Ethio-Jan Construction. ኢትዮ-ጃን ኮንስትራክሽን
Open in Telegram
🔨እጅግ ጠቃሚ የ ኮንስትራክሽን እውቀቶች🔖 📄በ አማርኛ እና ኢንግሊዘኛ ማንኛውም መረጃ ለማግኘት YouTube ቻናላችን ይቀላቀሉ 👉👉👉 channel https://www.youtube.com/channel/UCgeGlbMAAI_ooU7yiYPX0Ng
Show more2 082
Subscribers
+224 hours
+177 days
+10930 days
Posts Archive
💥የሕንፃ አዋጅ ለተቋራጮች ይነበብ🛑🛑
የሕንፃ አዋጅ ቁጥር 624/2001 መሰረት የአዋጁን ድንጋጌዎች በመተላለፍ የግንባታ ሥራ ፈቃድን በሚሰጡ የመንግሥት ኃላፊዎች እና ይህንኑ እንዲያከናውኑ ሃላፊነት በተሰጣቸው ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች፣ በተመዘገቡ ባለሙያዎች ወይም ሥራ ተቋራጮች፣ እንዲሁም በግንባታ ባለቤቶች የሚፈፀሙ ጥፋቶች እንደሁኔታው ከ6 ወር ጀምሮ እስከ 15 አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከ500 (አምስት መቶ) ብር እስከ 50000 (ሀምሳ ሺ) ብር የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ተደንግጎ ይገኛል፡፡
በተጨማሪም በ1996 የወጣው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 501 የህንጻ ስራ ደንቦችን መጣስ በሚል ርእስ ስር ማንም ሰው ማንኛውንም አይነት የህንጻ ስራ ወይም የህንጻ ማፍረስ ስራ ሲቆጣጠር፣ ሲመራ ወይም ሲፈጽም በህግ የተደነገገውን ወይም በህንጻ ስራ ሙያ ወይም ልምድ የሚሰራባቸውን የጥንቃቄ ደንቦችን አስቦ በመጣስ የህዝብን ደህንነት ወይም የሰዎችን ሕይወት፣ ጤንነት ወይም አካል ወይም የሌላውን ሰው ንብረት አደጋ ላይ የጣለ እንደሆነ ከ3 ወር በማያንስ ቀላል እስራት እና በመቀጮ የሚቀጣ ሲሆን ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኝነት እንደ ሆነ ከ1 አመት በማይበልጥ ቀላል እስራት እና በመቀጮ እንደሚያስቀጣ ያመለክታል፡፡
በአጠቃላይ ማንኛውም የሕንፃ ግንባታ ሥራ በሚከናወንበት ወቅት ጉዳት እንዳያደርስ የግንባታ ሥፍራውን ተቀባይነት ባላቸው ቁሶች መከለል፣ በቁፋሮ ወቅት ከመሬት በታች ሊኖሩ የሚችሉ የመሠረተ ልማት መሥመሮች እንዳይጎዱ፣ በአካባቢው የትራፊክ እንቅስቃሴ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ለመከላከል፣ ተቀጣጣይነት ያላቸውን የግንባታ ቁሳቁሶች በአያያዝ ጉድለት ለእሳት አደጋ እንዳይጋለጡ በማድረግ፣ በግንባታ ሥራ ላይ ለተሠማሩ ሠራተኞችና ጐብኚዎች የደህንነት መጠበቂያዎችን በማሟላት፣ ለግንባታ የሚውሉ የኬሚካል ውጤቶች በአጠቃቀም ወቅት በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ እና ብናኝ ጭስና አንጸባራቂ ጨረር የመሳሰሉ አዋኪ ነገሮች አካባቢውን እንዳይረብሹ ተገቢው ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት በህጉ ተደንግጎ ይገኛል፡፡
@Ethiojan_construction
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች የተጠየቀከትን ጥያቄዎች video አዘጋጅተናል በቅርቡ እንለቃለን
⚠️በተጫማሪ አዳዲስ ስልጠናዎች ለመጀመር አስበናል
👇👇👇👇👇👇👇👇
የ ETABS ፣ SKETCHUP ፣ ARCHICAD እና BLENDER
👉ሀሳባችሁን ኮሜንት ላይ ግለጹልን
👉ኮንስትራክሽን
🚧አስገዳጁ ረቂቅ አዋጅ . . .
🌟የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ፤ ትላልቅ ተቋራጮች ከአነስተኛ የግንባታ ተቋራጮች ጋር በጥምረት እንዲሠሩ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
ረቂቁ በሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ቀርቦ እንደሚገመገም ተገልጿል።
ረቂቁ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ ሲደረግ በኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማረም በአገሪቱ የሚገኙ ትላልቅና ዋና ዋና ተቋራጮች ከአነስተኛ ትናንሽ ተቋራጮች በጥምረት እንዲሠሩ ዕድሉን የሚፈጥር ነው ተብሏል።
ረቂቅ ህጉን በአስገዳጅነት እንዲዘጋጅ የተደረገው አነስተኛ አቅም ያላቸው ተቋራጮች ሰፊ ልምድና አቅም ካላቸው ተቋራጮች ጋር በመሥራት ልምድ እንዲያገኙና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ በማሰብ ነው ተብሏል።
አነስተኛ ደረጃ ያላቸው ተቋራጮች ያልተገባ ተግባር ሲፈጽሙ ተጠያቂ እንዲሆኑ እና ክፍያ ላይም ምንም ዓይነት ችግር እንዳይገጥማቸው የሚያስችል ሕግ መሆኑ ተገልጿል።
አዋጁን በማርቀቅ ሂደት ፦
- የሕንፃ አማካሪ ድርጅቶች፤
- የሕንፃ ተቋራጭ ማህበራት፤
- በአገሪቱ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች፤
- ፕሮጀክት ያላቸው አካላት፤
- የገንዘብ ሚኒስቴር፤
- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
- በኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚሠሩ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እንደተሳተፉበት ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ፤ አነስተኛ ደረጃ ያላቸው የግንባታ ተቋራጮች እራሳቸውን ብቁ አድርገው መንግሥት በሚያሰማራቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ድርሻ ይዘው ለመሥራት ከወዲሁ ዝግጅት ያድርጉ ብሏል።
@ethiojan_construction
#ETHIOJAN+CONSTRUCTION
🚫ውድ የኢትዮጃን ኮነስትራክሽን ቤተሰቦች
Video እንዳልቅ ቻናላችን ላይ ያጋጠመን ችግር አሁንም ባለመስተካከሉ ስለሆነ በቅርቡ እንደተስተካከለ በቆንጆ ሀሳብ እንመለሳለን በ telegram የጠየቃችሁትን ጥያቄዎችም ለመመለስ እንሞክራለን ።
👉ቻናሉን ማስተካከል የሚችሉ Youtuber ካሉ በዚ link @ethiojancon እንድታናግሩን እንጠይቃለን
እንደተለመደው ከጎናችን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ውድ የኢትዮጃን ኮነስትራክሽን ቤተሰቦች
የ Youtube ቻናላችን ላይ ትንሽ ችግር ተፈጥሮ እሱን በማስተካከል ለ1ወር በመጥፋታችን በጣም ይቅርታ በቅርቡ እንደተስተካከለ በቆንጆ ሀሳብ እንመለሳለን
የጠየቃችሁትን ጥያቄዎችም ለማድረስ እየሰራን እንደተለመደው ከጎናችን እንድትሆኑ እንጠይቃለን 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
