መሆን አንችልም›› እያሉ ስለ እራሳቸው የሚመሰክሩ፣ ‹‹የኦሮሞን ጦር ማረክነው›› የሚል ፕሮፖጋንዳ ሲነዙ ‹‹እሰይ የእኛ ጀግኖች›› እያሉ የሚያደንቁ መሆናቸው ነው፡፡ አግራሞት የሚጭረው… ዐቢይን አውርደው ደጺን፣ ጀኔራል ብርሐኑን ጥለው ጀኔራል ጻድቃንን፣ ፣ ሌ/ጄ ጫላ ደበሌን አስወግደው ጀኔራል ሐጎስን፣ የኦሮሞ ልዩ ሃይልን አስማርከው የትሕነግ ጦርን በኢትዮጵያና በኦሮሞ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ለመጫን የሚንደፋደፉ ገረዶች ከኩሩውና ከጀግናው የኦሮሞ ሕዝብ አብራክ መፍለቃቸው ነው፡፡ ፌስቡክ ላይ Share ማድረግ እንዳይረሳ

ከኮሜንት ወደ ሪፖርት የምንሻገረው መቼ ነው? ➖➖ አብዛኛው የአማራ አክቲቪስት ከፓርቲና ድርጅት ባለፈ ጸረ ሕዝብ የሆኑ የጥላቻ ጽሑፎችን አይጽፍም፡፡ ያም ሆኖ ግን ቴሌግራም ላይ የተደረጃ የጁንታ ቁራጭ በሚያደርገው ሪፖርት የበርካቶች የፌስቡክ አካውንት እየተዘጋ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ የአማራን ሕዝብ የሚያጥላሉና የሚያንቋሽሹ የትሕነግ እና የአሽከሮቹ አክቲቪስቶች በነጻነት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ እነ ብርሐነ መስቀል አበበ ሰኚ፣ እነ ሰሎሞን ተካልኝ፣ እነ አሉላ ሰሎሞን፣ እነ ግርማ ጉተማ፣ እነ ስታሊን፣ እነ ሴቭ አድና ዘ ጸአት ውሸትን እና ጥላቻን ሲያሰራጩ ይውላሉ፡፡ ማሕበራዊ ሚዲያ የሚጠቀመው አብዛኛው አማራ ግን በቁጥር እጅግ ብዙ ቢሆንም የጥላቻ ጽሑፎችን ሲመለከት ሪፖርት አድርጎ አካውንታቸውን ከማሳገድ ይልቅ ኮሜንትና ስክሪን ሾት እያደረገ የተከታዮቻቸውን ቁጥር በማሳደግ ላይ ተጠምዷል፡፡ ቴሌ ግራም ላይ የተደራጁት የጁንታው ልጆች ፕሮፖጋንዳቸውን የሚያከሽፉባቸውንና የሚጠሏቸውን የአማራ አክቲቪስቶች በሥም ዝርዝር ለይተው ሪፖርት እያደረጉ ስለ ትሕነግ መጻፍ የማይቻልበትን ሁኔታ ሲፈጥሩ የእኛ ሰው ግን ሕዝብን በጅምላ የሚያንቋሽሹ አክቲቪስቶችን እንኳን አደብ ማስገዛት አልቻለም፡፡ ይህ ሁኔታ ግን ከዚህ በኋላ መቀጠል የለበትም፡፡ በቅርቡ የትዊተር ዘመቻ እንደጀመርነው ሁሉ ሪፖርት ማድረግንም ልምድ በማድረግ የጥላቻ ማሽኖቹን ከጥቅም ውጭ ልናደርጋቸው ይገባል፡፡ በሐሰት ሪፖርት እነ ጌታቸው ሽፈራሁን እያስቀጡ ፌስቡክ ላይ ብቻቸውን የሚፏልሉትን የባንዳ ፈረሶች በተጨባጭ ማስረጃ ላይ ተመስርተን ሪፖርት በማድረግ አፋቸውን መለጎም ግድ ይለናል፡፡ በተረፈ በትናንቱ ማስታወቂያችሁ 5 ሺህ ተከታይ ያፈራችሁልኝን እያመሰገንኩ ግዴታችሁን ያልተወጣችሁ ደግሞ ከስር ያለውን ሊንክ በማስተዋወቅ ተመሳሳዩን አበርክቶ ታደርጉልኝ ዘንድ እጠይቃለሁ። https://m.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/?ref_component=mbasic_home_header&ref_page=MNotificationsController&refid=48&ref=opera_speed_dial&paipv=1

የክተት አዋጅ አሳዬ ደርቤ የትሕነግ ቡችሎች ተደራጅተው በሚያደርጉት የሐሰት ሪፖርት ማርክ ዙከርበርግ የተባለ ‹‹ነጭ ትሕነግ›› ከሦስት ቀን እስከ ሰባት ቀን በሚደርስ እስራት አካውንቴን ሲዘጋው ሰነ
+1
የክተት አዋጅ አሳዬ ደርቤ የትሕነግ ቡችሎች ተደራጅተው በሚያደርጉት የሐሰት ሪፖርት ማርክ ዙከርበርግ የተባለ ‹‹ነጭ ትሕነግ›› ከሦስት ቀን እስከ ሰባት ቀን በሚደርስ እስራት አካውንቴን ሲዘጋው ሰነበተ፡፡ ትናንት ደግሞ ባንዳን አለመጥላት ይቻል ይመስል ‹‹ትሕነግን በሚመለከት የጻፍከው ጽሑፍ ጥላቻ ተንጸባርቆበታል የሚል ሪፖርት ስለደረሰኝ በዚህ አካውንት ለሠላሳ ቀን ያህል ምንም አይነት መልዕክት ማስተላለፍ አትችልም›› የሚል ማዕቀብ ጣለብኝ፡፡ ‹‹የሠላሳ ቀኑን ቅጣት ስትጨርስ ደግሞ ለ84 ቀናት ያህል የምትጽፋቸው ነገሮች ለጥቂት ተከታዮችህ ብቻ የሚታዩ ይሆናሉ›› በማለት ተነባቢ እንደማልሆን ገለጸልኝ፡፡ ሆኖም ግን የትሕነግ ልጆች ሪፖርት ፌስቡክን ማሳሳት ቢችሉም እኔን ግን ተስፋ አላስቆረጡኝም፡፡ እንደውም በዘመቻ ያስጣሉብኝ ማዕቀብ ወገንን የሚጠቅምና እነሱን የሚያወድም ሐሳብ እያስተላለፍኩ መሆኔን ነው የገለጸልኝ፡፡ ይሄንንም ስረዳ አካውንቴን አዘጉት ብዬ እረፍት በመውሰድ ፈንታ የአቅሜን ማበርከት እንደሚገባኝ በማመን አዲስ አካውንት አውጥቼ ባዶ ቤት ተቀምጬላችኋለሁ፡፡ ከዚህ ባለፈም ልክ እንደኔ ሁላ የበርካታ ወንድሞቻችንን አካውንት በሐሰት ክስ እያዘጉ ሕዝባችን ላይ የጥላቻ ልሃጫቸውን የሚለግጉ እፉኝቶች አካውንት ማዘጋት የምንችልበትን ስልት ነድፌያለሁ፡፡ ይሄም እቅድ ይሳካ ዘንድ እዚህ ቴሌግራም ላይ የተሰባሰባችሁ ወዳጆቼ በሙሉ ከዚህ ጽሑፍ ስር ያለውን ሊንክ የፌስቡክ ግድግዳችሁ ላይ በማስተዋወቅ ተዋጊ ጦር ታሰባስቡልኝ ዘንድ በታፋኙ ማሕበረሰብ ሥም ስጠይቃችሁ... በነገው እለት አሥር ሺህ ተከታይ እንደሚኖረኝ በማመን ነው፡፡ 😁 አክባሪያችሁ https://m.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/?ref=opera_speed_dial

የትሕነግ ቡችሎች ተረባርበው አካውንቴን አዘግተውታል 😁
+1
የትሕነግ ቡችሎች ተረባርበው አካውንቴን አዘግተውታል 😁

ግድባችን ሞልቶ መፍሰስ ጀምሯል። እንኳን ደስ አለን!
ግድባችን ሞልቶ መፍሰስ ጀምሯል። እንኳን ደስ አለን!

የሶማሌ ተኳሽ- ‹‹እንቢ አልዘምትም›› ብሎ- ቆሟል ከእኛ ጋራ የሚል ሃሜት ፈጥሮ- ስታሊን ሲፎክር- አሉላ ሲያቅራራ አብሮ መጥቷልና- የጦሩ አባወራ- የኦመር ሰመተር ልጅ፤ ከታንኩ ላይ ወርደህ- አም
+2
የሶማሌ ተኳሽ- ‹‹እንቢ አልዘምትም›› ብሎ- ቆሟል ከእኛ ጋራ የሚል ሃሜት ፈጥሮ- ስታሊን ሲፎክር- አሉላ ሲያቅራራ አብሮ መጥቷልና- የጦሩ አባወራ- የኦመር ሰመተር ልጅ፤ ከታንኩ ላይ ወርደህ- አምቡላንስ አዘጋጅ።

ከህውሓት ጋር የሚካሄድ ጦርነት ጦርነትን እንደመዋጋትና ሰላምን እንደማምጣት የሚቆጠር ነው፡፡ ይህ ጦርነት… በብሔር ብሔረሰቦች መሃከል ግጭት የሚቀሰቅሰውን….. ዜጋን በዘር የሚከፋፍለውን… እኔ የማልግጣት አገር ጦርነትና ድህነት ያራቁታት የሚለውን…. ሕዝብን በጠላትነት የሚፈርጀውን…. ከሆዱና ከእራሱ ውጭ ለየትኛውም ሕዝብ የማያስበውን……….. የሚሊዮን ሕዝብ መኖሪያ የሆነች አገር አፈራርሶ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ለልጆቹ ማውረስ የሚፈልገውን………….. ኢትዮጵያዊነትን እያስጣለ ግብጻዊነትን እና ባንዳነትን የሚያስተምረውን………… ኑሯችንን እና ሰላማችንን የደመሰሰውን………… ጤናማ ፖለቲካን እና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ተሳትፎን አምክኖ በሤራ መጠላለፍን እና ክሕደትን ያሰፈነውን........... ክፉ መንፈስ እንደመደምሰስ የሚቆጠር ነው፡፡ ህውሓት እስካለ ድረስ ጦርነትና ግጭት ሤራና መከራ፣ ድህነትና እጦት ሕያው ናቸው፡፡ ሌላው ደግሞ ከትሕነግ ጋር የሚደረግ ጦርነት "የእርስ በእርስ" ተብሎ የሚገለጽ ሳይሆን ከግብጽ እና ከሱዳን ብሎም ኢትዮጵያን ማፈራረስ ከሚሹ ምዕራባውያን ጋር የሚደረግ ተጋድሎ ነው። ከዚህ ውጭ ትሕነግ ልክ እንደ ሌሎች ብሔር ብሔረሶች ሁሉ ትግራይን ከኢትዮጵያ ለመነጠል የሚጥር እኩይ ድርጅት እንጂ ትግራይን እና ኢትዮጵያን የሚያስተሳስር እትብት ስላልሆነ በእሱ መደምሰስ የሚታደስ አንድነት ካልሆነ በቀር የሚበጠስ ግንኙነት አይኖርም፡፡ ስለሆነም ሰላምን፣ ኢኮኖሚያዊ እድገትን፣ አገራዊ አንድነትን፣ ፖለቲካዊ መረጋጋትን የምትወድ ከሆነ ከትሕነግ ጋር የሚደረገውን ጦርነት ማገዝ እንጂ ማውገዝ አይጠበቅብህም፡፡ ኢትዮጵያን የምትወዳት ከሆነ ህውሓትን አለመጥላት አይቻልህም፡፡ በትሕነግ መቃብር ላይ ኢትዮጵያ ትዕስር!

አቶ አገኘሁ ተናገረው የተባለውን የወረደ ንግግር ስትሰማ የድምጽ ቅጂውን የለቀቀው አካል ዋነኛ ዓላማ አትርሳ! ‹‹እንዴት እንዲህ ብሎ ይናገራል?›› ብለህ ከመጠየቅ ባለፈም ‹‹ባሁኑ ሰዓት ይሄን ንግግር መልቀቅ ለምን አስፈለገ?›› ብለህ አስብ! የድምጽ ቅጂው በይፋ የተለቀቀው አገኘሁን በመጣል ብአዴንን ለማሻሻል ወይስ የጎጥ ጨዋታ ውስጥ አስገብቶ ሕዝብን ለመከፋፈል?›› ብለህ ጠይቅ! በበኩሌ ከተናጋሪው አንደበት ባለፈ መረጃውን ስለለቀቁት አካላት ሳስብ ቁጭታቸው ሳይሆን ሤራቸው ነው የታየኝ፡፡ ‹‹ብአዴን እያለ ድል ማድረግ ስለማትችሉ ትሕነግን ተውና የክልሉን መሪዎች ታገሉ›› የሚል መልዕክት ነው የደረሰኝ፡፡ ፕሬዝዳንቱ የአንድ አውራጃ እንጂ የአንድ ክልል ስላልሆነ በተናጋሪው ዙሪያ አጥቂና ጠባቂ ሆናችሁ ተሸካሸኩ›› የሚል ድምጽ ነው የተሰማኝ፡፡ "የአማራ ኤሊት ላይ የማወራርደው ሒሳብ አለኝ" ሲል ከርሞ ወደ ጎንደር ኤሊት የወረደው የትሕነግ ቡድን በአገኘሁ ተሻገር ንግግር (ቅንብር) ይሄን የመነጣጠል ሕልሙን ለማሳካት እየጣረ መሆኑን የተረዳሁኝ! ይህ ደግሞ የሚሳካ አይደለም። በግለሰብ ንግግር የሚከፋፈል ሕዝብ ቀርቶ ቤተሰብ የለንም!!

ጥያቄ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ➜ህውሓት የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ሲከፍት ድምጹን የሚያጠፋው መንግሥት ውጊያው ሲጀመር አጸፋውን በመመለስ ፈንታ ምሽጉን አስረክቦ የፕሮፖጋንዳ ጦርነት ውስጥ የሚዘፈቀው ስለምን ይሆን? የዚህ አይነቱ አካሄድ በየግንባሩ የተሰለፈውን ሠራዊት ለስልችትና ለሞራል ውድቀት እያደረገው አይደለም ወይ? ➜በኮረምና አላማጣ የነበረው ጦር ለምን እንደወጣ ግልጽ መረጃ በመስጠት ፈንታ ድብብቆሽ መጫወት ለምን አስፈለገ? ➜አሸባሪ አማጺያንን የሚደመስሰው አየር ሃይላችን ከአየር መንገዳችን ጋር ተቀላቅሎ ሲቪሎችን ማጓጓዝ ጀመረ ወይ? ➜ትሕነግን ለመደምሰስ ከየክልሉ የተውጣጣውን ጦር ዝም ብሎ ከማሰልፍ ይልቅ ጠላትን ለማሸነፍ የሚያስችል የአጭር ጊዜ የአቅምና የአቋም ግንባታ ፈጥሮ ማዝመት አይሻልም ነበር ወይ? ➜ከፍተኛው አመራር የችግኝ ተከላውን ለግብርና ሚኒስቴር አስረክበው የችግር ነቀላው ላይ ቢመክሩና ቢሰማሩ አይሻልም ወይ? ➜የምር ግን ብልጽግና ትሕነግን ደምስሶ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ይፈልጋል ወይ? ‹‹ታግለናል›› ከማለት ባለፈ ‹‹ድል አድርገናል›› ለማለት የሚያስችል ዘመቻ እያካሄደ ነው ወይ? ➜ህውሓት የከባድ መሣሪያ ባለቤት የሆነውና ነፍስ እየዘራ የመጣው በእራሱ ብርታት ወይስ በተጋጣሚው የአመራር ድክመት? ➜‹‹የሒሳብ ማወራረጃ እናደርገዋለን›› እየተባለ ከሚፎከርበት ክልል የወጣ አክቲቪስት የአቶ አገኘሁ ተሻገርን ንግግር በአደባባይ እየዘረገፈ ሕዝብን የመከፋፈያ ቀርቶ የመወያያ ርዕስ ማድረግ ይገባዋል ወይ? ብአዴንስ ከእራሱ የሥልጣን ሽኩቻ ወጥቶ የሕልውና ዘመቻ ቢያደርግ አይሻልም ወይ? በወልቃይትና በራያ ጉዳይስ የያዘው አቋም ተመሳሳይ ነው ወይ?

የህውሓት መንታ ሽንፈት አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ጀግኒት እንዳለችው ‹‹ክልሉን ለማስከበር የአማራ ልዩ ሃይልና ሚኒሻ ከበቂ በላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን አንድነት ለማሳየት ግን የሁሉም ክልል ደጀንነትና ሕብረት ያስፈልጋል፡፡›› ትሕነግ በሽፍትነት ከኖረበት የደደቢት በረሃ ወጥቶ ቤተ-መንግሥት ውስጥ እስኪሸብት ድረስ አማራን በጠላትነትና በአሀዳዊነት ሲፈርጅ ብሎም ይሄን ሕዝብ ይታገሉ ዘንድ ብሔር ብሔረሰቦችን ሲያደራጅ የኖረ ድርጅት ነው፡፡ የብሔር ብሔረሰቦችን ማንነት ማስከበር ቀርቶ ቁጥራቸውን በውል ማወቅ ተስኖት ‹‹ከሰማንያ በላይ›› እያለ አማራ ጠልነት የፌደራሊስትነት መገለጫ ይሆን ይመስል እልም ያለ በዝባዥ አሃዳዊ መንግሥት መስርቶ ሲዘርፍና ሲያወናብድ የኖረ ፓርቲ ነው፡፡ በጌታቸው ረዳ አንደበት ‹‹እሳትና ጭድ›› ተብለው በተገለጹት ሕዝቦች ትግል ከፌደራል ከተባረረ በኋላም ሲነዛቸው የነበሩ ፕሮፖጋንዳዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማንነት ቀምተው በአማራነት የሚፈርጁ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ለእርስ በእርስ መጠፋፋት የሚያዘጋጁ፣ ከአማራዎች ይልቅ ሱዳኖች ወዳጁ መሆናቸውን የሚያውጁ ነበሩ፡፡ የመከፋፈል ፍልስፍናውን በማጠናከርም ከግብጽና ሱዳን የሚላክለትን ድርጎ ኢትዮጵያን መሰነጣጠቅ ለሚፈልጉ ድርጅቶችን ሲያካፍልና ሲያስታጥቅ ነበር፡፡ ኢሳያስን ወዳጅ ማድረግ እንደማይቻል ሲገባውም ኤርትራውያንን ‹‹ቆለኞቹ›› እና ‹‹ደገኞቹ›› እያለ ከመከፋፈል ባለፈ ፕሬዝዳንቱን ለማስገደልም ሲጣጣር ነበር፡፡ (ሌላው ቀርቶ በኢትዮጵያ ሥም የተደራጀውን የሰሜን እዝ ላይም ጥቃት ሲፈጽምም በማንነት ሸንሽኖ ነበር፡፡) ታዲያ የትሕነግ አሸናፊነት በመከፋፈል መርሕ ላይ የተመሠረተ እንደመሆኑ ሽንፈቱና ሞቱ ደግሞ ከኢትዮጵያ አንድነት የሚቀዳ ነው፡፡ በመሆኑም ትሕነግ ከሰሞኑን ያጋጠመው መራር ሽንፈት መንታ ሆኖበታል፡፡ በዚህም መሠረት የሚፎክርበት ታጣቂው በሠዓታት ውስጥ በአማራ ሠራዊት ተለብልቦ ከመሸኙቱም በላይ ከየስፍራው በሚተምመው የኢትዮጵያ ሠራዊት ደግሞ ስነ ልቦናውን አንኮታኩቶ ‹‹ወደ ራያ የሄድኩበት እግሬ በተሰበረ ኖሮ›› ብሎ እንዲመኝ አድርጎታል፡፡ ➜ትሕነግ ብልጥ ነኝ ብሎ የሚያስብ ሞኛ ሞኝ ድርጅት በመሆኑ ሲዳማ ክልል ስትሆን ‹‹እልልልልል›› የሚል መግለጫ ስላወጣ ብቻ የሲዳማ ሕዝብ በእልልታ የሚምታታ ይመስል መላሹን ክዶ ከአፋኙ ጋር የሚሰለፍ ይመስለዋል፡፡ ➜‹‹የትኛውም ሕዝብ ያስባል›› ብሎ ስለማያስብ አንድ የወላይታ መምሕር ጋብዞ ‹‹አጼ ምኒልክ በወላይታ ሕዝብ ላይ ግፍ የመፈጸም ሐሳብ ነበረው›› ማስባል ከቻለ ድፍን የወላይታ ሕዝብ ከእሱ ጋር የተሰለፈ ያህል ይሰማዋል፡፡ ➜ልክ እንደሱ ቀየ ዳውድ ኢብሳና የኦሮሞ ሕዝብ አንድ ሆነው ይታዩታል፡፡ አብዲ ኢሌና ሶማሌ ይምታታበታል፡፡ የሰሞኑ ዘመቻ ታዲያ ወደ ሞት ቀጠና ከሚነዳው ሠራዊት ባለፈ ክልሉን እና እራሱን ሲደልልበት የኖረውን የውሸት ትርክት አፈር ድሜ ያስበላ ነው፡፡ በዚህም መሠረት፡- አገኘሁ ተጣርቶ- ጌታቸው አቅራርቶ- ፎክሮ ሳይጨርስ ከገብርዬ ጋራ- መቃብር ፈንቅሎ- ተነስቶ ቴዎድሮስ በኮረም ማይጸብሪ- ባንዳ እና ከሃዲን- ሲጀምር መደምሰስ የአብደሳ አጋ ወራሽ፥ የአቢቹ፣ የባልቻ ጸረ አገርን መቅበር፥ ማነው የፈቀደው፥ ለአማራዎች ብቻ? ከሚል ጥያቄ ጋር፥ አገሩን ሊታደግ፥ ድንገት ከተፍ ሲል፤ እንቆቆ እየጠጣ አፋሩ፣ ሲዳማው፥ ሶማሌው ደቡቡ፥ ጋምቤላው ሲከተል፤ ያጋጠመው ሽንፈት፥ ያ የአንጀት ኮሶ ትል ከአገሬው ሆድ ወጥቶ- ከኪሲ እንደመጣል፡፡💪 #Share

Exactly
Exactly

አቶ አገኘሁን 'ሽጉጥህን ጠጣው' ሲሉ ለነበሩ ተሸናፊዎች (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖➖ ትሕነጎች ውጊያ ባይችሉም በውሸት ወሬ ግን ነፋስ በጎራዴ የሚከታትፉ ናቸው፡፡ በጥይት ተመትተው ሲያጣጥሩ ብታገኟቸው እንኳን ‹‹እየገደልን ነው›› እንጂ ‹‹ተመትተን ነው›› አይሏችሁም፡፡ ሰሜን እዝን ጨፍጭፈው ጦርነቱን በለኮሱ ማግሥት ሲነዙት የነበረውን ውሸት መለስ ብላችሁ አስታውሱት እስቲ… ጄት እንጥላለን፣ ነፍጠኛውን እንቀብራለን… እያሉ ነበር ከፕላኔት ሆቴል ቆላ ተምቤን ዋሻ ውስጥ የገቡት! ያም ሁኖ ግን የክልሉ ኤሊትና አክቲቪስት ተነጥሎ በማሰብ መርሕ ሃቁን ተጋፍጠው ክልላቸውን ከመታደግ ይልቅ ‹‹ጥይትን በውሸት ማሸነፍ ይቻላል›› የሚለውን የትሕነግን መርሕ ባንድ ልብ ተቀብለው መንኮታኮት የሚመርጡ በመሆናቸው ‹‹በባዶ ትምክሕት በጀመራችሁት ጦርነት ለውድመትና ውርደት ዳረጋችሁን›› ብለው ሊወቅሷቸው አይሞክሩም፡፡ ፡ ይሄን ሁሉ ማለት ያስፈለገኝ እንደነሱ በውሸት ፕሮፖጋንዳ እራሳችንን እንደልል ወይም ደግሞ የክልሉ መንግሥት የሚሠራውንና የሚናገረውን ሳንመረምር ባንድ ልብ እየተቀበልን ለውድቀት እንዳረግ ለማለት አይደለም፡፡ ይልቅስ ‹‹የክልሉን መሪዎች ያላግባብ ሥማቸውን አናጥፋ›› ለማለት ፈልጌ ነው፡፡ ለምሣሌ ያህል አቶ አገኘሁ ተሻገር ‹‹ወልቃይትና ራያን ያስወሰድኩ ቀን ሽጉጤን እጠጣለሁ›› በማለቱ ኢትዮ 360ን ጨምሮ በርካታ የአማራ አክቲቪስቶች መሳለቂያ አድርገውት ነበር፡፡ በበኩሌ ግን በጦርነት ላይ ጠላትን ለመደምሰስ ወደ ፊት መገስገስ ብቻ ሳይሆን ወደ ኋላ መመለስም ግድ የሚል መሆኑን መገንዘብ ቢሳነን እንኳን ‹‹ፈጠን ብለህ ራያን አስመልስ›› ማለት ሲቻል በቅጽበት ውስጥ እራስን ተሸናፊ አድርጎ ‹‹ሽጉጥህን ጉረስ›› እያሉ አቶ አገኘሁን መዝለፍ ልክ አይደለም እላለሁ፡፡ ሰሜን እዝ ላይ ትንኮሳ በፈጸመች ማግሥት ተደምስሳ ብሎም ወልቃይትን ራያን ለባለቤቱ መልሳ የሸሸችውን ህውሓትን ከአሸናፊ ተርታ መድቦ አቶ አገኘሁን ተሸናፊ ማድረግ ስህተት ነው›› እላለሁ፡፡ አንዳንድ የጦር መሪዎችን መዝለፍ ከዲጂታል ወያኔዎች እንጂ ከአማራ አክቲቪስቶች የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ሌላው ቀርቶ አቶ ጌታቸው ረዳንም ስንተች ክብሩን በሚጠብቅ መልኩ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ጌቾ በቀልማዳ ምላሱ በሚነዛው ፕሮፖጋንዳ እስካሁን ድረስ ህውሓትን እንጂ እኛን ጎድቶን አያውቅም፡፡ ለምሳሌ ያህል እሱ ‹‹የአማራ ኤሊት ላይ የምናወራርደው ሒሳብ አለን›› የሚል መረጃ ባይሰጠን ኖሮ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ‹‹ሆ›› ብለን ባልተነሳን ነበረ፡፡ ሲቀጥል ደግሞ ከበላይ አካል በመጣ ትዕዛዝ ጦሩ ከኮረምና አላማጣ ከመውጣቱ ጋር ተያይዞ የጁንታው ልጆች እራሳቸው በለጠፉት ፖስት የሱዳማን ሕዝብ ከጎናቸው አሰልፈው ሲደሰቱ ነበር፡፡ ‹‹የአማራና የኦሮሞ ሕዝብ እሳትና ጭድ ናቸው›› በሚል ንግግሩ ህውሓትን ከፌደራል ያስባረረው አቶ ጌታቸው ረዳ ግን አላማጣ ላይ ሆኖም በብስጭት እየተንተከተከ ‹‹ኢትዮጵያን ለማንም እንዳትበጅ አድርገን እናፈራርሳታለን›› የሚል መረጃ ለኒዮርክ ታይምስ በመስጠት የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ከአማራና ከአፋር ልዩ ሃይል ጋር ተሰልፎ አገሩን ይታደግ ዘንድ ጥሪ አስተላለፈ፡፡ ስለሆነም አላማጣ ገብቶ እናቱን ከጠየቀ በኋላ በሠዓት 120 ኪሎሜትር በመሮጥ ላይ የሚገኘው አቶ ጌታቸው ረዳ ‹‹እቸኩላለሁ›› የማይል ከሆነ በመኪና ልንሸኘው እንጂ ልንዘልፈው አይገባም እላለሁ፡፡ 😁 ፌስቡክ ላይ ሼር ማድረግ እንዳይረሳ!

የኦሮሚያ ልዩ ሃይል "ከአሸባሪ ጋር የሚደረገው ጦርነት ኢትዮጵያን የሚመለከት እንጂ በአማራ ብቻ የሚመከት መሆን የለበትም" በሚል አቋም ከአማራ እና ከአፋር ልዩ ሃይል ጎን ሊሰለፍ ጉዞ ጀምሯል። ድጋ
+1
የኦሮሚያ ልዩ ሃይል "ከአሸባሪ ጋር የሚደረገው ጦርነት ኢትዮጵያን የሚመለከት እንጂ በአማራ ብቻ የሚመከት መሆን የለበትም" በሚል አቋም ከአማራ እና ከአፋር ልዩ ሃይል ጎን ሊሰለፍ ጉዞ ጀምሯል። ድጋፍና እንክብካቤ ለኦሮሚያ ልዩ ሃይል 💪

"ፈርዖን እስራኤላዊያንን ተከትሎ ባይመጣ ኖሮ ከመላው ሠራዊቱ ጋር በኤርትራ ባሕር ሰምጦ አይቀርም ነበር። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ትሕነግም መከላከያን ተከትሎ የሚመጣ ከሆነ በአማራ ልዩ ሃይል ዱላ ሰምጦ
"ፈርዖን እስራኤላዊያንን ተከትሎ ባይመጣ ኖሮ ከመላው ሠራዊቱ ጋር በኤርትራ ባሕር ሰምጦ አይቀርም ነበር። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ትሕነግም መከላከያን ተከትሎ የሚመጣ ከሆነ በአማራ ልዩ ሃይል ዱላ ሰምጦ የሚጠፋበት ባሕር "ተከዜ" ይሆናል" የሚለው ትንቢት ሰምሯል💪 ፌስቡክን በዚህ ፎቶ አጥለቅልቁልኝማ 😁 #Share

5 ሚሊዮን ስንዴ የሚሰፈርለት ሕዝብ ያላት ክልል ማዕበል አስነስታ 50 ሚሊዮን ነፍጠኛ ስትጠራርግ አስበኸዋል? 😁 ማይጠብሪ ላይ ደቁሰናታለን💪