AL MADAD ( المدد )
Open in Telegram
8 612
Subscribers
+324 hours
+237 days
+19030 days
Posts Archive
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ ተፍሲር ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ የጀዋሚዒል ከሊም ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
«የእኔ፣ የእናንተ እና የዚች ዓለም ምሳሌ፣ ጭጋጋማ የበረሃ መንገድን እንደተጓዙ ሕዝቦች ምሳሌ ነው።
የሄዱበት ይበልጣል ወይስ የቀራቸው የሚለውን እንኳን ማወቅ እስከማይችሉበት ደረጃ ከተጓዙ በኃላ ስንቃቸውን ጨረሱ፤ የመጓጓዣ እንስሶቻቸውም ደከሙ፤ በበረሃውም መሀል ላይ ያለ ስንቅ እና ያለ መጓጓዣ ቀሩ። መሞታቸውንም አመኑ።
በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ፣ ከፀጉሩ ውሀ የሚንጠባጠብ ምርጥ ልብስ የለበሰ ሰው ብቅ አለባቸው።
እነሱም፦ “ይህ ሰው ለም ከሆነ መሬት የመጣ ነው፤ ወደ እናንተ የመጣውም ቅርብ ከሆነ ቦታ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም” አሉ።
እነሱ ዘንድ በደረሰም ጊዜ፦ “እናንተ!” አላቸው። እነሱም፦ “አንተ!” አሉት።
እርሱም፦ “በምን ሁኔታ ላይ ናችሁ?” አላቸው።
እነሱም፦ “በምታየው ሁኔታ ላይ ነን” አሉ።
እርሱም፦ “ጥማትን ወደሚያቆርጥ ውሃ እና ወደ ለምለም ጨፌዎች ብመራችሁ ምን ታደርጋላችሁ?” አላቸው።
እነሱም፦ “በምንም ነገር ላይ ትእዛዝህን አንጥስም” አሉት።
እርሱም፦ “በአላህ ስም ቃል ኪዳናችሁን እና መሐላችሁን ስጡኝ” አላቸው።
በምንም ነገር ላይ ላለመቃወም በአላህ ስም ቃል ኪዳናቸውን እና መሐላችውን ሰጡት።
ጥማትን ወደሚያቆርጥ ውሃ እና ወደ ለምለም ጨፌዎች መራቸው።
አላህ የሻውን ያህል ጊዜ ቆዩ።
ከዚያም፦ “አሁን እንጓዝ” አላቸው።
እነሱም፦ “ወደ የት?” አሉት።
እርሱም፦ “ከዚህ ውሃችሁ ወደ ተሻለ ውሃ እና ከዚህ ጨፌዎቻችሁ ወደ ተሻሉ ጨፌዎች” አላቸው።
አብዛኞቹም፦ “በአላህ እንምላለን! ይህንን ያገኘነው ፈጽሞ አናገኘውም ብለን ካሰብን በኋላ ነው። ከዚህ ከበለጠ መልካም ሕይወት ሌላ ምን ያደርግልናል?” አሉ።
ቁጥራቸው ያነሱት ግን እንዲህ አሉ፦“ለዚህ ሰው በምንም ነገር ላይ ላለመቃወም በአላህ ስም ቃል ኪዳናችሁን እና መሐላችሁን አልሰጣችሁትም ነበርን? በመጀመሪያው ንግግሩ እውነተኛ ሆኖላችኋል፤ በአላህ እንምላለን! በመጨረሻውም እውነተኛ ይሆንላችኋል!” አሉ።
ከተከተሉት ሰዎች ጋር ተጓዘ፤ቀሪዎቻቸው ግን ወደኋላ ቀሩ። ጠላትም ድንገት ደረሰባቸው፤ ከፊሉ የታሰሩና ከፊሉ የተገደሉ ሆነው አነጉ።»
*******************
ይሄ ምሳሌ ሰይዳችንﷺ እራሳቸውን ከመሰሉበት ምሳሌዎቻቸው ውስጥ አንዱ ነው:: በዱንያም ምርጡን እና ትክክለኛውን መንገድ እንደመሩን ሁሉ በላጩንና ዘውታሪው የአኼራ ሀገር አሳሳቢ እንደሆነ አመላክተውናል::
አሏህ ለባርያዎቹ ይመጥናቸዋል ብሎ የገነባውን ውድ የጀነት ሀገርንና ልዩ መስተንግዶውን በምንም አይነት መልኩ በዚች በርካሽ ዱንያ የማንለውጥ ብልጦች መሆን ይገባናል::
በሰይዳችንﷺ በረካ ከተመረጡ፣ ከሰይዳችንﷺ ኃላ የሚቀመጡ፣ ከሐውዳቸውም የሚጠጡ፣ መፅሀፋቸውንም በቀኝ እጆቻቸው የሚሰጡ የአሏህ ባርያች አሏህ ያድርገን☺️
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ ተፍሲር ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
ሰይደቲ ዓኢሻ (رضي الله عنها) በሌሊትወቅት አንድ ነገር ትሰፋ ነበር፤ በዚህ መሃል መርፌዋ ጠፋባት፡ መብራቱም ጠፋ። ሰይዳችንም ﷺ በዛች ሰዓት ላይ ወደ እሷ ገቡ፡ በሳቸው ﷺ ብርሃንም ቤቱ በራ፡ መርፌዋንም አገኘቻት።
እሷም፡ «የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ፊትዎ ምንኛ የሚያበራ ነው!» አለች።
እሳቸውም፡ «በቂያማ ቀን እኔን ለማያየኝ ሰው ወዮለት!» አሉ።
እሷም፡ «እርስዎን የማያይዎት ማን ነው?» ስትል ጠየቀች።
እሳቸውም፡ «ስስታም» አሉ።
እሷም፡ «ስስታሙ ማን ነው?»
እሳቸውም፡ «ስሜን በሰማ ጊዜ በእኔ ላይ ሶለዋት (ሰላምና እዝነት) የማያወርድ ሰው ነው» አሉ።
📍 «الدر المنضود في الصلاة والسلام على صاحب المقام المحمود» (ص 195).
*************
ታላቁ የሰይዳችንﷺ ወዳጅ ሰይዲ አህመድ ሐባል ሪፋዒይ እንዲህ ይሉ ነበር : " አላህ ተወዳጁን ነብያችንን ﷺ አንድ ግዜ ቢያሳያቹ ፤ አይናቹ ይሀን ኑርና ውበትﷺ አንድ ግዜ ቢመለከትና ይሀ ኑር ልባቹ ውስጥ ቢገባ ሰለዋት ዐለ ነቢን ﷺ አጠግቡም ነበር .. የሰይዳችንﷺወዳጆች ሆይ .. ሰላትና ሰላም እሳቸው ላይ ማውረድ አብዙ .. እሳቸውን ማየትን አላህ ይቻራቹ .."
አሏህ እሳቸውንﷺያሳየን፣ እሳቸውﷺ ጋር ያቅርበን፣ እሳቸውﷺ ዘንድ ያስወድደን፣ እሳቸውንﷺ ልባችን ላይ ያስበልጥልን☺️
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ የጀዋሚዒል ከሊም ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
መውሊድ ማለት አሏህ ከዋለልን ትልልቅ ጸጋዎች ሁሉ ታላቅ የሆነውን ጸጋ ማስታወሻ ነው ፤ በሰይዳችንﷺ ብርሃን ለዓለም ፈንጥቋል፣ በሰይዳችንﷺ ምክንያት ሰዎች ወደ ቅኑ መንገድ ተመሪዎች ሆነዋል፣ በሰይዳችንﷺ ልቦች በርተዋል፣ ከሰይዳችንምﷺ ወደ አላህ የሚያደርሰውን የፍቅር መንገድ ተምረዋል።
በሳቸው ﷺ ትውስታ ልባችን ሕይወት ይዘራል:: በፍቅር፣ መንገዳቸውን በመከተልና በጥሩ ሥነ ምግባር ከሳቸውﷺ ጋር ያለንን ቃል ኪዳን እምናድስበት ወሳኝ ክስተት ነው።
እንኳን አደረሰን☺️
ተደስተንባቸው እሳቸውም በኛ የሚደሰቱብን ውድ የሰይዳችንﷺ ወዳጆች አሏህ ያድርገን
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
በጊዜው የመዲና ከተማ መሪ የነበረው ሳሊም ቢን ቃሲም ለታላቁ መሪና ጀግና ሰላሑዲን አል-አዩቢ በሰይዳችንﷺ ረውዳ አቅራቢያ ከበቀለ ዘንባባ የተሰራች ነጭ ማራገቢያ በስጦታ መልክ አዘጋጀላቸው።(በሙቀት ሰአት ፊታቸውን ለቅዝቃዜ ያራግቡበት ነበር)
ልክ ሲሰጣቸውም ፡ «እርሶም ሆኑ አባቶቻቹ እንደዚች ያለች ስጦታ አላዩም» አላቸው። ሱልጣን ሰላሀዲንም በንግግሩ ተናደው ማራገቢያዋን ከእጁ ሲቀበሉት፣ በእሷ ላይ እነዚህ ስንኞች ተፅፎ አገኙ ፡
أنا من نخلةٍ تُجاورُ قَبرَا
سادَ مَن فيه سائرَ الخلقِ طُرَّا
شَمِلَتني سعادةُ القَبر حتَّى
صرتُ في راحةٍ ابن أيُّوب أُقرَا
“..እኔ ፍጥረታትን በሙሉ የላቁት ነብይﷺ ካሉበት መቃብር አጠገብ ካለች አንዲት ዘንባባ ተቆረጥኩኝ፣”
“የመቃብሩ በረካ እኔንም አጠቃሎኝ በኢብን አዩብ መዳፍ ላይ ሆኜ ለመነበብ በቃሁኝ”.. እንደማለት ነው
ሱልጣን ሰላሀዲን አል-አዩቢም ይህን ባነበቡ ጊዜ ስጦታውን ተቀብለው ራሳቸው ላይ በክብር አድርገውት ፤ «እውነት ተናገርክ! እውነት ተናገርክ!» ብለው በክብር ግምጃ ቤታቸው ውስጥ እንድትጠበቅ አዘዙ።
**************
እሳቸውንﷺ ያከበረ በሁለቱም ሀገር ይከብራል:: የእውነት አክባሪም እሳቸውንምﷺ ከሳቸው የቀረበን ነገርንም ሁሉ ያከብራል ይወዳል:: በታሪክም ደረጃ በንጉስም ይሁን በዓሊም ዓለም ከእሳቸውﷺ ጋር ያለው ትስስር የጠነከረው ነው በረካቸው ደርሶት ለዲንም ለዱንያውም ለአኼራውም ትርፍ አትርፎ የተጏዘው::
በሰይዳችን ﷺ በረካ የምናተርፍ፣ ከአሏህ ቁጣ የምንተርፍ፣ በፍቅራቸው የምንከንፍ፣ በሱናቸውም የማንሰንፍ አሏህ ያድርገን☺️
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ ተፍሲር ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ ተፍሲር ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
በተወለዱበት ወር፣ ሰለዋት አብዙብኝ ባሉባት ለሊት፣ ሰለዋትን አብዝተው፣ ሰይዳችንምﷺ ጋር ተሰምተው፣ ጀማላቸውንﷺ አይተው፣ ልባቸውን በሳቸው ፍቅር ሞልተው፣ እሳቸውን እሳቸውንﷺ ሸተው ከሚያነጉ ውድ ባርያዎቹ አሏህ ያድርገን☺️
የሰለዋትን ኑር እንድንለብስ፣ ዘላቂ ክብርና ጥቅምን እንድናገኝ በተመረጡት ሰይዳችንﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድን እናብዛ፤ በማታም ሆነ በጠዋት ምላሳችንን በሰለዋት እናርጥብ።
በሰይዳችንﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድ በጁሙዐ ሌሊትና ቀን ላይ ብቻ የሚፈጸም ስርዓት ሳይሆን፤ የዕድሜ ልክ ተግባር፣ ለሳቸውምﷺ ያለንን ክብርንና ምስጋናን መግለጫ ነው።
በተለየ ደግሞ የጁሙዐን ቀን በበለጠ ሰላዋት ለይተን እናስውበው። በሰለዋት አላህ ልባችንን ያሰፋልናል፣ ወንጀላችንን ይምርልናል፣ ጭንቀታችንንም ይበቃናል።
ሰይዳችንﷺ ሰለዋትን ለሚያበዛ ሰው፦“እንግዲያውስ ጭንቀትህ ይበቃሃል፣ ወንጀልህም ይማርልሃል” ብለዋል።
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
"ከአሏህ የሆነ መልካምን እና ጭማሪ ስጦታን ከማየት አልተቋረጥንም.."
ይህ የሰይደቲ ሐሊማ (رضي الله عنها) ሰይዳችንንﷺ አቅፋ ቤቷ ካስገባች ቡኃላ ያገኘችውን ኒዕማና ችሮታ ዘርዝራ የጨረሰችበት ማጠቃላያ ንግግሯ ነው::
ኢማሙል ቡሰይሪ'ይ ይሀን ክስተት ሲናገሩ:
أخصب العيشُ عندها بعد مَحلٍ *** إذ غدا للنبي منها غِــذاءُ
"..እሷ ዘንድ ቢቀለብ የዓለሙ ጥላﷺ
ህይወቷ ለም ሆነ ከችግር ቡኃላ .."
ሰይደቲ ሐሊመት ከሰው ወደኃላ ቀርታ፣ተንከራታ፣ደክማ፣ ተቀደምኩ ብላ፣ ተስፋ ቆርጣ መካ ብትደርስም የትልቆች ሁሉ አለቃﷺ፣ የበላጮች ሁሉ መሪﷺ፣ የፍጥረታቱን ሁሉ አይነታንﷺ የሆኑትን አቅፋ ቀድማለች፣ነግሳለች::
እሳቸውንﷺ ያገኘ ቢቆይም ቀድሟል፣ ቢቆምም ደርሷል፣ ባይሰራም አፍሷል፣ ቢደክምም በልጧል።
እሳቸውንﷺ ውስጣችን እናድርግ፣ ልባችን ውስጥ ይንገሱ፣ ህይወታችንን ይላበሱ፣ ከዛ ይሀን የማይቋረጥ ኸይርና የአሏህን ኒዕማ ሳይቋረጥ ሲፈስብን እናያለን::
አሏህ ፍቅራቸውን ከተቸሩ፣ በሸውቃቸውም ከሰከሩ ባርያዎች ያድርገን☺️
8 612
✅ ዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻ የጀዋሚዒል ከሊም ደርስ ይኖረናል ኢንሻአሏህ
ቦታ : ጠሮ- ዑስማን ቢን ዐፋን መስጊድ
አህለን ወሰህለን
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
8 612
“የሰይዳችንﷺ ዓይን ሰፋፊና ቆንጆ፣ የዐይናቸው ብሌን በጣም ጥቁር፣ ሽፋሽፍቱም ረዥም፣ ዐይነ‐ኩሌ በአዘል የተኳሉነበሩ..ﷺ"
ይሄ የዟሂሩ የዓይናቸውን ማማር ነው የነገሩን ::የሚያዩትናﷺ ያዩት ከታሰበማ የዛን ዓይን ሚስጥር ማን ሊያውቀው ! አሏህን ማየት የታደለ ዓይን እኮ ነው ::
ዓይኑ ሲርገበገብ ሲከፈት ሲከደንﷺ
ይመስላል ያየውን በጀማል ለማደን☺️
ጌታዬ በዛ ዓይን በዛ ጀማል የመታደን እድሉን አድለን
#ረቢዑልቁሉብ
T.me/Ustaz_shemsudin_hamza
