ጃን ያሬድ | Jan Yared
Open in Telegram
እግዚአብሔርን አመስግኑ ምህረቱ ለዘላለም ነውና!!! ማን ነው ህይወትን ማግኘት የሚፈልገው ማን ነው ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል መማር የሚፈልገው ማን ነው ስለ እመብርሀን ስለ ድንግል ማርያም መማር ማወቅ የሚፈልገው እንግዲያውስ አሁንኑ ይፍጠኑ እና ይቀላቃሉ
Show more1 460
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-2930 days
Posts Archive
1 460
Repost from ተዋሕዶ ርትዕት (ዘዳግም ቲዩብ)
‼ሓደ መዓልቲ ቀርይዎ ‼
#You_Tube ፕሮግራምና ክጅምር እዩ ኩክካትኹም እናኣተኹም #Subscribe, #Share ,#Like ክትገብሩ ነተሓሳሳብ ።
👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@Abotatna1
1 460
If you want to learn, and Order any Design or Animation. ❇️Graphics Design
❇️Motion Graphics
❇️Brand Design/Logo
❇️3D Animation,Modeling
❇️Video Editing
please call us! ✅@0903189956 @AschuGraphics
1 460
ዐሥራ ሦስት የአብነት ደቀ መዛሙርት ዲቁና ተቀበሉ
| ጃንደረባው ሚድያ | ግንቦት 6 2016 ዓ.ም.|
አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በጃን እስጢፋኖስ ላለፉት ሁለት ዓመታት በአዳር የአብነት ትምህርት ያስተማራቸውንና መሥፈርቱን ያሟሉ ዐሥራ ሦስት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሄኖክ አንብሮተ ዕድ ማዕረገ ዲቁናን ተቀብለዋል:: የኢጃት ቦርድ ሰብሳቢ ዲ/ን ዶ/ር ዳዊት "ኢጃት ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በጃን ማዕተብ ከሰባ በላይ ንዑሰ ክርስቲያንን ለምሥጢረ ጥምቀት ፣ ብዙኃንን በጃን ዮሐንስ ለምሥጢረ ንስሓና ቁርባን ፣ በጃን ቃና ዘገሊላ ደግሞ ለምሥጢረ ተክሊል ያበቃ ሲሆን አሁን ደግሞ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ለምሥጢረ ክህነት አብቅቶአል" ብለዋል::
"ዲያቆናቱ በአግባቡ የተማሩና ለአገልግሎት ዝግጁ የሆኑ ናቸው" ያሉት የጃን እስጢፋኖስ ሰብሳቢ መምህር ኤፍሬም ሲሳይ ሲሆኑ "ተማሪዎቹ ምንም ዓይነት ትምህርት ሳይኖራቸው ወደ ኢጃት መጥተው በአግባቡ ተምረው ለዚህ በመብቃታቸው እጅግ ደስ ብሎናል:: ትምህርት ሳይጨርሱ ወዴትም እንዳይሔዱ በማስገደድም በአበው ልማድ መሬት ላይ እየተኙ በሌሊት እንዲማሩና ከአብነት ትምህርቱ ጋር መሠረታዊ ነገረ ሃይማኖትም እንዲማሩ ተደርጓል" ብለዋል:: በማያያዝም "በቅርቡ ሱባኤ እስጢፋኖስ የተሰኘ የዲያቆናት ብቻ ሱባኤ ጉባኤ ለማካሔድም ዝግጅታችንን ጨርሰዋል ብለዋል" ዲያቆናቱን አስተምረው ለዚህ ካበቁ መምህራን መካከል አንዱ የሆኑት መምህር ኃይለ ኢየሱስ ተሻለ በበኩላቸው "ወደ አገልግሎት ለመግባት በአግባቡ ደጅ ጸንተውና የአገልግሎቱን ምንነት ተረድተው ለዚህ መብቃታቸው ቤተ ክርስቲያንን የበለጠ ለማገልገል ያስችላቸዋል:: ለዚህ ደርሰው ማየታችን ለኢጃት ትልቅ ደስታ ነው" ብለዋል::
1 460
ነጻ የሚያወጣ ፍቅር
|ጃንደረባው ሚድያ | መጋቢት 2016 ዓ.ም.|
✍🏽 ዮርዳኖስ ዘሪሁን እንደጻፈው
ንፁህ እና እውነተኛ ፍቅር ለምንወደው ሰው ያለ ምንም ገደብ ታላቅ ነፃነትንና ሰላምን ይሰጣል። ይህም ሰላም እና ነፃነት የሚፈጠረው ከምንም በላይ አብልጠን የምንወደው ሰው ከቶ በኛ ቁጥጥር ውስጥ እንዲሆን ባለመፍቀዳችን ነው። ማለትም አንድን የምንወዳትን ወፍ በማሰርያ ውስጥ አስረናት የኛ እንድትሆን ከማድረግ ይልቅ እንደልቧ እንድትበር ፈቅደን ነገር ግን ቤት አዘጋጅተንላት በነጻነት በራሷ ፍላጎት ተመልሳ ወደሰራንላት ቤት እንድትመጣ ነፃነትን መስጠት እንደማለት ነው።
1 460
+ " ጽኑ እምነት " +
ይህ መዳን አለባቸው ባልናቸው የሕይወት አንዱ ችግሮቻችን ውስጥ ቢመጣ አይለወጥ ይሆን ሕመሙን ባታስታግስም ከአንተ አልርቅ አልክድህ ወዳንተ እጠጋለሁ ፀናለሁ እንል ይሆን ከድህነት ባታድነኝም ባጣም አንተን ከማጣት አይበልጥብኝም አልክድልህም እስርነቴ አመታት ቢያልፍ ሰው መሳለቂያ ሆኜ አፋቸው እንደ እሳት ቢበላኝ እያየህም ባታስፈታኝ አልክድህም እንል ይሆን ለእኔ ግን ማንፀና ምንደክም ይመስለኛ ትግስት ባለመግኘት ይቻላቸዋል ብለን ወደምናስብው ወደ ቆሙ ወደማይሰሙ ጣዖታት ምንሮጥ ።
ዳንኤል 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል ፥
¹⁸ ነገር ግን፥ ንጉሥ ሆይ፥ እርሱ ባያድነን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ አሉት።
የሦስቱን ወጣቶች እምነት "አባ ሄሮኒመስ" ሲገልፅ
‹‹ እግዚአብሔር እንደሚያድነን እናምናለን አሉ በኃጢአታቸው ምክንያት ከምድራዊው እሳት ባያድነንም ከዘላለም እሳት እንደሚያድነን እናምናለን ፥ የምናምነው በዚህ ዓለም ኑሮ ብቻ አይደለም ። በሰማያዊውም በሚመጣውም ሕይወት እናምናለን ። የምናምነው ከነበልባል ለማምለጥ ስንል ብቻ አይደለም ፣ ይህንን እሳት በማምለጥ ዘለዓለማዊ እሳት ውስጥ እንወድቅ ይኾናል ፥ ስለዚህ ማድረግ የምትፈልገውን ፣ እቶኑን አዘጋጅ ፣ ያም ለመንፃታችን ይሆናል ›› ። " ይለናል ። ነዶ ከማያልቀው እሳት ያድነናል ከአሁኑ ይልቅ ዘላለማዊውን እያዩ የፀኑ እምነተ ጠንካሮች ። በእነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያቶች ላይ ብቻ አዳኝነቱን ተስፍ ምናደርግ አለን እስከሺበታችን ጊዚያቶች ግን ጌትነቱ ትዝ ማይለን የወጣትነታቸው ሕይወት እሱን ከማመን ያላስቆማቸው እንዲፈሩት የተጣሉበት እሳት ፈርቶአቸው ያላቃጠላቸው እንዲመላለሱበትም መንገድ ያበጃጀላቸው ለአምላካቸው ባሳዩት ጽኑ እምነት ነው ።
1 460
እግዚአብሔርን አመስግኑ ምህረቱ ለዘላለም ነውና!!!
ማን ነው ህይወትን ማግኘት የሚፈልገው
ማን ነው ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል መማር
የሚፈልገው
ማን ነው ስለ እመብርሀን ስለ ድንግል ማርያም
መማር ማወቅ የሚፈልገው
እንግዲያውስ አሁንኑ ይፍጠኑ እና ይቀላቃሉ
ከሲዖል የሚጠብቅ የእግዚአብሔር ቃል እንዳያመልጥዎ1 460
#ዕጣንና_ጽንሃ_በቤተክርስቲያን
#ዕጣን
ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዕጣንን የተመላ ሰማያዊ ማዕጠንት በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እየሰገዱ ለአለም ድህነት የሚለምኑበት ነዉ፡፡ በቤተክርስቲያን ካህናት መንፈቀ ሌሊት ፡ በነገህ ጊዜ በቅዳሴ ጊዜ በየማዕዘኑ ዕጣን ያጥናሉ ቅዳሴውን ጸሎቱንና ልመናዉን ወደ እግዚአብሔር ያሳርጉበታል ፡፡
ስለ እጣን የመፅሀፍ ቅዱስ ማስረጃ
ዘጸ 30፥1 የዕጣን መሰዊያዉን ስራ ከግራር እንጨት አድርገው።
ዘጸ 30፥35 በቀማሚ ብለሀት እንደተሰራ፥ በጨዉም የተቀመመ ንጹህና ቅዱስ እጣን አድርገው፡፡
ዘጸ 30፥34 እግዚአብሄርም ሙሴን አለዉ፦ ጣፋጭ ሽቱ ዉሰድ የሚንጠባጠብ ሙጫ በዛጎል ዉስጥ የሚገኝ ሽቱ፥ የሚሸትትም ሙጫ፥ ጥሩም ዕጣን ዉሰድ የሁሉም
መጠን ትክክል ይሁን፡፡
ዘፀ 40፥5 ለዕጣንም የሚሆነዉን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ታኖራለህ፥ በማደሪያዉም ደጃፍ ፊት መጋረጃዉን ትጋርዳለህ፡፡ ዘጸ 40፥27 የጣፋጩን ሽቱ ዕጣን አጠነበት፡፡
ዘሌ 10፥1 የአሮንም ልጆች ናዳብና አብድዩድ በየራሳቸዉ ጥናዉን ወስደዉ እሳት፥ በላዩም ዕጣን አኖሩበት በእግዚአብሔር ፊት እሱ ያላዘዛቸውን ሌላ እሳት አቀረቡ፡፡
ዘሌ 16፥12 በእግዚአብሔር ፊት ካለዉ መሠዊያ ላይ የእሳት ፍም አምጥቶ ጥናዉን ይሞላል፥ ከተወቀጠውም ከጣፋጭ እጣን እጁን ሙሉን ይወስዳል ወደ መጋረጃውም
ዉስጥ ያመጣዋል፡፡
ዘኁ 16፥7 ነገም በእግዚአብሔር ፊት እሳት አድርጉባቸው፥ ዕጣንም ጨምሩባቸው እንዲህም ይሆናል እግዚአብሔር የሚመርጠው እርሱ ቅዱስ ይሆናል እናንተ የሌዊ ልጆች
ሆይ እጅግ አብዝታችኀል ብሎ ተናገራቸው፡፡
ዘዳ 33፥10 ፍርድህን ለያዕቆብ፥ ህግህንም ለእስራኤል ያስተምራሉ ፤ በፊትህ ዕጣንን፥ በመሰዊያህም የሚቃጠል መስዕዋት ይሠዋሉ፡፡
መዝ 140፥2 ጸሎቴን በፊትህ እንደ እጣን ተቀበልልኝ ፥ እጅ መንሳቴም እንደሰርክ መስዕዋት ትሁን፡፡
ማቴ 2፥11 ወደ ቤትም ገብተው ህጻኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር እዩት፥ ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥኖቻቸዉንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤን አቀረቡለት፡፡
ሉቃ 1፥10 በዕጣንም ጊዜ ህዝቡ ሁሉ በዉጭ ቆመውዉ ይጸልዩ ነበር፡፡
ራእ 5፥8 መጽሀፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንሰሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳዳቸም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ፡፡
ራእ 8፥3 ሌላም መለአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለዉ በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ
እጣን ተሰጠዉ
#ጽንሃ
ጽንሃ የእጣን ማሳረጊያ ወይም ማጠኛ ነው። ሦስት ሰንሰለቶች አሉት። ሰንሰለቶቹ ሶስት መሆናቸው የሚስጢረ ሥላሴ ምሳሌ ነው። በሰንሰለቶቹ ላይ ቢያንስ አስራ ሁለት (12) ቢበዛም ሃያ አራት (24) ሻኩራዎች ይኖሩታል።
‘’ሻኩራ’’ ማለት ሶስቱ ሰንሰለቶች ላይ ያሉት ክብ ነገሮች ናቸው። የሻኩራዎቹ ቁጥር አስራ ሁለት (12) መሆኑ የሐዋሪያት ምሳሌ ነው። ሃያ አራት (24) መሆኑ ደግሞ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ምሳሌዎች ናቸው ። ከስሩ እጣኑ የሚቀመጥበት ሙዳይ የመሰለ ክፍል የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ሲሆን: መለኮት ከሥጋዋ ሥጋ ነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑን ያመለክታል። ፍሙ የጌታችን የመለኮትነቱ ምሳሌ ሲሆን እጣኑ እንደሚቃጠልና መዓዛው ሁሉን እንደሚያውድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ብዙዎች ኃጢያት ራሱን መስዋዕት በማድረግ አቅርቦ ዓለሙን ሁሉ ማዳኑን ያሳያል።
1 460
1 አቤቱ አምላኬ ፥ ባንተ ታመንኹ፤ ከሚያሳድዱኝ ዅሉ አድነኝና አውጣኝ ፥
2 ነፍሴን እንደ አንበሳ ነጥቀው እንዳይሰብሯት ፥ የሚያድንና የሚታደግ ሳይኖር።
3 አቤቱ አምላኬ ፥ እንዲህስ ካደረግኹ ፥ ዐመፃም በእጄ ቢኖር ፥
4 ክፉ ላደረጉብኝም ክፉን መልሼላቸው ብኾን ፥ ጠላቴንም በከንቱ ገፍቼው ብኾን ፥
5 ጠላት ነፍሴን ያሳዳት ያግኛትም ፥ ሕይወቴንም በምድር ላይ ይርገጣት ፥ ክብሬንም በትቢያ ላይ ያዋርዳ ት።
6 አቤቱ ፥ በመዓትኽ ተነሥ ፥ በጠላቶቼ ላይ በቍጣ ተነሣባቸው፤ አቤቱ አምላኬ ፥ ባዘዝኸው ትእዛዝ ንቃ።
7 የአሕዛብም ጉባኤ ይከቭኻል ፥ በእነርሱም ላይ ወደ ከፍታ ተመለስ።
8 እግዚአብሔር በአሕዛብ ይፈርዳል፤ አቤቱ ፥ እንደ ጽድቄ ፍረድልኝ ፥ እንደ የዋህነቴም ይኹንልኝ።
9 የኃጥኣን ክፋት ይጥፋ ፥ ጻድቁን ግን አቅና፤ እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል።
10 እግዚአብሔር የጽድቅ ጋሻዬ ነው ልበ ቅኖችን
የሚያድናቸው።
11 እግዚአብሔር የእውነት ዳኛ ነው ፥ ኀይለኛም ታጋሽም ነው ፥ ዅልጊዜም አይቈጣም።
12 ባትመለሱ ግን ሰይፉን ይስላል ፥ ቀስቱን ገተረ አዘጋጀም፤
1 460
"ሰው ምንድን ነው?"
ከ ሐመር መጽሔት ፳፯ኛ ዕትም የተወሰደ
ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረው ሰው ግሩምና ድንቅ ሆኖ የተፈጠረ ፍጡር ነው፡፡ (መዝ.፻፴፰÷፲፬) ሰው አስቀድሞ በፈጣሪው በልዑል እግዚአብሔር ሲፈጠርም አፈጣጠሩ በብዙ መንገድ ከሌሎች ፍጥረታት ልዩ ሆኖ የተፈጠረ ክቡር ፍጥረት ነው፤በሥነ ፍጥረት ትምህርት እንደተማርነው እግዚአብሔር በዓለም ያሉ ፍጥረታትን በኃልዮ (በሐሳቡ ይሁኑ በማለት) በነቢብ (በቃል በመናገር ይሁኑ በማለት) ሲፈጥር ሰውን የፈጠረው ግን በገቢር በእጆቹ ነው፡፡ ነቢዩ “እጆችህ ሠሩኝ፤ አበጃጁኝም” ብሎ እንደመሠከረ፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በእርሱ መልክና እንደ ምሳሌው አድርጎ ነው፡፡ “እግዚአብሔርም አለ፥ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር” ተብሎ እንደተጻፈ፡፡
የእግዚአብሔር መልክ የሚባለው እንደ ምንድን ነው ቢሉ አበው እንዳስተማሩት የእግዚአብሔር መልክ የሚባለው ቅድስና፣ ፍቅር፣ ቸርነት፣ ነጻነት፣ ጥበብ፣ ገዥነት፣ ክብር፣ ንጽሕና፣ ፍትሐዊነት፣ ርኅራኄ፣ አሳቢነት፣ ዕውቀትና የመሳሰሉት ነው፡፡ እነዚህ የአምላካችን የእግዚአብሔር የባሕርይው መገለጫዎች የሆኑ ነገሮች ሰው በተፈጠረ ጊዜ በጸጋ ተሰጥተውታል፡፡ (መክ.፯÷፳፱፣ ዘሌ.፲፱÷፪፣ ሉቃ.፮÷፴፮፣ ፩ኛጴጥ.፩÷፲፮)
እነዚህን የቅድስና መንፈሳዊ ባሕርያት መገለጫዎች እያጎለበተና እያሳደገ ሲሄድም ሰው የእግዚአብሔር ምሳሌ ወደ መሆን ይደርሳል፡፡
ሰው ምንድነው? የሚለውን ጉዳይ በእውነትና በእምነት ስንረዳም በሰው ሰውነት ውስጥ የእግዚአብሐርን ፈታሒነት፣ ከሀሊነት፣ ቸርነትና ባዕለጠግነት እንዲሁም ዐዋቂነቱን፣ ነባቢነቱንና ዘለዓለማዊነቱን እናውቃለን በመጨረሻም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እንደርሳለን።
አንድ ገበሬ በራሱ እርሻ ላይ ያሻውን ዘር ሊዘራ ይችላል፤ ከእርሱም በቀር በእርሻው ላይ ማንም አያዝም፡፡ አስቀድመን እንደተናገርነው እኛ በክርስቶስ ወርቀ ደም የተገዛን የእርሱ እርሻዎች ነንና የእርሱ እርሻ በሆነ ሰውነታችን እንደ ዐረምና ቋያ የሆነ ክፉ ነገርን፣ የኑፋቄና የክህደት ትምህርቶችን፣ እርሱን የሚያስክዱ ሰብዓዊነትን፣ መተባበርንና መተዛዘንን የሚያጠፉ ርዕዮተ ዓለምንና ፍልስፍና መሰል መራዥ አስተሳሰቦችን፣ የነፍሳችንን ነገር ሙሉ ለሙሉ አስለቅቀው ለሥጋችን ፈቃድ ብቻ እንድንኖር የሚገፉ ዲስኩሮችን እንዳንዘራ ልንጠነቀቅ ይገባናል
“ሰው ክቡር ፍጥረት ሆኖ ሳለ አላወቀም፡፡ ነገር ግን እንደሚጠፉ እንስሳት መሰለ” ተብሎ እንደተናገረ እንዳንሆን፡፡ (መዝ.፵፰÷፲፪)
ምንጭ፡ ሐመር መጽሔት ፳፯ኛ ዕትም ፳፻፲፩ ዓ.ም
1 460
በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው። ዐውሎንም ጸጥ አደረገ፥ ሞገዱም ዝም አለ። ዝም ብሎአልና ደስ አላቸው፤ ወደ ፈለጉትም ወደብ መራቸው።
መዝሙረ ዳዊት 107:28-30
1 460
🌼 የምወድህ ልጄ ሆይ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ🥰
ልጄ ሆይ....... ወጣትነት ፈትኖህ፤ለስጋህ አድልተህ፤ነፍስህን አቀጭጨኻት ከአለም የኖርክበትን ዓመትህን ጥለኸው በንሰሐ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ..... በአዲስ አመት ለአምላክህ የሚገባህን ግብር ትፈፅም ዘንድ በፍቅሩ አፀድ እንድትገኝ ካለመታዘዘ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ....... በአፈር ከሚሸነፈው ስጋዊ ዘርህ ወጥተህ ሰማያዊነትን ከሚያለብስህ ከማይጠፋው ሰማያዊ ዘር ክብረት ታደርግ ዘንድ ሰውን ካለመውደድ ጥላቻ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... በምክንያቶች ተደልለህ አፅዋማትን ዘለህ፤ምስጋናን ነፍገህ፥አገልግሎትን ንቀህ ከአለም ጫጫታ ውስጥ የዘፈቀውን ማንነትህ እንዳያጠፋህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... ዲያቢሎስ በቃል እንዳያስትህ፤በማማለል እንዳይጠልፍህ የመንጋውን ጠባቂ ቃልን ስማ፤ የመታዘዝን በረከት ታገኝ ዘንድ ከትምህክትህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ .....ቀናት ሳይሆን መንፈስህ ይለወጥ፤ፀሐይ ሳትሆን የህይወት ጀንበርህ ይለወጥ።
ልጄ ሆይ ......ዕለታት አይሰልጥኑብህ፤ ዘመናት እስከ ሞትህ ጥግ ድረስ እስኪገፉህ ሳትጠብቅ አንተም እንደ ዘመንህ ተለወጥ
ልጄ ሆይ .....የእግዚአብሔር ፍቅር ለተከፈተ ልብ ቸር ነው ። ርህራሄው ጥልቅ ነው ። በአምሳሉ ፈጥሮሃል እና እንዳትጠፋ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የደረስ ጥልቅ ፍቅር አሳይቷል ። ስለዚህ ከዘመንህ ቀድመህ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...አዛኝቷን ተለማመን፤መላአኩን ተማለደው ፤ቀደምት ቅዱሳን አባቶችህን ጥራ፤ ፃድቃንን ዘክር እንጅ ላለመለወጥ ተማምለው ቀናት ብቻ ከሚለወጥባቸው ሰልፈኞች ተርታ አትገኝ ።
በንስሐ ወደ በረቱ የምንመለስበት ዘመን ይሁንልን! አሜን
🌻 መልካም አዲስ ዓመት ይሁን ለኹላችን | ሠናይ ሐዲስ ዓመት ይኲን ለኲልነ
🙏🏾ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏🏾
🥰ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!🥰
1 460
በአንተ የሚታመኑት ሁሉ ግን ደስ ይላቸዋል፤ ለዘላለሙ ደስ ይላቸዋል፥ እነርሱንም ትጠብቃለህ፤ ስምህንም የሚወድዱ ሁሉ በአንተ ይመካሉ።
መዝሙረ ዳዊት 5:11
1 460
በልቤስ በደልን አይቼ ብሆን ጌታ አይሰማኝም ነበር። ስለዚህ እግዚአብሔር ሰማኝ፤ የልመናዬን ድምፅ አደመጠ።
መዝሙረ ዳዊት 66:18,19
@Hiwotegziabher
1 460
ሸክሙን ወደዚያ ጣሉት!
ዛሬ መሸከም የሌለባችሁንና ለእናንተም ሆነ ለሌሎች ሰዎች ሕልውና ወሳኝ ያልሆኑ ነገሮችን ወደዚያ ጣሉ!!!
መሸከም የሌለባችሁን የሰው አጉል ባህሪይ . . .
መሸከም የሌለባችሁን የኑሮ ውጥረት . . .
መሸከም የሌለባችሁን የውስጥ ጭንቀት . . .
መሸከም የሌለባችሁን የስራ ጫና . . .
በቃ መሸከም ካልቻላችሁና ብትሸከሙትም ሆነ ባትሻከሙት ለውጥ ከሌለው፣ አውጥታችሁ ጣሉት!
1 460
ያለህን ሳይሆን ማንነትህን መዝነው!
ያለህንና የሌለህን ከመቁጠርህ በፊት ማንነትህን ለካው፡፡ የሕይወትህ ጥራት የሚመዘነው በማንነትህ ጥራት ስለሆነ ማለት ነው፡፡
የማንነት ጥራት ስኬትን ያመጣል እንጂ ስኬት የማንነትን ጥራት አያመጣም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህ እውነታ ይምታታባቸዋል፡፡ ስለዚህም፣ ተሳክቶላቸዋል ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች ጨዋ ማንነትና አመለካከት ይመለከቱና፣ “እኔም በእውቀት፣ በሃብትና በመሳሰሉት ሁኔታዎች እዚህ ደረጃ ብደርስ ኖሮ ጥራት ያለው ሕይወትና ማንነት ይኖረኝ ነበር” ብለው ያስባሉ፡፡
ይህ ጉዞ የምኞት ጉዞ ነው እንጂ የእውነታ ጉዞ አይደለም፡፡ እነዚያ ሰዎች የጀመሩት ከማንነት ለውጥ መሆኑንና ሁኔታቸውን ከመለወጣቸው በፊት ማንነታቸውን ለመለወጥ ጥረት ማድረጋቸውን አልተገነዘቡም፡፡ ምናልባትም ሰዎቹ ከማንነት ጥራት ሳይነሱ የተለያዩ ነገሮችን ማካበት ላይ ዘልለው ከገቡ፣ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ነገሩ መፈራረሱ አይቀርም፡፡
ከማንነት ጥራት ቀድሞ የመጣ ነገር የኋላ ኋላ የመፈራረሱ ምስጢር ያለው የሚመጣውን የስኬት ሸክም መሸከም የሚችል የማንነት ብቃት ባለመኖሩ ነው፡፡ ስለዚህም፣ ጊዜአዊ ስኬት ከዚህና ከዚያ ሊለቃቀምና በእጅ ሊገባ ይችላል፡፡ ዘላቂና ጥራት ያለው ስኬት ግን መነሻው ጥራት ያለው አስተሳሰብና ማንነት ነው፡፡
ስኬትህን ከቁሳቁስ ብዛት አትጀምረው፤ ምክንያቱም እሱኛው ስኬት ስላልሆነ ማመለት ነው፡፡ በተቃራኒው ግን፣ ስኬትህን ከማንነት ጥራት ጀምረው፡፡
የማንነት ጥራት ማለት . . .
• ሲሳካለት አጉል ትምክተኛነት የማይሰማው ማንነት . . .
• ሳይሳካለት ሲቀር በዝቅተኝነት የማይመታ ማንነት . . .
• ከዘር ምንነት፣ ከገንዘብ አቅምና ከእውቀት ደረጃ በዘለለ ሁኔታ ሁኑን ሰው እኩል የሚያይ ማንነት . . .
• የበላይነት የማግኘትን እድል ሰዎችን ለመደቆስ ሳይሆን ለሰዎች ጥቅም የሚያውል ማንነት . . .
• ሁለት መልክና ሁለት ምላስ የሌለው ማንነት . . .
“የማንነትህ መለኪያ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ፡፡
