en
Feedback
Borkena

Borkena

Open in Telegram

Ethiopian News

Show more
7 256
Subscribers
+1724 hours
+237 days
+17730 days
Posts Archive
Borkena
7 257
አማራን የከዳ ፥ ውጉዝ ከመ አሪዮስ ፤ የቆመበትም መሬት ትክዳው!  https://shorturl.at/m0zpt #Ethiopia #politics #tsemdo #EthiopianPolitics 

Borkena
7 257
የደረጀ ገረፋ ስልታዊ የማንነት ድምሰሳ ጥሪ (ከምንያህል አጋ) https://shorturl.at/bwF8n #Ethiopia #politics #oromumma  #EthiopianPolitics #EthiopianPolitics 

Borkena
7 257
አገራዊ አንድነትን እና የዜጎች ሰላምን የማስከበር አካል ለሆነው የዐማራው የኅልውና ትግል  አጋር ማነው? ትብብር ለምን ዓላማ እና ልዕለ ግብ? በምን ሁኔታ እና ከማን/ከነማን ጋር?  https://shorturl.at/nXflv #Ethiopia #politics #tsemdo #EthiopianPolitics 

Borkena
7 257
ሶስት ንጹሃን በትግራይ በድሮን ጥቃት ተገደሉ ፤ "ህወሓት ኃላፊነት የማይሰማው ነው" ኦባሳንጆ ፡፡ https://youtu.be/9_0_Y8909Nk #Ethiopia #News #Ethipoiannews #TPLF #Dronestrike #TPLF #Obassanjo  #BorkenaChannel  

Borkena
7 257
ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ በህወሓት መሪዎች ለቀረበባቸው ቅሬታ ምላሽ ሰጡ። ኦባሳንጆ በማሸማገል ሂደታቸው ከፌደራል መንግሥቱ ትዕዛዝ እንደማይቀበሉ እና ህወሀትን ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲሉ ተችተዋል። የትግ
ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ በህወሓት መሪዎች ለቀረበባቸው ቅሬታ ምላሽ ሰጡ። ኦባሳንጆ በማሸማገል ሂደታቸው ከፌደራል መንግሥቱ ትዕዛዝ እንደማይቀበሉ እና ህወሀትን ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲሉ ተችተዋል። የትግራይ ጦርነትን ያበቃው የፕሪቶሪያ ስምምነት አሸማጋይ የሆኑት የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ በህወሀት መሪዎች ገለልተኛ አይደሉም በሚል ለቀረበባቸው ክስ ምላሽ ሰጥተዋል። ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ፍጥጫ ውስጥ የገቡት የህወሓት መሪዎች ትላንት ባወጡት መግለጫ የቀድሞውን የናይጄሪያ መሪ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የገለልተኛ አደራዳሪነት መርኅ አልታየባቸውም በማለት ወቅሷል። ኦባሳንጆ ለቀረበባቸው ወቀሳ በጽህፈት ቤታቸው በኩል ባወጡት መግለጫ ላይ በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ የፕሪቶሪያን ስምምነት የሚጥሱ ሙከራዎች እንዲሁም "ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ጠብ ጫሪ" ሁኔታዎች መታየታቸው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲጀምሩ ምክንያት እንደሆናቸው ጠቅሰዋል። በማሸማገል ሂደታቸው ከፌደራል መንግሥቱ ትዕዛዝ እንደማይቀበሉ እና ትኩረትን ለማግኘት ጥንቃቄ የሚፈልጉ እና ምሥጢራዊ መረጃዎችን ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ኃላፊነት የጎደለው ነው ብለዋል። አንዳንድ የህወሓት አመራሮች ለራሳቸውን አጀንዳ እንዲመች ጥረቱ ለማጣጣል ሲሞክሩ የአሁኑ የመጀመሪያው እንዳልሆነ በመጥቀስ በፕሪቶሪያው ድርድር ወቅትም ተመሳሳይ ሙከራ አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል ብለዋል። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #tplf #tigray #obasanjo #ኢትዮጵያ #ትግራይ #አብይ_አህመድ #ህወሀት #ኦባሳንጆ #ደብረጽዮን #ፕሪቶሪያ #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና

Borkena
7 257
በቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በደረሰ የፀጥታ ችግር ምክንያት ኩባንያው ሥራውን አገደ። ​የእንግሊዙ ከፊ ወርቅ እና መዳብ ልማት ኩባንያ በርካታ የፀጥታ አካላት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና አንድ የኩባን
በቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በደረሰ የፀጥታ ችግር ምክንያት ኩባንያው ሥራውን አገደ። ​የእንግሊዙ ከፊ ወርቅ እና መዳብ ልማት ኩባንያ በርካታ የፀጥታ አካላት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና አንድ የኩባንያው ሰራተኛ ሕይወታቸው ያለፈበትን የፀጥታ ክስተት ተከትሎ በኢትዮጵያ የሚያካሂደውን የቱሉ ካፒ ወርቅ ማውጣት ፕሮጀክት ማገዱን አስታውቋል። ​ኩባንያው ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አደጋው የተከሰተው ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በሰው ሕይወት መጥፋት በእጅጉ ማዘኑን በመግለጽ ለተጎጂዎች እና ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል። ​ከአካባቢው የሕብረተሰብ ተወካዮች፣ ከኢትዮጵያ የመንግሥት አካላት እና ከፀጥታ ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ አካባቢ እስኪፈጠር ድረስ ሁሉንም የፕሮጀክት ዝግጅትና ልማት እንቅስቃሴዎች በጊዜያዊነት ማገዱን ገልጿል። ​ኩባንያው በመግለጫው የሰራተኞቻችን፣ የኮንትራክተሮች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ደኅንነት ለኩባንያችን ከፍተኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ሲል ገልጾ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ መኖሩ እስካልተረጋገጠ ድረስ ወደ ሥራ እንደማይመለስ አረጋግጧል። መንግስት በበኩሉ ኢትዮጵያ አስተማማኝ ሰላም ያለባት እና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሀገር መሆኗን በተደጋጋሚ ይገልፃል። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #oromia #mining #አብይ_አህመድ #ሽመልስ_አብዲሳ #ኦሮሚያ #ንፁሃን #ግድያ #ማዕድን #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና

Borkena
7 257
በትግራይ 3 ሰዎች በድሮን ጥቃት ተገደሉ። አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ ማይ ሽመት ልዩ ቦታ ላይ ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮ
በትግራይ 3 ሰዎች በድሮን ጥቃት ተገደሉ። አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ ማይ ሽመት ልዩ ቦታ ላይ ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮን ደብደባ መፈፀሙ ታውቋል። የድሮን ጥቃቱ ኢላማ የህውሃት የጦር መሳሪያ ክምችት ላይ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ህውሃት በበኩሉ በጥቃቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሦስት ሰዎች የአራት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ ሲሞቱ፣ የሟቾች እናት ደግሞ በጽኑ መቁሰላቸውንና በንብረት ላይም ከባድ ውድመት መድረሱ አሳውቋል። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #Tigray #drone_attack #ትግራይ #ህንጣሎ #የድሮን_ጥቃት #ንፁሃን #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና

Borkena
7 257
The First Customer Question Should Change the Product Record. Read more.  https://borkena.com/the-first-customer-question-should-change-the-product-record/ #Ethiopia #China #Business #customerquestion 

Borkena
7 257
Catholic Church  Installed   Abba Tsefaselassie as Archbishop of Addis Ababa. Read more.   https://borkena.com/abba-tsefaselassie-installed-as-archbishop-of-addis-ababa/ #Ethiopia #News #CatholicChurch #AddisAbaba 

Borkena
7 257
Ethiopia at a Crossroads: The Strategic Case for a Broad National Political Alliance. Read more.   https://borkena.com/ethiopia-at-a-crossroads-the-strategic-case-for-a-broad-national-political-alliance/#Ethiopia #Politics #Coalition #Tsemdo 

Borkena
7 257
A New Geopolitical Strategy For The Gulf Of Aden And Bab El-Mandeb. Read more.  https://borkena.com/a-new-geopolitical-strategy-for-the-gulf-of-aden-and-bab-el-mandeb/ #GulfofAden #BabElMandab 

Borkena
7 257
Fano Urge Families To Enroll Their Children For This Academic Year. Read more.   https://borkena.com/ethiopia-fano-urge-families-to-enroll-their-children-for-this-academic-year/ #Ethiopia #Fano #Amhara #EthiopianNews 

Borkena
7 257
Abeshige District Residents Plan Border March Amid Oromia Security Tensions. Read more.   https://borkena.com/ethiopia-abeshige-district-residents-plan-border-march-amid-oromia-security-tensions/ #Ethiopia #Gurage #Oromummaa #news #EthiopianNews 

Borkena
7 257
Somaliland President Arrives in Washington to Push for Recognition. Read more.   https://borkena.com/somaliland-president-arrives-in-washington-to-push-for-recognition/ #Somaliland #USA #recognition

Borkena
7 257
SputnikPro Partners Discuss Project Experience. Read more.  https://borkena.com/sputnikpro-partners-discuss-project-experience/ #Sputnik #Africa @sputnik_afrique

Borkena
7 257
ቦርከና ቻናላችንን ስብስክራይብ ያድርጉ፡፡ ዜናዎቻችንን ሼር ያድርጉ፡፡  youtube.com/@borkenamedia #ቦርክና #ዜና #EthiopianNews #BorkenaChannel

Borkena
7 257
ፋኖ በ2019 ትምሕርት ቤቶች ስራ እንዲጀምሩ ቅስቀሳ ጀመረ። የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ - አፋብን በተቆጣጠራቸውና በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ያሉ ትምሕርት ቤቶች በአዲሱ ዓመት ስራ እንዲጀምሩ ጥ
ፋኖ በ2019 ትምሕርት ቤቶች ስራ እንዲጀምሩ ቅስቀሳ ጀመረ። የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ - አፋብን በተቆጣጠራቸውና በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ያሉ ትምሕርት ቤቶች በአዲሱ ዓመት ስራ እንዲጀምሩ ጥሪ ማድረጋቸው ተሰምቷል። ባለፉት ሦስት ዓመታት ትምሕርት ስራ እንዳይካሄድ ክልከላ ጥለው የቆዩት አንዳንድ የፋኖ ታጣቂዎች ተቆጣጥረዋቸው በቆዩት የክልሉ አካባቢዎች ተቋርጦ የቆየው የትምህርት አሠጣጥ ሂደት እንዲጀመር ለተለያዩ አደረጃጀቶቹ መመሪያ አስተላልፈዋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ -አፋብን አመራሮች ገደቡን ሙሉ በሙሉ ማንሳታቸውን ለአካባቢው ማህበረሰብና ለመምህራን ነግረዋቸዋል ነው የተባለው። የቡድኑን ውሳኔ ተከትሎ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዲያስመዘግቡ ቅስቀሳ ማድረግ መጀመራቸው ቦርከና ከዋዜማ ዘገባ ያገኘው መረጃ ያመላክታል። ባለፉት ሦስት ዓመታት፣ ታጣቂዎቹ በተቆጣጠሯቸው በርካታ የገጠር አካባቢዎች ትምህርት ተቋርጦ የቆየ ሲሆን፤ በተለይም በጎጃም ዞኖች ከከተሞች ውጪ የሚገኙ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉና በከፊል ተዘግተው ይገኛሉ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የክልሉም ሆነ የፌዴራል መንግስት የሰጠው ማብራሪያ የለም። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #Abiy_Ahmed #Zemene_Kassie #Amhara_fano #ኢትዮጵያ #ፋኖ #አብይ_አህመድ #ዘመነ_ካሴ #ትምህርት #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና

Borkena
7 257
ቻይና በአባይ ጉዳይ ላይ የግብጽን ህጋዊ ጥቅም እደግፋለሁ አለች ፤ ፋኖ በአማራ ክልል ትምህርት እንዲጀመር ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡  https://youtu.be/FIdZTZiav-A?si=lIPOnUwWgUaooh_e #Ethiopia #News #EthiopianNews #AmharicNews #Fano #Egypt #China 

Borkena
7 257
ግብጽ ጥቅሟን የማስከበር ህጋዊ መብት አላት - ቻይና ቻይናው አባይን በተመለከተ ለግብጽ እውቅና ሰጠች። ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ በግብፅ ባደረጉት ጉብኝት የሰጡት መግለጫ የግብፅን የውሃ ሀብት ተጠቃሚነ
ግብጽ ጥቅሟን የማስከበር ህጋዊ መብት አላት - ቻይና ቻይናው አባይን በተመለከተ ለግብጽ እውቅና ሰጠች። ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ በግብፅ ባደረጉት ጉብኝት የሰጡት መግለጫ የግብፅን የውሃ ሀብት ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ነው ተብሏል። የሁለቱ አገራት መሪዎች ያወጡት የጋራ መግለጫ ግብፅ ከኢትዮጵያ የምትወዛገብበትን የአባይ ውሃ ጉዳይ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የአዲስ አበባ ዋነኛ አጀንዳ የሆነውን የቀይ ባሕር ጉዳይን አንስቷል። በግብፅ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ይፋ ያደረገው የጋራ መግለጫ ሁለቱ አገራት አንዳቸው የሌላኛቸው መሠረታዊ ጥቅሞች እና ዋና ስጋቶችን በተመለከተ የማይናወጥ የጋራ ድጋፍ እንዳላቸው ጠቁሟል። የቻይና ወገን ናይል ወንዝ የግብፅ ዋነኛ የሕይወት መስመር በመሆኑ ያለውን ወሳኝ ጠቀሜታ እንደሚረዳ ያረጋግጣል ይላል መግለጫው። ግብፅ የውሃ እና የምግብ ዋስትናዋን እንዲሁም የልማት ጥቅሞቿን የማስጠበቅ ሕጋዊ መብት እንዳላትም ቻይና በዚህ መግለጫ እውቅና ሰጥታለች። በተጨማሪም ሁለቱም ወገኖች ሁሉም የናይል ተፋሰስ አገራት ጉዳት ያለመፍጠር ግዴታን መወጣትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ሕግን እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርበዋል። የቀይ ባሕር ጉዳይ በተነሳበት የመግለጫው ክፍል ላይ ደግሞ፣ ፕሬዝዳንት ዢ እና የግብፅ ፕሬዝዳንት አልሲሲ በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋትን የማጠናከር ተግባር የቀጣናውን አገራትን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማክበርን እንደሚጠይቅ ገልፀዋል። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #China #Egypt #nile #red_sea #ኢትዮጵያ #ዢ_ጂፒንግ #ቻይና #ግብፅ #አባይ_ወንዝ #ቀይባህር #ጂኦፖለቲካ #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና

Borkena
7 257
በትግራይ ክልል ዩኒቨርስቲዎች ተማሪ ላይመደብ ይችላል ተባለ። በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክል
በትግራይ ክልል ዩኒቨርስቲዎች ተማሪ ላይመደብ ይችላል ተባለ። በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግቢ ውስጥ የሚገኙ የጦር ቄስፎች እና ታጣቂዎች በአስቸኳይ እንዲነሱና ግቢዎቹ ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲደረጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል። ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች በላኩት ደብዳቤ፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ ኃይሎችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው የተማሪዎችን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር-ማስተማር ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ አክሎም፣ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው በበቂ ሁኔታ ካልተረጋገጠ ሚኒስቴሩ ወደ ተቋማቱ ተማሪዎችን እንደማይመድብ አስታውቋል። በጦርነቱ የተጎዱ እና የቆሰሉ ታጣቂዎች ሰሞኑን ወደ አዲግራት፣አክሱምና መቀሌ ዩኒቨርስቲ ሲገቡ እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል። #Ethiopia #ethiopia_today #ethiopian_news #addis_ababa #amharic_news #borkena_news #tigray #ministryofeducation #ኢትዮጵያ #አብይ_አህመድ #ትምህርት_ሚኒስቴር #ትግራይ #ብርሃኑ_ነጋ #ዩኒቨርሲቲ #አማርኛ_ዜና #ዜና #ቦርከና_ዜና