en
Feedback
Catholic songs የካቶሊክ መዝሙሮች

Catholic songs የካቶሊክ መዝሙሮች

Open in Telegram
1 992
Subscribers
-224 hours
No data7 days
+1830 days
Posts Archive
መዝሙረ ዳዊት 121:1-2 (AMH) •••••••••• ¹ ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? ² ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ዳዊት አይኖቼን ወደ ተራራ አነ
መዝሙረ ዳዊት 121:1-2 (AMH) •••••••••• ¹ ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? ² ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ዳዊት አይኖቼን ወደ ተራራ አነሳሁ ሲል( ከኔ የበላይ ለሆኑ or የተሻለ position ወዳላቸው ሰዎች/መንግስታት ያደርጉልኛል ይደርሱልኛ ወዳላቸው ተስፋ አደረኩ ማለቱ ነው ። ሰው ነንና እከሌ ይረዳኛል/ያግዘኛል ብለን ተስፋ እናደርጋለን (አረ እሱንማ አውቀዋለሁ ብለን እንሄዳለን)በራሳችን የጀመርነው መንገድ ሳይሳካ ቢቀር ስብራቱ ከባድ ይሆናል..! ነገር ግን የሚረዳም .../የሚረዳንንም ሰው  የሚያዘጋጅልን እርሱ እና እርሱ ብቻ ነው #ዳዊትም_ኢሄንኑ_ሀሳብ ነው የተናገረው የሚረዳን ሰው እራሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላከ ሰው ነው። እግዚአብሔር ያንን ሰው እንዲረዳን ከላከው ምድር ላይ ያለ ምንም ሀይል አያግደውም።ቃል ይናገር እንጂ ² ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ተሰፋ ወደሚጣልበት አምላክ እንጠጋ ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው / መልስ ወደ ማይታጣበት መለኮት(ጌታ) ብቻ  አይኖቻችንን እናንሳ..!! ቢዘገይም/ቢፈጥን እርሱ መንገድ አለው.!!እርሱን ጠብቆ ያፈረ የለምና ልክ እንደ ሀና🙌

የማቴዎስ ወንጌል 27:40 (AMH) •••••••••• ⁴⁰ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት። #እንደዚህ_ያሉት_ሰ
የማቴዎስ ወንጌል 27:40 (AMH) •••••••••• ⁴⁰ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት። #እንደዚህ_ያሉት_ሰዎች_ያልገባቸው ነገር 👉መች እራሱን ሊያድን መጣ እራሱን ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ እንጂ.!! 👉እነርሱንም (የሚሰቅሉትንም) ጨምር ሰማይ የሚያስገባ መንገድ ለመስራት መስቀል ላይ እንደሆነ አልገባቸውም.!!😟 👉ከድቅድቅ ጨለማ ሊያወጣቸው እንደመጣ አልገባቸውም 👉ሕይወት ሊሆናቸው ከሰማይ በአብ ፍቃድ እንደመጣ አልተረዱትም 👉የነበረ/ያለ/የሚኖር/አልፋና ኦሜጋ ህያው መሆኑን አልገባቸውማ😟 👉እራሱን ስለእነርሱም ጭምር ሀጥያት መስዋዕት ሊሆን እንደመጣ አላወቁም 😟 👉ከዛ መስቀል መውረድ ለእነርሱ ትልቅና ቁምነገር አድርገውት ነበር አይወርድም እንጂ ቢወርድ እስካሁን በጨለማ እንደሚንገላቱ ...! ከህግ እስራት እንደማይላቀቁ..!! የዛሬን እንጂ የነገን ስለማያውቁ ነው። እኛ ግን መንፈስ ቅዱስ የገለጠልን የገባን እንደዚህ እንናገራለን ትንቢተ ኢሳይያስ 53:5 (AMH) •••••••••• ⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።

#በጸጋ_ድነናል ፤ #ለዘላለም_አንጠፋም !!     ✍️በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።         ዮሐንስ 3፥16 ✍️አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል።    2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥10-11       ይህ #የቅዱስ_ቃሉ አስተምዕሮ ነው። # ጸጋ የትምህርት ርዕስ ሳይሆን ማንነት ነው፤ እርሱም #ጌታችንንና_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ነው። 👉እኛ እውነትኛ አማኞች የዳነው #በጸጋ ነው፤ የሕይወታችን ለውጥም በዚው #ጸጋ ነው። ✍️በአጠቃላይ #ከጸጋው የተነጠለ ሕይወትም ኑሮም የለንም።     #ጸጋው ማንነታችን ነው። ✍️አንድ በእርግጠኛነት ይህንን #የጸጋ አስተምዕሮ በሙሉ ያመነና የተማረ እውነትኛ ክርስቲያን ኃጢአትን እንደፈለገ እያደረገና ልማዱ እያደረገ ፈጽሞ መኖር አይችልም። ምክንያቱም ...👉    👉1ኛ ዮሐንስ 3፥9 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአትን አያደርግም፤ የእርሱ ዘር በውስጡ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደም ኀጢአትን ሊያደርግ አይችልም።       1ኛ ዮሐንስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት)        ሕያው ቃልን በደንብ አንብቡት ። 👉ቲቶ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤ ✍️ይህ ማለት ደግሞ ፈጽሞ ሊደክም አይችልም ማለት እንዳልሆነ ግልጽ ነው ። ነገር ግን ከዚህ ድካም ማምለጫው ደሞ :- 👉እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።    ዕብራውያን 4፥16 ...በዚህ መንገድ ይወጣል። 👉 #በጸጋ ድነናል ፤ ለዘላለም አንጠፋም።           👉 #ጸድቀናል በኃጢአታችን አይደለንም።  

ወደ ገላትያ ሰዎች 2:16 ¹⁶ ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን
ወደ ገላትያ ሰዎች 2:16 ¹⁶ ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል። 👉 መዳን በስራና ህግን በመፈፀም የሚገኝ ቢሆን ኖሮ የአብርሃም ልጅ ተብሎ መለኮት አይመጣም ሊታረድ በግ ሆኖ.!! መዳን በክርስቶስ በእግዚአብሔር ልጅ ብቻ የሚገኝ ስለሆነ አዳምን ሊቤዠው ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ወረደ 🙌 #ኢየውልህ_ጎበዜ ተራራ በመውጣት ህግንና/ስርአትን በመከተል ያልተገኘ ድህነት ፅድቅ ተፈፅሟል ያኔ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ የተነሳ እለት ። #እናማ..... ስለዚህ እኛን ሀጥያተኞቹን በደሙ ሊያጥበን ጌታ ስለመጣ ብቻውን ሊያድነን በሚቻለው መሲሕ በንስሐ እንምጣ( በፊቱ እንቅረብ ) 👉ያለምንም እጅመንሻ 👉ያለምን መልካም ስራችን 👉መስፈርት ሳይኖረን 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:17 ¹⁷ ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። እንደሚል ቃሉ ንፁህ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ህዝቤ ሆይ ኑ ዳኑ እያለ እየጠራን ነው ለዚሂ ታላቅ ድምፅ  እንታዘዝ🙌🙌

መልካም የሆነ ምልልሳችን ለእግዚአብሔር እንደተለየን ማሳያ ነው እንጂ ደኅንነታችን(መዳናችን) ፍጽምናን እንዲያገኝ የምንሰራው ድኅነት ማስቀጠያ ክትባት አይደለም።
መልካም የሆነ ምልልሳችን ለእግዚአብሔር እንደተለየን ማሳያ ነው እንጂ ደኅንነታችን(መዳናችን) ፍጽምናን እንዲያገኝ የምንሰራው ድኅነት ማስቀጠያ ክትባት አይደለም።

ደህንነት ማለት ምን ማለት ነው? 👉ደህንነት ማለት ከሚመጣው ፍርድ መዳን ብቻ ሳይሆን በህይወት ሳሉ ከኃጥያት ኃይል መዳን ማለት ነው (አንድ ሰው ከዳነ በኋላ ከኃጥያት ይለያል የክርስቶስ ኢየሱስ የ
ደህንነት ማለት ምን ማለት ነው? 👉ደህንነት ማለት ከሚመጣው ፍርድ መዳን ብቻ ሳይሆን በህይወት ሳሉ ከኃጥያት ኃይል መዳን ማለት ነው (አንድ ሰው ከዳነ በኋላ ከኃጥያት ይለያል የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ስጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።ገላ 5:24 ) (አዲስ ፍጥረት ይሆናል ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው አሮጌው ነገር አልፎአል እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።2ቆሮ 5:17):( ይቀደሳል በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል ተቀድሳችኋል ጸድቃችኋል 1ቆሮ 6:11)። Ezekiel 36 አማ - ሕዝቅኤል 26: አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ፤ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።

አካል የለበሰ ክርስትና .aac10.65 MB

የኤማሁሰ መንገደኞች ሉቃሰ24፥13፦33🥺ኤማሁሰ ማለት ተሰፋ ቆርጠን ከሄድንበት መንገድ እግዚአብሔር የሚመልሰን ቦታ ነው።ሁሉም ሰው የራሱ ኤማሁሰ አለው። እንዳንዴ ሰው በእግዚአብሔር ተሰፈ ቆርጦ”
የኤማሁሰ መንገደኞች ሉቃሰ24፥13፦33🥺ኤማሁሰ ማለት ተሰፋ ቆርጠን ከሄድንበት መንገድ እግዚአብሔር የሚመልሰን ቦታ ነው።ሁሉም ሰው የራሱ ኤማሁሰ  አለው። እንዳንዴ ሰው በእግዚአብሔር  ተሰፈ ቆርጦ” ከእንግዲህ ወዲያ ምን ያደርግልኛል” የሚልበት ከእግዚአብሔርም የሚርቅበት የሕይወት ክፍል ነው ኤማሁሰ።በዝህ ሁሉ ግን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው🥹እኛ ደክሞን ጠውልገን መንገድ የቀየርን ጊዜ፣እርሱ እኮ ረሰቶናል ብለን የስንፍናን ቃል በራሳችን ላይ ባወጅን ጊዜ፣ያድነናል ብለን አምነን የተከተልነው አምላክ እኮ ጉድ ሰራን ከማዳን እኮ እጅ አጥራለች ብለን ባሸሟጠጥንበትም ጊዜ ሁሉ፥ እርሱ ይከተለናል ወደ መልካሙም ህይወት ጎዳና እንደገና ይመልሰናል።

ቀናችን እንደፈቃድህ ዘመናችን ለፈቃድህ ይዋል🙌 የመንፈስህ ረሀብተኞች የድምጽህ ሱሰኞች አድርገን 🙌 ቅድስና ንግግራችን ሳይሆን ህይወታችን ይሁንልን 🙌 ቃልህ ምግባችን ጸሎት ምሽጋችን ይሁነን🙌
ቀናችን እንደፈቃድህ ዘመናችን ለፈቃድህ ይዋል🙌 የመንፈስህ ረሀብተኞች የድምጽህ ሱሰኞች አድርገን 🙌 ቅድስና ንግግራችን ሳይሆን ህይወታችን ይሁንልን 🙌 ቃልህ ምግባችን  ጸሎት ምሽጋችን ይሁነን🙌 የምትወደውን አጥብቀን ወዳድ: የምትጠላውን ያለ ስስት አሽቀንጥረን የምንጥል ጨካኝ ክርስቲያን አድርገን🙌 ባንተ ጉዳይ ልባችን ስስ ይሁን🙌በዚች ትንሽ ልብ እና አጭር እድሜያችን ፍቅርህን ሙላባት🙌 አንተን በመውደድ በረከት ባርከን🙏

#የመፅደቅና_የመቀደስ_ልዩነቶች #መፅደቅ ☑️የህግ ብያኔ ውሳኔ ነው, ውጫዊ ህጋዊ ስፍራችን ነው ☑️በህይወት ዘመን አንድ ጊዜ የሚፈፀም ነው ☑️ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ስልጣንና ውሳኔ ነው ☑️በዚህ
#የመፅደቅና_የመቀደስ_ልዩነቶች #መፅደቅ ☑️የህግ ብያኔ ውሳኔ ነው, ውጫዊ ህጋዊ ስፍራችን ነው ☑️በህይወት ዘመን አንድ ጊዜ የሚፈፀም ነው ☑️ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ስልጣንና ውሳኔ ነው ☑️በዚህ ህይወት ፍፁምና የተሟላ ☑️ለሁሉም አማኞች እኩል የተወሰነ ነው የመፅደቅ መበላለጥ የለም። #መቀደስ 🗝ውስጣዊ ሁኔታ ነው። 🗝በህይወት ዘመን ሁሉ የሚያድግ የሚቀጥል ነው 🗝የአማኙ ፍቃድና ድርሻ አለበት 🗝በዚህ ህይወት ምሉዕ አይሆንም 🗝አንዱ አማኝ ከሌላኛው አማኝ ይለያያሉ

ወደ ሮሜ ሰዎች 8:18 ¹⁸ ለእኛም ይገለጥ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ምንም እንዳይደለ አስባለሁ። ምንም ብናገኝ ምንም ብናጣ በሰማይ ከተዘጋጀልን ክብር በላይ የሚያጓጓ እ
ወደ ሮሜ ሰዎች 8:18 ¹⁸ ለእኛም ይገለጥ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ምንም እንዳይደለ አስባለሁ። ምንም ብናገኝ ምንም ብናጣ በሰማይ ከተዘጋጀልን ክብር በላይ የሚያጓጓ እና የሚናፍቅ አለም የለም ኢቺ አለም ጊዜያዊ ናት ለጊዜ ብንጨነቅም ዘላለም እረፍት ወዳለበት እንሄዳለን ። ልወስደን ይመጣል 🙌🙌

የማቴዎስ ወንጌል 23 : 1_5_13_28 🎙🎙🎙 ✅@medanihalem✅    ✅ @medanihalem✅             🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 📲ሼር ማድረግዎን እዳይረሱ📲

ነገ እሁድ ነው ቤተክርስቲያን እንዳትቀሩ 🙌🙏 እግዚአብሔርን በህብረት እናመልካለን 🙏 ፀጋው ይብዛላችሁ 🙏🙏

የእግዚአብሔር ጊዜ .aac8.53 MB

“በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።” — ማቴዎስ 15፥28 አለ አይደል ያ እንደውም አንተ/ቺና ጌታ ብቻ
+1
“በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።”   — ማቴዎስ 15፥28 አለ አይደል ያ እንደውም አንተ/ቺና ጌታ ብቻ ምታውቁት 🤔 እንደውም በጓዳ ሆነህ/ሽ የለመንከው/ሽው የተማፀንከው/ሽው...... እረፍት ነስተሽ ጌታ ሆይ ብለህ/ሽ የጠየከው/ቅሽው ጥያቄ የለም 🤔 ኣ...........ዎ እሱ ጥያቄ 🗝ከአሁን ሰአት ጀምሮ በናዝሬቱ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የአመታት ጥያቄዎቻችሁ ከዛሬ ጀምሮ ፍሬ ማፍራት ይጀምሩላችሁ።🙌 🗝እግዚአብሔር ፊቱን ወደናንተ ይመልስ🙌 🗝በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እግዚአብሔር እንባችሁን ያብስ🙌 🗝ያ የተማመናችሁበት አምላክ ምርኮዋችሁን ይመልስ🙌 🗝እንደ ሀና ለምስጋና በቤቱ ለምስክርነት ያቁማችሁ🙌 🗝አመስጋኝ ያድርጋችሁ 🗝ጥያቄዎቻችሁ ተመልሰው ፊታችሁም በደስታ አንደበታችሁ በእልልታ ይሞላ🙌 እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው የሚያስደነግጠኝ ማን ነው? አይደል ያለው ዳዊት 🗝እርሱ መታመኛሁ ይሁን 🗝የተማመናችሁበት እርሱ ውድቀታችሁን በሚጠባበቁ ፊት በድል/በሞገስ/በክብር ከፍ ያድርግሽ🙌🙏

#ተከፍሏል_በልልኝ🙏 አንዱ አዳም በሰራው በደል መተላለፍ ፣ ፍጥረት ተበክሎ ከእግዚአብሔር ሲኳረፍ፣ ለስጋው ፍቃድ ቀርቦ ከአምላክ ፈቃድ ሸሸ፣ በዓለም ፍቅር ግሎ ለጥፋት ተሟሸ። ከርኩሰት ደጃፍ ላይ
#ተከፍሏል_በልልኝ🙏 አንዱ አዳም በሰራው በደል መተላለፍ ፣ ፍጥረት ተበክሎ ከእግዚአብሔር ሲኳረፍ፣ ለስጋው ፍቃድ ቀርቦ ከአምላክ ፈቃድ ሸሸ፣ በዓለም ፍቅር ግሎ ለጥፋት ተሟሸ። ከርኩሰት ደጃፍ ላይ በሞት ተጠቅልሎ፣ ህይወት ማንነቱ በሲኦል ተስሎ፣ ነፍስያው በሲቃ ተንገላታ ሳለ፣ ከእለታት ባ'ንዱ ቀን... አንድ እውነት በርቶለት መስቀል ይዞ አየ። የታየው እንዲህ ነው... አንድ ንፁህ ወጣት ፍጹም ነውር አልባ፣ ለሰው ልጆች ኃጢያት ተሰቅሎ ጎልጎታ፣ በድብደባው ብዛት የጎድኑ አጥንት እስኪቆጠር ታይቷል፣ ስጋው ተተልትሎ መስቀል ላይ ተከፍሏል። በመስቀሉ መቃን በደሙ እ'ፋሎት ውስጥ የሚጮህ ድምጽ አለ፣ ለሚያምንብኝ ሁሉ ለዘላለም መዳን ተከፈልኩ ያለ። ከአብ የሚመጣ የቁጣው ክምችት ከቶ እንዳያገኘኝ፣ በርሱ ስላመንኩ ነፃ ነህ ተባልኩ ፍቅር ተከፍሎልኝ። እናም.. ይህን መዳን ለፍጥረታት ሁሉ አሁን አውጃለሁ፣ በጥረት ያልሆነ የእግዜር ጽድቅ ይሄ ነው። እናም ይህን የምስራች.. በጨለማው ዓለም በድንግዝግዝ ላለው አሁን መስክርልኝ፣ ከፍ ባለ ቦታ በእግሮችህ ውጣና ከፍ ባለ ድምፅ ተከፍሏል በልልኝ።         

ኢሳይያስ 49 🎙️🎙️🎙️ ✅@medanihalem✅    ✅ @medanihalem✅             🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 📲ሼር ማድረግዎን እዳይረሱ📲

ኑሩ ስትለን እንኖራለን ኑ ስትለን እንመጣለን ሳናተርፍ እንዳንመጣ ሳታፍርብን እንድንመጣ ይህቺ በምድር ላይ ያለችው ትንሿ እድሜያችን ፍቃድህን ትፈፅም አባቴ ዘመናችንን ...... ጊዜያችንን.....
ኑሩ ስትለን እንኖራለን ኑ ስትለን እንመጣለን ሳናተርፍ እንዳንመጣ ሳታፍርብን እንድንመጣ ይህቺ በምድር ላይ ያለችው ትንሿ እድሜያችን ፍቃድህን ትፈፅም አባቴ ዘመናችንን ...... ጊዜያችንን..... ጉልበታችንን ላንተ አድርገው ጌታ ሆይ🙌🙌