The Power of Thought
Open in Telegram
ሀሳቦቻችን እጣፈንታችንን ይወስናሉ። Transform Your Thinking. Transform Your Life. Think. Grow. Succeed. Contact us @RadiantEphrem
Show more456
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
ዓላማ የሌለው ህይወት እና መሪ የሌለው መርከብ
መርከብ ግዙፍ ቢሆንም፣ ሞተር ቢኖረውም፣ በውቅያኖስ ላይ የሚንሳፈፍበት በቂ ነዳጅ ቢኖረውም... መሪ ከሌለው ግን የነፋስና የሞገድ መጫወቻ መሆኑ አይቀርም። የሰው ልጅ ህይወትም እንዲሁ ነው።
📍 1. አቅጣጫ አልባ ጉዞ
ዓላማ የሌለው ሰው ጉልበት አለው፣ ጊዜ አለው፣ ምናልባትም እውቀት አለው፤ ነገር ግን እነዚህን ሀብቶቹን የት ላይ እንደሚያውላቸው አያውቅም። ነፋስ ወደመራው እንደሚሄድ መርከብ፣ እርሱም በሰው ወሬ፣ በወቅታዊ ሁኔታዎችና በስሜት ግፊት ብቻ ይነዳል እንጂ የራሱ የሆነ ፅኑ አቅጣጫ የለውም።
📍 2. የትም ቢደርስ ደስታ የለም
ይህ የዓላማ እጦት ትልቁ መርገም ነው። መድረሻውን የማያውቅ መንገደኛ፣ ለምለም ቦታ ላይ ቢደርስ እንኳን እዚህ ነው መድረሻዬ? የሚል ጥርጣሬ ስላለበት እውነተኛ እርካታ አይሰማውም። ስኬት የሚለካው ካሰብነው ግብ አንጻር እንጂ፣ ዝም ብሎ በማግኘት ብቻ አይደለም። ዓላማ ሲኖርህ ግን ትናንሽ ስኬቶችህ ትልቅ ትርጉም ይሰጡሃል።
📍 3. የጊዜና የጉልበት ብክነት
መሪ የሌለው መርከብ በክብ (Circle) እየተሽከረከረ ነዳጅ ይጨርሳል እንጂ ወደፊት አይራመድም። ብዙዎቻችን ቀኑን ሙሉ እንደክማለን፣ እንሮጣለን፤ ነገር ግን ማታ ላይ ዛሬ ለዓላማዬ ምን ፈጠርኩ? ብለን ስንጠይቅ መልስ እናጣለን። ይሄ "በከንቱ የመድከም ስሜት ለጭንቀትና ለተስፋ መቁረጥ ይዳርጋል።
💡 መፍትሄው ምንድን ነው?
*አላማህን እወቅ*
መድረሻህን ወስን፦ ዛሬ ካለህበት ተነስተህ ከአምስት ዓመት በኋላ የት መድረስ እንደምትፈልግ በግልጽ አስብ።
መሪህን ጨብጥ፦ ውሳኔዎችህ በዓላማህ ላይ የተመሰረቱ ይሁኑ። ይህ የማደርገው ነገር ወደምፈልገው ቦታ ያደርሰኛል? ብለህ ጠይቅ።
በትንሽ ጀምር፦ ትልቅ ዓላማ ይኑርህ እንጂ፣ ጉዞህን በትንንሽና በየቀኑ በሚሰሩ ተግባራት ጀምር።
"ዓላማ ያለው ሰው በጠባብ መንገድ ላይ እንኳን ፈጥኖ ይጓዛል፤ ዓላማ የሌለው ግን ሰፊው መንገድ ላይ እንኳን ዳተኛ ነው።""አላማ ለድርድስ የሚቀርብ ሸቀጥ አይደለም" ሲሳይ ምህረት 📍 ይህ መልዕክት ለጓደኞቻችሁ እንዲደርስ Share አድርጉ! #ዓላማ #ህይወት #ስኬት
🕒 "ነገ እሰራዋለሁ" - የህልም ነጣቂው በሽታ!
ብዙዎቻችን ጎበዝ ከመሆን ይልቅ "ነገ እጀምራለሁ" በማለት ጊዜያችንን እናባክናለን። ማራዘም ማለት የዛሬን ስራ ለነገ ማስተላለፍ ብቻ አይደለም፤ የዛሬን ስኬት ለነገ መግፋትም ጭምር ነው።
ለምንድነው ነገሮችን የምናራዝመው? ብዙ ጊዜ ስራው ከባድ ስለመሰለን ወይም "ሁሉ ነገር ተሟልቶልኝ እጀምራለሁ" ስለምንል ነው። ነገር ግን ማወቅ ያለብህ
"ለመጀመር ጎበዝ መሆን አያስፈልግህም፤ ግን ጎበዝ ለመሆን መጀመር አለብህ።" — ዚግ ዚግላር
ማራዘምን ለማሸነፍ 3 ቀላል መንገዶች፡
በ5 ሰከንድ ውስጥ ጀምር፦ አንድን ስራ ለመስራት ስታስብ አእምሮህ ሰበብ ሳያደርድርልህ በፊት "5-4-3-2-1" ብለህ ቁጠርና ወዲያውኑ እጅህን ወደ ስራው ክተት።
በትንሽ ነገር ጀምር፦ ትልቅ ስራን በአንዴ ለመጨረስ አትጨነቅ። ለምሳሌ መጽሐፍ ለማንበብ ካሰብክ "ዛሬ 1 ገጽ ብቻ አነባለሁ" ብለህ ጀምር። ትንሿ ጅምር ትልቅ ጉልበት ትሰጥሃለች።
የመጨረሻውን እርካታ አስብ፦ ስራውን ስትጨርሰው የሚሰማህን ደስታና እረፍት አስብ።
የዛሬ መልዕክት፦ "ነገ" የምትባል ቀን የለችም። ያለህ "ዛሬ" ብቻ ናት። ዛሬ የምታደርጋት አንዲት ትንሽ እርምጃ፣ ነገ ልትደርስበት ለምትመኘው ቦታ መሰረት ናት።
"ከአንድ አመት በኋላ 'ዛሬ በጀመርኩ ኖሮ' ብለህ መቆጨትህ አይቀርም።" — ካረንላምብ
ጥያቄ ለእናንተ፦ ዛሬ መጀመር ሲገባችሁ ለነገ ያስቀመጣችሁት ስራ ምንድነው? አሁኑኑ ጀምሩት!
#ጊዜ #ስኬት #አሁኑኑ_ጀምር #Inspiration
📌 የአመለካከት ቀመር፡ 10/90 ህግ
ብዙዎቻችን ህይወት በድንገት የሚገጥሙን ክስተቶች ውጤት ትመስጠናለች። ነገር ግን እውነታው ከዚህ የተለየ ነው። ታዋቂው ጸሐፊ ቻርለስ ስዊንዶል እንዲህ ይላል፦
"ህይወት 10% የሚገጥመን ነገር ሲሆን፣ 90% ግን ለገጠመን ነገር የምንሰጠው ምላሽ ነው!"
ይህ ማለት ምን ማለት ነው?
1. ያጋጠመህ ነገር (10%)፦ ከቁጥጥርህ ውጪ የሆኑ ነገሮች ናቸው። ለምሳሌ፦ መጥፎ የኑሮ ሁኔታ፣ ስራ ማጣት፣ኪሳራ፣ የሰው ንግግር፣ ወይም የምትፈልገውን ውጤት አለማምጣት ሊሆኑ ይችላሉ። እነዚህን ልታስቆማቸው አትችልም።
2. አንተ የምትሰጠው ምላሽ (90%)፦ ይህኛው ክፍል ሙሉ በሙሉ በአንተ ቁጥጥር ስር ነው። በገጠመህ ነገር ላይ የምታሳየው አመለካከት ቀሪውን የህይወትህን መስመር ይወስነዋል።
ለምሳሌ ያህል፦ በስራ ቦታህ ላይ አንድ ሰው መጥፎ ቃል ቢናገርህ (ይህ 10ሩ ፐርሰንት ነው)።
አማራጭ ሀ፦ ተናደህ ቀኑን ሙሉ ስትበሳጭ ከዋልክና ስራህን ካበላሸህ 90ው ፐርሰንት በአሉታዊ አመለካከት ተበላሸ ማለት ነው።
አማራጭ ለ፦ ይህ የሰውየው ባህሪ እንጂ የእኔ ማንነት አይደለም ብለህ በፈገግታ ካለፍከው፣ ቀሪው 90 ፐርሰንት የቀን ውሎህ በሰላም ያልፋል።
ባጭሩ፦ ችግሮች መፈጠራቸው አይቀሬ ነው፤ ዋናው ቁልፍ ግን ችግሩ ላይ ሳይሆን እኔ ለዚህ ችግር ምን አይነት ምላሽ ልስጥ? ብሎ ማሰብ ላይ ነው። አመለካከትህን ስትቀይር፣ ለውጡ የሚጀምረው ከውስጥህ ሳይሆን ከሚገጥሙህ ሁኔታዎች በላይ መሆን ስትጀምር ነው።
ለዛሬው ጥያቄ፦ በባለፉት ጊዜያት በገጠመህ መጥፎ አጋጣሚ ላይ የሰጠኸው ምላሽ ምን ይመስል ነበር?
90ውን ፐርሰንት ተቆጣጥረኸዋል ወይስ አሳልፈህ ሰጥተሃል?
ሀሳባችሁን በኮመንት አጋሩኝ 👇
መልካም ቀን🙏
#አመለካከት #Mindset #የህይወት_ቀመር #ተነሳሽነት #Ethiopia
የዛሬው የስኬት ስንቅ
በመንገድ ላይ ስትጓዝ ሁለት አማራጮች ቢገጥሙህና የትኛው እንደሚሻል ባታውቅ፣ አንዱን መርጠህ መጓዝ ጀምር። መንገዱ ዝግ ቢሆን እንኳ ተመልሰህ ሌላውን ለመጀመር ልምድ ይኖርሃል።
ቆመህ ከመቅረትና 'ልሞክረው አልሞክረው' እያሉ በጥርጣሬ ጊዜን ከማባከን፣ መሳሳትም ቢሆን የራሱ የሆነ እድገት አለው።"
ለምን መሰላችሁ?
ልምድ የሚገኘው ከመንገዱ እንጂ ከቆሙበት ቦታ አይደለም።
ስህተት ራሱ ትክክለኛው መንገድ የትኛው እንደሆነ ማሳያ ኮምፓስ ነው።
መዘግየት ግን የሁሉንም በሮች መዝጊያ ነው።
መልዕክቱ፦ ከመጠራጠር መጀመር፣ ከመቆም ደግሞ መሳሳት ይሻላል። ምክንያቱም ስህተት ይታረማል፤ የባከነ ጊዜ ግን አይመለስም።ጥያቄ፦ በጥርጣሬ ምክንያት ሳትጀምሩት የቀራችሁት ነገር አለ? ዛሬውኑ የመጀመሪያውን እርምጃ ለመውሰድ ወስኑ! 📢 ለጓደኞችዎ ያጋሩ (Share) https://t.me/The_secretsOfsuccess
ቢዝነስ የጀግኖች እንጂ የሰበብ ሰብሳቢዎች መድረክ አይደለም!
ኑኖ ተወደደ ፣ ገንዘብ የለኝም፣ ቤተሰብ አልረዳኝም፣ ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ... እነዚህ ሁሉ እውነታዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ነገር ግን በእነዚህ ምክንያቶች ቆመህ እንድትቀር የሚያደርግህ የሁኔታዎቹ ከባድነት ሳይሆን ሀላፊነት ለመውሰድ መፍራትህ ነው።
ስኬታማ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች ሁኔታዎችን አይወቅሱም፤ ሁኔታዎችን ይለውጣሉ። "ለምን አልተሳካም?" ብለህ ሌላውን ከመጠየቅ፣ "ምን ባደርግ ይሳካል?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ስልጣኑ ያለው እጅህ ላይ ነው!
አስታውስ ሀላፊነትን መሸሽ ጊዜያዊ እረፍት ይሰጣል፤ ሀላፊነትን መውሰድ ግን ዘላቂ ስኬትን ያመጣል።
https://t.me/The_secretsOfsuccess
ትልቁ ፀፀት የትኛው ነው? 💡
ብዙ ሰዎች በሕይወታቸው መጨረሻ ላይ የሚፀፀቱት በሞከሩትና በወደቁበት ነገር ሳይሆን፣ ሳይሞክሩት በቀሩት እድሎች ነው።
ውድቀት ትምህርት ይሰጥሃል፤
መሞከር ልምድ ይሆንሃል፤
ሳይሞክሩ መቅረት ግን ሁሌም አብሮህ የሚኖር "ቢሆንስ ኖሮ?" የሚል የፀፀት ጠባሳን ይተዋል።
እድል ልክ እንደ ፀሐይ መውጫ ናት፤ ብዙ ከቆየህ ታመልጥሃለች። ፍርሃትህ እንዳያስቆምህ፤ ወድቀህ ብትነሳ ካለህበት ትንቀሳቀሳለህ፤ ሳይሞከር የቀረ እድል ግን ካለህበት አስሮ ያስቀርሃል።
"በሃያ ዓመትህ፣ ካደረግካቸው ነገሮች ይልቅ ባላደረግካቸው ነገሮች ይበልጥ ትፀፀታለህ።" — ማርክ ትዌይን
ዛሬ ራስህን ጠይቅ፦ ለመጀመር ፈርተህ ያቆየኸው ያ አንድ እድል ምንድን ነው? ዛሬውኑ የመጀመሪያውን እርምጃ ውሰድ! 🚀
https://t.me/The_secretsOfsuccess
🚀የልማድ ኃይል! 🚀
"እኛ የምንሆነው በየቀኑ ደጋግመን የምናደርገውን ነው፤ ስለዚህ ስኬት ድርጊት ሳይሆን ልማድ ነው!" — አሪስቶትል
ብዙዎቻችን ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ እርምጃ መውሰድ ያለብን ይመስለናል፡፡ ነገር ግን እውነታው ከዚህ የተለየ ነው፡፡ በየቀኑ የምናደርጋቸው ትንንሽ ነገሮች ተደምረው ማንነታችንን ይወስናሉ፡፡
✅መጥፎ ልማድ እንደ ምቹ አልጋ ነው፤ ለመተኛት ቀላል፣ ለመነሳት ግን በጣም ከባድ ነው፡፡
✅ጥሩ ልማድ ደግሞ እንደ ባቡር ሀዲድ ነው፤ መጀመሪያ ላይ ለመዘርጋት ቢከብድም፣ አንዴ ከተገነባ ግን ጉዞህን ያቀልልሃል፡፡
ዛሬ ራስህን ጠይቅ፦ አሁን እያዘወተርካቸው ያሉ ልማዶችህ ወደምትፈልገው ሕይወት እየወሰዱህ ነው ወይስ ካለህበት አስረው አስቀርተውሃል?
https://t.me/The_secretsOfsuccess
Join us
🚀የምስጋና ሀይል🚀
ህይወት ጉዞ ናት፤ በጉዞዋ ውስጥ ደግሞ ብዙ ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶችና መውደቆች አሉ። እኔ ግን ዛሬ ቆም ብዬ እንዲህ እላለሁ
🌟 ስለሆነልኝ ሁሉ፦ ላገኘኋቸው ድሎች፣ ለተሳኩልኝ ህልሞች፣ ለሰጠኸኝ ጤና እና በዙሪያዬ ላሉ ውድ ሰዎች ሁሉ ምስጋና ይሁን። እነዚህ የህይወቴ ብርሃኖች ናቸው።
🛡️ ስላልሆነልኝ ሁሉ፦ ይህ ትልቁ ምስጋናዬ ነው። የፈለኩት ሳይሆን ሲቀር አዝኜ ነበር፤ ዛሬ ግን ሳስበው ያልሆኑልኝ ነገሮች ከትልቅ አደጋ እንደጠበቁኝና ለተሻለ መንገድ እንዳዘጋጁኝ ተረድቻለሁ። የዘጋኸው በር ሁሉ ከክፉ እንደጠበቀኝ አውቃለሁ።
🌅 ስለሚሆንልኝ ሁሉ፦ ነገ በእጅህ እንደሆነ አምናለሁ። ገና ለሚመጡት በረከቶች፣ ለሚከፈቱት አዳዲስ በሮች እና ለሚታዩት ተዓምራት ሁሉ ካሁኑ አመሰግናለሁ። በነገው ተስፋዬ ላይ ሙሉ እምነት አለኝ።
በህይወታችን ምስጋና ሲኖር፣ የሌለን ነገር ላይ ከማተኮር ይልቅ ያለን ነገር ላይ እንድንደሰት ያደርገናል። በህይወታችሁ ስላልሆነላችሁ ነገር አመስግናችሁ ታውቃላችሁ?
ካልሆነ ከዛሬ እንጀምር
ስላልሆኑልኝ ሁሉ አመሠግናለሁ እንበል
ተመስገን! 🙌
#Gratitude #LifeJourney #Blessings #Faith
#ምስጋና #አዎንታዊ_አስተሳሰብ
ትልቁ መዳረሻህ ዛሬ በምትወስደው እርምጃ ውስጥ ነው!
ብዙ ጊዜ የምናስበው ስለ ርቀቱ ወይም ስለ መጨረሻው መዳረሻ (Destination) ነው። ነገር ግን ትልቁ ስኬት መድረሻው ላይ ሳይሆን "መጀመሩ" ላይ ነው።
ለምን ዛሬ መጀመር አለብህ?
የማይጀመር መንገድ መድረሻ የለውም፦ ሺህ ኪሎ ሜትር ቢሆንም ጉዞው የሚጀምረው በአንዲት እርምጃ ነው።
ጊዜ አይጠብቅም፦ መድረሻህ እንዲቀርብህ ከፈለግህ፣ አንተ ወደ መድረሻህ መቅረብ አለብህ።
ልምምድ ብቃትን ያመጣል፦ መዳረሻህ ላይ ስትደርስ የሚጠብቅህን ትልቅ ሃላፊነት የምትሸከመው፣ በጉዞው ላይ በምታገኘው እውቀት ነው።
ዛሬ ያደረግኸው ጥረት ነገ ለምትደርስበት ክብር መሰረት ነው። መድረስ ለምትፈልግበት ቦታ ዛሬ ምን እየሰራህ ነው?
መንገዱንስ ጀምረሀል?
አስታውስ፦ የምትደርሰው መጓዝ ስትጀምር ብቻ ነው! 🚀
#ReachYourGoal #StartNow #Progress #SuccessMindset
ለውጥ የሚጀምረው ከውስጥ ነው!
ብዙዎቻችን ዓለም እንዲቀየር እንፈልጋለን፤ ነገር ግን ራሳችንን ለመቀየር አንፈቅድም። እውነታው ግን ይሄ ነው፦ አስተሳሰብህ ሳይቀየር ህይወትህ አይቀየርም!
ለውጥ ማለት የግድ በአንድ ጀምበር ተራራን መናድ ማለት አይደለም። ለውጥ ማለት፦
የትላንት ስህተትህን ዛሬ አለመድገም ነው፤
አዳዲስ ነገሮችን ለመማር ራስህን ክፍት ማድረግ ነው፤
ካለህበት የልመድ (Comfort Zone) ወጥተህ አዳዲስ ፈተናዎችን መጋፈጥ ነው።
ባለህበት ከቆምክ አለም ጥላህ ትሄዳለች። ምክንያቱም ህይወት በየሰከንዱ እየተለወጠች ነው። ዛሬ የምታደርጋት አንዲት ትንሽ የባህሪ ወይም የእውቀት ለውጥ፣ ከዓመታት በኋላ ላንተ ትልቅ የታሪክ መጽሐፍ ትሆናለች።
አስታውስ፦ በሩን ሳይከፍቱ ብርሃን አይገባም፤ አንተም ለለውጥ ራስህን ሳትከፍት አዲስ ህይወት አይመጣም።
ለውጥን አትፍራው፤ ተቀበለው! 🌟
ንስር አሞራ እስከ 70 አመት የሚኖር የእድሜ ባለፀጋ ነው የሚል ሰምተህ ወይም አንብበህ ሊሆን ይችላል።
ትክክል ነው!
ነገር ግን 70 አመት ሙሉ በደስታ ከመኖሩ በፊት በእድሜው አጋማሽ ማለትም በ35 - 40 ባለው እድሜው ላይ ከባድ ነገር ይገጥመዋል ...
የመጀመሪያው :- ምግቡን ለማደን የሚገለገልበት ጥፍሮቹ ከመጠን በላይ ስለሚያድጉ ምግቡን ከመሬት ላይ ማንሳት ያቅተዋል ...
ሁለተኛው :- አጥንትን ሳይቀር መስበር አቅም ያለው አፉ(መንቁሩ) ስለሚታጠፍና ስለሚጣመም ምግቡን እንደወትሮው መመገብ ይሳነዋል ...
ሶስተኛው:- ክንፉና በአካሉ ላይ ያሉ ላባዎች ስለሚከብዱት ያ ሰማየ ሰማያትን እየሰነጠቀ ይበር የነበረው ሀይሉ ይክደዋል።
እነዚህ ሶስት ከባድ ነገሮች ንስር አሞራ በእድሜው አጋማሽ የሚያጋጥሙት ከባድ ችግሮች ናቸው። አሁን ንስር አሞራ ያለው ምርጫ ሁለት ነው።
1ኛ. ካረጀ አካሉ ጋር ዝም ብሎ በመቀመጥ ሞቱን መጠበቅ ?
2ኛ. አምስት ወር የሚፈጅ ስቃይና መከራ ያለበት መስዋዕትነትን ከፍሎ ቀሪውን 35 አመት በደስታ ማሳለፍ ?
የመጀመሪያውን ከመረጠ በእድሜው አጋማሽ ይሞታልና ታሪኩ እዛ ጋር ያበቃል።
ሁለተኛውን ምርጫ ከመረጠ ግን እነዚህን አምስት መስዋዕትነቶች ማለፍ ይኖርበታል።
፩ኛ. ከፍተኛ ተራራ ላይ በመውጣት የብቻውን ጎጆ ይቀልሳል።
፪ኛ. ጎጆ ከቀለሰ በኋላ የመጀመርያ ስራዉ የአፉን መንቁር ከአለት ጋር በማጋጨት ነቅሎ ይጥላል።
፫ኛ. ይህን ካደረገ በኋላ አዲስ መንቁር ይወጣለታል፡፡ መንቁሩ እስኪያድግ ድረስ ታግሶ በጎጆው ምንም አይነት ምግብ ሳይመገብ መቆየት ግዴታው ይሆናል፡፡
፬ኛ. አዲስ መንቁር ከበቀለለት በኋላ በአዲሱ መንቁሩ የገዛ እግሩን አሮጌ ጥፍር ነቃቅሎ ይጥለዋል።
፭ኛ. አዲሱ የእግር ጥፍር ከበቀለለት በኋላ ደግሞ ይህንን አዲስ ጥፍር እንደ መሳርያ በመጠቀም በሰዉነቱ የተጣበቁትን እንዳይበር እንቅፋት የሆኑትን የገዘፉና ያረጁ ላባዎችን ነቃቅሎ ይጥላል። በምትኩ አዲስ ላባ ያበቅላል።
ይህን 5 ወር በዚህ መልኩ በጀግንነት ከተወጣ በኋላ እንደገና ራሱን በራሱ ወልዶና ወጣት ሆኖ ወደ ንስሮች መንደር ብቅ ይላል፡፡
•
•
•
አንተም በተመሳሳይ መንገድ አልፈህ በአዲስ ህይወት ከፍ ብለህ መብረር ትችል ዘንድ .....ከንስር አሞራ ህይወት ተማርበት!
እንኳን ወደ ቴሌግራም ቻናሌ በደህና መጡ
እኔ ሰዎች በአመለካከት በገቢና የአመራር ክህሎትን እንዲያሳድጉ እያገዝኩ እገኛለሁ
ምን ይፈልጋሉ
✔ተጨማሪ ገቢ
✔ምክሮችን
✔የቢዝነስ እድገት
✔የግል ስብዕና እድገት
"ዝግጁ" ብለው ይፃፉ
@RadiantEphrem
Welcome to my Telegram channel 👋 I help people grow mindset, income, and leadership skills. If you're looking for:
✔ additional income
✔ mentorship
✔ business growth
✔ personal growth
Send me: “READY”
@RadiantEphremለምሳሌ ሰውን መርዳት የማይወድ ወይም ለሰው ምንም ግድ የለለው ሰው የህክምና ባለሙያ ቢሆን፤ በሽተኞቹን እንደ ገንዘብ ማግኛ ከመቁጠር በቀር ለጤንነታቸውም ሆነ ለደስታቸው ደንታ አይሰጠውም። ስለዚህ የምንሰራው ነገር ምን ያህል ደስታ ወይም እርካት ይሰጠናል? የሚለው ጥያቄ በተሰማራንበት መስክ ሁሉ እራሳችንን ልንጠይቀው የሚገባ ጥያቄ ነው።
#መርህ_አንድ:- ፍላጎት (Desire)
የመጀመሪያው የስኬት መርህ ፍላጎት ነው። ከልብ የመነጨ ፍላጎት። ፍላጎታችንን እንደ ዘር ልናየው እንችላለን። ፍሬ እንደሚያፈራ አምነን የምንዘራው ዘር። ነገር ግን ዛሬ ዘርተነው ዛሬውኑ ፍሬ የሚሰጠን ተክል የለም።
ፍላጎታችንም ልክ እንደ በቆሎ ወይም ማንኛውም ዘር ዛሬ ተዘርቶ በቂ ውሃ፤ በቂ ጸሃይ፤ በቂ እንክብካቤ ፤ካገኘ በኋላ በግዜው የሚያሽት ነው።
የምንፈልገውን ነገር ጥርት ባለ መልኩ ማወቁ ይጠቅመናል። ለመረጥነው ነገር ምን ያህል ፍላጎት እንዳለን ለማወቅ የምናደርጋቸውን ነገሮች መቃኘት ያስፈልገናል። ከምንም በላይ በውስጣችን ያለው የትዕግስት መጠን ፍላጎታችን ምን ያህል እንደሆነ ያስረዳናል።
ለምሳሌ ሰዓሊነት ፍላጎቱ የሆነ ሰው ባይከፈለው እንኳን ስዕል መሳሉን አያቆምም። አላማ ብለን ለመረጥነው ነገር በቀላሉ ሊገደብ የማይችል ፍላጎት ሊኖረን ይገባል። ጥልቅ ፍላጎት ማለት ወደኋላ እንዳናፈገፍግ የመመለሻውን ድልድይ እንደማቃጠል ያህል ነው።
#መርህ_ሁለት:- እምነት (Faith)
እምነት አላማችን የሚገነባበት መሰረት ነው። የምንፈልገው ነገር ምንም ይሁን ምን እምነት ከሌለን ነዳጅ የሌለው መኪናን ለመንዳት እንደመሞከር ይሆንብናል። ደግነቱ እምነት በመጀመሪያ ባይኖረንም፤ በሂደት ልንገነባው የምንችለው ጥበብ ነው።
ለአእምሮአችን ቀና የሆኑ ነገሮችን በመመገብ እምነትን በሂደት ማዳበር ይቻላል። የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት እምነት እጅግ ወሳኝ ነገር መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ማርቲን ሉተር ኪንግ ስለ እምነት ደስ የሚል አባባል አለው ” እምነት ማለት ሙሉውን ደረጃ እስከየት እንደሚያደርሰን ባናውቅም እንኳ የመጀመሪያውን ደረጃ መውጣት ነው” ይላል።
#መርህ_ሦስት:- እራስን ማሳመን (Auto Suggestion-አውቶ ሰጀሽን)
አእምሮአችን እውነት ብሎ የሚቀበለው ነገር ደጋግመን የምንመግበውን ነው። እዚህ ላይ ይህንን በደንብ የሚያስረዳ አንድ ታሪክ ትዝ አለኝ። ታሪኩ እንዲህ ነው
ሁለት ውሾች የነበሩት አንድ ሰው ነበር። አዘውትሮ እኒህን ውሾች አደባባይ እየወሰደ እንዲደባደቡ ያደርግ ነበር። ታዲያ ተመልካቾቹ የትኛው ውሻ በእለቱ እንደሚያሸንፍ ሲጠይቁት “በደንብ የምመግበው ውሻ ነው” ሲል መለሰላቸው። ሁላችንም ውስጥ ሁለት ዉሾች አሉ የመልካም እና የክፋት፤ የልማት እና የጥፋት፤ የእውቀት እና የድንቁርና፤ የውድቀት እና የድል ውሾች። የበላይ ሆኖ የሚመራን ውሻ ዘወትር የምንመግበው ነው።
ለዚህ ነው ናፖሊዮን ሂል “አውቶ ሰጀሽን” ወይም ለራስ መልካም ነገሮችን ደጋግሞ በመንገር አእምሮአችንን ወደፈለግነው መንገድ መምራት እንደምንችል የሚነግረን። መንገር ብቻም ሳይሆን የሚያሳስበን!
#መርህ_አራት:- በአንድ ነገር ላይ እራስን የተካኑ ማድረግ (ስፔሻላይዝድ ኖውሌጅ)-
ልንሰማራበት በመረጥነው ወይም ፍላጎት ባለን ሙያ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን መተዋወቁ እና ቅርርብ መፍጠሩ ወሳኝ ነገር ነው። ጊዜያችንን የምናሳልፈው ከነማን ጋር ነው? የምናውቃቸው ሰዎች ወይም ጓደኞቻችን ለምንፈልገው ሙያ የሚያግዙን ናቸው?
ለምሳሌ:- ፕሮፌሰር ለመሆን ፍላጎት ያለው ሰው በተቻለው መጠን ዩንቨርሲቲ አካባቢ ካሉ ሰዎች ጋር ግንኙነቱን ቢያዳብር ይጠቅመዋል። ተዋናይ መሆን የሚመኝ ሰው እራሱን ከቲያትር መድረክ አካባቢ ማራቅ የለበትም። ሁላችንም የምንማረው ቀድመውን ካወቁት ነውና፤ የምንፈልገውን ነገር በቅጡ የሚያውቁ ሰዎችን ማወቁ ይጠቅመናል።
#መርህ_አምስት:- ነገሮችን በህሊናችን መሳል- (Imagination)
ሁሉም ነገር ሃሳብ ነበር። ምንም ነገር እውን ሆኖ ከማየታችን በፊት በአንድ ሰው አይምሮ ውስጥ የተጠነሰሰ ሃሳብ ነበር። የምንፈልገውን ነገር እውን ሆኖ ከማየታችን በፊት በህሊናችን መሳል ትልቁ የስኬት ሚስጥር እንደሆነ ብዙዎች የተስማሙበት ነው። አላማችን ቁልጭ ብሉ በህሊናችን ከታየን ለጉዟችን ትልቅ ጉልበት አገኘን ማለት ነው። ምክንያቱም የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚሳካ አእምሮአችን እየነገረን ነው።
#መርህ_ስድስት:- እቅድ ማውጣት- (Organized planning)
እቅድ ማውጣት ጊዜን በአግባቡ እንድንጠቀም ከማድረጉም በላይ፤ በአንድ ጊዜ አንድ ደረጃ እየወጣን ጉዟችን አድካሚ እንዳይሆን ያደርግልናል። እቅድ ስናውጣ ነገሮች ሳይደራረቡብን ቀስ በቀስ ወደ ግባችን እንደርሳለን።
እቅድ ስናወጣ ግን እራሳችንን በሚያጨናንቅ እና ካልፈጸምነው የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን በሚያደርግ ሁኔታ ሳይሆን፤ ከጊዜያችን ፤ ከባህሪያችን እንዲሁም ከማንነታችን ጋር የሚስማማ እቅድ ነው ማውጣት አለብን። ምክንያቱም ሌላው ያቀደበት መንገድ ለኛ ላይስማማ እና ከግባችን ላያደርሰን ስለሚችል ነው።
#መርህ_ሰባት:- ውሳኔ (Decision)
የሰው ልጅ ውድቀት አንደኛው መንስዔ የውሳኔ ማጣት ነው። አንድ ሰው ምንም ያህል እምቅ እውቀት ቢኖረው፤ ምንም ያህል የሚያስደንቅ ሃሳቦችን ማመንጨት ቢችልም ውሳኔ መወሰን ካልቻለ ግን አቅሙ ሁሉ ከውስጡ አይወጣም።
ውሳኔ በማጣት የተነሳ ብዙ ሙዚቃዎች ሳይሰሙ፤ ብዙ መጽሐፎች ሳይጻፉ፤ ብዙ ግኝቶች ሳይገኙ፤ ወደ መቃብር ይወርዳሉ።.በሁላችንም ውስጥ ለኛ ብቻ የተሰጠ ስጦታ አለ፤ ይህን ስጦታ ግን አውጠን ሌሎች እንዲያዩት ማድረግ የምንችለው ውሳኔ መወሰን ስንችል ብቻ ነው። የምንወስነው ምንድን ነው ካላችሁ፤ መልሱ የምንወስነው መሆን የምንፈልገውን ነው።
#መርህ_ስምንት:- ጽናት (Persistence)
ውሳኔ ብቻውን አቅም የለውም። ውሳኔያችን ባህሩን አቋርጦ ከአላማችን ዳርቻ እንዲደርስ የሚያደርገው ሃይል ጽናት ነው። ብዙዎቻችን የተለያዩ ውሳኔዎችን እዚህና እዚህ እንወስናለን ነገር ግን ጽናት ኖሮን አንገፋበትም።
ለዚህ ነው ናፖሊዮን ሂል የውድቀት እና የስኬት ዋናው መለያ ጽናት ነው ያለው። ለምሳሌ ከመጠጥ ሱስ መላቀቅ የሚፈልግ ሰው መቶ ጊዜ ለማቆም ቢወስንም ከውሳኔው ጋር ጽናት ካልተደመረበት በቀር ውሳኔው ብቻውን ምንም ዋጋ የለውም። ስለዚህ በውስጣችን ያለውን የጽናት መጠን መፈተሹ እጅግ ወሳኝ ነገር ነው።
#መርህ_ዘጠኝ:- ጥምር ሃይል (Power of the master mind)
“ሁለት ጭንቅላቶች አንድ ላይ ሲሆኑ ሶስተኛ ጭንቅላት ይወለዳል”። አንድ ሰው የራሱ የሆነ ሃሳብ ወይም ግኝት ሊኖረው ይችላል፤ ከሌሎች ሰዎች ሃሳብ ጋር ሲደመር ደግሞ ይበልጥ ይሰምራል።
“ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሐኒቱ” እንዲል የሃገራችን ሰው በጋራ የመስራትን ልምድ ማዳበር መቻል አለብን። አብሮ መስራት መቻል ትልቅ ክህሎትም ጭምር ነው።
#መርህ_አስር:- የምታደርገው ነገር ደስታን ሊስጠህ ይገባል– (Enthusiasm)
ስቲቭ ጆብስ በህይወት በነበረበት ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር “የምንሰራውን ነገር የማንወደው ከሆነ እስከመጨረሻው ለመሄድ አንችልም፤ የሚሰራውን የማይወድ ማንኛውም ሰው ተስፋ ቢቆርጥ አይፈረድበትም”።
እውነት ነው የምንወደውን ነገር ስናደርግ በቀላሉ ተስፋ አንቆርጥም። ሙያችን እንዲሆን የምንመርጠው ነገር የምንወደው ነገር ከሆነ በዛ ነገር ላይ እውቀታችንን ለማዳበርም ሆነ ልምድ ለማግኘት ፍላጎት ይኖረናል።
ሴት ልጅህ ደሃ ወንድ እንድታገባ ትፈቅዳለህ?ሲል ጋዜጠኛው ቢልጌትን ጠየቀው፦ቢልጌትም በመጀመሪያ አንድ ነገር ላብራራልህ በማለት ንግግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ።"ማንም ሰው ትክክለኛ አስተሳሰብ ካለው ደሃ አይደለም፤እውነተኛው ድህነት የገንዘብ ማጣት ሳይሆን ለመለወጥ ፍላጎትና ህልም ማጣት ነው።የሚሰራ ሰው ከሚሰራው እየተማረ ወደ ህልሙ የሚያደርሰውን እርምጃ ይወስዳል።ህልም የሌለው ሰው ግን ሰበብ የሚያበዛና በከንቱ ጊዜውን የሚያጠፋ እንዲሁም ለማደግ ፍላጎት የሌለው ነው።ህልም ያለው ሰው ዛሬ ገንዘብ ባይኖረው ነገ ሚሊዮኖችን ማግኘቱ የማይቀር ነው።እውነተኛ ሃብት ማሰብ መስራትና እሴትን መፍጠር ነው።ስለዚህ ልጄ እንድታገባው የማልፈቅደው ገንዘብ የሌለው ሳይሆን የአስተሳሰብ ደሃ ለሆነ ሰው ብቻ ነው"።
*ከዚህ ሃሳብ እንደምንረዳው አስተሳሰባችንን አጎልብተን ጊዜያችንን በአግባቡ ከተጠቀምን በህይወታችን ለውጥ እንዳናመጣ የሚያግደን አንዳች ኃይል እንደሌለ ነው።
https://t.me/The_secretsOfsuccess
"ግብ አስቀምጦ እንዴት ይሆናል ብሎ የሚጨነቅ ሰው ዘር ዘርቶ ተፈጥሮአዊ ጊዜውን እና አበቃቀሉን ከመጠበቅ ይልቅ እንዴት ? የሚለው ላይ ያተኮረ እንደሚበቅል ያላመነ ገበሬን ይመስላል "
ተፈጥሮን ያላመነ ገበሬ መሬት ውስጥ መቆየቱ ስለሚያሳስበው አለጊዜው እየቆፈረ ለማረጋገጥ ይሞክራል ዘሩንም ያበላሻል። ዘሩን ከመሬት ያገናኘ ገበሬ በቅሎ እስኪያየው ድረስ በእምነት ይጠብቃል ምክንያቱም መሬት ውስጥ ነው ያለው ማለት በወቅቱ መሬቱን ሰንጥቆ አይታይም ማለት ስላልሆነ ነው ። ምን የዘሩት እና የሚያጠጡት ህልም አልዎት ? አለመብቀሉ የሚያሳስብዎት ?
የሰው ልጅ ማተኮር ያለበት ዘሩ ላይ እና ከእርሱ የሚጠበቀው እንክብካቤ ላይ ነው። ሌላው ተፈጥሯዊ ጊዜውን ጠብቆ ይከናወናል።
ማንጎ የተከለ እና ስንዴ የዘራ በእኩል ወቅት እንዲበቅል አይጠብቅ ፣ አፈሩን አለስልሶ የተከለ እና እንዲሁ ደረቅ መሬት ላይ የዘራም እኩል ውጤት አይጠብቅ ፣ በየወቅቱ ያጠጣ የተንከባከበ እና ዘርቶ አረም እንዲውጠው በግድየለሽነት የተወ እኩል ምርት አይጠብቅም ።
ወዳጆቼ ;
1. ምንድነው የዘራውት ?
2. በየጊዜው እየተንከባከብኩ ነው ?
3. ውጤቱን አውቀዋለው ?
4. ትኩረቴ እንዴት ላይ ነው ወይስ የምሻው ውጣት ላይ ?
ሌላው ተፈጥሯዊ ነው ። በእምነት መጠበቅ ብቻ ነው !!!
ህይወት ምርጫ ፣ ሂደት እና ውብ ናት !!!
ሕልምህ ጋር የሚያደርስህን ማንነት አሁን ተላበሰው።
ሼር ሼር
👇👇👇👇
https://t.me/The_secretsOfsuccess
እኔ የተሸከምኩት ነገር ቡችላ አይደለም!!!
~~~
አንዲት ዝሆን እና ውሻ በተመሳሳይ ግዜ አረገዙ። ከሦስት ወራት በኃላ ውሻዋ ስድስት ቡችላዎችን ወለደች ። ከስድስት ወር በኋላ ውሻዋ እንደገና ፀነሰች፤ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ሌላ ደርዘን ቡችላዎችን ወለደች። እንዲህ እንዲህ እያለች ውሻዋ ማርገዝ እና መውለዷን ቀጠለች።
በ18ኛው ወር ውሻዋ ወደ ዝሆኗ ቀረባ፡- "ግን እርጉዝ መሆንሽን እርግጠኛ ነሽ? በአንድ ቀን ፀንሰናል እኔም በርካታ ቡችላዎችን ወልጄያለሁ። እነሱ አሁን ትልልቅ ውሾች ሆነዋል፣ አንቺ ግን አሁንም 'እርጉዝ' ነሽ። ምን እየሆነ ነው?" ስትል ጠየቀች
ዝሆኗም ረጋ ብላ "እንዲገባሽ የምፈልገው ነገር አለ፣ እኔ የተሸከምኩት ቡችላ ሳይሆን ዝሆን ነው፣ በሁለት አመት ውስጥ አንድ ብቻ ነው የምወልደው። ልጄ መሬት ሲመታ ምድር ይሰማታል፣ ልጄ መንገዱን ሲያቋርጥ የሰው ልጅ ቆም ብሎ በአድናቆት ይመለከተዋል። እኔ የተሸከምኩት ሀይለኛ ፣ ታላቅ እና ጊዜ የሚወስድ ነው።" ብላ መለሰችላት
አንተ ያረገዝከው ሀሳብ፣ አላማ፣ ራዕይ ምንድነው...?
ምን ሠራለሁ ብለው አስበሀል፣ የት ለመድረስ አቅደሀል...?
ሌሎች በአቋራጭ ስለተሳካላቸው ወይም ህልማቸውን አሳንሰው በትንሽ ነገር ስለተደሰቱ ባንተ ጊዜ መውሰድ ተስፋ አትቁረጥ። ትልቅ ሀሳብ ፣ ግልፅ ራዕይ ያለው ሰው ሀሳቡን ከግብ ለማድረስ ግዜ ሊወስድበት ይችላል ግን ከፍፃሜ ሲደርስ ለሀገር ብሎም ለዓለም በርከት መሆን ይችላል።
ህልም እና ራዕይህ ትልቅ ይሁን።
መልካም ቀን! 😊
#keepmoving #positivity
SHARE #LIKE #JOIN
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
Repost from Breakthrough Trading S.C ®
📎 የአልፋ ኃያል ሂደት ስልጠና በቅርብ ቀን
📍በቢሾፍቱ - አልፋ ኃያል ሂደት ስልጠና
የስልጠናውን መርሐ-ግብር መሳተፍ የሚችሉት አስቀድመው ምዝገባ ያጠናቀቁ እና ስልጠናው ከሚሰጥበት ሁለት ቀናት በፊት በቴሌግራም ወይም በአካል የተመዘገቡ ብቻ ይሆናሉ።
ስልጠናው ከሚጀምርበት ቀን በፊት የተግባር መጽሀፍ(work book) በስፓንሰሮቻችሁ(አፕላይን) በኩል ወይም ከ E-PIN Agent በመቀበል ይዛችሁ እንድትመጡ ስንል እናሳስባለን ።
=== አልፋ ለስኬትዎ ጉልህ ድርሻ! ===
📍አዲስ አበባ፣ ቦሌ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 3 አለምነሽ ፕላዛ 6ተኛ ፎቅ
🌐 www.alphagenuine.com
☎️ +251930020395 Bole Branch
+251988010611 Megenagna Branch
